3 156
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5330 days
Posts Archive
3 156
በየትኛም የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኝ ኢትዮጵያዊ ሀገሩን ለማዳን እንዲነሳ የፌዴራል መንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ጥሪ አቀረበ።
https://www.amharaweb.com/በየትኛም-የኢትዮጵያ-ክፍል-የሚገኝ-ኢትዮ/
አዲስ አበባ፡ ጥቅምት 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የፌዴራል መንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶክተር) በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያን ሊያፈርስ የተነሳውን የትህነግ የሽብር ቡድንን ለማጥፋት ሁሉም በየአካባቢው እንዲዘጋጅ አሳስበዋል። በቀጣይ ትግሉን ለማቀጣጠል አቅጣጫዎች መቀመጣቸውንም አስረድተዋል። ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ኢትዮጵያ አሁን የሚያስፈልጋት ታታሪ ወታደር እና ታታሪ ሠራተኛ እንጂ ታታሪ ወረኛ አይደለም ብለዋል። ሀገሪቱ አሁን የተደቀነባትን የሕልውና አደጋ ለመመከት [...]
3 156
"ድሉን ለማፍጠን በወሬ የማይሸበር የሕዝብ ደጀን ወሳኝ ነው!" የቀድሞው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት አባላት
ደሴ፡ ጥቅምት 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በግንባር የተሰለፈው ሠራዊት ድሉን እንዲያፈጥን እና አኩሪ ጀብድ እንዲያስመዘገብ በወሬ የማይሸበር የሕዝብ ደጀን ወሳኝ መሆኑን በደቡብ ወሎ ዞን የሚገኙ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት አባላት ለአሚኮ ተናግረዋል።
መቶ አለቃ መሠለ መኮንን የደቡብ በወሎ ዞን የቀድሞው የኢትዮጵያ ጦር ኀይሎች ማኅበር ሊቀመንበር ናቸው። "በአሉባልታ የማይሸበር ጠንካራ የሕዝብ ደጀን ለሠራዊቱ ሞራል በመስጠት ፈጣን ድል እንዲያስመዘግብ ወሳኝ ሚና አለው" ብለዋል።
"የሕዝቡ ተግባር ከሽብር ወሬ ርቆ ሠራዊቱን መደገፍ ብቻ ነው" የሚሉት መቶ አለቃ መሠለ ወታደራዊ ትግሉን ለጦር መሪዎች ብቻ መተው እንዳለበትም ጠቅሰዋል። ሠራዊቱም ይህንን ማዕበል የሆነ ሕዝባዊ ደጀንነት ተመርኩዞ በአጭር ጊዜ ድል ያስመዘግባል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል።
በቀድሞው የኢትዮጵያ ሠራዊት የምድር ጦር አባል የነበሩት ሻምበል ሀሽም ጀማል በበኩላቸው በኢትዮጵያ ታሪክ ለሠራዊት እንደ አሁኑ ማዕበል የሆነ የሕዝብ ደጀን ታይቶ አይታወቅም ይላሉ። ሠራዊቱ ይህንን ጠንካራ ሕዝባዊ ደጀን ተጠቅሞ በአጭር ጊዜ ድል ያደርጋል ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል።
በጦርነት ውቅት ፍጹም የተረጋጋና ወታደራዊ ሚስጥሮችን ለጦር መሪዎች የተወ ሕዝባዊ ደጀንነት ለድሉ ቁልፍ ነው የሚሉት ሻምበል ሀሽም ወታደራዊ ሙያ በመስዋእትነት ላይ የተመሰረተ ነውና ሕዝቡ ከበሬ ወለደ ወሬ እራሱን ጠብቆ አስተማማኝ ደጀንነቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የቀድሞው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት አባላት የካበተ ወታደራዊ ሙያቸውን ተጠቅመው ለሀገራቸው አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ:– ግርማ ሙሉጌታ-ከደሴ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ በቆጋ መስኖ ፕሮጀክት የለማ የአቮካዶ እና የተለያዩ ሰብሎች ጉብኝት እየተካሄደ ነው።
ፍኖተ ሰላም፡ ጥቅምት 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በቆጋ መስኖ ፕሮጀክ ጉብኝት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል። በቆጋ ተፋሰስ መስኖ ፕሮጀክት ከ6 ሺህ 500 ሄክታር መሬት በላይ በአቮካዶ፣ ስንዴ፣ በቆሎ እና የተለያዩ የጓሮ አትክልቶች በመልማት ላይ እንደሚገኙ የፕሮጀክቱ ልማት ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አብዮት ብሩ ገልጸዋል። በዚህም 10 ሺህ አርሶ አደሮች በመስኖ ልማቱ እየተሳተፉ ይገኛሉ ነው ያሉት።
ከ2009 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ ለፍራፍሬ ልማት በተለይም ለአቮካዶ ልማት ትኩረት መሠጠቱንም ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል። በዚህ ወቅት በመስኖ ፕሮጀክቱ በ10 ቀበሌዎች በ12 ኩታገጠም 260 ሄክታር መሬት በአቮካዶ እንደለማ ተነስቷል፤ በልማቱ 845 አርሶ አደሮች ተሳታፊ ናቸው።
