en
Feedback
UNION FELLOWSHIP©✝

UNION FELLOWSHIP©✝

Open in Telegram

#we deal about the strength and weakness of our fellowship #we advertise what programmes we have and had in the week. #we address you an information about such things whole over Ethiopia. #PRAYER IS THE ONLY MEANS OF RECEIVING SPIRITUAL POWER!!!!! @UACSFF

Show more
553
Subscribers
+124 hours
+17 days
No data30 days
Posts Archive
Selam beteseboch endemin nachu sile tinanitnawu gize Geta yibarek ena kelay yalu photowoch lemasitawesha yahil nw yasikemexinewu kezih befit endetelemedewu be programoch yetegegnu photowochn bezignawu channelachn endeminlek yitawekal silezih yetinanitnawun program masitaweshawochn beziwu silemnaskemix program lay leneberu hulu lijoch eyen channel share eyaderegachu join asidergu beteseb endihonu ena photowachewu endiyagegnu yehulachunum beziwu enilekalen tebareku sile hulum Geta yibarek Ahunun Join👇👇👇👇👇👇 UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff ☝☝☝☝☝🖕🖕🖕🖕🖕🖕

photo content

photo content
+3

photo content

photo content
+8

photo content
+9

photo content

ጸጋና ሙሉ ሰላም ይብዛላችሁ ውዶች። የትናንትናውን ስላላቀረብኩ በጣም ይቅርታ እጠይቃለሁ...🙏🙏🙏🙏 የመጨረሻውን ሃሳብ አሁን እንቀጥላለን ..... ይህም ዓላማ :- ሀ, እግዚአብሔርን እንድንፈልገው መርምረን እንድናገኘው ተፈጥረናል የዓለሙ ሁሉ ፈጣሪ የሆነው እግዚአብሔር በክርስቶስ ከተገለጠ በኃላ ዘወትር እንድንፈልገው የእርሱ ፍላጎት እንደሆነ እንረዳለን። የሰውን ሁኔታ ስንመለከት አፈጣጠሩ ራሱ ነገሮችን ጠይቆ ምክንያት ሰጥቶ ወደ አንድ ሁኔታ ላይ ለመድረስ ተመራማሪ የሆነ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ስለዚህም ከቅዱስ ቃሉ በሚገኘው እውነተኛ ብርሃን እግዚአብሔርን ያገኘው ዘንድ "ነገሩ እንደዚህ ይሆንን?" እያለ ዕለት ዕለት መጻሕፍትን መመርመርና ቃሉን በሙሉ ፈቃድ መቀበል ይገባል። (ሐዋ17:11) እንግዲህ እግዚአብሔርን በቃሉ ውስጥ ተመራምረን እናገኘዋለን። እንዲሁም እግዚአብሔርን እንድንፈልገው የእርሱ ፍላጎት ስለሆነ እግዚአብሔርን ለመፈለግ መሻቱ ሊኖረን ይገባል ምክንያቱም የመፈጠራችን ዓላማ ራሱ እርሱን እንድንፈልግ ተፈጥረናልና ነው (ሐዋ 17:26-27)። ለ, እግዚአብሔርን የምንፈልግ አንድ ቤተሰብ ሆነን ተፈጥረናል እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥረው በመጀመሪያ ደረጃ የሰውን ወገን ወይም ዘር ከአንድ እንደፈጠረ እንመለከታለን። ይህ ማለት ለሁላችንም አንድ አባት አለን ማለት ነው። ስለዚህ ሁላችንም አንድ ቤተሰብ ስንሆን እግዚአብሔር ደግሞ የሁሉም ፈጣሪ ነው ስለዚህ እንደ አንድ ቤተሰብ በአንድ ልብ እግዚአብሔርን ልንፈልገው ይገባል። የተፈጠርነው ለዚሁ ነውና። ሐ, እግዚአብሔርን ለመፈለግ በዘመን ተገድበን ተፈጥረናል በሦስተኛ ደረጃ ከሐዋ ሥራ 17:26-28 የምንመለከተው ጉዳይ እንድንፈልገው የተፈጠርን እግዚአብሔር "የተወሰነ ዘመን እንዲሁም ለምንኖርበት ዳርቻ መድቦልናል" ስለዚህ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ብንፈጠርም በጊዜ በሰዓትና በዘመን የተገደብን እንጂ ዘለዓለማዊ የሆነ የምድር ቆይታ የለንም። ቃሉ እንደሚል የሰው ዕድሜ ሰባ ቢበረታ ሰማንያ ከዚያ በላይ ሲሆን ድካም ነው ያም ቢሆን ማብቂያ አለው (መዝ 89(90):10) ስለዚህ በተመቻቸልን የዕድሜ ዘመንና ጊዜ እግዚአብሔርን መፈለግ የእኛ ድርሻ ነው። እንዲሁም በቦታ የተወሰንን ነን ልንኖር ያለነው አሁን በምድር ነው። በምድር ሳለን እግዚአብሔርን ማምለክ መከተል እንችላለን። ከዚያ በኃላ ከዚህ ምድር ሕይወት በኃላ እነዚህ ነገሮች ሁሉ ያበቃሉ። ስለዚህ በዚህ የምድር ኑሮ ያለንን ጊዜና ዕድል ተጠቅመን ጌታን እንፈልገው። ማጠቃለያ :- "አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፣ አቤቱ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።" (መዝ (27):8) በእርግጥ ይህን የእግዚአብሔርን ሃሳብ የምናነብ ጌታ በመንፈስ ፊቱን እንድንፈልግ እሹኝ በሚልበት በዚህ ጊዜ የጌታን ፊት ልንሻ ልባችንን በማንሳት እግዚአብሔርን ልንፈልግ ልንጠማ ይገባል እንጂ እግዚአብሔርን ከመፈለግ ይልቅ ዓለምንና በዓለም ያለውን በመመኘት ለሥጋችን ፍላጎት ብቻ በመሮጥ ጊዜአችንን በከንቱ ልናቃጥል አይገባም። ይህ የምንፈልገው እግዚአብሔር (በሐዋ 17:26) ላይ እንደተገለጸው እርሱ "ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።" እንዲያውም የምንኖረውና የምንንቀሳቀሰው ያለነውም በእርሱ ነው። ስለዚህ ከእኛ ያልራቀውን እስትንፋሳችንን ሁሉ የያዘውን የምንኖርበትን የምንንቀሳቀስበትን ሕያው አምላክ እግዚአብሔርን እ_ን_ፈ_ል_ገ_ው። ተጠናቀቀ❗❗ አመሰግናለሁ 🙏🙏 "እንፈልግሃለን...❗" ዛሬ ከሰዓት 8:30 ገነት ቤ/ክ እንገናኝ...🏃🏃🏃

