en
Feedback
UNION FELLOWSHIP©✝

UNION FELLOWSHIP©✝

Open in Telegram

#we deal about the strength and weakness of our fellowship #we advertise what programmes we have and had in the week. #we address you an information about such things whole over Ethiopia. #PRAYER IS THE ONLY MEANS OF RECEIVING SPIRITUAL POWER!!!!! @UACSFF

Show more
553
Subscribers
+124 hours
+17 days
No data30 days
Posts Archive
‹‹በእግዚአብሔር መገኘት ወይም ሓልዎት ውስጥ ለመሆን፣ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሆን የግድ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ልባችንን በማንኛውም ጊዜ ከእርሱ ጋር ለመነጋገር መግባት የምንችልበት የግላችን ቤተ መ
‹‹በእግዚአብሔር መገኘት ወይም ሓልዎት ውስጥ ለመሆን፣ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሆን የግድ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ልባችንን በማንኛውም ጊዜ ከእርሱ ጋር ለመነጋገር መግባት የምንችልበት የግላችን ቤተ መቅደስ ማድረግ እንችላለን፡፡ ይህ ከእርሱ ጋር የምናደርገው ንግግር፣ ማንኛውም ሰው ሊኖረው የሚችል ፍቅርና መግባባት ሊሆን ይችላል፡፡ ታዲያ፣ ያንን ማድረግ ላለመጀመር በቂ ምክንያት አላችሁ?›› @uacsff @uacsff

photo content

¶ ጸጋ ይብዛላችሁ ቅዱሳን። ትናንት "እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት ምን ማለት እንደሆነ በጥቂቱ አይተን ነበር ፤ ዛሬ ደግሞ አዲስ ሃሳብ እንጀምራለን እንድትከታተሉ ጋበዝኳችሁ...። 👤👤 የሰው የመፈጠሩ ዓላማ የነገሮች መጋጨትና መደባለቅ የአጋጣሚ ግኝት ወይም በዘገምተኛ ለውጥ ሳይሆን በእግዚአብሔር አምሳልና መልክ የተፈጠረው የእግዚአብሔር ፍጡር የሆነው ሰው ነፍሱ ስትፈጠር ቅዱስና ጠቢብ ስትሆን በኃጢአት ከመውደቁ በፊት በጽድቅና በዕውቀት ነፍሱ የከበረች ነበረች እንዲሁም አካሉ ከበሽታና ከሞት ነጻ የነበረ ሲሆን ኑሮውም በኤደን ገነት የተባረከ እንደነበረ መጽሐፍ ቅዱስ (በዘፍ 2) ላይ ይነግረናል። ነገር ግን በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረው ሰው በሰይጣን ተንኮል ተታልሎ የአምላኩን ትዕዛዝ በመተላለፍ በኃጢአት ሲወድቅ እግዚአብሔርን መፈለግ፣ መከተል፣ እንዲሁም ለማምለክ የማይችል ሆነ። ይህም የሚያመለክተው በአንድ ሰው ምክንያት "ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ" (ሮሜ 5:12) እዚህ ላይ ማስተዋል የሚገባን በአንድ አዳም አለመታዘዝ ምክንያት ኃጢአት የሰውን ዘር ተፈጥሮ ከመጸነሱ ጀምሮ በመቆጣጠር ሰውን ከፍጥረቱ ጀምሮ ከእግዚአብሔር ለየው። ስለዚህ ነው (ኤፌ 2:1-2) "በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ... እንደሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን" የሚለው። ስለዚህ በስጋ ከምድራዊ ወላጆቹ የተወለደ ሰው በክርስቶስ በማመን ዳግም መወለድ አለበት። 🔑 የዳነ በክርስቶስ ያመነ፣ ያላመነውም ለምን ተፈጠርኩ❔ብሎ ይጠይቃል። ይህን መጠየቁ የዚህ ምድር ኑሮውን በስኬት ለማሳለፍ ካለው ጉጉት የመነጨ ሲሆን ለዚህም ጥያቄው ደግሞ መልስን ለማግኘት ዘወትር ያስባል፣ የተቻለውን ሁሉ በማድረግ ለምን እንደተፈጠረ የተፈጠረበትን ዓላማ ለማወቅ ይጥራል። መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ ለምን እንደተፈጠርን የተለያዩ እውነቶችን ቢነግረንም በዚህ ጽሑፍ የተፈጠርንበትን አንዱንና ዋነኛውን ዓላማ እንመለከታለን። "ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደሆነ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ሥፍራ ዳርቻ መደበላቸው ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።" ሐዋ 17:26-27 ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ቃል በሚያስተምርበት ጊዜ በተሰሎንቄና በቤሪያ ከሚያሳድዱት ሰዎች የተነሳ ወደ አቴና እንደመጣ (በሐዋ 17:1-15) ተጽፎ እናገኛለን። ጳውሎስ ወደ ግሪክ ከተማ አቴና በመጣ ጊዜ ከተማይቱ የንግድ ማዕከል ስትሆን በፖለቲካውም አንጻር ኃያል የነበረች ዲሞክራሲ የሰፈነባት ከተማና በትልልቅ ሕንጻዎች የተዋበች እንዲሁም በስነ ጽሑፍና በሥነ ግጥም ትታወቅ ነበር። እስከዛሬም ድረስ የገጣሚዎቻቸውና የተመራማሪዎቻቸው ሥራ እየተጠና እንደሆነ የሥነ ምርምር ጥናቶች ይጠቁማሉ። ጳውሎስ በዚህች ከተማ ውስጥ ከታላላቅ በፍልስፍና ከረቀቁ መስማትና መናገርን ከሚወዱ ሰዎች ጋር ንግግሩን የጀመረው (በሐዋ 17:24) እንደምንመለከተው "እግዚአብሔር ፈጣሪያችን" በሚለው በሚያግባባቸው ቃል ነበር። ምክንያቱም (በሐዋ 17:17-28) እንደምናነበው በዚያን ዘመን የነበሩት የኤፌቆሮስና የኢስጦኢኮች ፈላስፎች ከጳውሎስ ጋር ተገናኝተው ነበር። እነዚህ ፈላስፋዎች በጥንት የግሪክ ትምህርት የተማሩ ሲሆኑ በመጠየቅና በመመለስ ይታወቃሉ። 🔎 በተለይም የመኖራችን፣ የመፈጠራችን ዓላማ ምንድነው❔የሚለውን ሲመልሱ እንዲህ ይሉ ነበር :- ⏩ ነገ ይቀጥላል...❗ " እንፈልግሃለን "

