en
Feedback
etrade.gov.et

etrade.gov.et

Open in Telegram

ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel etrade.gov.et

Channel etrade.gov.et (@etrade_gov_et) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 16 715 subscribers, ranking 6 225 in the Business category and 1 835 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 16 715 subscribers.

According to the latest data from 23 July, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 73 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 July, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Business category.

16 715
Subscribers
No data24 hours
+367 days
+7330 days
Posts Archive
ውድ ደንበኞቻችን ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መሰጠታቸው ይታወሳል። ቢሆንም በረካታ ባለጉዳዮች አገልግሎት ጠይቃችሁ አገልግሎቱን ያላጠናቀቃችሁ በሙሉ፣ የመክፈያ ኮድ መሰረት በአስቸኳይ የአገልግሎት ክፍያ በመጸም የምስክር ወረቀታችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን።

ከ300ሺ በላይ አገልግሎት በኦንላይን ተሰጠ:: ============================ አዲስ አበባ 26/12/2015ዓ.ም (ንቀትሚ) ከሐምሌ 1 እስከ ነሐሴ 24/2015 ከ300ሺ በላይ የንግድ
ከ300ሺ በላይ አገልግሎት በኦንላይን ተሰጠ:: ============================ አዲስ አበባ 26/12/2015ዓ.ም (ንቀትሚ) ከሐምሌ 1 እስከ ነሐሴ 24/2015 ከ300ሺ በላይ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን በኦን ላይን መሰጠጥ መቻሉ ተገለጸ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከሐምሌ1/2015 ዓ.ም ጀምሮ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጡን በሀገር ደረጃ በኦን ላይን ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህ መሰረት ከሀምሌ 1 እስከ ነሐሴ 24/2015 ከፌደራል እስከ ክልል ባሉት መዋቅሮች 300,298 አገልግሎቶችን በኦን ላይን መስጠት መቻሉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል ፡፡ የተሰጡት የአገልግሎት አይነቶችም የንግድ ምዝገባ፣ አዲስ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ እድሳት፣የንግድ ስራ ፈቃድ ስረዛ፣ የንግድ ስም ማሻሻያ እና ሌሎችም ሲሆኑ አገልግሎቱ በኦን ላይን በመሰጠቱ የተገልጋዮችን እንግልት ማስቀረት፣ ወጪ እና ጊዜያቸውንም በመቆጠብ ምቹ አሰራርን መፍጠር አስችሏል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

የግብር ካፋይ መለያ ቁጥሩን ይላኩ?

Online ስመዘገብ ስህተት ነበረው። ህጋዊ አቋም የሚለው "ግለሰብ ነጋዴ" መሆን ሲገባው "ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር" አድርገውታል። እንደገና online ለመመዝገብ አስቸገረኝ። መፍትሔው ምንድነው???

የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ይላኩልን።

ውድ ደንበኞቻችን የአገልግሎት ክፍያ ስርዓቱ መክፈል እንዳልቻለችሁ ገልጻችሁልናል። በመሆኑም አሁን በትክክል እሰራ መሆኑን በቴክኒክ ክፍላችን ስለተረጋገጠ ክፍያ አልሰራ ያላችሁ ደንበኞች መክፈል የምትችሉ መሆኑን እንገጻለን። =============================== Dear customers, you have informed us that you have not been able to pay the service fee. Therefore, since our technical department has confirmed that it is working properly, we will let you know that the customers who have not paid can pay.

ከህግ አግባብ ውጪ ሲሰሩ በተገኙ 107 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ ======================================== አዲስ አበባ 3/12/2015ዓ.ም (ንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በ2015 በጀት ዓመት በ1,294 የንግድ ድርጅቶች ላይ ባደረገው የክትትልና የቁጥጥር ስራ 107 (አንድ መቶ ሰባት) የንግድ ድርጅቶች ከህግ ዉጪ ሲሰሩ በመገኘታቸው አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡ እርምጃ የተወሰደባቸው ንግድ ድርጅቶች ከተሰጣቸው የንግድ ፈቃድ መስኮችና ዓላማዎች ውጪ ሲሰሩ የነበሩ፣ ለኢንፔክሽን ስራ ፍቃደኛ ያልሆኑ፣ ባልፀና ወይም ባልታደሰ ንግድ ፊቃድ ሲነግዱ፣ ባስመዘገቡት የስራ አድራሻ ያልተገኙ እንዲሁም የቅርንጫፍ አድራሻ ያላስመዘገቡ ሲሆኑ ይህን መነሻ በማድረግ በ49 ንግድ ድርጅቶች ላይ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያና በ58 ንግድ ድርጅቶች ላይ የእግድ እርምጀ ተወስዷል፡፡ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቀጣይም በንግድ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው የቁጥጥርና የክትትል ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስታውቋል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

