en
Feedback
etrade.gov.et

etrade.gov.et

Open in Telegram

ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel etrade.gov.et

Channel etrade.gov.et (@etrade_gov_et) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 16 715 subscribers, ranking 6 225 in the Business category and 1 835 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 16 715 subscribers.

According to the latest data from 23 July, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 73 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 July, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Business category.

16 715
Subscribers
No data24 hours
+367 days
+7330 days
Posts Archive
ማስታወቂያ ======== አዲስ አበባ 29/03/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) በ2015/16 የምርት ዘመን በውልና ኢንቨስትመት እርሻ ያመረቱ ላኪ ድርጅቶች ከነሐሴ 15/2015 እስከ መስከረም 15/2016 ዓ.ም ድረስ ውላቸውን ለሚኒስቴር መ/ቤቱ እንዲያስመዘግቡ እንዲሁም ያስመረቱትን ምርት ከጥቅምት 15 እስከ ህዳር 30/2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የምርት መረከቢያ ማእከላት እንዲያስመዝኑ በተፈቀደው መሰረት ምርታቸውን በማስመዘን ለውጪ ገበያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ ሆኖም በውልና በኢንቨስትመንት እርሻ የወጪ ምርት አስመርተው በተለያዩ ምክንያቶች በወጣው የመመዝገቢያ ጊዜ ገደብ ውስጥ ያላስመዘገቡ አምራች ላኪ ድርጅቶች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከታህሳስ 1 እስከ 20/2016 ድረስ ብቻ በሚኒስቴር መ/ቤቱ ምዝገባ እንደሚካሄድ እናሳውቃለን። በ2015/16 የመኸር ምርት ወቅት በውልና በኢንቨስትመት እርሻ የተመረተ የአኩሪ አተር ምርትን ያለማችሁ አምራች ላኪ ድርጅቶች ብቻ በምርት ዘመኑ ያስመረታችሁትን ምርት የምዘና አገልግሎት ከታህሳስ 1 እስከ ጥር 15/2016 ድረስ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የምርት መረከቢያ ማእከላት በማቅረብ ማስመዘን እና ለውጪ ገበያ ማቅረብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡ በተመሳሳይ በ2015/16 የመኸር ምርት ወቅት በውልና በኢንቨስትመት እርሻ የተመረተ የሰሊጥ፣የማሾ እና የተለያዩ የቦሎቄ ዝርያ ምርቶች የምዘና አገልግሎት ከጥቅምት 16 እስከ ታህሳስ 1/2016 ድረስ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የምርት መረከቢያ ማእከላት የሚዛን አገልግሎት የተካሄደ ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች አስመዝነው ያላጠናቀቁ ላኪ ድርጅቶች ምርታቸውን ማስመዘን እንዲችሉ የሚዛን አገልግሎቱ እስከ ታህሳስ 20/2016 ድረስ የተራዘመ መሆኑን አውቃችሁ ምርታችሁን እንድታስመዝኑ እናሳስባለን፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et fakebook:-https://www.facebook.com/people/Ethiopian-Ministry-of-Trade-and-Regional-Integration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። ====================== አዲስ አበባ 25/03/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከህዳር 26/03/2016ዓ.ም ጀምሮ ቀደም ሲል በስራ ላይ በነበረበት ዋጋ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ:: ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ውድ ደንበኞቻችን ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መሰጠታቸው ይታወሳል። ቢሆንም በሺህዎች ባለጉዳዮች አገልግሎት ጠይቃችሁ አገልግሎቱን ያላጠናቀቃችሁ በሙሉ፣ የመክፈያ ኮድ መሰረት በአስቸኳይ የአገልግሎት ክፍያ በመጸም የምስክር ወረቀታችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን። ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ Dear customers, since July 1, 2015 E.C, many business registration and license services have been provided. However, we urge all those who have requested service and not completed the service, to collect your certificate by paying the service fee immediately according to the payment code. =============================================================

ማስታወቂያ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸውን ላኪዎችም ሆነ አዲስ የንግድ ፍቃድ ፈላጊዎችን አስመልክቶ ጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም የጫት ላኪነት የንግድ ስራ ቅድመ ፍቃድ ብቃት ማረጋገጫ መስፈርት ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መስፈርት መሰረት ላኪዎች በሚኒስትር መስራቤቱ በመገኝት የተዘጋጀውን መስፈርት በሟሟላት የቅድመ ፈቃድ የብቃት ማረጋገጫ በማውጣት የንግድ ስራ ፈቃዳቸውን እንዲያሳድሱ እስከ ህዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም የጊዜ ገደብ የተሰጠ ቢሆንም በእስከአሁኑ አፈፃፀም የተወሰኑ ላኪዎች መስፈርቱን አሟልተው የተመዘገቡ ቢሆንም መስፈርቱ አማካዩን የንግድ ማህበረሰብ ማሳተፍ ባለመቻሉ የተወሰነ ማሻሻያ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በመሆኑም የተሻሻለውን መስፈርት የሚያሟሉ ላኪዎችን በሙሉ መመዝገብ እንዲችሉ የመመዝገቢያ ጊዜው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን ከታህሳስ 1ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ በነባር የጫት የንግድ ስራ ፍቃድ ምንም አይነት አገልግሎት መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስትር መስራ ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