የምርቱን ጥራት አስጠብቆ ወደ ውጭ ለመላክ የሚያስችል ማቀዝቀዣ ማሽን በ18 ሚሊዮን ብር ግዥ መፈጸሙን የመስኖ ፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ለጎብኝዎቹ አብራርተዋል። የመስኖ ፕሮጀክቱ ግድብ 83 ሚሊዮን ሜትር ኪዩቢክ ውኃ የመያዝ አቅም ያለው የክልሉ ከፍተኛ የልማት ፕሮጀክት እንደሆነም ነው የተገለጸው።
የቆጋ መስኖ ፕሮጀክት በ2003 ዓ.ም ተጠናቅቆ ወደ ሥራ ገብቷል። 7 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት የማልማት አቅም እንዳለውም ታውቋል።
ዘጋቢ፦ ዳግማዊ ተሠራ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በባሕርዳር ከተማ ዘንዘልማ ቀበሌ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ አደረገ፡፡
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ከዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ተፈናቅለው በባሕርዳር ከተማ ዘንዘልማ ቀበሌ ተጠልለው ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የምግብና የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል።
ድጋፉን ያስረከቡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሸባሪው ትህነግ በአማራ ክልል ያደረሰው ግፍና በደል በመላ ኢትዮጵያ የደረሰ ነው ብለዋል፡፡
ከንቲባዋ አሸባሪ ቡድኑን መላ ኢትዮጵያዊያን ተረባርበው በመቅበር ተፈናቃዮችን ወደ ቦታቸው መመለስ እና ማቋቋም እንደሚገባቸው ነው የተናገሩት፡፡ ዛሬ የተደረገው ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የምግብና የአልባሳት ድጋፍም ከተማ አስተዳደሩ ከተፈናቃዮች ጎን መሆኑን ለማሳየት እንደሆነ ነው ያብራሩት።
ከንቲባ አዳነች ተፈናቃዮች ዛሬ በጊዜያዊ መጠለያ ብትኖሩም ከድል በኃላ ወደ ቀያችሁ እንደምትመለሱ አንጠራጠርም ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ተፈናቃዮችን ለማቋቋም በሚደረገው ሥራም እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የአማራ ክልል ርእስ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶክተር) አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዚህ በፊት በሽብር ቡድኑ ከተፈናቀሉ ወገኖች ጎን በመሆን አጋርነቱን አሳይቷል ብለዋል። ዛሬም ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ክልሉ ከሁሉም የጸጥታ ኀይሎችና ከሕዝቡ ጋር በመሆን አሸባሪ ቡድኑን ለመደምሰስ እየሠራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ርእሰ መስተዳድሩ ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሽብርተኛውን ቡድን ለመደምሰስ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ዘጋቢ ፦ አዳሙ ሽባባው
3 156
የሽብር ቡድኑ አባላት በኩታበር፣ ቦሩ እና ተሁለደሬ እየተማረኩ ነው።
ጥቅምት 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአሸባሪው ህወሓት ቡድን አባላት በኩታበር፣ ቦሩ እና ተሁለደሬ ከነመሣሪያዎቻቸው እየተማረኩ መሆኑ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://t.me/amaramassmida
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
አሸባሪው ሕወሐት መሣሪያዎቹን ሲጨርስ ምላሱን መተኮስ ጀምሯል!
ሰሞኑን በደረሰበት ከባድ ምት ከተበታተነው ወራሪ ኃይል መካከል በጣት የሚቆጠረው በቦሩ ሜዳ አቅጣጫ በየወንዙ፣ በየጢሻውና በየሸለቆው ተደብቆ ከርሞ ነበር። ለቀናት ከተደበቀ በኋላ ርሃብና ውኃ ጥም ሲከብደው የእሩምታ ተኩስ በመክፈት ከጉድጓድ እየወጣ የአካባቢውን ሕዝብ ለማደናገር ሞክሯል። አይጥ ከጉድጓዷ በራቀች ቁጥር እንደምትመታው፣ ይሄም የተቆረጠ አሸባሪ ወዲያው ተመትቷል።
የተቆረጠው ኃይል ወደ ሲኦል እየተሸኘ ባለበት፣ በውስጥ ያሠረጓቸው ኃይሎች ጁንታው ወሎ ዩኒቨርስቲ አካባቢን እንደተቆጣጠረ በማስመል የውሸት ፕሮፓጋንዳ እየነዙ ይገኛሉ። ጀግናው መከላከያና መላው የጸጥታ ኃይላችን እነዚህን ባንዳዎች በመልቀም ርምጃ እየወሰደ ነው። ቦሩ ሜዳም ሆነ ከቦሩ ሜዳ ራቅ ያሉት አካባቢዎች በጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን እጅ ላይ ይገኛሉ።
ኅብረተሰቡ የሐሰተኛ ወሬ ፈጣሪዎችንም ሆነ አስተላላፊዎችን ለሕግ እያቀረበ አካባቢውንና ቀዬውን አሁንም በንቃት መጠበቅ ይኖርበታል።
የደሴ ከተማ ሕዝብ የሽብር ቡድኑን የሚያሸንፈው በጽናትና በትግል ብቻ ነው።
በወሬ የተገነባ ከተማ ስለሌለ፣ በወሬ የሚያዝ ከተማ አይኖርም! ሊኖርም አይችልም!
