en
Feedback
አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

Closed channel
3 156
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5330 days
Posts Archive
አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኀይል በግንባር ለመፋለም ዝግጁ መሆናቸውን የደቡብ ጎንደር ዞን የመንግሥት ሠራተኞች ገለጹ፡፡ ደብረታቦር፡ ጥቅምት 23/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን የመንግሥት ሰራተኞች ትግሉን በሚቀላቀሉበት ጉዳይ ላይ ከዞኑ አስተዳደር ጋር መክረዋል፡፡ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል በኢትዮጵያውያን ደም እና አጥንት የተገነባችን ሀገር እኔ ካልመራኋት አፈርሳታለው በሚል የአማራ እና አፋር ክልሎችን ወርሮ እያመሰ እንደሆነ የደቡብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ ይርጋ ሲሳይ ተናግረዋል፡፡ የአሸባሪው ፍላጎት የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን በሙሉ በተጽኖ ውስጥ ማስገባት እንደሆነም አብራርተዋል፡፡ ለዚህም መደበኛ እና መደበኛ ያልሆነ ውጊያ በማድረግ ፍላጎቱን ለማሳካት እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል፡፡ የሽብር ቡድኑ የታጠቀ እና ያልታጠቀ ኀይል በማደራጀት እየተወጋ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በተለይ መደበኛ ያልሆነው የሽብር ቡድኑ አሰላለፍ ከፍተኛ እንደሆነ ያስረዱት አስተዳዳሪው በትግራይ የሚገኝ ከሕጻናት እስከ አዛውንት፤ ካልተማረ እስከ ምሁር ድረስ ያሉ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በማደራጀት ለዘረፋና ለጦርነት ማሰለፉን አስረድተዋል፡፡ ዋና አስተዳዳሪው ጠላት በማንኛውም አሰላለፍ ቢመጣ በዛው አሰላለፍ ልክ መታገል እንደሚገባም ነው የገለጹት፡፡ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል በወረራ በያዛቸው የአማራ አካባቢዎች እኩይ ዓላማውን እየፈጸመ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ የሀገር መከላከያ ከልዩ ኀይል፣ ከሚሊሻ እና ከፋኖ ጋር በጥምረት ከአሸባሪ ቡድኑ ጋር እየተፋለሙ ነው የሚሉት ዋና አስተዳዳሪው እንደ አማራ ክልል ባለው አቅም ልክ ኀይሉን ገና እንዳላሰለፈ ነው ያስረዱት፡፡ ሕዝቡ ይህን የሽብር ቡድን በቃህ ብሎ በየአካባቢው ተደራጅቶ እረፍት ሊነሳው እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት፡፡ አባቶች በጀግንነት ጠብቀው ያስረከቧትን ሀገር አሁን ያለው ትውልድ ሊያስደፍራት እንደማይገባ ጠቁመዋል፡፡ ለዚህም ሁሉም ወደ ግንባር መሰለፍ እንዳለበት ነው ያስገነዘቡት፡፡ ዋና አስተዳዳሪው በዞኑ በተለያየ ምክንያት መዝመት ያልቻሉ ዜጎች ስንቅ በማዘጋጀት እና የኋላ ደጀን በመሆን እንዲታገሉ ነው መመሪያ የሰጡት፡፡ ሁሉም የድርሻውን ሲወጣ ጠላት እንዳልነበር ሆኖ እንደሚቀበር ነው ያስረዱት፡፡ የመንግሥት ሰራተኞች በበኩላቸው እሾህ የሆነ አደረጃጀት በመፍጠር ጠላትን በአጭር ጊዜ ለማጥፋት መዘጋጀታቸውን ነው የተናገሩት፡፡ ማን ታግሎ ነጻ እንዲያወጣን እንፈልጋለን ያሉት የመንግሥት ሰራተኞቹ ሀገር ሲወረር ቆመው እንደማይመለከቱ ነው ያስረዱት፡፡ ከጠላት ያነሰ አቅምም ሆነ ሥነልቦና የለንም ያሉት የደቡብ ጎንደር ዞን የመንግሥት ሰራተኞች ሀገሩ ሲወረር ቁጭ ብሎ የሚመለከት ትውልድ ይኖራል የሚል እምነት እንደሌላቸው ነው የሚገልጹት፡፡ የአማራ ክልል የመኖር እና ያለመኖር እጣ ፈንታ የሚወሰነው በዚህ ትውልድ እንደሆነም ነው የመንግሥት ሰራተኞቹ የሚገልጹት፡፡ የተበላሽ ታሪክ ለቀጣዩ ትውልድ እንደማያስረክቡም ተናግረዋል፡፡ ሕዝባዊ ማእበሉም በጠንካራ የሕዝብ ሰንሰለት እና አመራር ሊመራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በመሰዋእትነት ይህን የሽብር ኀይል ደምስሰው ትውልዱን ነጻ እንደሚያወጡ አረጋግጠዋል፡፡ መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ ለመታገል ፍቃደኝነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ - ከደብረታቦር ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል በአማራ ላይ እየፈጸመ ያለውን ግፍ ለማስቆም ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ የባሕርዳር ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 23/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር በክተት ጥሪዉ ዙርያ ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር ውይይት አካሂዷል። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዶክተር ድረስ ሳህሉ አሸባሪው ትህነግ ወደ ጫካ ከገባ ጀምሮ አማራን በጠላትነት በመፈረጅ ያደረሰውን ግፍና በደል አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል። ይህንን አማራ ጠል ቡድን ወጣቱ በመደራጀት ክልሉን ከወራሪው ኀይል ነጻ የማውጣት ታሪካዊ ኀላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። የሕዝብ ማዕበል መፍጠርና ጠላትን መደምሰስ፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊትንና ልዩ ኀይልን በሰው ኀይል ማጠናከር እና የሀብት ማሰባሰብ ሥራም ትኩረት እንደሚሰጠው አንስተዋል። ማኅበረሰቡ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚለቀቁ መረጃዎችን ትክክለኛ ምንጭ መመርመር እና ማረጋገጥ እንደሚገባውም ነው የተናገሩት። አማራን ለማጥፋት፣ ሀብት እና ንብረቱን ለመዝረፍ ከህጻን እስከ አዋቂ ተሰልፎ በአማራ ላይ የዘመተውን ወራሪ ኀይል አይቀጡ ቅጣት ለመቅጣት መዘጋጀታቸውን ተሳታፊዎች ተናግረዋል። አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል አማራን በጅምላ እየገደለ መኾኑን በመገንዘብ ዳግም በባርነት ቀንበር ላለመውደቅ ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ ነው ተሳታፊዎች ያነሱት። በማኅበረሰቡ ውስጥ ሆነው መረጃ የሚያቀብሉ እና የሀሰት መረጃ በመንዛት ሕዝቡን የሚያደናግሩ ኀይሎችን በተቀናጀ አግባብ ለሕግ ለማቅረብ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል። ዘጋቢ፦ ዳግማዊ ተሠራ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