10 minutes! That is all it took to #renew my 2 #business #licenses. I could download the soft copies of the renewed licenses within 10 minutes of starting the application on #etrade. Last year, somebody from my office had to go to the Trade Bureau to get the records checked as error messages about missing documents kept coming. This year is amazing!!!! What is different this year? 1. I was not asked to submit any document, as their database was up to date. 2. Even more surprising was the fact that I was not asked to submit tax clearance. It was automatically pulled over from MoR database (data integration). Good Job Ethiopian Ministry of Trade and Regional Integration!

የጫት ላኪነት ንግድ ስራ ፍቃድ ቅድመ ፈቃድ መስፈርትን ማሳወቅ ይመለከታል፡፡ አዲስ አበባ 30/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ)

ከህግ አግባብ ውጪ ሲሰሩ በተገኙ 37 ንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ ===================================== አዲስ አበባ 30/02/2016 ዓ.ም (የንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በበጀት ዓመቱ ሶስት ወራት ህግን ተከትለው ባልሰሩ 37 ንግድ ድርጅቶች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ገለጹ፡፡ በበጀት ዓመቱ መጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት 402 የንግድ ድርጅቶች ላይ በተደረገው የክትትልና የቁጥጥር ስራ 365 ንግድ ድርጅቶች በህግ አግባብ የሚሰሩና 37 ንግድ ድርጅቶች ደግሞ ህግን ተከትለው የማይሰሩ መሆኑን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል፡፡ እርምጃ የተወሰደባቸው ንግድ ድርጅቶች ከተሰጣቸው የንግድ ፈቃድ መስኮችና ዓላማዎች ውጪ ሲሰሩ የነበሩ፣ ባልፀና ወይም ባልታደሰ ንግድ ፊቃድ ሲነግዱ የተገኙ ፣ባስመዘገቡት የስራ አድራሻ ያልተገኙ እንዲሁም የቅርንጫፍ አድራሻ ያላስመዘገቡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

የጫት ላኪነት ንግድ ስራ ፍቃድ ቅድመ ፈቃድ መስፈርትን ማሳወቅ ይመለከታል፡፡ አዲስ አበባ 29/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ)

ይህ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተገልጋዮች የዜጎች ቻርተር ነው።

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። ====================== አዲስ አበባ 27/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከጥቅምት 28/02/201
+1
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። ====================== አዲስ አበባ 27/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከጥቅምት 28/02/2016ዓ.ም ጀምሮ ቀደም ሲል በስራ ላይ በነበረበት ዋጋ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ:: ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ኤስ ቨ ኤስ ሳልት ፕሮዳክሽን ኃ/የተ/የግል ማህበር የሚያመርተው አዮዳይዝድ ጨው ለገበያ ላይ እንዳይቀርብ ታገደ። ============================ አዲስ አበባ 24/02/ 2016 ዓ.ም (ንቀትሚ) ኤስ ቨ ኤስ ሳልት ፕሮዳክሽን ኃ/የተ/የግል ማህበር የሚያመርተው አዮዳይዝድ ጨው ምርት ላይ በተደረገው የኢንስፔክሽን ስራ ምርቱ አስገዳጅ የኢትዮጵያ ደረጃ ያላሟላ በመሆኑ ለገበያ ላይ እንዳይቀርብ እገዳ መጣሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የጨው ምርት ፋብሪካ ላይ በተደረገ ምልከታና በተወሰደ የላብራቶሪ ፍተሸ ምርቱ በአስገዳጅ ደረጃ CES 70:2017 የተደነገገውን የጥራት መስፈርቶች አሟልቶ ባለመገኘቱ እገዳ የተጣለበት መሆኑን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል፡፡ ምርቱ በገበያ ላይ ቀርቦ ሸማቹ ህብረተሰብ ላይ አስከፊ ጉዳት እንዳያደርስም የክልል ንግድ ቢሮዎችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ማድረግ እንደለባቸው ሚኒስቴር መስሪያቤቱ አሳስቧል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ግብር ራችሁን ያጠናቀቃችሁ እና የግብር ክሊራንስ የወሰዳችሁ ደንበኞቻችን በሙሉ የኢትየጵያ በጀት ዓመት አቆጣጠር ተጠቃሚዎች ንግድ ፈቃድ የማደሻ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት በመሆናቸው ፍቃዳችሁን ያለቅጣት እንድታድሱ እናሳስባለን። +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ Dear customers who have completed their taxes and received tax clearance to renew their licenses without penalty as there are a few days left for the renewal of business licenses of Ethiopian budget year. =========================================================