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
3 156
አሸባሪው የትህነግ ቡድን የከፈተውን ወረራ በድል መክተው ወረዳቸውን መታደጋቸውን የጻግብጂ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሄኖክ ነጋሽ ገለጹ፡፡
ጥቅምት 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ከጥቅምት እስከ ጥቅምት በቀጠለው ህልውናን የመታደግ ትግል ብዙ የሕይወትና የንብረት መስዋእትነትን ከፍለዋል፡፡ መስዋእትነት ያላንበረከካቸው የጻግብጂ ወረዳ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን አርበኞች ዛሬም አካባቢያቸውን አስከብረዋል፡፡ መስዋእትነት በመክፈል ሀገርን እስከ ነጻነት ለማሻገር ከጥቅምት እስከ ጥቅምት ስምንት ጊዜ ፊትለፊት ከአሸባሪውና ወራሪው ትህነግ ጋር የገጠሙት የጻግብጂ አርበኞች ታሪክ በድል የደመቀ ነው፡፡
ለኢትዮጵያ የነጻነት ጥሪ፣ ጠላትን ለመቅበር የዋግ ልጆች በሁሉም ግንባር እየተፋለሙ ነው፡፡
አሸባሪው የትህነግ ቡድን በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር እንዲቀበር ከጻግብጂ ሚሊሻዎች ጀብድ በተጨማሪ እንቢ ለባርነት ባሉ የነጻነት አርበኞች እየተለበለበ ነው፡፡
በሰቆጣ፣ በአበርገሌ፣ በዝቋላና በስሃላ ሰየምት ወረዳዎች በሚሊሻ በየቦታው ሽንፈቱን እየተከናነበ ነው፡፡ ዲሽቃና ስናይፐር በክላሽ የሚማርኩ ሚሊሻዎች ጀብዱዎችን እፈጸሙ ይገኛሉ። ይህንን ገድል ከጥቅምት እስከ ጥቅምት "ዱር ቤቴ" ብቻ ሳይኾን "ቤቴን አሳልፌ አልሰጥም" ያለው ጀግናው የጻግብጂ ሚሊሻ በድንጋይ ውርወራ ክላሽ የማረኩ ጀብደኞችንም አሳይቷል፡፡ ሚሊሻዎቹ ከእናቶች አንገት ሀብልና ጀሮ ጌጥ የሰረቀው፤ ከእናት ጎዳ ገብቶ ሊጥና ዱቄት ገልብጦ የወሰደው፤ እንስሳቶቻቸውን በየቦታው እያረደ የጨረሰውን ኃይል "ነገ ይፈታዋል" ከማለት ይልቅ ከዚህ የባሰ ምን ይመጣል ብለው በመስዋእትነት ታሪክን ለመሥራት በየአውደ ውጊያው ጀግንነታቸውን አስመስክረዋል፡፡
ከጥቅምት እስከ ጥቅምት አሸባሪው የትህነግ ቡድን ስምንት ጊዜ የከፈተውን መደበኛ ጦርነት በድል መክተው ወረዳቸውን ከአሸባሪው ሴራ መታደጋቸውን የጻግብጂ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሄኖክ ነጋሽ ተናግረዋል፡፡
ጠላት የታጠቃቸው ዘመናዊ መሳሪያዎችን እና ተተኳሾችን በመማረክም የአባቶቻቸውን ታሪክ እያስቀጠሉ ነው ብለዋል፡፡
ሚሊሻዎቹ የተማረኩ የባንዳው ትህነግ አባላትንም ለመከላከያ ሠራዊት በመስጠት ጀብዳቸውን ማስመስከራቸውን አቶ ሄኖክ ገልጸዋል፡፡
አሸባሪውና ወራሪው ትህነግ ንጹሐንን ገድሏል፤ የመንግሥት እና የግል ንብረቶችንም አውድሟል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ይሁን እንጂ ይህ መሰሪ የግፍና የበደል ተግባር የሕዝቡን አንድነት አጠናክሯል ብለዋል፡፡ ጠላትን ለመቅበር በሚደረገው ርብርብም ሚሊሻና ሕዝቡ ተናበው ድል እያስመዘግቡ መኾናቸውን አብራርተዋል፡፡
አቶ ሄኖክ "ለጠላት እጅ አልሰጥም" በማለት አኩሪ ገድል የሠሩ ሚሊሻዎች ታሪክ ሲዘከር የሚኖር ከመኾኑ ባሻገር ለትውልድ ጀግንነትን ማጋቢያ መሠረት እየኾነ ነው ብለዋል፡፡
የጻግብጂ ወረዳ ሚሊሻ ወረዳውን ከጠላት ነጻ ከማድረግ ባሻገር ወደ ወሎ የመትመም ዘመቻ በመሳተፍ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡
አስተዳዳሪው አሸባሪው ትህነግ በወረራቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች ኅብረተሰቡ ለጠላት የእግር እሳት በመኾን የኢትዮጵያን ሰላም በማረጋገጥ ሊሠራ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ግርማ ተጫነ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
ጣሊያን እና ሕንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የየሀገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ገለጹ።
ጥቅምት 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የጣሊያኑ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉጊ ዲ ማዮ እና የሕንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ሱብራማንያ ጄይሻንካር ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ሚኒስትሮቹ አቶ ደመቀ መኮንን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በመሾማቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
የጣሊያኑ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲ ማዮ በመግለጫቸው የጣሊያን እና ኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ረዥም ዕድሜ ያስቆጠረ ግንኙነት በቀጣይ ወደ ተሻለ ደረጃ መሸጋገር ይገባዋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ቁልፍ ሀገር በመሆኗ አሁን ላይ በውስጧ ያጋጠማትን ፈተና ለማለፍ እያደረገችው ያለውን ጥረት ጣሊያን ትደግፋለች ነው ያሉት።
የሕንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ሱብራማንያ ጄይሻንካር በበኩላቸው ኢትዮጵያ እና ሕንድ በመካከላቸው ያለውን አቅም ሙሉ በሙሉ በመጠቀም ለሁለቱ ሀገራት ዜጎች ይበልጥ ተጠቃሚነት እንደሚሠሩ ያላቸውን ተስፋ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
“የተሰነዘረብንን ጥቃት በመመከት የሀገራችንን አንድነትና ሉዓላዊነት እንጠብቃለን” የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት
https://www.amharaweb.com/የተሰነዘረብንን-ጥቃት-በመመከት-የሀገራ/
አሸባሪው የትህነግ ኃይል በ27 ዓመታት የሥልጣን ዘመኑ አያሌ ዜጎች ላይ መከራና እንግልት በማድረስ የሀገርን ሐብት ሲዘርፍና ሲያዘርፍ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ትህነግ በውስጥና በውጭ እንዲሁም በሐሳብ በተደረገው የተቀናጀ ትግል የሀገራችንን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚመጥን ሐሣብ የማመንጨት አቅም መንምኖበት በ2010 ዓ.ም ከሥልጣን ተወገደ፡፡ ይህ ትግል ያስገኘው ድል ለሀገራችንና ህዝባችን በተስፋ የተሞላ አዲስ ምዕራፍ መክፈት ችሏል፡፡ ይሁን እንጂ አሸባሪው [...]
3 156
በአሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን የተፈናቀሉ ወገኖችን ሁሉም እንዲደግፍ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ጌታቸው ጀንበር ጠየቁ፡፡
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ ያደረጉት የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ጌታቸው ጀንበር አሸባሪው ትህነግ በአማራ ሕዝብ ላይ በፈጸመው ወረራ ከፍተኛ ግፍ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ይህንን ወራሪ ቡድንም ሕዝቡ ሆ ብሎ በመነሳትና በመደምሰስ የአባቶቹን ታሪክ መድገም እንደሚገባው ገልጸዋል፡፡
"ወረራውን መቀልበስና ጠላትን መደምሰስ ካልተቻለ እንደ አማራ ሕዝብ ክብራችንን አስጠብቀን መኖር አንችልም" ነው ያሉት፡፡
ክብርንና ማንነትን ለማስቀጠል በግንባር የሚደረገውን ትግል የሚያግዝ የሎጅስቲክ ድጋፍ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል፡፡ እስካሁን ባለው እንቅስቃሴ ሁሉም እየተረባረበ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የታጠቀ ኃይል ለመፍጠርና ለማዋጋት ከፍተኛ ሃብት እንደሚጠይቀም ገልጸዋል፡፡ ጦርነቱን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ብዙ ሀብት አሰባስቦ፣ ጦርነቱ የሚፈልገውን አሟልቶ ወደ ሥራ መግባት እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡
የተከፈተውን ጦርነት ለመቀልበስና ጠላትን ለመደምሰስ የሎጅስቲክስ እንቅስቃሴው አበረታች መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ወራሪው ካልተቀለበሰና ካልተደመሰሰ እንደ አማራ መኖር አይቻልም ያሉት ምክትል ርእሰ መስተዳድሩ እየተደረገ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል፡፡ ሁሉም ጦርነቱን በሎጅስቲክስ መደገፍ አለበት ነው ያሉት፡፡ የተሰበሰበው ሀብት ለተፈለገው አገልግሎት በፍጥነት ወደ ግንባር እየተላከ የወገን ጦርን አቅም እንዲገነባ ጥረት እናደርጋለንም ብለዋል፡፡ የሚገባው ሀብት በቁጥጥርና በስርዓት እየተዳረሰ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በርካታ ወገኖች መፈናቀላቸውን ያነሱት ምክትል ርእሰ መስተዳድሩ የተሰበሰበው ሀብት ለተፈናቀሉ ወገኖች እየተዳረሰ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የተፈናቃይ ወገኖች ቁጥር በርካታ በመሆኑ በቂ ድጋፍ እንዳልደረሳቸውም ገልጸዋል፡፡ ሁሉንም አቅም በማሰባሰብ ወገኖችን መደገፍ ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ሁሉም ተፈናቃይ ወገኖችን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
ጠላትን ለመቅበር ከዳር እስከ ዳር በመትመም መደምሰስ አለብንም ነው ያሉት፡፡ የታጠቀው ኃይል፣ ወጣቶች ወደ ግንባር በመሄድ፣ ባለሀብቶች ሀብት በማሰባሰብ እና ደጀኑ ሕዝብ ስንቅ ከማቀበል ባለፈ ወደ ግንባር የሚሄዱ ዘማች ቤተሰቦችን መንከባከብ አለበትም ብለዋል፡፡
ሕዝቡ የአካባቢውን ሰላምና ደኅንነት መጠበቅ እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡ ለጸጥታ ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ እንቅስቃሴዎችን በንቃት በመከታተል የድርሻውን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ጠላትን መውጫና መግቢያ ማሳጣት እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
በመንግሥት ሥራ ውስጥ ያሉና ለመታገል ዝግጁ የሆኑ ወደ ግንባር እንዲሄዱም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አሁን በግልና በመንግሥት ተቋማት ተቀጥረው የሚሠሩ የመከላከያ ሠራዊት አባል የነበሩ ደመወዛቸውን እየከፈሉ ጦርነቱ ተጠናቆ በድል እስከሚመለሱ ድረስ ፈቃድ ሰጥተው እንዲሸኟቸውም አሳስበዋል፡፡
"ከቤት ተቀምጦ ድል የሚናፍቅ ከሆነ ድል ማግኘት አይቻልም" ነው ያሉት፡፡ ችሎታውና ብቃቱ ያለው ማድረግ ያለበትን ሁሉ ማድረግ አለበትም ብለዋል፡፡ ጦርነቱ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታርቆ ክንዴ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
አሸባሪው ትህነግ በኩታበር ግንባር ከባድ ሰባዊና ቁሳዊ ውድመት ደርሶበታል።
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው የትህነግ ቡድን በኩታበር ግንባር በደረሰበት ሰባዊና ቁሳዊ ውድመት በርካታ የዲሽቃ ጥይቶችን ተማርኳል።
የድሽቃ ጥይቶችንም ወጣቶች በግንባሩ ለሚፋለመው የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ሠራዊት አስረክበዋል። የድሽቃ ጥይቶችን ለሕዝባዊ ሠራዊቱ ሰብስበው ካስረከቡ ወጣቶች መካከል አሕመድ አራጌ የአሸባሪው ትህነግ ቡድን በኩታበር ግንባር ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበት መመልከቱን ተናግሯል።
በግንባሩ ከሚፋለሙ የወገን የሠራዊት አባላት መካከል ፋኖ ሀብታሙ በላይ የደሴ ከተማ ሕዝብ የሚያደርግላቸውን ድጋፍ አመስግኖ ወጣቱ ለህልውና ዘመቻው ከሕዝባዊ ሠራዊቱ ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ አቅርቧል።
ዘጋቢ:–ካሳሁን ኃይለሚካኤል–ከደሴ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
”የአማራ ሕዝብ ነጻነቱን የሚያስከብረው በክንዱ ነው“ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ጌታቸው ጀንበር
https://www.amharaweb.com/የአማራ-ሕዝብ-ነጻነቱን-የሚያስከብረው/
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 18/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ሕዝብ በጥንተ ጠላቱ ትህነግ ዛሬም የተለያዩ በደሎች እየደረሱበት ነው፡፤ ለዓመታት በኢትዮጵያ ስልጣነ መንበር ላይ የቆየው አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ስብስብ በአማራ ላይ እልፍ በደሎችን ፈጽሟል፤ ዛሬም መፈፀሙን ቀጥሏል፡፡ በመዋቅር የታገዘ በደል ሲፈጽም የነበረው አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ዛሬ ደግሞ ጦርነት ከፍቶ አማራን ወርሯል፣ ንጹኀንን ገድሏል፣ ሴቶችን ደፍሯል፣ ሀብት ዘርፏል፣ [...]