“ትዳሬ እና ልጆቼ ከሀገሬ አይበልጡም” ወደ ግንባር ለመዝመት የተዘጋጁ የሚሊሻ አባል ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 23/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የክተት ጥሪ ተቀብለው ለመዝመት የተመዘገቡ ሚሊሻ አባል የሽብርተኛውን ትህነግ ወራሪ ቡድን ለመደምሰስ ከአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የተላለፈውን የክተት ጥሪ ተከትሎ በርካቶች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ወደ ግንባር እየተመሙ ነው፡፡ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የክተት ጥሪው ምላሽ በተመለከተ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተመዝጋቢዎችን አነጋግሯል፡፡ አቶ ወተቱ አሰፋ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የግሽዓባይ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ አቶ ወተቱ የሚሊሻ ስልጠና ወስደው ክፍለ ከተማውን ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ አቶ ወተቱ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ናቸው፡፡ በሚያገኙት ገቢ ልጆቻቸውን በግል ትምህርት ቤት ያስተምራሉ፡፡ ባለቤታቸው የስኳር ህመም ቢኖርባቸውም ሁሉም ነገር በሀገር ነውና በክተት ጥሪው እንዲሳተፉ ፈቅደዋል፡፡ አቶ ወተቱ እንዳሉት ሽብርተኛው የትህነግ ወራሪ ቡድን በአማራ እና በአፋር ክልሎች ዘር የማጥፋት ወንጀል እየፈጸመ ነው፡፡ ይህ ጭካኔ በየደጃችን እንዳይደርስ ልናስቆመው ይገባል ብለዋል፡፡ ይህንን ዘራፊ እና ጨፍጫፊ ቡድን ለማስቆም ሁሉም መረባረብ አለበት፤ እኔም “ትዳሬ እና ልጆቼ ከሀገሬ አይበልጡም” በማለት የክተት ጥሪውን ተቀብለው ወደ ግንባር ለመዝመት ዝግጅት አጠናቀዋል፡፡ አቶ ወተቱ አማራን ብሎም ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተነሳውን የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን ለመደምሰስ ዛሬ ነገ አያስፈልገውም ብለዋል፡፡ እንደ ግሽዓባይ ክፍለ ከተማ ሁሉም የመንግሥትም ሆነ የግል ታጣቂ በየአደረጃጀቱ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የክልሉ ወጣቶች ሀገራቸውን ለማዳን መሰለፍ እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ አቶ ሙሉጌታ ወርቅነህ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳዳር ግሽዓባይ ክፍለ ከተማ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት የሻለቃ መሪ ናቸው፡፡ አቶ ሙሉጌታ ቤተሰቦቻቸውን በንግድ ሥራ ያስተዳድራሉ፡፡ ሽብርተኛው የትህነግ ወራሪ ቡድን እያደረሰ ያለውን ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት ለማስቆም የክልሉ መንግሥት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ ተቀብለው ወደ ግንባር ለመዝመት ተዘጋጅተዋል፡፡ አቶ ሙሉጌታ እንደተናገሩት ሽብርተኛው የትህነግ ወራሪ ቡድን አማራን በማጥፋት ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተነሳ ነው፤ ይህን ሽብርተኛ ቡድን ለመደምሰስ ደግሞ ሁሉም ወደ ግንባር መዝመት አለበት፡፡ “ነግዶ ማትረፍ ሰርቶ መብላት በሀገር ላይ ነው፤ ሀገራችንን ከውድመት ለመታደግ ከሁሉም ቅድሚያ መሰለፍ ያለበት የሰለጠን የሚሊሻ አባላት በመሆናችን ለመዝመት ተዘጋጅተናል” ብለዋል፡፡ ማንኛውም የአማራ ክልል ነዋሪ ሀገሩን ከመፍረስ ለመታደግ እንዲዘምትም ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ አባቶቻችን ደማቸውን አፍስሰው እና አጥንታቸውን ከስክሰው ያቆዩአትን ሀገር ለወራሪ አሳልፎ ላለመስጠት ሁሉም መስዋእትነት መክፈል አለበት፤ ለዚህም መዘጋጀት ተገቢ ነው ብለዋል፡፡ የሀገራችን እጣ ፈንታ የሚወሰነው በወጣቱ ላይ ነው፡፡ ወጣቱ ጉልበት፤ እውቀት፣ ብልሀት አለው ሊጠቀምበት ይገባል ነው ያሉት፡፡ ዘጋቢ፡- ትርንጎ ይፍሩ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

