en
Feedback
አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

Closed channel
3 156
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5330 days
Posts Archive
ኑ ኢትዮጵያን በጠላቶቿ የማትበገር ሀገር እናድርግ- የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ጥሪ ጥቅምት 17/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ከአፍሪካ ሀገራት መካከል በነፃነት ቀንዲልነት ኢትዮጵያ ቀዳሚ ሆና ስትጠራ ነፃነቷ በልመና ወይም በችሮታ የተገኘ አልነበረም፡፡ ኢትዮጵያ የምዕራባውያኑን የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ በመርህ ደረጃ እንኳን እንዳይነሳ አድርጋ የሰባበረችው በልጆቿ የተባበረ ክንድ ነው፡፡ ሞትን ንቀው የሀገራቸውን ነፃነት እና ክብር የሚያስቀድሙ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ጥንትም ነበሩ ዛሬም አሉ፡፡ ከውስጥ ባንዳ ከውጭ ጠላት አጥታ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከማህጸኗ ጀግኖችም ነጥፈውባት አታውቅም፡፡ ደረታቸውን ለጦር እግራቸውን ለጠጠር ሰጥተው ሀገራቸውን ከጠላት የሚታደጉ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ሆነው አልፈዋል፡፡ ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ነባሩ ለተተኪው አደራ እያለ ያቆያት ሀገር ናት፡፡ ዛሬ እና ነገም ፈተናዎቿ የማይከስሙት ኢትዮጵያ ነፃነቷ እና ሉዓላዊነቷ በልጆቿ ብርቱ ክንድ ብቻ የተረጋገጠ ነው፡፡ “ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራ እና ተከብራ ትኖራለች” ለኢትዮጵያውያን ውርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ወቅት የገጠማትን ፈተና ተሻግራ ለመቀጠል ከትውልዱ ምን ይጠበቃል? ስንል በግንባር የሚገኙ የሠራዊቱን አባላት አነጋግረናል፡፡ በልጆቿ አጥንት እና ደም ታፍራ እና ተከብራ የኖረችውን ኢትዮጵያ ለማስቀጠል ወጣቱ መከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ፲ አለቃ ፋሲካው ዘገየ ስለሀገሩ ክብር እና ስለሕዝቦቿ ደኅንነት ሲል ሁለት ጊዜ የሀገር መከላከያ ሠራዊት መለዮን ለብሷል፡፡ የመጀመሪያውን የውትድርና ሕይዎት በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ እንደተቀላቀለ የሚናገረው ፲ አለቃ ፋሲካው ከሚወደው የውትድርና ሙያ እንዲገለል ያደረገው ብሔር ተኮር ብልሹ አሠራር ነበር፡፡ ፲ አለቃ ፋሲካው ሽብርተኛው ትህነግ በሥልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሀገር መከላከያን ማፍረስ ብሎ ሲተገብራቸው በነበሩ ኢ-ፍትሐዊ የሆኑ አሠራሮች ከሚወደው ውትድርና ሙያ እንዲወጣ አደረጉት፡፡ የስድስት ቤተሰብ አስተዳዳሪ የሆነው እና በርካታ ሃብት እና ንብረት አፍርቶ ሕይዎትን በሌላ መንገድ የሚመራው ፲ አለቃ ፋሲካው ከ10 ዓመታት በኋላ ወደሚወደው የውትድርና ሙያ እንዲመለስ አጋጣሚ ተፈጠረ፡፡ አሸባሪው እና ወራሪው የትህነግ ቡድን ሀገር እና ሕዝብን አደጋ ላይ በሚጥል መልኩ ወረራ መፈጸሙን ተከትሎ በታወጀው የክተት ጥሪ መከላከያን ተቀላቅሎ ሀገሩን በድጋሚ እያገለገለ ይገኛል፡፡ በወቅቱ የነበረው ቅሬታ በሽብርተኛው ትህነግ መራሹ ሥርዓት እንጂ በሀገሩ አለመሆኑን የተናገረው ፲ አለቃ ፋሲካው ሽብርተኛው ትህነግ ለኢትዮጵያ አደጋ መሆኑን ሁሉም ሊያውቀው እንደሚገባ ገልጿል፡፡ ይህንን የሀገር ጠላት በመደምሰስ ኢትዮጵያን ከህልውና ስጋት ለመታደግ ሀገሩን እያገለገለ መሆኑን ተናግሯል፡፡ የውትድርና ሙያን ከተቀላቀለ ዓመታትን እንዳስቆጠረ የነገረን ደግሞ ፲ አለቃ ቢኒያም ዳኘ ነው፡፡ “ሞት የትም፣ መቼም እና በማንም ላይ አለ” የሚለው ፲ አለቃ ቢኒያም ለሀገር ክብር እና ለሕዝቦቿ ደኅንነት ራስን መስዋእት ማድረግ ግን ልዩ ነው ይላል፡፡ እናም ሀገሩ በየጊዜው የሚያጋጥማትን ፈተና በጽናት እንድትሻገር ወጣቱ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን መቀላቀል እንዳለበት አስገንዝቧል፡፡ “ከራስ በፊት ለሕዝብ እና ለሀገር” የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሚመራባቸው መሰረታዊ ቁልፍ ዕሴቶች አንዱ እንደሆነ የነገረን ፶ አለቃ ጥበበ መገርሳ ሀገር አፈርሳለሁ ብሎ የተነሳው ሽብርተኛው ትህነግ እንደማይሳካለት ተናግሯል፡፡ ምክንያቱም አሁን ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ የተላበሰ፣ ምንጊዜም የላቀ ጀግንነት ያለው እና በማንኛውም ግዳጅ የላቀ ውጤት የሚያስመዘግብ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እየተገነባ መምጣቱን ገልጿል፡፡ ከራስ በፊት ለሕዝብ እና ለሀገር የቆመ የሀገር መከላከያ ሠራዊት መገንባት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ያለን ፶ አለቃ ጥበበ ይህንን መሰረታዊ ቁልፍ ዕሴት ለመተግበር ወጣቱ መከላከያ ሠራዊትን መቀላቀል አለበት ብሎናል፡፡ ፶ አለቃ ጥበበ ሕዝቡ ለሀገር መከላከያ ሠራዊቱ እያሳየ ያለው ፍቅር፣ ክብር እና ደጀንነት ተጨማሪ ጉልበት እየሆናቸው መሆኑንም ገልጿል፡፡ ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

በአማራ ክልል የተፈናቀሉ ወገኖችን እንዲደገፉ ለማስቻል ያለመ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ፡፡ ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 16/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አምስት የተራድኦ ድርጅቶች በአማራ ክልል የተፈናቀሉ ወገኖችን መደገፍ እንዲቻል የአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክት ይፋ አድርገዋል፡፡ የተራድኦ ድርጅቶቹ የተፈናቀሉ ወገኖችን መደገፍ በሚያስችላቸው ጉዳይ ላይ ከአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ እና ከከልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር ምክክር አድርገዋል፤ ተፈራርመዋል፡፡ የተራድኦ ድርጅቶቹ ይፋ ያደረጉት ፕሮጀክት ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግበትም ታውቋል፡፡ ለፕሮጀክቱ ገንዘብ አፈላላጊው ኮምፓሽን ኢንተርናሽናል የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት መሆኑም ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ልማት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይዎት ቤተክርስቲያን ልማት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን የልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን እና የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የእርዳታና ልማት ማኅበር ደግሞ የፕሮጀክቱ አስፈጻሚዎች ናቸው ነው የተባለው፡፡ የተራድኦ ድርጅቶቹ አሁን ላይ ከሚያድጉት ደራሽ ድጋፍ በተጨማሪ ተፈናቃዮች በዘላቂነት እንዲቋቁሙ እንደሚሠሩም ተገልጿል፡፡ ዘጋቢ፡- ግርማ ሞገስ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንስት አናብስት! https://www.amharaweb.com/የኢትዮጵያ-መከላከያ-ሠራዊት-እንስት-አና/ ጥቅምት 16/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ጀግኖቹ በስሌት እና በቀመር የሚተኩሱት ተተኳሽ ዶግ አመድ የሚያደርገው የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት ክምር መረማመጃ ያሳጣል፡፡ በተረበሸው የጠላት ምሽግ ዙሪያ እንደ ዘንዶ የተጠመጠሙት የእናት ኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ድልን ለማጣጣም መጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል፡፡ ሴት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላትም ከወንድሞቻቸው ጋር ጠላት የገባበት ጉድጓድ ገብተው ወደ ቋመጠው ሞት በመሸኘት ኢትዮጵያ [...]

❝የሽብርተኛው ህወሓት የሐሰት ፕሮፖጋንዳ የሠራዊታችንን የድል ግስጋሴ አይገታውም !❞ መከላከያ ሠራዊት https://www.amharaweb.com/❝የሽብርተኛው-ህወሓት-የሐሰት-ፕሮፖጋን/ ሽብርተኛው ከሚታወቅባቸው ስልቶቹ መሀል አንዱ ቅጥፈቱ ነው ፡፡ ጉልበት ሲያንሰው ምላሱ ይረዝማል ፤ ያልሆነውን ሆንኩ ፣ ያላደረገውንም አደረኩ…ይላል ፡፡ ይህ ደግሞ ጥርሱን የነቀለበት እና ተወልዶ ያረጀበት ባህሪው ነው ፡፡ አንድም ቀን ከአፉ እውነት ተገኝታ የማታውቀው ይህ ሽብርተኛ ፣ ሽንፈቱን የሚሸፍነው የሠራዊታችንን ስም በማጠልሸት ነው ፡፡ ደጋፊዎቹ ኪሳራውን እንዳያወቁ ፣ ሰላማዊው ሕዝብ ልጆቹን እና ምግብ እንዳይጠይቅ [...]

❝የወገን ጥምር ጦር የፀረ ማጥቃት ርምጃ፣ ወራሪውን መንጋ መውጫ መግቢያ እያሳጣው ነው❞ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት https://www.amharaweb.com/❝የወገን-ጥምር-ጦር-የፀረ-ማጥቃት-ርምጃ፣/ ጥቅምት 15/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ጀግናው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖና ሚሊሻ በወሎ ግንባር በወረባቦ፣ በተሁለደሬ፣ ኩታበርና ደላንታ በወሰዱት የፀረ ማጥቃት ርምጃ በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሱ መሆናቸውን የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ጠላት በወረባቦ፣ በተሁለደሬ፣ ኩታበርና ደላንታ አካባቢዎች ያሰለፈው ኃይል ሙትና ቁስለኛ ሆኗል። ከጥቃቱ የተረፈውም እግሬ አውጪኝ [...]

“አሸባሪው ትህነግ በወሎ ይቀበራል” ያሉ የአዲስ አበባ ወጣቶች ወደ ወሎ ዘመቱ። https://www.amharaweb.com/አሸባሪው-ትህነግ-በወሎ-ይቀበራል-ያሉ-የአ/ ደሴ፡ ጥቅምት 15/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶክተር) ያስተላለፉትን "ሁሉም ወደ ወሎ ይዝመት" የክተት ጥሪ የተቀበሉ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ወደ ወሎ ዘምተዋል፡፡ ወጣቶቹ "አሸባሪው ትህነግ በወሎ ይቀበራል" በሚል ወኔ ወደ ወሎ ግንባር መዝመታቸውን ነው ለአሚኮ የተናገሩት። ይልማ ሙሉጌታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ሲሆን የከተማዋን ወጣቶች በማስተባበር በወሎ ግንባር ተሰልፈው ጠላትን [...]

የኮምቦልቻ ከተማ ወጣቶች የአሸባሪውን ቡድን ግብዓተ መሬት ለመፈፀም ግንባር ከትተዋል። ደሴ፡ ጥቅምት 14/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ግንባር የተሰለፉት ወጣቶቹ ለ27 ዓመታት አሸባሪው ቡድን ሀገር ሲያጠፋ በትግስት ታልፏል አሁን ግን ለ27 ሰከንድም መታገስ አይገባም ብለዋል። በሕዝባዊ ንቅንቄ ከሳምንታት በላይ በምሽግ የሚገኙት የኮምቦልቻ ወጣቶች የወራሪ ቡድኑ መቀበሪያ በመጣበት ነው ሲሉም ገልጸዋል። ወጣቶቹ ለመከላከያዉ ስንቅና ትጥቅ ከማቅረብና ደጀን ከመሆን ባሻገር በግንባር በነቂስ በመሰለፍ የተጠናከረ እንቅስቃሴ አድርገዋል። የሚጠበቅባቸውን የህይወት መስዋእትነት በመክፈል አካባቢያቸውን ለመጠበቅ ተዘጋጅተዋል። በግንባር በመፋለም ሳምንታትን ያስቆጠረው ወጣት ከማል ኢብራሂም አሸባሪውን ቡድን ለመቅበር ጊዜ ሊሰጠው አይገባም ብሏል። ስንቅና ትጥቅ ከማቀበል ወጥተን ለመስዋእትነት ተዘጋጅተናል ያለው ደግሞ ወጣት አቡበከር ነው። ወጣት ነብዩ ሰይድ በበኩሉ ኮምቦልቻን ያዝኩ ካለ ሳምንት ያስቆጠረው አሸባሪው ቡድን እንኳን ኮምቦልቻን ሊይዝ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጠን በመጓዝ ነው ግንባር ላይ የምንገኘው ብሏል። ወጣቶቹ ለመከላኪያ፣ ለልዩ ኀይሉ እና ለፍኖው መጠነ ሰፊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑንም ተገልፃል። ዘጋቢ:–ሀበሻ አንለይ–ከኮምቦልቻ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

“ጎበዝ ጥይት ግዛ በወገብህ ደርድር፣ አልተደላደለም ገና ነው በጌምድር” https://www.amharaweb.com/ጎበዝ-ጥይት-ግዛ-በወገብህ-ደርድር፣-አል/ ጥቅምት 14/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት ለአማራ ሕዝብ አዲሱ አይደለም፡፡ እንኳን ወገኑ ተነክቶበት፣ እህቱ ተደፍራ፣ በሬዎቹ ታርደው፣ “በጥቅምት ስንቅና ትጥቅህን ይዘህ ወረኢሉ ላይ እንድንገናኝ” ተብሎ ጥሪ በቀረበለት ጊዜም ቃሉን የጠበቀና ሀገሩን ያስከበረ ሕዝብ ነው፡፡ የእቴጌ ጣይቱ ልጆች ባሎቻቸውን አጀግነው ልጆቻቸውን መርቀው ሲሸኙ ለተመለከተ ያ የወረኢሉ ታሪክ እየተደገመ ስለመሆኑ አያጠራጥርም፡፡ የራስ ጉግሳ ወሌ ቤተሰቦች [...]

"የገጠመንን ሀገር እና ትውልድን የማሻገር ታሪካዊ ዕድል ወደ ማይቀለበስ ድል ለመቀየር የጋራ ኀላፊነትን በጥንቃቄ መወጣት ይጠይቃል"ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 13/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ዛሬ በጦላይ 20ኛ ዙር የፌዴራል ፖሊስ ሰልጣኞች መመረቃቸውን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ምሩቃኑ ሀገርን ከጠላት የመታደግ ዕድል ወደ ማይቀለበስ ድል የመቀየር ታሪካዊ ኀላፊነታቸውን እንደሚወጡ ይጠበቃል ብለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው እንዳሉት አሸባሪው እና ወራሪው ቡድን ሁሉንም ምድራዊ ጥፋቶች በሕዝባችን ላይ እየፈፀመ፤ የጥፋት ወሰኑን እያሰፋ ይገኛል፡፡ ወራሪ ቡድኑ ከዚህ በላይ ከተፈቀደለት ሀገርን ከማጥፋት ውጪ የተለየ ዓላማ ስለማይኖረው፤ በገሃድ የሚታየውን አደጋ በመመከት ረገድ ሁላችንም ግንባር ቀደም መሆን ይገባናል ብለዋል፡፡ ነፃነትን አሳልፎ መስጠት እና ክብርን አዋርዶ መኖር ከቶውኑ በህይወት እንደመኖር ሊቆጠር ስለማይችል፤ ስለእናት ሀገራችን ብለን የምንወጣው የጋራ ኀላፊነት ከመኖር በላይ መሆኑ ልብ ይሏል ነው ያሉት። አባቶች እንደሚሉት ዕድል መጀመሪያ እግር ላይ ታርፋለች፤ ቀስ በቀስ ወደ ራስ ላይ ትወጣለች፤ በዘዴ እና በጥበብ ከተያዘች በቀላሉ አትወርድም ብለዋል፡፡ በዚሁ አግባብ የገጠመንን ሀገር እና ትውልድን የማሻገር ታሪካዊ ዕድል ወደ ማይቀለበስ ድል ለመቀየር የጋራ ኀላፊነትን በጥንቃቄ መወጣት እንደሚጠይቅ አቶ ደመቀ አስገንዝበዋል፡፡

በአሸባሪው ትህነግ መቃብር ላይ ለትውልድ የሚተላለፍ የድል ታሪክ እንጽፋለን ያሉ የወሎ ወጣቶች እየዘመቱ ነው፡፡ ደሴ: ጥቅምት 13/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ከተለያዩ የወሎ አካባቢዎች ደሴ ከተማ የተሰባሰቡ ወጣቶች የሽብርተኛውን እና ወራሪውን ትህነግ ግብዓተ መሬት በመፈፀም ዘመን ተሻሪ የድል ታሪክ እንጽፋለን በማለት ወደ ግንባር እየዘመቱ ይገኛሉ። የአማራ ክልል መንግሥት ያስተላለፈውን “ሁሉም ወደ ወሎ ይትመም፣ ይዝመት” የክተት ጥሪ ተቀብለው የደሴና የአካባቢው ወጣቶች ወደ ግንባር በመዝመት ከሀገር መከላከያ ሠራዊትና ከአማራ ልዩ ኀይል ጎን በመሰለፍ ላይ ናቸው። ከኮምቦልቻ ከተማ ተነስቶ ወደ ሐይቅ እየዘመቱ ከሚገኙ ወጣቶች መካከል ወጣት አማረ ፈቃደ በኮምቦልቻ ከተማ ወጣቶች እየተደራጁ በመዝመት ላይ እንደሚገኙ ነግሮናል። “እኔም የጠላት የሐሰት የፕሮፖጋንዳ ጋጋታ ሳይበግረኝ ቀድሜ ወደ ሐይቅ እየዘመትኩ ነው” ብሏል። ወደ ግንባር ሄደን መከላከያ እና ልዩ ኀይላችንን በመቀላቀል አሸባሪውን ትህነግ እንፋለመዋለን ብሏል። ወጣቱ አሸባሪውን ትህነግ ለመቅበር ወጣቶች እየተደራጁ ወደ ግንባር መዝመት እንዳለባቸውም ተናግሯል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት መምበር ፍቃዱ “ወራሪውን ተደራጅቶ መመከት ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም፤ በመዝመት አሸባሪውን ትህነግ ከምድረ ገጽ ማጥፋት የወጣቶች ብቸኛ አማራጫችን ነው” ብሏል። በተለያየ መንገድ ወጣቱን የሚያዘናጉ አካላት ከድርጊታቸው ታቅበው ወጣቱ ለህልውናው እንዲታገል ማነሳሳት እንደሚገባም አስተያየቱን ሰጥቷል። ወጣት መሐመድኑር ከድር “ሀገር የኹሉም ናትና ወጣቶች ሀገራችንን ማስከበር አለብን፤ በክልላችን መንግሥት የተላለፈውን የክተት ዘመቻ ጥሪ ተቀብለን አሸባሪውን ባለበት ለመፋለም ቆርጠን ተነስተናል” ብሏል። ወጣት መሐመድኑር እንዳለው ትግሉ የአሸባሪውን ትህነግ ግብዓት መሬት እስከመፈፀም ነው፤ ስለዚህ ወራሪው እያለ አንድም ቀን ደሴ መቀመጥ አያስፈልግም፤ ከጠላት ጋር እዛው ግንባር መዋደቅ እና መደምሰስ ይገባል ነው ያለው። “ሁላችንም በጋራ ጠላትን ባለበት ልንፋለም ተነስተናል” ብሏል፡፡ ሌላኛው ዘማች ወጣት ደሳለኝ ሲሳይ “መከፋፈሉ ያጠፋናል፤ ሁሉም ወጣት ሽብርተኛው ትህነግን መቅበሪያው ጊዜው አሁን ነውና ራሳችንና አካባቢያችን ለመጠበቅ በቁርጠኝነት ተነስተናል፤ ወጣቶች በአንድነት ቆመን ጠላትን በመደምሰስ ደማቅ ታሪክ እንጽፋለን” ሲል ገልጿል፡፡ ዘጋቢ:- ግርማ ሙሉጌታ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