3 156
የባሕር ዳር ከተማ ሕዝባዊ ሠራዊት ወደ ግንባር ሽኝት ተደረገለት፡፡
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 18/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል መንግሥት የክተት ጥሪውን የተቀበሉ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሕዝባዊ ሠራዊት አባላት ዛሬ ሽኝት ተደርጎላቸዋል፡፡
አሸባሪው ትህነግ ለአማራ ሕዝብም ኾነ ለመላው ኢትዮጵያውያን ስጋት በማይሆንበት ደረጃ ለማጥፋት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የክተት ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡ ለቀረበው ጥሪ ከኹሉም የክልሉ አካባቢዎች ተግባራዊ ምላሽ እየተሰጠ ነው፡፡ በባሕር ዳር ከተማ መሠረታዊ ወታደራዊ ስልጠና የወሰዱና የክተት ጥሪውን የተቀበሉ የሕዝባዊ ሠራዊት አባላት ሽኝት ተደርጎላቸዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዶክተር ድረስ ሳኅሉ ባስተላለፉት መልዕክት ሕዝባዊ ሠራዊቱ የሚሰጠውን የግዳጅ ቀጣና በብቃት እንደሚሸፍኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡ ወደፊትም መንግሥት በሚሰጠው አቅጣጫ መሠረት ተጨማሪ ኀይል አሰልጥኖ የማሰማራት ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ ሌሎች ወጣቶችም የከተማቸውን ሰላም እየጠበቁ ለቀጣይ የቤት ሥራ እንዲዘጋጁ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አስተያየታቸውን የሰጡ ዘማች የሕዝባዊ ሠራዊት አባላት አሸባሪውን ቡድን ለመደምሰስ የሚሰጣቸውን ማንኛውንም ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም በቂ ወታደራዊ ስልጠና ማግኘታቸውን ነው ያስታወቁት፡፡
ንጹሐን እየተገደሉ፣ ሴቶች እየተደፈሩ፣ አርሶ አደር የዘራው ሰብል በወራሪ እየታጨደ እጃችንን አጣጥፈን አንቀመጥም ብለዋል የሕዝባዊ ሠራዊት አባላቱ፡፡ አስፈላጊውን መስዋእትነት በመክፈል ሕዝቡን ነጻ ለማውጣት ቆርጠው መነሳታቸውንም ተናግረዋል፡፡
ወጣቱ ካልባሌ ቦታ እና ከሱስ ተጋላጭነት ራሱን ነጻ በማውጣት መደራጀት፣ መታጠቅና መዝመት እንዳለበትም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ መሪዎች ወጣቶችን በማስተባበር ወደ ግንባር እንዲዘምቱ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እየተማሩ ነው፡፡
https://www.amharaweb.com/በወልቃይት-ጠገዴ-ሰቲት-ሁመራ-ዞን-ሕፃናት/
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው ትህነግ አማራ እና አማርኛ ቋንቋ ከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ምድር እንዲጠፋ መዋቅራዊ ሰነድ በማዘጋጀት ታሪክ የማይረሳው ግፍ ፈጽሟል፡፡ በሽብርተኛው ትህነግ የግዞት ዘመን በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተወለዱ ሕጻናት የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የሆነውን አማርኛ በመናገራቸው ብቻ እንደ ወንጀል ሲቆጠርባቸው ቆይቷል፡፡ በትምህርት ቤትም በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የመማር መብታቸውን ነፍጎ [...]
3 156
የአውሮፓ ሕብረት የትህነግን የሽብር ድርጊት እንዲያወግዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጠየቁ፡፡
https://www.amharaweb.com/የአውሮፓ-ሕብረት-የትህነግን-የሽብር-ድር/
አዲስ አበባ፡ ጥቅምት 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ መግለጫ ሰጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአውሮፓ ሕብረት የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ኮሚሽነር ጁታ ኧርፕላኔን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ የአውሮፓ ሕብረት የትህነግን የሽብር ድርጊት [...]
3 156
“ጎማ በጣም ከጮኸ የመተንፈሱ ምልክት ነው!” የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት
https://www.amharaweb.com/ጎማ-በጣም-ከጮኸ-የመተንፈሱ-ምልክት-ነው-የ/
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በሀገር መከላከያ ሠራዊት የሚመራው የወገን ጦር፣ በሕዝቡ ያልተቋረጠ ደጀንነት ሰሞኑን በኩታበር፣ ተሁለደሬ፣ ወረባቦና ጭፍራ ግንባር ፀረ ማጥቃት ርምጃ መውሰዱን የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት አስታውቃል። በተመረጡ የጁንታው አሸባሪ ቡድን ማሠልጠኛዎች፣ የጦር ማደራጃና መገናኛ አውታሮች፣ የጸጥታ አካላት፣ አልባሳትና መሣሪያዎች ማምረቻ ላይ በንሥሩና በጀግናው የአየር ኃይል እንዳይነሡ ተደርገው መመታታቸውን ነው የገለጸው። በየግንባሩ በገፍ [...]
3 156
በአሸባሪው ትህነግ 832 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ዘረፋ እና ውድመት እንደደረሰባቸው የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው እና ወራሪው የትህነግ ቡድን ለወራት በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በፈጸመው ወረራ እና ምዝበራ በሰሜን ወሎ ዞን ብቻ 832 ትምህርት ቤቶች ከጥቅም ውጭ ሆነዋል፡፡ የሽብር ቡድኑ በዞኑ በፈጠረው ዘርፈ ብዙ ችግር በእነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ከ330 ሺህ 600 በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ለመሆን ተገደዋል፡፡
በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ በአንድ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን ተገኝቶ ሽብርተኛው ትህነግ ያደረሰውን ጉዳት ተመልክቷል፡፡ በትምህርት ቤቱ የተማሪ መማሪያ ክፍሎች በጥይት ተበሳስተዋል፤ የመማሪያ ክፍሎች መጸዳጃ ሆነዋል፤ ወንበሮች ተፈልጠው ተማግደዋል፤ ጥቁር ሰሌዳ ተሰባብሮ መኝታ ሆኗል፤ የተማሪዎች መማሪያ መጽሐፍት እና መረጃ ወድሟል፡፡
የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን በመማሪያ ክፍሎች ላይ የሕፃናትን አዕምሮ የሚጎዱ የጥላቻ ጽሑፎችን ጽፏል፡፡
በመቄት ወረዳ 80 የመጀመሪያ ደረጃ ሙሉ ሳይክል እና አምስት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዳሉ የወረዳው ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኅላፊ አቶ ዋጋው መንበር ተናግረዋል፡፡ በወረዳው ከ44 ሺህ በላይ ተማሪዎች አሉ፡፡ አቶ ዋጋው እንደተናገሩት የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን በ19 ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ 580 ኮምፒውተሮችን እና 60 ፕላዝማዎችን ዘርፏል፤ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የተለያየ ዓይነት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ እስካሁን የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን ተደምስሶ ነፃ በወጡ 28 ቀበሌዎች 60 ትምህርት ቤቶች በደረሰባቸው ጉዳት የመማር ማስተማር ሥራውን መጀመር አልቻሉም፡፡
የአሸባሪው የትህነግ ወራሪ ቡድን በወረራቸው ሁሉም የሰሜን ወሎ ዞን አካባቢዎች 832 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ዘረፋ እና ውድመት ደርሶባቸዋል ያሉት ደግሞ የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ምክትል ኅላፊ አቶ ሰጠ ታደሰ ናቸው፡፡ በ2014 የትምህርት ዘመን መማር የነበረባቸው 330 ሺህ 638 ተማሪዎች እስካሁንም ከትምህርት እድል ውጭ እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ሥራ በባህሪው በእቅድ እና ቅደም ተከተል የሚመራ ነው ያሉት ምክትል መምሪያ ኅላፊው ሁሉም ትምህርት ቤቶች ሃብትና ንብረታቸው በመዘረፉ እና ሽብርተኛው ትህነግ የጦር ካምፕ አድርጓቸው ስለነበር መማር ማስተማሩን በቅርብ ለመጀመር ፈታኝ ይሆናል ነው ያሉት፡፡
ምክትል መምሪያ ኅላፊው እንደገለጹት ሽብርተኛው ትህነግ በፈጠረው መጠነ ሰፊ ማኅበራዊ ቀውስ አርሶ አደሮች በክረምቱ የእርሻ ወቅት በሚገባ ሥራቸውን ማከናወን አልቻሉም ነበር፤ ማኅበረሰቡ በጭንቅ ውስጥም ሆኖ ያረሰውን የተወሰነ ሰብል የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት ሰለጨፈጨፉበት እና ስለዘረፉበት በዞኑ ውስጥ ከሚገኙ ተማሪዎች መካከል ከ265 ሺህ በላይ የሚሆኑት የትምህርት ቤት ምገባ ያስፈልጋቸዋል፡፡
የሽብርተኛው ትህነግን ወራሪ ቡድንን በተባበረ ክንድ በመደምሰስ አካባቢውን በአጭር ጊዜ ሙሉ በሙሉ ነፃ ማድረግ ጊዜ የሚሰጠው አለመሆኑን አቶ ሰጠ ገልጸዋል፡፡
የባከነውን የትምህርት ጊዜ በሚያካክስ መልኩ ወደ ሥራ ለመግባትም መንግሥት፣ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች፣ ተቋማት እና ሕዝቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው -ከመቄት
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
በቦስተን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአሸባሪው ትህነግ ወረራ ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ117 ሺህ ዶላር በላይ ድጋፍ አደረጉ።
ጥቅምት 17/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በአሜሪካ ቦስተን ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በአሸባሪው ትህነግ ወረራ ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ የሚውል ከ117 ሺህ በላይ የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ማድረጋቸውን በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ አስታውቀዋል።