#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 5ተኛ ዙር #pp #challenge በ UNION FELLOWSHIP #ግንቦት 5 ከ 8:30 ጀምሮ #ሀዋሳ ገነት ቸርች ከያኔት የጤና ኮሌጅ 100m ገባ ብሎ Profile Chal
#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 5ተኛ ዙር #pp #challenge በ UNION FELLOWSHIP #ግንቦት 5 ከ 8:30 ጀምሮ #ሀዋሳ ገነት ቸርች ከያኔት የጤና ኮሌጅ 100m ገባ ብሎ Profile Challenge ✅UNION FELLOWSHIP 4additional information 👇👇👇👇👇👇👇 @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff join share👆👆👆👆👆👆

“እኔ ከምሰጠው ውኃ የሚጠጣ ሁሉ ግን ለዘላለም አይጠማም፥ እኔ የምሰጠው ውኃ በእርሱ ውስጥ ለዘላለም ሕይወት የሚፈልቅ የውኃ ምንጭ ይሆናል እንጂ አላት።” — ዮሐንስ 4፥14 እዚህ ላይ ውሃ የተባለው
“እኔ ከምሰጠው ውኃ የሚጠጣ ሁሉ ግን ለዘላለም አይጠማም፥ እኔ የምሰጠው ውኃ በእርሱ ውስጥ ለዘላለም ሕይወት የሚፈልቅ የውኃ ምንጭ ይሆናል እንጂ አላት።”   — ዮሐንስ 4፥14 እዚህ ላይ ውሃ የተባለው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ ዓለም በፍጹም ማርካት አይችልም፡፡ ማንኛውንም ዓለማዊ ርካታ በተመለከተ፣ ‘ማንም ከዚህ ውሃ የሚጠጣ ይጠማል፡፡’ ማለት ይቻላል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ግን ማንኛውንም የተጠማ ነፍስ የማርካት ኃይል አለው፡፡ የሰውን ልብ የሚያረካ መንፈስ ቅዱስና እርሱ ብቻ ነው፡፡ ልብህ ውስጥ ለሚመነጨውና ለሚፈሰው መንፈስ ቅዱስ ራስህን ከሰጠህ በፍጹም አትጠማም፡፡ በምን ዐይነት መነገር በማይችል ደስታ፣ በምን ዓይነት መግለጥ በማይቻል ርካታ፣ የእርሱ ሕያው ውሃ የብዙዎችን ነፍስ አርክቶ ይሆን፡፡ በውስጣችሁ ይህ ሕያው ምንጭ አለ? ያንን ምንጭ የደፈነ ምንም ነገር የለም? ለዘላለም ሕይወት በሚሆን ሁኔታ እየፈለቀ ነው? @uacsff @uacsff