ለሕልውና ዘመቻው ውጤታማነት ሕዝቡ እያደረገ ያለውን ትግል አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ጥሪ ቀረበ፡፡ https://www.amharaweb.com/ለሕልውና-ዘመቻው-ውጤታማነት-ሕዝቡ-እያደ/ ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 12/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኀላፊ ግዛቸው ሙሉነህ የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ለአሚኮ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ አቶ ግዛቸው አሸባሪው ትህነግ አሁንም በክልሉ በወረራቸው አካባቢዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ አረመኒያዊ ድርጊት እየፈጸመ መኾኑን አንስተዋል፡፡ ንጹሃን ዜጎችን በመግደል፣ ሀብት እና ንብረታቸውን ደግሞ በመዝረፍ ለረሃብ እየዳረገ እንደሚገኝ ነው አቶ ግዛቸው ያነሱት፡፡ ባለፉት ወራት መላው [...]

የአሸባሪው የህወሓት ቡድን ማሰልጠኛ ማዕከል ዛሬ የአየር ጥቃት ዒላማ ሆነ። https://www.amharaweb.com/የአሸባሪው-የህወሓት-ቡድን-ማሰልጠኛ-ማዕ/ የአሸባሪው የህወሓት ቡድን ማሰልጠኛ ማዕከል ዛሬ የአየር ጥቃት ዒላማ ሆነ። ጥቅምት 12/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአሸባሪው የህወሓት ቡድን ማሰልጠኛ ማዕከል ዛሬ የአየር ጥቃት ዒላማ መሆኑን የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ አስታውቋል። ማዕከሉ ለአሸባሪው ቡድን ወታደራዊ ሥልጠና ከመዋሉ በፊት የኢፌዴሪ መከላከያ ማሠልጠኛ ማዕከል እንደነበርም ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት አሸባሪው ቡድን በዚህ ተቋም ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና የሚሠጥበት፤ የውጊያ ግንኙነት [...]