photo content

Zetseat choir❤️❤️❤️❤️ ✅UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff join share👆👆👆👆👆👆

Story yideregi…… plus enitselyi 😍
Story yideregi…… plus enitselyi 😍

👂 🎷🥁SOUND CHECKUP 🎤🎹🎧 😍 እንፈልግሀለን concert 2015 ሊከናወን በጣት የሚቆጠሩ ስዓታት ቀሩን እኛ ዝግጅታችን ጨርሰናል እናንተም ቦታ ለማግኘት በጊዜ እንድትገኙ ስንል ጥ
+4
👂 🎷🥁SOUND CHECKUP 🎤🎹🎧 😍 እንፈልግሀለን concert 2015 ሊከናወን በጣት የሚቆጠሩ ስዓታት ቀሩን እኛ ዝግጅታችን ጨርሰናል እናንተም ቦታ ለማግኘት በጊዜ እንድትገኙ ስንል ጥሪያችንን እናቀርባለን ነገ ከሰዓት መንገዶች ሁሉ ወደ ሀዋሳ ገነት ቤተክርስቲያን ያመራሉ 😍😍

photo content

😍ሌሎቻችሁ post or story ስታደርጉ #mention ስለምታደርጉን ከልብ እናመሰግናለን 🙏
+7
😍ሌሎቻችሁ post or story ስታደርጉ #mention ስለምታደርጉን ከልብ እናመሰግናለን 🙏

🤩ሰላም ሰላም ሰላም እንዴት ቆያቹ Union fellowship ብለው search በማድረግ ወይንም ከላይ ባላው ምስል QR CODE SCAN #follow በማድረግ በ instagram የ Union fell
🤩ሰላም ሰላም ሰላም   እንዴት  ቆያቹ Union fellowship  ብለው search በማድረግ ወይንም  ከላይ  ባላው  ምስል QR CODE  SCAN   #follow  በማድረግ በ instagram የ Union fellowship ቤተሰብ ይሁኑ #ዋነኛው ስራ በ Ig story or post ስታደርጉ Union #fellowship ን #mention በማድረግ ተባበሩን ፀጋ ይብዛላችሁ ❤️❤️💯💯 #follow  #follow  #follow  #follow  #follow #follow  #follow  #follow  #follow #follow #follow #follow #follow ✅UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff join share share👆👆👆

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች። ⏩ ትናንት ካቆምንበት(እነዚህ ፈላስፎች በተለይም የመኖራችን፣ የመፈጠራችን ዓላማ ምንድነው? የሚለውን ሲመልሱ የሚሉትን) አሁን ቀጥለን እናያለን። ➤ "የኤፌቆሮስ መልስና እምነት በዚህ ጥያቄ ላይ :- 🔺 አማልክት ከእኛ በጣም የራቁና ስለሰዎች ትኩረት የሌላቸው ናቸው ይላሉ፣ 🔺 ሁሉም ነገር የሚሆነው በዕድል ነው ብለው ያምናሉ፣ 🔺 ትልቁ የሰዎች የመኖር ዓላማ ደስታ ሲሆን ያም ህመምና ስቃይ ሳይገኝበት የሚሆን ደስታ ነው ይላሉ። ➤ የኢስጦኢኮችን እምነት ስንመለከት ደግሞ :- 🔻 የእግዚአብሔር ሕይወት በሁሉም ነገር ውስጥ ይኖራል ስለዚህ ከእኛ ተለይቶ እግዚአብሔር ሊገለጥ አይችልም ይላሉ፣ 🔻 የትኛውም የሚሆነው ነገር ሁሉ በዕድል የተወሰነ ነው ይላሉ፣ 🔻 ከሁሉ በላይ መኖር በምክንያትና በሌሎች ላይ ባለመደገፍ ሊሆን ይገባል ብለው ያምናሉ።" ሐዋሪያው ጳውሎስ ለእነዚህ ሰዎች ምንም እንኳን አማልክትን የሚፈሩ የሃይማኖት ሰዎች ቢሆኑም ለማይታወቅ አምላክ በመስገዳቸው ያንን ሳያውቁ የሚያመልኩትን፣ የሚከተሉትን፣ የሚሰግዱለትን ሊያሳውቃቸው (በሐዋ 17:24-28) እንዲህ አለ የማይታወቅ አምላክ የምትሉት :- 💥 እርሱ የሁሉ ፈጣሪ ነው (ቁ.25) 💥 እርሱ በእጅ በተሠራ ሕንፃ ውስጥ አይኖርም (ቁ.27፣28) 💥 እርሱ በሰው ላይ አይደገፍም (ቁ.25) 💥 ሰው ግን በእርሱ ላይ ይደገፋል (ቁ.25) 💥 እርሱ የሁሉ ነው (ቁ26) ጳውሎስ በዚህ ክልል የመኖርን ዓላማ ላልተረዱ፤ ነገር ሁሉ በዕድል የተወሰነ ነው ለሚሉና እግዚአብሔር በሁሉ ነገር ውስጥ ይገለጣል ብለው ጥበባዊ ወግ እንጂ ስለ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ዕውቀት ለሌላቸው ፈላስፎችና ሊያዳምጡ ለተሰበሰቡ ሁሉ የእግዚአብሔርን ፍላጎት ይኸውም "እርሱን እንድንፈልገውና መርምረን እንድናገኘው" እንደሆነ በማሳየት ይህ እግዚአብሔር ደግሞ (በሐዋ 17:30-31) እንደተገለጸው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኝ ዕውቀት እንደሆነና ያለማወቅ ዘመን በክርስቶስ መገለጥ እንዳለፈ ዓለም ባያምነው እግዚአብሔር ባዘጋጀው በክርስቶስ እንደሚፈርድ ሲገልፅና ሲያስረዳቸው የአገሩን ዳኛ ጨምሮ ብዙዎች እንዳመኑና እንደተባበሩ ክፍሉ ያስረዳል። (ሐዋ 17:34) በሐዋ 17:26-27 ላይ ተጽፎ እንደምንመለከተው እግዚአብሔር የሰውን ወገኖች ከአንዱ ከአዳም ሲፈጥር ግልጽ የሆነ የተፈጠረበትን ዓላማ አስቀምጦልናል። ይህም ዓላማ :- ⏩ ይቀጥላል ...❗ "እንፈልግሃለን"