S,Etsube❤️❤️❤️ ✅UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff join share 👆👆👆👆

photo content

photo content

photo content

በደሙ የነጻችሁ፣ በቅዱሱ መንፈስ የተቀደሳችሁ ቅዱሳን ከአምላካችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ጸጋና ሙሉ ሰላም ይብዛላችሁ 🙌🙌 በቀደሙት ቀናት እግዚአብሔርን መፈለግ ከቅዱስ ቃሉ አንጻር በሁለት መሠረታዊ ሃሳቦች ላይ የተብራራ መልዕክት ያዘለ እውነት የሆነ ንድፍ እንደሆነና የመጀመሪያውን (እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት ምን ማለት) እንደሆነ ለማየት ሙከራ አድርገን ነበር። አሁን ሁለተኛውን መሠረታዊ ሃሳብ ከዚህ በመቀጠል ስለምንዳስስ እንዲትከታተሉ ይሁን። ● እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት በተሰጠ ሕይወት ሁለንተናን ለእግዚአብሔር ማቅረብና ማስገዛት ነው። "እንግዲህ ወንድሞች ሆይ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መስዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርህራሄ እለምናችኋለሁ እርሱም ለአዕምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው።" (ሮሜ 12:1) ➤ እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት በግልና በጋራ በተሰጠ ሕይወት በአምልኮ ራስን ማስገዛት ሲሆን ይህም እግዚአብሔርን መፈለግ በጸሎትና ቃሉን በማጥናት በጽድቅና በቅድስና በመኖር ፈቃዱንም መፈጸም በተሰጠ ማንነት እግዚአብሔርን የማምለክ ሕይወት ነው። ይህ በግልና በጋራ የሆነ በእግዚአብሔር ፊት የመገኘት ሕይወት በሦስት ምክንያቶች ሊከናወን ይችላል። ⓵ እግዚአብሔርን ለማወቅ " እንወቅ እናውቀውም ዘንድ እግዚአብሔርን እንከተል።" (ሆሴ 6:3) "... እግዚአብሔርን የፈለገ ሁሉ ከሰፈር ውጭ ወዳለው ወደ መገናኛው ድንኳን ይወጣ ነበር።" (ዘፀ 33:7) እግዚአብሔርን የሚወዱ ሁሉ ያመልኩታል ለሚወዱት ደግሞ ራሱን የሚገልጥ አምላክ ስለሆነ በጽድቅ በመኖር የጠራንን ለመምሰል ዘወትር በአምልኮ በጸሎትና ቃሉን በማጥናት ፊቱን የምንፈልግ ሁሉ ራሱን በመግለጥ የአምላክነቱን ኃይል ክብር ጥበብና ዕውቀት በመረዳት እንድናድግ ያስችለናል። ➁ ከእግዚአብሔር ምሪት ለመጠየቅ "... ብዙ ወገኖችና ኃይለኞች አሕዛብ በኢየሩሳሌም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ እግዚአብሔርንም ይለምኑ ዘንድ ይመጣሉ።" (ዘካ 8:21) የእግዚአብሔርን ፊት ስንፈልግ ከእርሱ ዘንድ ምሪትን፣ የፈቃዱን ዕውቀት፣ የተሰወረን ሚስጥር የምናገኝ ሲሆን እኛ ግን በተሰጠ ሕይወት በእውነትና በመንፈስ ዘወትር ልንፈልገው ይገባል። ⓷ ከእግዚአብሔር እርዳታውን ለመጠየቅ " እናንተ ፍርዱን የጠበቃችሁ የምድር ትሑታን ሁሉ እግዚአብሔርን ፈልጉ።" ( ሶፎ 2:3) እረፍትን፣ ፍትሕን፣ ጽድቅንና እውነትን ስንጠማ ለትሑታን ጸጋውን የሚሰጥ ትዕቢተኞችን ግን የሚቃወም የአስፈላጊ ጊዜ እርዳታውን በመግለጥ የተጠባበቁትንና የፈለጉትን የሚያሳርፍ እግዚአብሔር የማዳን ክንዱን የምናይ እንድንሆን በዘመናችን ሁሉ ያስችለናል። ⏩ ይቀጥላል ... ❗ ¶ እ_ን_ፈ_ል_ግ_ሃ_ለ_ን_____