ውድ ደንበኞቻችን ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መሰጠታቸው ይታወሳል። ቢሆንም በረካታ ባለጉዳዮች አገልግሎት ጠይቃችሁ አገልግሎቱን ያላጠናቀቃችሁ በሙሉ፣ የመክፈያ ኮድ መሰረት በአስቸኳይ የአገልግሎት ክፍያ በመጸም የምስክር ወረቀታችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን። ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ Dear customers, since July 1, 2015 E.C, many business registration and license services have been provided. However, we urge all those who have requested service and not completed the service, to collect your certificate by paying the service fee immediately according to the payment code. =============================================================

ነጋዴዎች ለሚሸጡት አገልግሎት እና እቃ የዋጋ ዝርዝር የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው:: ============================== አዲስ አበባ 20/02/2016ዓ.ም(ንቀትሚ) የንግድ ተቋማት ለሚሸጡት አገልግሎትና የንግድ ዕቃዎች የዋጋ ዝርዝር የመለጠፍና የማሳወቅ ግዴታ እንዳለባቸው በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሸማቾች መብትና ጥበቃ ዴስክ ሀላፊ አቶ ሰይፉ አየለ ገለጹ፡፡ የእቃዎችን ዝርዘርና ዋጋ መለጠፍ ለግዥው ግንፅነትን የመፍጠርና አድሏዊነትን ይቀንሳል ያሉት የሸማቾች መብትና ጥበቃ ዴስክ ኃላፊ አቶ ሰይፉ አየለ የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ 813/2006 ክፍል ሶስት ከአንቀጽ 15 እስከ 18 የንግዱ ማህበረሰብ ለሚሰጡ አገልግሎቶችና ለሚሸጡ እቃዎች የዋጋ ዝርዝር የመለጠፍ ግደታ እንዳለበት መደንገጉን አብራርተዋል፡፡ የገዥዎችን የመከራከር አቅም ታሳቢ በማድረግ አንድን እቃ በተለያየ ዋጋ መሸጥ አድሏዊነት ነው ያሉት አቶ ሰይፉ ዋጋ መለጠፍ፣ የድርጅት ስም የማሳወቅ፣የንግድ ዕቃዎች መግለጫ ማቅረብ፣ ደረሰኝ መቁረጥ የነጋዴዎች ግደታ ሲሆኑ በሌላ በኩል እነዚህን የማግኘት የሸማቹ ማህበረሰብ መብት እንዴሆነም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ የሸማቾች ጥበቃ መብት በማይተግብሩ ነጋዴዎች ላይ በገንዘብ ከ5ሺ እስከ 50ሺ ብር እና ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ወንጀል እንደሆነም አቶ ሰይፉ ተናግረዋል፡፡ የሸማቹን ማህበረሰብ የግንዛቤ ለማዳበር ለሚመለከታቸው የክልል ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት፣ ከሚዲያዎች ጋራ በጋራ የመስራት፣ ከህብረተሰቡ ጋር የገፅ ለገፅ ውይይት በማድረግ እንዲሁም በተቋሙ የፌስ ቡክ ገፅ እና በተለያዩ መንገዶች ግንዛቤውን ለማስፋት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

በአዳማ ከተማ 9127 የንግድ አገልግሎቶች በኦንላይን ተሰጥተዋል:: ================= አዲስ አበባ 10/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) በአዳማ ከተማ አስተዳደር ከሐምሌ1/2015 እስከ መስከረም/2016ዓ.ም መጨረሻ ድረስ 9127 የንግድ አገልግሎቶች በኦንላይን መሰጠቱን የከተማው ንግድ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ ሀገራዊ የንግድ ስርዓቱን ለማዘመንና አገልግሎት አሰጣጡን ለተገልጋዩ ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ተከትሎ ከሐምሌ1/2015 ጀምሮ በሀገር ደረጃ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች በኦንላይን እንዲሰጡ መደረጉ ይታወሳል፡፡ በአዳማ ከተማ አስተዳደር እስከ መስከረም 30/2016 ዓ.ም 9127 አገልግሎቶችን በኦንላይን መስጠቱን የአዳማ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጢሎ ዱግዳ ተናግረዋል፡፡ በኦንላይን የተሰጠው አገልግሎትም የደንበኞችን ጊዜ፣ ወጪና እንግልትን ያስቀረ መሆኑን ሀላፊው ጠቁመዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade