𝙞𝙨𝙡𝙖𝙢𝙞𝙘 𝙠𝙣𝙤𝙬𝙡𝙚𝙙𝙜
Open in Telegram
#የቴሌግራም_ቻናላችን_ሊንክ👇 https://t.me/joinchat/AAAAAEgolEJ2Rl3gT_bmuA የፌስቡክ ግሩፓችን 👇 #ፊዳካ_ኣቢ_ወዑሚ_ያረሱልለህ 👇 https://facebook.com/groups/3118579678388903/ #የፌስቡክ_ፔጅ👇 Facebook peg link https://www.facebook.com/323366755034719?referrer=whatsapp
Show more1 035
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2030 days
Posts Archive
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
«اللَّهمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ». متفق عليه.
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
…ታጋሽ ሁን!
ሰይዲና ኢብራሂም [ﷺ] በጌታቸው ተመኩ። ፍጡርን ከመሻት ቀልባቸውን ሰብስበው በአላህ ተብቃቁ። "ሐስቢየላህ ወኒዕመል‐ወኪል" አሉ።…
አላህስ ምን አደረገ?!
የማዳኑን ስራ ለሌላ አልተወውም። በኃያሉ ቁድራው ስር አደረገው። እሳትን በቀጥታ አዘዛት: ‐
(كوني بردا وسلاما على إبراهيم)
«እሳት ሆይ! በኢብራሂም ላይ ቀዝቃዛ፤ ሰላምም ሁኚ!»🌹
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“ምድር ሁሉ መስገጃ ቦታ ነው። የቀብር ቦታና ሽንት ቤት ሲቀር!✅
http://t.me/+TOuxbrki5gY2iIpt
http://t.me/+TOuxbrki5gY2iIpt
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
ሁለት ነገሮች ያንተን ማንነት ይወስኑታል
ትግስትህ ምንም ነገር ሳይኖርህ!
ስነ ምግባርህ ሁሉንም ነገር 💜
1 035
🙌
አረፋህ ሊመን አረፈህ🥰
ነገ ቤት የማፅጃ ወይ መጋረጃ የማውረጃ ቀን አይደለም። የኢድ ሸመታም ሆነ የመዝናኛ እንዲሁ!
ነገ አላህ የሰማይ ባለሟሎች ላይ በአረፋ ሰዎች የሚኩራራበት፤ የሰው ልጆች ከእሳት በገፍ ነፃ የሚባሉበት ከሁሉ በላይ ዱአዎች በሙሉ ተቀባይነት የሚያገኙበት እለት ነው።
ለይለቱል ቀድር ባትታወቅ የውሙ አረፋ ትታወቃለች። በለይለቱል ቀድር መላእክት ቢወርዱ በአረፋ አላህ (እሱን በሚመጥን አወራረድ) የሚወርድበት ነው!
ነገ አላህ በጊዜ ፀጋ ላጣቀማችሁ አንድ to do list ላካፍላችሁ
ጠዋት
ከፈጅር በፊት ከለይሉ ጥቂቱን መስገድ፣ ስሁር መመገብ እና ኢስቲግፋር ማብዛት!
ከሰላት በኋላ ቀጥታ ተክቢራ መጀመር ከዛም ፀሀይ እስክትወጣ ቁርአን፣ተህሊል፣ተህሚድ በአጠቃላይ በዚክር ማሳለፍ(አዝካረ ሰባህ ሳይረሳ)
ፀሀይ ስትወጣ የፀሃይ መውጣትን ሰላት እዛው ከመስገጃችን ሳንነሳ በመከወን ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሀጅ የማድረግን ምንዳ እንዲጎናጸፍ
ለቀን ኢባዳ ያግዘናል ብለን ካሰብን መጠነኛ እኝቅልፍ እንተኛ። ስንነሳ በትንሹ 4 ረክኣ ሰላተ ዱሃ እንስገድ!
ከሰአት
ከዝሁር ሰላት በኋላ ቁርዐናችንን እንቀራለን። የአረፋ ኹጥባ(ከመስጂደ ነሚራህ የሚተላለፈውን) መልእክት በጥብቅ መከታተል
ልባችንን ሊያረጥብ የሚችል መፅሐፍ ወይም ቪድዮ እየተመለከትን እራሳችንን እናርጥብ!
ከአስር በጥሎ እንዲሁ በቁርአን እና በዚክር መግሪብ 1 ሰአት አቅራቢያ እስኪቀረው ማሰለፍ!
የእለቱ ወሳኝ ሰአት ይህ ነው።
የተሰበረ የሚጠገንበት፤ የታመመ የሚፈወስበት፤ ተስፋ የቆረጠ ተስፋው ነፍስ ሚዘራበት ድንቅ ሰአት!
ዱኣ!!! ዱኣ ብቻ!
በዚህ ቀን ከእሳት ነፃ አለመባል ኪሳራ ነው። ምኞት ኖሮን ምኞታችንን ሳናሳካ መቅረት ቂልነት ነው!
ነገ አላህ አልመረጥንም እና እየተመለከታቸው ከሚኮፈስባቸው ጌታቸውን ለማላቅ በነጭ ተውበው ከአረህማን ድግስ ከሚታደሙት አልሆንም!
"አረፋ ተራራ ላይ መቆም ያልቻለ
አላህ ያሳወቀው ድንበር ላይ ይቁም
ሙዝደሊፋ ላይ ማደር ያልቻለ
በአላህ ትእዛዝ ላይ ይደር...ያቀርበዋልና!
ሚና ላይ እርዱን መከወን ያልቻለ
ምኞቱን ይረድ! ከፍ ይላልና።
ወደ ቤቱ በርቀት ምክንያት መድረስ ያልቻለ
ከደም ስሩ ቅርብ ወደ ሆነው የቤቱ ጌታ ይከጅል!"
ኢብኑ ረጀብ
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
❗️ሶላት የሌለው ሰው ዲን የለውም❗️
ሶላት የዲን ምሰሶ ነው (الصلاة عماد الدين)
☜قال الشيخ صالح الفوزان حفظه الله :
☞ሸኽ ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና እንዲህ ብለዋል።
【الَّذِي لا يُصَلِّي لا يَقُومُ لهُ دِينٌ، وإنْ شَهِدَ أنَّ لا إِلهَ إلَّا الله وأنَّ مُحمّدًا ﷺ رسولُ الله ،لأنّهُ يحتاجُ إلى عُمُودٍ يُقِيمُ عليهِ الدِّين، وهو لا يُوجَدُ إلا بِالصَّلاة】
✅ ሰላት የማይሰግድ ሰው ሸሀደተይን (ላኢላሀ ኢለላህ ሙሀመድ ረሱሉላህ) ቢል ራሲ ዲኑን (እስልምነውን) አይቆምለትም። ምክንያቱም ዲኑን የሚያቆምበት ምሰሶ የግድ ያስፈልገዋልና። የዚህ ማቆምያ ምሰሶ ደሞ ከሶላት ውጪ ምንም የለም።
📚(شرح الأصول الثلاثة - ص ٢٤٢)
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል።
✅ አንድ ሰው ሶስት ጊዜ አላህን ጀነት ከጠየቀ፦ ጀነትም አላህ ሆይ ይህ ሰው እኔ ውስጥ አስገባው ትላለች። ሶስት ጊዜ ከጀሀነም እሳት ጠብቀኝ ካለ፦ እሳትም አላህ ሆይ ይህ ሰው ከኔ ጠብቀው ትላለች።
📚(ቲርሚዚና ነሳእይ ዘግበውታል)
اللَّهُمَّ إنِّي أَسْأَلُكَ الْجَنَّةَ وَأَسْتَجِيْرُ بِكَ مِنَ النَّارِ
اللَّهُمَّ إنِّي أَسْأَلُكَ الْجَنَّةَ وَأَسْتَجِيْرُ بِكَ مِنَ النَّارِ
اللَّهُمَّ إنِّي أَسْأَلُكَ الْجَنَّةَ وَأَسْتَجِيْرُ بِكَ مِنَ النَّارِ
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
🕋 አስር ቁም ነገሮች ስለ ዙል ሒጃ አስር ቀናቶች
=========================
// የተለየ ደረጃ እንዳላቸው ሚጠቁሙ ማስረጃዎች//
❶ ``በነዚህ አስር ለሊቶች አላህ ቁርአን ላይ ምሎባቸዋል።
{ﻭَﺍﻟْﻔَﺠْﺮِ . ﻭَﻟَﻴَﺎﻝٍ ﻋَﺸْﺮٍ } [ ﺍﻟﻔﺠﺮ 2-1: ]
(( በንጋት እምላለ ⓵ በአስሩም ለሊቶች ⓶))
{ሱረት ፈጅር 1-2}
➻ኢብን ከሲር በዚህ የቁርአን አየቀፅ የተፈለገው አስሩ የዙል ሒጃ እንደሆነ ይጠቅሳል። ይህንን ደግሞ ኢብን አባስ: ኢብን ዙበይር: ሙጃሒድ እና ሌሎችም ብለውታል።
❷ በሀዲስም እንደመጣው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል
« ﻣﺎ ﺍﻟﻌﻤﻞ ﻓﻲ ﺃﻳّﺎﻡ ﺃﻓﻀﻞ ﻓﻲ ﻫﺬﻩ ﺍﻟﻌﺸﺮﺓ »
<< ምንም ስራ የለም በየትኛውም ቀን የሚሰራ በነዚህ ቀናቶች ከሚሰራ የሚበልጥ።>>
ጅሀድም ቢሆን? ብለው ሰሀቦች ጠየቋቸው።
<<ጅሀድም ቢሆን በነፍሱና በገንዘቡ ሊዋጋ ወጥቶ በምንም ያልተመለሰ ሰው ሲቀር>> አሏቸው። {ቡኻሪ ዘግቦታል}
❸ አላህ እንዲህ ማለቱ
ﻭَﻳَﺬْﻛُﺮُﻭﺍ ﺍﺳْﻢَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻓِﻲ ﺃَﻳَّﺎﻡٍ ﻣَّﻌْﻠُﻮﻣَﺎﺕٍ { [ ﺍﻟﺤﺞ 28: ]
(( አላህንም በታወቁት ግዜያቶች ሊያወሱ)) {ሀጅ 28}
➻ኢብን አባስ አሱሩ ቀናቶች ብሎ ፈስሮታል
❹ በሌላ ሀዲስም እንደመጣው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል
« ﻣﺎﻣﻦ ﺃﻳّﺎﻡ ﺃﻋﻈﻢ ﻋﻨﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺳﺒﺤﺎﻧﻪ ﻭﻻ ﺃﺣﺐ ﺇﻟﻴﻪ ﺍﻟﻌﻤﻞ ﻓﻴﻬﻦ ﻣﻦ ﻫﺬﻩ ﺍﻷﻳﺎﻡ ﺍﻟﻌﺸﺮ، ﻓﺄﻛﺜﺮﻭﺍ ﻓﻴﻬﻦ ﻣﻦ ﺍﻟﺘﻬﻠﻴﻞ ﻭﺍﻟﺘﻜﺒﻴﺮ ﻭﺍﻟﺘﺤﻤﻴﺪ » . ( ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﻄﺒﺮﺍﻧﻲ ﻓﻲ ﺍﻟﻤﻌﺠﻢ ﺍﻟﻜﺒﻴﺮ )
<< የትኛውም ቀን የለም አላህ ዘንድ ትልቅ የሆነ እና ስራ የተወደደበት ከነዚህ አስር ቀኖች ይበልጥ። በዛ ላይ ላሊላሀኢለላህ, አላሁ አክበር አልሐምዱሊላህ ከማለት አብዙ >>
{ኢማሙ ጠበራኒ ዘግበውታል}
➠ ኢብን ሀጀር እንዲህ ይላል
➻"ያ ግልፅ የሚሆነው አስሩ የዙልሒጃ ቀናቶች ከሌሎች የተለዩበት ምክንያት የኢባዳ እናቶች ስለ ተሰበሰቡበት ነው እነሱም #ሰላት_ፆም_ሰደቃ_ሀጅ ይህ በሌላ ግዜ አይመጣም።
========================
// በእነዚህ አስር ቀናቶች የሚወደድ ተግባር//
----- ❺ ሰላት
_ዋጅብ ሰላት ላይ ከሌላው ግዜ በበለጠ መልኩ ይበልጥ መጠናከር ሱና ሰላትንም ማብዛት ይወደዳል።
➻ምክንያቱም ሰላት ከትልልቆቹ መልካም ስራዎች መሐከል ነው በነዚህ ቀናቶች ደግሞ መልካም ስራ አብዙ ተብሏል
-------- ❻ ፆም
____ መልካም ስራ ከሚለው ውስጥ ፆምም ስለሚገባ። የአላህ መልእክተኛም ዘጠኙን የዙልሒጃ ቀናቶች ይፆሙ እንደነበር የመጣ ሐዲስ ስላለ
➻ኢማመ ነወዊ ዘጠኙን የዙልሒጃ ቀናቶች መፆም የጠነከረ ሱና መሆኑን ይገልፃሉ
----- ❼ ተክቢራን ማብዛት
____ ከላይ ተራ ቁጥር ❹ ላይ የጠቀስነው ሀዲስ ለዚህ በቂ ማስረጃ ነው።
ኢብን ኡመርና አቡ ሑረይራ ወደ ሱቅ ወጥተው ተክቢራ ያደርጉ ነበር ሰዎችም የነሱን ተክቢራ ሰምተው ተክቢራ ያደርጉ ነበር።
➻ተክቢራውን ጮክ ብሎ ማለቱ ይወደዳል
----- ❽ ከሰሀቦች እና ታብእዮች የመጡ የተክቢራ አይነቶች
◅ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ ﻛﺒﻴﺮًﺍ .
◅ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻّ ﺍﻟﻠﻪ، ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻭﻟﻠﻪ ﺍﻟﺤﻤﺪ .
◅ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻّ ﺍﻟﻠﻪ، ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻭﻟﻠﻪ ﺍﻟﺤﻤﺪ .
------❾ የአረፍ ፆም
➻የሁለት አመት ወንጀል እንደሚያስምር ኢማም ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ ላይ መጥቷ``ል
ﻗﺎﻝ ﻋﻦ ﺻﻮﻡ ﻳﻮﻡ ﻋﺮﻓﺔ : « ﺃﺣﺘﺴﺐ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻥ ﻳﻜﻔﺮ ﺍﻟﺴﻨﺔ ﺍﻟﺘﻲ ﻗﺒﻠﻪ ﻭﺍﻟﺴﻨﺔ ﺍﻟﺘﻲ ﺑﻌﺪﻩ » ( ﺭﻭﺍﻩ ﻣﺴﻠﻢ ) .
------❿ ሰደቃ
➻መልካም ስራ በነዚህ ቀናቶች የተወደደ ነው ተብሏል። ሰደቃም ደግሞ ከመልካም ስራዎች ውስጥ ነው።
▬▬▬▬๑۩🌹۩๑▬▬▬▬▬
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
የአረፋ ቀን ትሩፋቱ!
ረሱል (▫️) እንዲህ ብለዋል፦
﴿مِنْ يَوْمٍ أَكْثَرَ مِنْ أَنْ يُعْتِقَ اللَّهُ فِيهِ عَبْدًا مِنَ النَّارِ مِنْ يَوْمِ عَرَفَةَ، وَإِنَّهُ لَيَدْنُو، ثُمَّ يُبَاهِي بِهِمُ الْمَلَائِكَةَ، فَيَقُولُ : مَا أَرَادَ هَؤُلَاءِ﴾
“ከዐረፋ ቀን የበለጠ አላህ ባሪያውን ከአሳት ነፃ የሚያወጣበት ቀን የለም። እርሱም ይቀርባል። ከዚያሞ በነርሱ መላእክቶችን ይፎካከርባቸዋል። አንዲህም ይላል፦ ‘እነዚህ (ባሮቼ) ሞን ፈልው ነው?’”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1348
1 035
🛑👉እነዚህን ውድ አስር ቀናቶች በሰላም ላደረሰን አላህ የላቀ ምስጋና ይገባው።
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
📝 እድለቢስ ማለት ይህንን ትል ቅ አጋጣሚ በከንቱ የሚያሳልፍ ሰው ነው።
✅ እነዚህ የዙልሂዳ አስርቱ ውድ ቀናቶች ምናልባትም የእድሜያችን የመጨረሻ ሊሆኑ ይችላልና በኢባዳ ልንጠቀምባቸው ይገባል። እነዚህ ቀናቶች እስከ የውመል ቂያማ ድረስ በየአመቱ ይመላለሳሉ። አንተ ግን በህይወት ላታገኛቸው ትችላለህ። ምክንያቱም አጀልህ መች እንደሆነ አታውቅምና። ይህንን ትልቅ እድል ተጠቅመን ትንሽ ሰርተን ብዙ ልናተርፍ ይገባል።
✅በነዚህ አስር ቀናቶች ሸይጧንና ነፍሳችን መርታት ይጠበቅብናል። ትርፍ ሀጃዎቻችን በመቀነስ በመልካም ስራ ልንወጠር ይገባል። እነዚህ ቀናቶች ከዚህ በፊት ከነበሩ ቀናቶች በበለጠ መልኩ በኢባዳ ለየት ልናደርግባቸው ይገባል።
¶ተውበት በማድረግ
¶ፃም በመፃም
¶ተክቢራ በማለት
¶ከወንጀል በመራቅ
¶ቁርአንን በመቅራት
¶ሰደቃ በመስጠት
¶ሌሊት በመቆም
¶ዚክር በማብዛት
¶ዱአ በማብዛት
¶ኢልም በመፈለግ
¶ዳእዋ በማድረግ
¶ሱና ሶላቶች በማብዛት
¶ፈርድ ሶላት በጊዜው በመስገድ
¶ለእናት አባታችን መልካም በመዋልና
ሌሎችም መልካም ስራዎች ላይ እንበርታ።
አላህ ሆይ፦ እኔንም አጠቃላይ ሙስሊም ወንድም እህቶቼን በነዚህ ቀናት ከሚጠቀሙት አድርገን። በዚህም ላይ አግዘን። በውስጣቸው ያለውን መልካም ነገር ወፍቀን።
#
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ ۚ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ
ጌታችሁም አለ «ለምኑኝ፤ እቀበላችኋለሁና፡፡ እነዚያ እኔን ከመግገዛት የሚኮሩት ተዋራጆች ኾነው ገሀነምን በእርግጥ ይገባሉ፡፡❤️
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
ሰዎች ስህተት እንድትሰራ ሲጠባበቁህ
አሏህ ደግሞ በእዝነቱ ተውበት እንድታደርግ ይጠባበቅሀል💜
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
صلوات ربي وسلامه عليك حبيبي يارسول الله
صلى الله عليه وسلم♥♥
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
🌹እውነተኛ ጓደኝነት ምሳሌው
ልክ እንደ አይን እና እጅ ነው
🍂እጅ ሲታመም አይን ያለቅሳል
አይን ሲያለቅስ ደግሞ እጅ
እንባን ያብሳል!
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
ሁለቱ ቆንጆ ባህሪያት!
ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿عليْكَ بحسْنِ الخلُقِ، وطولِ الصمْتِ، فوالذي نَفْسِي بيدِهِ ما تَجَمَّلَ الخلائِقُ بِمِثْلِهِما﴾
“በመልካም ስነምግባር እና በረጅም ዝምታ ላይ አደራችሁን። ነፍሴ በእጁ በሆነችው እምላለሁ! ከፍጡራኖች በእነሱ (በሁለቱ ባህሪያት) እንደተዋበ አይነት ሰው ማንም የለም።”
📚 አልባኒ በሶሂህ አልጃሚ ውስጥ ሀሰን ብለውታል: 4048
1 035
Repost from 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻናል 📚
«ምኞትህን ሁሉ ሱጁድ ላይ አስቀምጠው ፣ጌታህ ዝቅ ብሎ የለመነውን ባሪያውን ፈፅሞ በባዶ አይመልስም»💜