ወጣቶች አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድንን በመደምሰስ የጀግኖች አባቶችን አኩሪ ታሪክ ሊደግሙ እንደሚገባ የአማራ ክልል የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ጥሪ አቀረበ፡፡ ባሕር ዳር: ጥቅምት 11/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ለህልውናው ዘመቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል። በድጋፉ ሥነሥርዓት ላይ የአማራ ክልል የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ሊቀመንበር ዳኝነት አያሌው አባቶች ሀገራቸው በየወቅቱ የሚገጥማትን ጠላት በዘር፣ በሃይማኖት፣ በቋንቋ ሳይከፋፈሉ እርስ በርሳቸዉ በመዋደድ ሲደመስሱ እንደነበር አስታውሰዋል። አባቶች ሀገራቸውን የሚወር ጠላት በመጣባቸዉ ጊዜ ሁሉ እንደብረት አንድነታቸዉን አጠናክረው ቀፎው እንደተነካበት የንብ መንጋ "ሆ!" ብለው የሀገራቸውን ሉዓላዊነት በማስከበር ለትውልድ እንዳስረከቡ አስረድተዋል። አባቶች የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ጠብቀዉ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሉዓላዊነትና ነፃነት አስከብረዉ ነፃ የሆነች ኢትዮጵያ ለአሁኑ ትዉልድ በክብር አስረክበዋል ነው ያሉት። አሁንም ቢሆን ወጣቱ ተመሳሳይ ታሪክ ሊደግም እንደሚገባ ያሳሰቡት ሊቀመንበሩ ኅብረተሰቡ በተለይ ወጣቱ የገንዘብ ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ የህልውና ዘመቻውን ሊቀላቀል እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አሸባሪው ትህነግ አማራ ጠላቴ ነዉ ሒሳብ አወራርዳለሁ፣ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲኦል እገባለሁ ብሎ በመነሳት የአማራና የአፋር ክልሎችን በመውረር የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈፀመ፣ እያፈናቀለ፣ የትምህርት፣ የጤናና ሌሎች የመንግሥትና የግል ተቋማትን እያወደመ እንደሚገኝ አስረድተዋል። አረመኔውን የጥፋት ቡድን ለመደምሰስ ብሎም እስከመጨረሻዉ የሰላምና ጸጥታ ስጋት ከማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኀይል፣ ሚሊሻና ፋኖ በግንባር ተሰልፈዉ ጠላትን ለመፋለም እያደረጉ ያሉትን ትግል የአማራ ክልል የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት በአድናቆት ያዩታል ነው ያሉት። የአማራ ክልል ጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባል ሻምበል ባሻ የኔው አባቶች ምንም አይነት ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ሳይኖራቸው የሀገርን ዳር ድንበር አስከብረዋል ብለዋል። አሁን ላይ ወራሪው የትህነግ ቡድን በምድር ላይ የማይተገበር ግፍ በሕዝብ ላይ እየፈጸመ ይገኛልም ነው ያሉት። ወጣቱ አንድነቱን ጠብቆ የዚህን አረመኔ ቡድን ሴራ ማክሸፍ እንደሚጠበቅበት ለአሚኮ ተናግረዋል። ወጣቱ ጠላትን ከመደምሰስ በተጨማሪ ድህነትን አጥብቆ መታገል እንደሚኖርበት አስረድተዋል። የፋግታ ለኮማ ወረዳ ጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ሊቀመንበር ታደለ ነጋሽ ጠላት በቆፈረው ምሽግ ውስጥ ራሱ እንዲቀበር ወጣቱ የአባቱን ታሪክ መድገም እንዳለበት ገልጸዋል። ጥንታዊ አርበኞችም ቢሆኑ ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ እስከ ግንባር ድረስ ለመዝመት ዝግጁ መሆናቸውን አስረድተዋል። ሕዝቡ የመንግሥትን ጥሪ ተቀብሎ ሀገሩን ከመደፈር መታደግ አለበት ብለዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን በ17 ወረዳዎች የሚገኙ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበራር አባላት ለህልውናው ዘመቻ የሚውል ከ100 ሺህ ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል። ድጋፉን የተረከቡት የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኀላፊ ጥላሁን መሐሪ (ዶክተር) ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል። ዶክተር ጥላሁን የማኅበራቱ ድጋፍ ኅብረተሰቡ ለህልውናው ዘመቻ ድጋፍ እንዲያደርግ አርዓያ ይሆናልም ነው ያሉት። ኀላፊው እንዳሉት ወራሪውን ቡድን ለመመከት ከወገን ኀይል ተጋድሎ በተጨማሪ ሕዝቡ በጉልበትና በዕውቅት ድጋፍ እያደረገ ነው። ዘጋቢ:- ቡሩክ ተሾመ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዶክተር ድረስ ሳህሉን በድጋሜ ተቀዳሚ ከንቲባ አድርጎ ሾመ። ባሕር ዳር: ጥቅምት 10/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር ምርጫ 10ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ዶክተር ድረስ ሳህሉ በድጋሚ የባሕር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል። ዶክተር ድረስ ለከተማው ምክር ቤት ተቋማትን የሚመሩ አዳዲስ ተሻሿሚዎችን አቅርበውም አፀድቀዋል። በዚህ መሠረት:- 1ኛ. አቶ ባየ አለባቸው ምክትል ከንቲባ 2ኛ. በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሤ 3ኛ. የከተማ አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኃይለየሱስ ፀጋየ 4ኛ. የባሕር ዳር ከተማ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ በትግሉ ተስፋሁን 5ኛ. የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ኃይለማርያም እሸቴ 6ኛ. የባሕር ዳር ከተማ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ የሻረግ ፈንታሁን 7ኛ የባሕር ዳር ከተማ ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጤናው ምህረቴ 8ኛ. የባሕር ዳር ከተማ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉዓለም ተፈራ 9ኛ. የባሕር ዳር ከተማ ሰላምና ደኅንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ አደራ ጋሼን አድርጎ ሾሟል። ዘጋቢ:- ሙላቴ አስማረ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

#Semera : በአፋር ክልል መዲና ሰመራ በአሁን ሰዓት በርካቶች የተገኙበት የውይይት መድረክ እየተካሄደ መሆኑን አፋር ማስ ሚዲያ ዘግቧል። ውይይቱ #በወቅታዊ_ጉዳይ ዙሪያ መሆኑ ተገልጿል። በውይይቱ ላይ የአፋር ክልል ወጣቶች ፣ ሴቶች እና ሌሎችም የማህበረሰብ ክፍሎች ተካፋይ መሆናቸው ተነግሯል።

የሽብርተኛው ትህነግን ፍፃሜ ለማፋጠን የፀጥታ ኀይሉ የሚሰጣቸውን ግዳጅ በብቃት እየተወጡ መሆኑን የመቄት ወረዳ ሕዝባዊ ሠራዊት አባላት ተናገሩ፡፡ https://www.amharaweb.com/የሽብርተኛው-ትህነግን-ፍፃሜ-ለማፋጠን-የ/ ጥቅምት 10/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው እና ወራሪው የትህነግ ቡድን በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በከፈተው ወረራ በርካቶች “ዱር ቤቴ” ብለው እየተፋለሙት ይገኛሉ፡፡ በመንግሥት እና በግል የታጠቁት እና እምቢ ለወራሪ ያሉት የሕዝባዊ ሠራዊት አባላት በገቡበት ጫካ ውስጥም ኾነው የሽብር ቡድኑን እንቅስቃሴ በመከታተል እና ፊት ለፊት በመፋለም አኩሪ ገድል ፈጽመዋል፤ እየፈጸሙም ይገኛሉ። አኩሪ ጀብዱ ከተፈጸመባቸው አካባቢዎች የሰሜን ወሎዋ [...]

የተፈናቀሉ ወገኖችንና የዘማች ቤተሰቦችን በመርዳት የመውሊድ በዓልን እንደሚያከብሩ በደባርቅ ከተማ የሚኖሩ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ገለጹ፡፡ ደባርቅ: ጥቅምት 07/2014 ዓ.ም (አሚኮ) 1 ሺህ 496ኛው የነብዩ መሐመድ ልደት (መውሊድ) በዓል ነገ ይከበራል። የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በደባርቅ ከተማ የበዓሉ ዋዜማ አከባበር ላይ ተገኝቶ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችን ስለበዓሉ አከባበር አነጋግሯል፡፡ በደባርቅ ከተማ የሚኖሩ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች በዓሉን ኢትዮጵያ ካለችበት ፈተና እንድትወጣ ዱዓ በማድረግና ከተለያዩ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ወገኖችንና የዘማች ቤተሰቦችን በመርዳት እንደሚያከብሩ ተናግረዋል፡፡ የከተማዋ ነዋሪ ኡስታዝ አሊ የኑስ መረዳዳትና መደጋገፍ የነብዩ መሐመድ መርህ ነው፤ የልደት በዓላቸውን ስናከብር ደግሞ መርኃቸውን ተከትለን የተፈናቀሉና በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖችን በመርዳትና በመደገፍ ማክበር ይገባል ብለዋል፡፡ በአሸባሪው የትህነግ ቡድን የተፈናቀሉ በርካታ ወገኖች በከተማችን ስላሉ በቅድሚያ ለነሱና ለታጋይ ወገኖች በመስጠት የመውሊድን በዓል እናከብራለን ያሉት ደግሞ በደባርቅ ከተማ የመስጊዶች አስተዳዳሪ ሼህ ኢብራሂም አደም ናቸው፡፡ ሌላኛዋ ነዋሪ ወይዘሮ ኑሪት ያሲን በበኩላቸው ኢትዮጵያ ካለችበት ፈተና እንድትወጣ ጸሎት ስናደርግ ቆይተናል ነው ያሉት፡፡ በዓሉንም በጸሎት እናሳልፈዋለን ብለዋል፡፡ የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሰብሳቢ የሱፍ ሱሌማን አሸባሪው የትህነግ ቡድን የከፈተውን ወረራ ለመቀልበስ እየተካሄደ ባለው የህልውና ዘመቻ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ጠንካራ ትግል በማድረጋችንም የመውሊድን በዓል በነፃነት ለማክበር በቅተናል ነው ያሉት። የምክር ቤቱ ጸሐፊ ካሳ እስማኤል ወቅቱ ከምንጊዜውም በላይ ልንረዳዳና ልንተጋገዝ የግድ የሚልበት ወቅት ብለዋል፡፡ በዓሉን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በየአካባቢው ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን መርዳት ያስፈልጋልም ነው ያሉት፡፡ በደባርቅ ከተማ የመውሊድ በዓል ዋዜማ ለተጎዱ ወገኖችና ለበዓሉ የሚሆን ምግብ በማዘጋጅትና ጸሎት በማድረግ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ዘጋቢ፡- አድኖ ማርቆስ -ከደባርቅ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

❝ርእሰ መሥተዳድሩ የሚጠቀሙበት በስማቸው የተከፈተ የፌስቡክም ኾነ ሌሎች የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች የላቸውም❞ የአማራ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ባሕር ዳር: ጥቅምት 07/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ስም የሚሠራጨው መረጃ ሐሰተኛ መሆኑን የክልሉ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል። የክልሉ ርእሰ መሥተዳደር መልእክት ያስተላለፉ በማስመሰል አንዳንድ ግለሰቦች ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆኑን ተገንዝበናል ያለው ቢሮው ርእሰ መሥተዳድሩ የሚጠቀሙበት በስማቸው የተከፈተ የፌስቡክም ኾነ ሌሎች የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች የሌላቸው መሆኑን እናሳውቃለን ብሏል። የሚሰራጨው መረጃ የርእሰ መስተዳድሩ አለመሆኑን የገለጸው ቢሮው ወደፊት የሚኖራቸውን ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጽ አማራጮች እንደሚያሳውቅም ገልጿል። ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