#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 2ተኛ ዙር #pp #challenge በ_ UNION_FELLOWSHIP #ግንቦት_5_ከ_8:30_ጀምሮ #ሀዋሳ_ገነት_ቸርች_ከያኔት_የጤና_ኮሌጅ #100m _ገባ _ብሎ Profile-
#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 2ተኛ ዙር #pp #challenge በ_ UNION_FELLOWSHIP #ግንቦት_5_ከ_8:30_ጀምሮ #ሀዋሳ_ገነት_ቸርች_ከያኔት_የጤና_ኮሌጅ #100m _ገባ _ብሎ Profile-Challenge ✅UNION FELLOWSHIP 4additional information 👇👇👇👇👇👇 @uacsff @uacsff @uacsff       @uacsff @uacsff join share 👆👆👆👆👆

🙌🙌 በጌታ የተወደዳችሁ ውዶች ጸጋና ሙሉ ሰላም ይብዛላችሁ። ____ትናንት ካቆምንበት ትምህርታችንን እንቀጥላለን ..... ወደ እግዚአብሔር የመመለስ የመጠጋት፣ የመቅረብ፣ ዕርቅንም የመፈጸም እና እርሱን የመፈለግ ሕይወት በግለሰብም ይሁን በማህበረሰብ ሕይወት ውስጥ ሊከናወኑ የሚችሉባቸውን ምክንያቶች ትናንት ሁለቱን ለማየት ሞክረናል ዛሬ ደግሞ የተቀሩትን ለማየት እንሞክራለን። ❸ መለኮታዊ ተቀባይነትን ለማግኘት " እናንተ ትሹኛላችሁ በፍጹም ልባችሁም ካሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ" ( ኤር 29:13-14)። መለኮታዊ ተቀባይነትን በማግኘት እግዚአብሔር ወዳየልንና ወደ ገባልን ተስፋ ለመድረስ እያንዳንዳችን ሀጢአታችንን ሳንሰውር በመናዘዝና በመተው በፍጹም ልባችን የእግዚአብሔርን ፊት በመፈለግ ለመመለስ ፈቃደኛ ስንሆን ያን ጊዜ እንደ ባለማዕረግ በክብር ተቀብሎን ጽድቁንና እውነቱን ለብሰን እንደባለጠግነቱ መጠን ባርኮቱንና ምህረቱን በማየት ሞገሱን እንድንለማመድ ያስችለናል። ❹ ከእግዚአብሔር እርዳታን ለማግኘት " በደላቸውንም እስኪያውቁ ድረስ ፊቴንም እስኪሹ ድረስ ሄጄ ወደ ስፍራዬ እመለሳለሁ በመከራቸውም ጊዜ እጅግ አድርገው ፊቴን ይፈልጋሉ" (ሆሴ 5:15)። በክፋታችን ጸንተን ለማንመለስና ሀጢአታችንን ተገንዝበን ምህረትን ለማንጠይቅ የእግዚአብሔር ቁጣ በእኛ ላይ ሲሆን በእውነተኛ ንስሐ ፍቱን ለምንፈለግና ለምንመለስ ግን ምህረቱን በማብዛት በመከራችን ሁሉ በመርዳት የማዳን ኃይሉንና ብርታቱን እንድንለማመድ ያስችለናል። ⏩ ይቀጥላል ....❗ "እንፈልግሃለን..."