"ወጣቶች አሸባሪውን ወራሪ ቡድን ለመፋለም ተዘጋጅተዋል" የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 22/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የሽብርተኛውን ትህነግ ወራሪ ቡድን ለመደምሰስ ከአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የተላለፈውን የክተት ጥሪ ተከትሎ የሰሜን ሸዋ ዞን ወጣቶች በግንባር ለመፋለም ዝግጅት መጀመራቸውን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ገብረፃዲቅ አስታውቀዋል፡፡ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ዝግ ተደርገው ማንኛውም እድሜው ከ18 ዓመት በላይ የሆነው የዞኑ ማኅበረሰብ ግንባር ለመሰለፍ በዝግጅት ላይ መሆኑን ነው ዋና አስተዳዳሪው ያነሱት፡፡ ወጣቶች ግንባር ከመዝመት ባለፈ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት አካባቢያቸውን በንቃት እየጠበቁ እንደሚገኙም ነው አቶ ታደሰ የነገሩን፡፡ ሰርጎ በመግባት የሽብር ሥራ ለመሥራት የሚሞክሩ አካላት ላይም እርምጃ እየተወሰደ ነው ብለዋል፡፡ አሸባሪው ትህነግ ሀገሪቱን ለማፍረስ አቅዶ እየሠራ መሆኑን ያነሱት አቶ ታደሰ ይህንን እኩይ ዓላማ ለማክሸፍ የመላው ኢትዮጵያውያንን የጋራ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ በጋራ በመሰለፍ ሁሉም ሀገሩን ሊታደግ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዞኑ አሸባሪውን ትህነግ ለመደምሰስ እየተደረገ ባለው ዘመቻ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ነው አቶ ታደሰ የጠቀሱት፡፡ ዘጋቢ፡- ዳግማዊ ተሠራ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

“እስካሁን ባለው ሂደት ወደ ግንባር ለመዝመት በርካታ ቁጥር ያለው ሕዝባዊ ሠራዊት ተመዝግቧል” የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር https://www.amharaweb.com/እስካሁን-ባለው-ሂደት-ወደ-ግንባር-ለመዝመ/ ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 22/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው እና ወራሪው የትህነግ ቡድን በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የከፈተውን መጠነ ሰፊ ወረራ ለመቀልበስ የክልሉ መንግሥት የክተት ጥሪ አስተላልፏል፡፡ የሽብር ቡድኑ ወረራውን ሕዝባዊ በማድረግ ሰብዓዊ ጉዳቶችን፣ ዘረፋና ውድመት እያደረሰ ነው ያለው የክልሉ መንግሥት ሕዝባዊ ወረራ የሚቀለበሰው በሕዝባዊ ማዕበል መሆኑንም አስታውቋል፡፡ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ድረስ ሳኅሉ [...]

ደቡብ ጎንደር ዞን ሕዝባዊ ማዕበሉን በፍጥነት ማደራጀት ጀምሯል፡፡ https://www.amharaweb.com/ደቡብ-ጎንደር-ዞን-ሕዝባዊ-ማዕበሉን-በፍጥ/ ደብረታቦር፡ ጥቅምት 22/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ከአያቶቻችን የወረስነው ስለ ሀገር ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት እና ስለ ሕዝብ ክብር መራራ መስዋእትነትን መጎንጨትን ነው። አማራ ሕልውናውን፣ ሀገሩን እና ክብሩን ለባንዳ አሳልፎ ከሚሰጥ ሞትን ይመርጣል። አሁን የአማራነት ጥግ የሚፈተንበት ታሪካዊ ወቅት ላይ ነን። ይህ ወቅት አቅሙ የፈቀደ ሁሉ ከሽብርተኛዉ ትህነግ ወራሪ ቡድን ጋር አንገት ለአንገት ተናንቆ ዘመን ተሻጋሪ ታሪኩን [...]

“በስደት መኖር ስለማይቻል እንዲኹም ሀገር ለቅቆ የትም ስለማይደረስ ጠላትን በርትታችሁ ልትታገሉ ይገባል” በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ካሊፎርንያ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መምህር ሀብተማሪያም እማኛው https://www.amharaweb.com/በስደት-መኖር-ስለማይቻል-እንዲኹም-ሀገር/ ደባርቅ፡ ጥቅምት 22/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ካሊፎርንያ ሀገረ ስብከት በወቅታዊ ሀገራዊ ችግር ለተፈናቀሉ ወገኖች 1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የምግብ ድጋፍ አድርጋለች። በአሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ምክንያት ከቀያቸው ተፈናቅለው በደባርቅ ከተማ የተገኙት አበባው መንግሥቱ በየወቅቱ ለሚደረግላቸው ድጋፍ በማድነቅ አመስግነዋል። "ተፈናቃይ ወጣቶች ዘመቻውን በመቀላቀል ለስደት የዳረጋቸውን ጠላት መደምሰስ ይኖርባቸዋል" ብለዋል። እናኑ [...]

የሽብር ቡድኑ በትላንትናዉ ምሽት ከ100 በላይ የኮምቦልቻ ወጣቶችን መግደሉን የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ https://www.amharaweb.com/የሽብር-ቡድኑ-በትላንትናዉ-ምሽት-ከ100-በላይ/ አዲስ አበባ፡ ጥቅምት 22/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥቷል። ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ በጠቅላይ ሚኒስትር እና በፌዴራል እና በክልል አመራሮች በባሕርዳር በተካሄደዉ ዉይይት አሸባሪውን የትህነግ ቡድን ላንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት የተለያዩ ዉሳኔዎች ተላልፈዋል ብለዋል። በዚህም መሰረት የአማራ ክልል የክተት ጥሪን ያስተላለፈ ሲሆን ሌሎች ክልሎችም የተለያዩ ዉሳኔዎችን እንደሚያሳልፉ [...]

ከአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የተላለፈ የአስቸኳይ ጥሪ! የትህነግ አሸባሪና ወራሪ ኃይል በአማራ ክልል ሕዝቦች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት እየፈፀመ ሕዝቡን እየገደለና እያዋረደ፤ ንብረቱን እየዘረፈ፣ እያወደመ እና ኢትዮጵያን ለማፍረስ የመጨረሻ የሞት ሽረት ትግል እያደረገ ነው፡፡ ይህንን በተጨባጭ እየገጠመን ያለዉን የሕልዉና አደጋ ለመቀልበስ በመደበኛዉ የሕግ ማስከበር ሥርዓት ብቻ ማሸነፍ የማይቻል ሆኖ በመገኘቱ፤ የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ባካሄደዉ 6ኛ ዙር፣ 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የሚከተሉትን የአስቸካይ ጥሪ ዉሳኔዎች አስተላልፏል፡፡ 1. ከሚሰጡት አገልግሎት አስፈላጊነት አኳያ እየተመዘነ የሚወሰን መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ማንኛዉም የመንግሥት ተቋም መደበኛ አገልግሎቱን አቋርጦ በጀቱን ጨምሮ ሁሉንም ነገር የገጠመንን የህልዉና ዘመቻ ለመቀልበስ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲረባረብ ተወስኗል። 2. ሁሉም የመንግሥት ተሸከርካሪ ወደ አንድ ማዕከል በማሰባሰብ ለሕልዉናዉ ዘመቻ አገልግሎት እንዲዉል እንዲደረግ። 3. የግል ተሸከርካሪ ባለቤቶች ለሕልዉና ዘመቻዉ ስኬት ሲባል በተፈለገ ጊዜ ሁሉ ተሸከርካሪዎቻቸውን በመስጠት ኃላፊነታቸዉን እንዲወጡ ተወስኗል። 4. በየደረጃዉ የሚገኝ አመራር የሕልዉና ዘመቻዉን ተቀብሎ የሚሰለፈዉን ሕዝብ አደራጅቶ ከፊት ሆኖ እየመራ ወደ ግንባር እንዲዘምት ይህን በማያደርጉ አመራሮች ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተወስኗል። 5. ሁሉም የመንግሥትና የግል የጦር መሳሪያ የታጠቀ በሙሉ ለሕልዉና ዘመቻዉ አገልግሎት እንዲዉል ተወስኗል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛዉም የግል መሳሪያ የታጠቀ የክልሉ ነዋሪ በማንኛዉም ምክንያት በሕልዉና ዘመቻዉ ላይ የማይሳተፍ ከሆነ የታጠቀዉን የግል መሳሪያ በአደራ ለመንግሥት እንዲያስረክብ ወይም እድሜዉ ለትግል ለደረሰ እና አካላዊ ጤንነት ላለዉ ለቤተሰብ አባሉ ወይም ለሌላ ሰዉ በማስተላለፍ ለህልዉና ዘመቻዉ አገልግሎት እንዲዉል እንዲያደርግ። 6. በደጀንነት የሚገኘዉ ሕዝባችን ለሕልዉና ዘመቻዉ የሚያስፈልገዉን የሎጂስቲክስ አገልግሎት በማቅረብ የሕልዉና ዘመቻዉን ዉጤታማ እንዲያደርግ፣ በየደረጃዉ የሚገኘዉ አመራርም አቅርቦቱ የተሳለጠ እንዲሆን አስፈላጊዉን እንዲፈጽም ተወስኗል። 7. የሕልዉና ዘመቻዉን ተቀብሎ በግንባር ለመፋለም ከሚሰማሩት ዉጭ ያለዉ ማንኛዉም የክልሉ ነዋሪ በየአካባቢዉ ተደራጅቶ የአካባዉን ጸጥታ እንዲጠብቅ፣ ጸጉረ ለዉጦችንና ሰርጎ ገቦችን እንዲከታልና ለሕግ አስከባሪ አካላት አሳልፎ እንዲሰጥና ለሕልዉና ዘመቻዉ የበኩሉን ኃላፊነት ሁሉ እንዲወጣ። 8. የህልዉናዉን ዘመቻ ዉጤታማ ለማድረግ በሚደረገዉ እንቅስቃሴ ላይ ለትግሉ በተለያየ መንገድ እንቅፋት በሚሆን ማንኛዉም ሰዉ ወይም ቡድን ላይ በየደረጃዉ እየተወሰነ የጸጥታ አካሉ አስፈላጊዉን እርምጃ እንዲወስድ ተወስኗል። 9. የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጡ ከተፈቀደላቸዉ ተቋማት ዉጭ በሁሉም ከተሞች ከምሽቱ 2፡00 እስከ ንጋቱ 12፡00 እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም። እነዚህን ዘጠኝ አስገዳጅ ዉሳኔዎች ዝርዝር አፈጻጸም በተመለከተ በክልል ደረጃ በተቋቋመዉ የዘመቻ መምሪያ በሚቀመጥ አሰራር የሚወሰን ይሆናል፡፡ ጥቅምት 21/2014 ዓ.ም ባሕር ዳር ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

የአሸባሪውን ትህነግ ወራሪ ቡድን ለመደምሰስ በተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውኃ ከተማ ፋኖዎች ገለጹ። ገንዳ ውኃ: ጥቅምት 21/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው ትህነግ ወረራ ከፈጸመባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች አንዱ ምዕራብ ጎንደር ዞን ነው። ከሱዳን በመነሳት በቲሃ በኩል የገባው አሻባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ሽንፋንና አካባቢውን ለማተራመስ ሙከራ ቢያደርግም በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻ፣ ፋኖና በዞኑ ኅብረተሰብ አይቀጡ ቅጣት መቀጣቱ የሚታወስ ነው። የክልሉ መንግሥት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ ተከትሎም በየትኛውም አቅጣጫ የሚመጣን የአሸባሪውን ትህነግ ወራሪ ቡድንና ተላላኪዎቹን ለመደምሰስ በተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውን የገንዳውኃ የፋኖ አባላት ተናግረዋል። የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ሀገርን ለማፍረስ የፈጸመውን ወረራ በመመከት የማያዳግም ርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን የፋኖ አባል ታያቸው ጥሩነህ ተናግረዋል። የጥፋት ተልዕኮውን ለመፈጸም በቲሃ በኩል የገባው የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን የተደመሰሰው ባደረጉት ዝግጁነትና ቁርጠኝነት መሆኑን ሌላኛው የፋኖ አባል ፈንታ ባዬ ገልጿል፡፡ “አማራን ለማጥፋት የመጣውን አሸባሪውን የትህነግ ወራሪ ቡድን ሁሉም ሕዝብ ሊዋጋው ይገባል” ብሏል ፋኖ ፈንታ። የአሸባሪውን ትህነግ ወራሪ ቡድን እንዲደመሰስ ኅብረተሰቡ ከአሁን በፊት በፈጸመው ጀብድ መዘናጋት የለበትም ያለው ደግሞ የፋኖ አባል ታያቸው ጥሩነህ ነው። አሁንም ለቀጣይ ትግል ራስን ዝግጁ ማድረግ ይጠበቃል ነው ያለው። ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የክልሉ መንግሥት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ ተቀብሎ ወደ ጦር ግንባር እንዲዘምትም ጠይቋል። የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ኢትዮጵያን ለማፍረስ አልሞ ቢንቀሳቀስም የፋኖ አባላት ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን አይቀጡ ቅጣት እየቀጡት መሆኑን ፋኖ ታያቸው ተናግሯል። በጠላት ላለመደፈር ወጣቱ በሞራልና በትጥቅ መዘጋጀት እንዳለበትም የፋኖ አባላቱ አስገንዝበዋል። ግንባር ከመዝመት ባሻገር የሽብር ቡድኑን ተልዕኮ ለመፈጸም የሚንቀሳቀሱ ሰርጎገቦችንና ጸጉረ ልውጦችን ኅብረተሰቡ ያለምንም መዘናጋት መከታተል አለበት ብለዋል። ዘጋቢ፦ ቴዎድሮስ ደሴ -ከገንዳ ውኃ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

መቀሌ አቅራቢያ የሚገኘው አጉላእ የጁንታው ታጣቂ ማሠልጠኛ ተቋም በአየር ኃይል ተመቷል። ተቋሙ በርካታ የቡድኑ አባላት ለሸብር ተልእኮ ተመልምለው የሚሠለጥኑበት ነው። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

“የአሸባሪው ትህነግን የመጨረሻ እስትንፋስ ለመዝጋት የተደራጀ ሕዝባዊ ትግልና ደጀንነት ወሳኝ ነው” የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ እንግዳ ዳኛው እንጅባራ: ጥቅምት 21/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን በአማራ እና በአፋር ክልሎች ወረራ በመፈጸም ኢትዮጵያን የማፍረስ ዓላማውን ለማክሸፍ ለታወጀው የህልውና ዘመቻ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እያደረጉ ነው፡፡ የሽብር ቡድኑን የመጨረሻ ግብዓተ መሬት ለመፈጸምም የአማራ ክልል መንግሥት የክተት ጥሪ አስተላልፏል፡፡ ሕዝቡም ፈጣን ምላሽ እየሰጠ ነው፡፡ ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻና ፋኖ ጎን በመሰለፍ ሽብርተኛው ትህነግን በመደምሰስ ሁሉም ደማቅ ታሪክ በመጻፍ ላይ ይገኛል። የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ነዋሪዎች ለህልውና ዘመቻው የሚደረገው የተደራጀና ወገናዊ ድጋፍ ሀገርና ወገንን ክዶ ዘግናኝ ግፍ እየፈጸመ የሚገኘውን ሽብርተኛው ትህነግ በአጭር ጊዜ ለመደምሰስ እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ ስለሚደረገው ድጋፍ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ያነጋገራቸው የእንጅባራ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ጠጄ ወሌ እንደገለጹት ሽብርተኛው ትህነግ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት ነው፤ ይህ የሽብር ቡድን እስከመጨረሻው እስኪደመሰስ እያደረጉት ያለውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡ የሽብርተኛው ትህነግን እድሜ ለማሳጠር ተከታታይነት ያለው ድጋፍ ማድረግ እና መንግሥት ላስተላለፈው የክተት ጥሪ ፈጣን ምላሽ መስጠት ግድ ይላል ነው ያሉት፡፡ የሽብርተኛው ትህነግን የመጨረሻ ግብዓተ መሬት ለመፈጸም ለመዝመት ብቁ የሆነ ሁሉ ወደ ግንባር መዝመት አለበት ብለዋል፡፡ ግንባር ድረስ በመሄድ መፋለም የማይችሉ ኢትዮጵያውያን በሽብርተኛው ትህነግ ግፍ ምክንያት ያለቀሱ የእናቶችን እንባ ማበስ የሚችሉት ለህልውና ዘመቻው በሚያደርጉት የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሌላው የእንጅባራ ከተማ ነዋሪ በላይነህ አየለ ሽብርተኛው ትህነግ እየፈጸመ ባለው ግፍ ስቃይ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ነጻ ለማውጣት ሁሉም ዜጋ ግንባር ድረስ በመዝመት መፋለም እና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ እሳቸውም እያደረጉት ካለው ተከታታይ እና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ በተጨማሪ ወደ ግንባር በመዝመት ለመፋለም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ እንግዳ ዳኛው “የአሸባሪው ትህነግን የመጨረሻ እስትንፋስ ለመዝጋት የተደራጀ ሕዝባዊ ትግልና ደጀንነት ወሳኝነት አለው” ብለዋል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ሕዝብም የክልሉ መንግሥት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ በመቀበል ወደ ወሎ እየዘመተ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ሌላው ነዋሪ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከአማራ ልዩ ኃይል፣ ከሚሊሻ፣ ፋኖ እና ከተፈናቀሉ ወገኖች ጎን መሆኑን ለመግለጽ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ዋና አስተዳዳሪው አስታውቀዋል፡፡ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል፡፡ ዘጋቢ፦ አዳሙ ሽባባው ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

የአማራ ክልል መንግሥት ባስተላለፈው የሕልውና ዘመቻ የክተት ጥሪ መሰረት ሽብርተኛው ትህነግን ለመፋለም እንደሚዘምቱ አርሶአደሮች ገለጹ፡፡ ደብረማርቆስ: ጥቅምት 21/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አርሶ መመገብ የሚቻለው ሀገር ሰላም ሲሆን በመሆኑ መንግሥት ያደረገውን የክተት ጥሪ በመቀበል ወደ ግንባር ለመዝመት መዘጋጀታቸውን በምሥራቅ ጎጃም ዞን የባሶሊበን እና አነደድ ወረዳ አርሶአደሮች ገልጸዋል። አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ያነጋገራቸው አርሶአደር ቤዛ ዓለሙ “የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት ለወረራ የመጡት ትርፍ ነፍስ አስቀምጠው አይደለም፤ እንደኛ አንድ ነፍስ ይዘው እንጂ፤ በመሆኑም በጋራ ተሰልፈን እንዋጋቸዋለን” ብለዋል። አርሶ አደር ወርቅነህ አስማረ ማምረት እና አርሶ መብላት የሚቻለው ሀገር ሰላም ሲሆን በመሆኑ እያመረትን እንታገላለን ብለዋል። በሽብርተኛው ትህነግ ወረራ ለተፈናቀሉ ዜጎች እና ለህልውና ዘመቻው በገንዘብ እና በዓይነት ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል። አሁንም ድጋፉ ተጠናከሮ ይቀጥላል ብለዋል። አርሶ አደር ወርቅነህ ሽብርተኛው ትህነግ በወገኖች ላይ እየፈጸመ ያለው ግድያ እና ሰቆቃ በአጭር ጊዜ እንዲያበቃ ሁሉን አቀፍ ትግል ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ጎጃም ሉሌ ለሕልውና ዘመቻው እና በሽብርተኛው ትህነግ ወረራ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተጠናከረ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሴቶች በታሪክም ለሀገራቸው ግንባር ቀደም እንደነበሩ አንስተው አሁንም በሽብርተኛው ትህነግ ወረራ ምክንያት ችግር ውስጥ የወደቁ ወገኖችን ለመደገፍም ኾነ ግንባር ተሰልፎ ለመፋለም ቁርጠኛ እንደሆኑ ነግረውናል፡፡ ዘጋቢ፦ ዳግማዊ ተሠራ