የመውሊድ በዓልን ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ በማሰባሰብና የተቸገሩትን በመርዳት እንደሚከበር በገንዳ ውኃ ከተማ የታላቁ ዑመር መስጅድ ኢማም ገለጹ፡፡ ገንዳውኃ: ጥቅምት 07/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃ ከተማ በታላቁ ዑመር መስጅድ 1ሺህ 496ኛውን የነብዩ ሙሐመድ የመውሊድ በዓል ዋዜማ አከባበር ምን እንደሚመስል ቅኝት አድርጓል። በበዓል ዋዜማው ያገኛናቸው የታላቁ ዑመር መስጅድ ኢማም ሼህ ሙሐመድ አብዱልከሪም 1 ሺህ 496ኛውን የመውሊድ በዓል ምክንያት በማድረግ ለመላው የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። በዓሉ ሲከበር የተቸገሩትን በመርዳት፣ ለተፈናቃዮች ሃብት በማሰባሰብና ለሀገር ህልውና ሲባል የማይተካ ሕይወታቸውን ለከፈሉ እና እየከፈሉ ላሉ ሁሉ ጸሎት በማድረግ እንደሆነ የታላቁ ዑመር መስጅድ ኢማም ሼህ ሙሐመድ አብዱልከሪም ገልጸዋል። ያለ ሰላም ሀገርን ማጽናት፣ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓትን መከወን አይቻልምና የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን በአጭር ጊዜ ተወግዶ በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ጸሎት በማድረግ በዓሉ እንደሚከበር ነው ኢማሙ የተናገሩት። ሼህ ሙሐመድ “ሀገር እንደ ሀገር እንድትቀጥል ሰላም ያስፈልጋል፤ የሰላም ምሰሶ ደግሞ ጸሎት ነውና የመውሊድ በዓልን ስናከብር ስለ ሰላም እንፀልያለን፤ ስለ ሰላም ለምዕመናኑ እናስተምራለን፤ ስለሰላም እንዘክራለን፤ ስለ ሰላም አላህን እንማፀናለን” ነው ያሉት። በበዓል ዋዜማው የእርድ ሥነ ሥርዓት የተፈጸመ ሲሆን አንድ ሦስተኛው ለተቸገሩ ወገኖችና ለዘማች ሚሊሻ ቤተሰቦች እንደሚሰጥም ነው የገለጹት። በግፍ ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖች ሃብት ማሰባሰባቸውን የገለጹት ደግሞ የመተማ ወረዳ የእስልምና ጉዳዮች ሊቀመንበር አቶ ሑሴን አሕመድ ናቸው። አሸባሪው የትህነግ ወራሪ ቡድን በከፈተው ጦርነት ሙስሊሙ ሰለቸኝና ደከመኝ ሳይል ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሰለፍ ሁለንተናዊ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ነግረውናል፡፡ ሽብርተኛው ትህነግ ሙሉ ለሙሉ እኪደመሰስ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ሑሴን አስታውቀዋል። በአዲስ የተመሰረተው መንግሥት ጦርነቱን በአጭር ጊዜ በመቋጨት ዜጎችን ከሞትና ከእንግልት ሊታደግ ይገባል ያሉት የሃይማኖት መሪዎቹ ሽብርተኛው ሸኔ በአማራ ላይ እየፈጸመ ያለውን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት አውግዘዋል። ዘጋቢ፡- ቴዎድሮስ ደሴ -ከገንዳ ውኃ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

“የአማራ ሕዝብ ህልውና ጸንቶ የሚኖረው በአሸባሪው ትህነግ መቃብር ላይ ነው” የአማራ ክልል መንግሥት https://www.amharaweb.com/የአማራ-ሕዝብ-ህልውና-ጸንቶ-የሚኖረው-በአ/ የክልሉ መንግሥት በወቅታዊ ጉዳይ ያወጣው መግለጫ ቀጥሎ ቀርቧል። የጀመርነውን የህልውና ዘመቻ ሳንቋጭ ሀሳብና ተግባራችን ከዓላማና ግባችን መንቀል ከፍተኛ ዋጋ እንዳያስከፍለን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። የህልውና ዘመቻው ተገደን የገባንበት እንደሕዝብ የመኖርና ያለመኖር መጻኢ እጣፋንታችን የምንወስንበት እንጂ የፓለቲካ ማሳለጫ አይደለም። ሊሆንም አይችልም። ፓለቲካም ይሁን ስልጣን ሕዝብና ሀገር ከመኖራቸው በኋላ የሚታሰቡ እና የሚመጡ ናቸው። ያለሕዝብና ያለሀገር የሚኖር ፖለቲከኛም [...]