ለወገን ደራሹ ወገን ነው በሚል በሌሎች ግዛቶች ተመሳሳይ ዝግጅቶች እንደቀጠሉም መሆኑን አምባሳደር ፍጹም አረጋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ይፋ አመላክተዋል፡፡
ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ የተዘጋጀውን መርኃግብር ላከናወኑት የቦስተን ግብረ ኀይል፣ የሃይማኖት መሪዎች እና ለጋሾችን አምባሳደሩ ምሥጋና አቅርበዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
የአውሮፓ ኅብረት ሱዳንን አስጠነቀቀ።
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 17/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አውሮፓ ኅብረት ሱዳን ወደነበረችብት የሽግግር ሂደትና የዴሞክራሲ መስመር በፍጥነት የማትመለስ ከሆነ የገንዘብ ድጋፍ ማቋረጥን ጨምሮ ጠንካራ ጫና የሚያመጡ እርምጃዎችን እንደሚወስድ አስጠነቀቀ፡፡
ኅብረቱ በወታደራዊ ቡድኑ የተፈፀመውን መፈንቅለ መንግሥት በጥብቅ ያወገዘው ሲሆን በፍጥነት ወደ ቀደመ የሽግግር ሂደት መመለስን ጠይቋል፡፡
ይህ ካልሆነ ግን ውጤቱ የከፋ እንደሚሆን ነው በኅብረቱ የውጭ ጉዳይና የፀጥታ ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይ እንዲሁም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጆሴፍ ቦሬል በኩል ባወጣው መግለጫ ያሳሰበው፡፡
ሀገራትና ኅብረቶች በሱዳን የተፈፀመውን መፈንቅለ መንግሥት በማውገዝ የሽግግር መንግሥቱ እንዲመለስ እየጠየቁ ነው፡፡
የመፈንቅለ መንግሥቱ መሪና የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤቱ ሊቀ መንበር ሌተናንት ጄኔራል አብዱል ፋታህ አል ቡርሃን ግን ምርጫ የሚደረገው በሐምሌ 2015 እንደሚሆንና እስከዚያ ወታደራዊ ኃይሉ ሥልጣን ይዞ እንደሚቆይ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3 156
በህልውና ዘመቻው በግንባር በመሰለፍ እና ደጀን በመሆን እየተደረጉ ያሉ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ገለጸ፡፡
ከሚሴ፡ ጥቅምት 17/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በአሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን የስልጣን ዘመን መላው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የጥቃት ሰለባ እንደነበሩ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሕመድ ሐሰን ገልጸዋል፡፡ የኦሮም ብሔረሰብ አስተዳደር ሕዝብም በማንነቱና በእምነቱ በዚህ አሸባሪ ቡድን በደልና ስቃይ ሲደርስበት ቆይቷል ብለዋል፡፡
አቶ አሕመድ እንዳሉት ይህንን አሸባሪ ቡድን የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ሕዝብ በጽኑ አምርሮ የሚታገለው በበቂ ምክንያት ስለሆነ በብሔረሰብ አስተዳደሩ ሁሉም ሕዝብ የሚሳተፍበት ራስን የመከላከልና ሀገርን የማዳን ጥሪ መተላለፉን ገልጸዋል፡፡
የአማራ ክልል መንግሥት ካስተላለፈው የመጀመሪያ የክተት ጥሪ ጋር በተያያዘ ከብሔረሰብ አስተዳደሩ የተውጣጡ በተለይም በባቲ በጭፍራ በኩል ከፍተኛ ጀብዱ ያስመዘገቡ የሚሊሻ አባላትና ወጣቶች በዘመቻው መሳተፋቸውን አብራርተዋል፡፡ አሁንም እናቶችን ጨምሮ የተሳተፉበት የስንቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አቶ አሕመድ ጠቁመዋል፡፡
ከሰሞኑ ከተላለፈው የክተት ጥሪ ጋር በተያያዘ አሸባሪውና ወራሪው ቡድን ጥቃት እንዳይፈጽም በባቲና በደዌ ሃረዋ በኩል ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በቅንጅት ከፍተኛ የጥበቃ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
አሸባሪው ቡድን ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሕፃን እስከ አዛውንት አሰልፎ የተነሳ በመሆኑ እና ይህ ጉዳይ የአማራና የአፋር ክልሎች ጉዳይ ብቻ ባለመሆኑ መላ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ኢትዮጵያን ለማዳን ጦርነቱን ሕዝባዊ አድርገው ፊት ለፊት መመከትና ጠላትን በጋራ ማጥፋት እንደሚገባቸው ዋና አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል፡፡
የብሔረሰብ አስተዳደሩ በህልውና ዘመቻው በግንባር በመሰለፍ እና ደጀን በመሆን እያደረጋቸው ያሉ ድጋፎች እስከመጨረሻው ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
አቶ አሕመድ ብሔረሰብ አስተዳደሩ ከግንባር ባሻገር ሰርጎ ገቦች ጥፋት እንዳይፈጽሙ ከሰሜን ሸዋ ዞንና ከአፋር ክልል አጎራባች ወረዳዎች ጋር በቅንጅት እየሠሩ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ በዚህም በርካታ የቡድኑን ተላላኪዎች በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉንም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡-ሥነ-ጊዮርጊስ ከበደ-ከከሚሴ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