contract farming directive .pdf1.22 MB

በ 2015 በጀት አመት 1ሚሊዮን 496ሺህ የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎቶች በኦንላይን ተሰጠ። =============================== አዲስ አበባ 14/11/2015 (ንቀትሚ) በ2015 በጀት ዓመት በሀገር ዓቀፍ ደረጃ 1ሚሊዮን 496ሺህ አገልግሎቶች በኦንላይን መሠጠት መቻሉን በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሠንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ጅራታ ነመራ ገለጹ። የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎቶች በበጀት አመቱ ከተያዘው እቅድ አንፃር የ117% አፈፃፀም አሳይቷል ያሉት መሪ ስራ አስፈጻሚው አገልግሎቱ በፌደራልና በክልሎች መሠጠት መጀመሩ የተቀላጠፈ አገልግሎት አሠጣጥ እንዲኖር ከማስቻሉም በላይ የተገልጋይ ጊዜንና ወጪን ለመቆጠብ እንደሚያስችልም ገልፀዋል፡፡ በ2016 በጀት አመት በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የኦንላይን አገልግሎቶችን ወደ 90% ለማሳደግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት መሪ ስራ አስፈፃሚው ይህን እቅድ ለማሳካትም ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በ2016 በጀትአመት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ1ጀምሮ ባለፉት 12ቀናት ብቻ 52ሺህ 129 አገልግሎቶች በኦን ላይን ተሠጥተዋል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ውድ ሚኒስትሮች፣ የክልል ንግድ ቢሮ ኃላፊዎች እና የንግድ ምዝገባና ፈቃድ ደንበኞች አገልግሎት መኮንኖች እንዲሁም የንግድ ሥርዓቱ ተገልጋዮች፤ እንኳን 2016 በጀት ዓመት አድረሳችሁ እያልን በመላው ሀገራችን ይሰጥ የነበረው የአስመጪና ላኪ ንግድ ፈቃዶች ወደ ፌደራል ንግድና ቀየጣናዊ ትስስር ሚንስቴር የዞሩ መሆኑን እየገለጽን፤ ውድ ደንበኞች ይህንን በመገንዘብ ማንኛውንም አስመጪና ላኪ ንግድ ፈቃዳችሁን በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ምዝገባና ፈቃድ ሥራ አስፈጻሚ በኩል በኦንላይን ( www.etrade.gov.et ) የምትገለገሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አገልግሎት መረጃ ለማግኝት የሚያስችል 965 የተባለ የጥሪ ማዕከል ይፋ ተደረገ አዲስ አበባ 26/10/2015ዓ.ም (ንቀትሚ) የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አገልግሎት መረጃ ለ
+5
የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አገልግሎት መረጃ ለማግኝት የሚያስችል 965 የተባለ የጥሪ ማዕከል ይፋ ተደረገ አዲስ አበባ 26/10/2015ዓ.ም (ንቀትሚ) የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አገልግሎት መረጃ ለማግኝት የሚያስችል 965 የተባለ የጥሪ ማእከል ይፋ ተደርጓል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጥራት መሠረተ ልማትና ማረጋገጫ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እንዳለው መኮንን የጥሪ ማዕከሉ መከፈት የንግድ ስራን ለመጀመር የሚፈልግ ግለሠብም ሆኑ ተቋማት በሁሉም የአገልግሎት አይነቶች ላይ ሙሉ መረጃ ለማግኘት እንደችሉ የሚያግዛቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የንግድ ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለጹ ሚኒስትር ዴኤታው ከሀምሌ 1 2016ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት በኦን ላይን መሰጠት እደሚጀመርም አስታውቀዋል፡፡ የንግድ ስራን የመጀመር ሂደትን አመቺ ለማድረግ፣ ቀልጣፋ አገልግሎትን ለመስጠት እና የንግድ ዘርፉን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በርካታ ስራዎች እየተሠሩ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው ለሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎችና ሀላፊዎች በድርጅት ስም፣ በንግድ ስም፣ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እና በአጠቃላይ በ19 አገልግሎቶች ላይ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

+1
Ethio_Djibouti_Border_Trade_implementation_Draft_Directive_2_Amharic.docx0.50 KB

ማስታወቂያ ኢትዮጵያ ከጅቡቲ እና ከደቡብ ሱዳን ጋር ቀደም ሲል በተፈራረመችው የጠረፍ ንግድ ስምምነቶች( border trade protocols) መሰረት የድንበር አካባቢ ማህበረሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጠረፍ ንግድ ማስፈጸሚያ ረቂቅ መመሪያዎች በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እየተዘጋጁ ይገኛል፡፡ እነዚህን የጠረፍ ንግድ ማስፈጸምያ ረቂቅ መመሪዎች አስመልክቶ ማንኛውም በዘርፉ ላይ ፍላጎት ያለው ግለሰብም ሆነ ተቋም፣ በተለይም በጠረፍ አካባቢ በሚገኙ በጋምቤላ፣ በሱማሌ  እና በአፋር ክልሎች የምትገኙ የአስተዳደር ዘርፍ ሀላፊዎችን ጨምሮ ማንኛውም በረቂቅ የጠረፍ ንግድ ማስፈጸሚ መመሪዎች ላይ  አስተያየት ያላችሁ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 የስራ ቀናት ውስጥ አስተያየታችሁን ከታች በተቀመጡት አማራጮች እድትልኩልን እየጠየቅን የጠረፍ ንግድ ማስፈጸምያ ረቂቅ መመሪውን ሙሉውን ሰነድ በቴሌግራም ገጻችን  :https://t.me/motri_gov_et ላይ ማግኝት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን ፡፡ አስተያየቶቻችሁን፡- • በቴሌግራም:- https://t.me/motri_gov_et • በኢሜል ፡-  sisaykebede47@gmail.com •  በፖስታ ሳጥን ቁጥር፡  704

935-2015 የንግድ ምዝገባ፣ ፈቃድ እና ድኅረ-ፈቃድ ኢንስፔክሽን መመሪያ ቁጥር- 935-2015

940 2015 የሲሚንቶ ግብይትን ለመቆጣጠር የወጣ መመሪያ ቁጥር 940 2015