ጸጋና ሙሉ ሰላም ይብዛላችሁ። ካቆምንበት እንቀጥላለን.... የእግዚአብሔር እጅ የምታድን ጆሮውም የምትሰማ ሆና ሳለች የሕዝቡ በደልና ሃጢአት ግን በእነርሱና በእግዚአብሔር መካከል ልዩነትን በመፍጠር እግዚአብሔርንና ሰውን ለያየ፤ ስለዚህ ጸሎታቸውን ላለመስማት ሕዝቡን ላለመርዳት እግዚአብሔር ፊቱን ሰወረ። ሀጢአት እግዚአብሔርን ከሰው ይሰውረዋል፣ ይደብቀዋል። ስለዚህ እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት በግለሰብና በሕዝብ ሃጢአት ምክንያት የተሰወረውን እግዚአብሔርን በሃጢአት ኑዛዜና ከተሳሳቱበት ሙሉ በሙሉ በመመለስ ወደ እግዚአብሔር መቅረብን፣ መጠጋትን ከእርሱ ጋር ሰላምንና ሕብረትን ዕርቅም መፍጠርን የሚያሳይ ሃሳብ ነው። ይህ ዓይነቱ ወደ እግዚአብሔር የመመለስ፣ የመጠጋት የመቅረብ ዕርቅንም የመፈጸም እርሱንም የመፈለግ ሕይወት በግለሰብም ይሁን በማሕበረሰብ ሕይወት ውስጥ በአራት ዋና ዋና ምክንያቶች ሊከናወን ይችላል። ❶ ከእግዚአብሔር የሃጢአት ይቅርታንና ፈውስን ለመቀበል " በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ ፊቴንም ቢፈልጉ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ ሃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ " (2ዜና 7:14)። ከእግዚአብሔር የሃጢአት ይቅርታን መቀበል ለሰው ልጅ ከሁሉ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። ስለሆነም እሱን በመፈለግ ይቅርታውንም በማግኘት የተበላሸብንን ህብረት ማደስና በሃጢአት ምክንያት የተሰወረውን እግዚአብሔርን ማግኘት በመንፈሳዊና በምድራዊ ሕይወታችን ፈውስን እንድንቀበል ያስችለናል። ❷ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ሕብረት ለማደስ "... ነገር ግን ከዚያ አምላካችሁን እግዚአብሔርን ትሻላችሁ በልብህም ሁሉ በነፍስህም ሁሉ የፈለግኸው እንደሆነ ታገኘዋለህ " (ዘዳ 4:29)። የእግዚአብሔር ሕዝቦች የሆንን ሁሉ ከአምላካችን መንገድ ዘወር ባልን ጊዜ ወደ እርሱ ተመልሰን ሕብረታችንን በማደስና ራሳችንን ሙሉ በሙሉ ለእርሱ በመስጠት በእውነተኛ ኑዛዜና መመለስ እግዚአብሔርን በመፈለግ ጤናማ አንድነትና ህብረት በመፍጠር ከአምላካችን ጋር ታርቀን በፊቱ በትህትና በመሄድ እርሱን በመፍራት እየታዘዝነው ለመውደድና ለማገልገል ያስችለናል። ⏩ ይቀጥላል...❗ " እንፈልግሃለን "

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ ምርጦች። እስከሚቀጥለው ቅዳሜ ድረስ ድንቅ "እግዚአብሔርን ስለ መፈለግ" የተዘጋጀ ትምህርት በቻናሉ የሚቀርብ ስለሆነ እንዲትከታተሉ በአክብሮት እንጋብዛችኋለን። አዘጋጅ ዳንኤል ደሣለኝ ¶ እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት ምን ማለት ነው? በክርስቶስ ኢየሱስ የዳነ የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ልጅ የሆነ አማኝ ከእርሱ ያልራቀውን የሚኖርበትንና የሚንቀሳቀስበትን እስትንፋሱን ሁሉ የያዘውን ሕያው እግዚአብሔርን ሊፈልገው ይገባል። እንዲሁም "ዋላ ወደ ውሃ ምንጭ እንደሚናፍቅ አቤቱ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች" (መዝ 42:1)። ተብሎ እንደተጻፈ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ሁሉ በከፍተኛ ናፍቆትና ጥማት ከነፍሱ ፍላጎት እግዚአብሔርን ሊፈልገው እንደሚገባ ከላይ በተገለጸው ክፍል የሚያስረዳን ሲሆን እግዚአብሔርን ስለመፈለግ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ድረስ በስፋትና በጥልቀት የተገለፀ በመሆኑ ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ አንጻር የዚህን ሃሳብ ትርጓሜ መመልከት ያስፈልጋል። ¶ እግዚአብሔርን የመፈለግ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ እግዚአብሔርን መፈለግ ከቅዱስ ቃሉ አንጻር በሁለት መሠረታዊ ሃሳቦች ላይ የተብራራ መልዕክት ያዘለ እውነት የሆነ ንድፍ ሲሆን ይህንንም መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ከዚህ በመቀጠል እናያለን። ● እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት:- በሃጢአት ምክንያት የተሰወረውን እግዚአብሔርን ለማግኘት የሚደረግ ኑዛዜና መመለስ ነው "እነሆ የእግዚአብሔር እጅ ከማዳን አላጠረችም ጆሮውም ከመስማት አልደነቆረችም ነገር ግን በደላችሁ በእናንተና በአምላካችሁ መካከል ለይታለች እንዳይሰማም ሃጢአታችሁ ፊቱን ከእናንተ ሰውሮታል" (ኢሳ 59:1-2)። ⏩ .... ይቀጥላል ❗ "እንፈልግሃለን"

#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 3ተኛ ዙር #pp_challenge በ_UNION FELLOWSHIP #ግንቦት_5_ከ_8:30_ጀምሮ #ሀዋሳ ገነት ቸርች ከያኔት ኮሌጅ 100m ገባ ብሎ profile-challenge
#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 3ተኛ ዙር #pp_challenge በ_UNION FELLOWSHIP #ግንቦት_5_ከ_8:30_ጀምሮ #ሀዋሳ ገነት ቸርች ከያኔት ኮሌጅ 100m ገባ ብሎ profile-challenge ✅UNION FELLOWSHIP 4additional information 👇👇👇👇👇👇👇 @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff join share👆👆👆👆👆👆

🖕🖕🖕🖕🖕🖕🖕

photo content

Awo wedajoche endemin nachu ene wendmachu Dagi negn I think kaliresawugn ke 3 amet be fit be Union fellowshipachn bexam ye midenk gize 🗣eyesus yimexal ✍ bemil ris yazegajenewu concert midenik gize hono alifo neber zarem kebizu gize buhala ya kibr beteshale kibr liyasdeniken ken eyekoxerinw enalachu zinbye yemiwedachu wedajoche😍😍 promotionun behulum menged enisira yane yetazezachu hulum ahunm bemetazez abiren enisira elalewu .be neger hulu Geta yirdachu ligegn balemechalewu bazinm gn be enanite mebarek des yilegnal zemenachu yibarek be digam ene wendmachu ye kedimo ye fellowshipu ageligay Dagi zinbye nw miwedachu🥰🥰🥰🥰🥰😍😍😍😍degimo saliresa eyen mitanebu hulachihum Pp lay adirgu Awo adirgu ye wendm tizaz nw👏👏👏👏👏👏👏👏 UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff 🖕🖕🖕🖕🖕🖕🖕

#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 2ተኛ ዙር #pp #challenge በ_ UNION_FELLOWSHIP #ግንቦት_5_ከ_8:30_ጀምሮ #ሀዋሳ_ገነት_ቸርች_ከያኔት_የጤና_ኮሌጅ #100m _ገባ _ብሎ Profile-
#እንፈልግሀለን_ኮንሰርት 2ተኛ ዙር #pp #challenge በ_ UNION_FELLOWSHIP #ግንቦት_5_ከ_8:30_ጀምሮ #ሀዋሳ_ገነት_ቸርች_ከያኔት_የጤና_ኮሌጅ #100m _ገባ _ብሎ Profile-Challenge ✅UNION FELLOWSHIP 4additional information 👇👇👇👇👇👇 @uacsff @uacsff @uacsff       @uacsff @uacsff join share 👆👆👆👆👆