❝አሸባሪው የህወሓት ቡድን ሀገር ለማፍረስ በአማራና አፋር ክልል ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን ጥፋት በጋራ በመመከት ግብዓተ መሬቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፈጸም በጋራ መነሳት አለብን❞ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ https://www.amharaweb.com/❝አሸባሪው-የህወሓት-ቡድን-ሀገር-ለማፍረ/ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ በወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ላይ መግለጫ ሰጥቷል። የመግለጫው መልዕክት ቀጥሎ ቀርቧል:- ኢትዮጵያን በታሪኳ የሞከረ እንጅ ያሽነፈ ኃይል አልነበረም፣ አይኖርም። ከጽንሰ ሐሳቡ እስከ ውልደቱና እድገቱ አልፎም የኖረበትን 27 ዓመታት በሙሉ ለስልጣኑ ሲል ኢትዮጵያን በዘር፣ በሃይማኖት፣ በጎሳና በጎጥ ከፋፍሎ ሲመዘብር የቆየው አሸባሪው ትህነግ ቡድን ብሶበት በሀገራዊ ለውጥ ምክንያት ስልጣኑን ካጣበት ጊዜ [...]

ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረው አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል። https://www.amharaweb.com/ደሴን-ለመውረር-አሰፍስፎ-የነበረው-አሸባ/ ጥቅምት 21/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በጢጣ በኩል ሰብሮ በመግባት የደሴ ከተማን ለመቆጣጠር የሞከረው አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል። የመጣውን ኃይልም ደሴ ከተማ ከመግባቱ በፊት ሙሉ በሙሉ ባለበት ማስቀረት መቻሉን በወሎ ግንባር ወራሪውን ኃይል እያጸዱ የሚገኙ የመከላከያና ደኅንነት ምንጮች ጠቁመዋል። የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለመ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ [...]

ሁሉም ነገር ሰላም ነው። ህዝባችን የማንም ደካማ መጫዎቻ የሆነበትን እንቆቅልሽ የግድ፣ የግድ እንፈታዋለን። ከአሁን በኋላ የማንንም ተኳሽና አስተኳሽ ታቅፈን እየቀለብንና በይሉኝታ ተቀፍድደን በመድፍ የምንደበደብበት አንዳች ምክንያት አይኖርም። ጋሻው መርሻንና እኔን ለመምታት ሶስት መድፍ ተተኩሷል። አንዱ መኪናችንን ስቷል፣ ሌላው የመኝታ ክፍላችንን አፍርሷል። ከተኳሹ አስተኳሹ! ከ30000 በላይ የትህነግ አስተኳሽ ታቅፎ የሚኖረው የደሴ ከተማ ህዝብ ከውስጥ ባይተኮስበት፣ በውዥንብር ባይፈታ ነበር የሚገርመው። ግን ይሄን ምስኪን ህዝብ የሚያስብለትና የሚያስተዳድረው ማን ነው? ደሴ ከተማ ለመግባት ከሞከረው ወራሪ ጋር መቀሌ እንደምንገናኝ ስነግራችሁ "የማይሰበር፣ የማይነጥፍ ቃል" መሆኑን በማረጋገጥ ነው። ከዚህ በኋላ በትግላችን እቀልዳለሁ ወይም አላግጣለሁ የሚል ካለ የብረት ገላ ካለው ብቻ ይሞክረው! እጅግ መራር በሆነ ምዕራፍ እንገናኝ!!! 📝የሱፍ_ኢብራሂም (ከደሴ) @warkatime

አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኀይል ለመደምሰስ እድሜ እና አካላዊ ብቃቱ የፈቀደለት የአማራ ክልል ሀገር ወዳድ ዜጋ ኹሉ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥቅምት 23/2014 ዓ.ም ድረስ ትጥቅ፣ ማንኛውንም መሣሪያ እና ስንቅ በመያዝ ወደ ወረዳ ማዕከል ክተቱን ተቀብሎ እንዲገባ የአማራ ክልል መንግሥት ታላቅ የኅልውና ዘመቻ አቀረበ። የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ ሰጥቷል። የመግለጫው ሙሉ መልዕክት ቀጥሎ ቀርቧል:- እጅግ የተከበርከው የአማራ ክልል ሕዝብ ሆይ! በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል ሀገርን ማፍረስ ዋነኛ ቀዳሚ ዓላማ አድርጎ ይህንኑ ፍላጎቱን ለማስጠበቅ በአይነቱ የተለየ፣ በተሳሳተ ትርክትና የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ የተጠለፈ ሕዝባዊ አሰላለፍ በመፍጠር መጠነ ሰፊ ወረራ መፈፀሙና እየፈፀመ መሆኑ ይታወቃል። እድሜያቸው ከ12 እስከ 65 ዓመት የሚደርሱ ወንድና ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞችና ነፍሰ ጡሮች፣ ካህናትና ሸኮች ሳይቀር እያስገደደ በማሰማራት ወደ አማራና አጎራባች የአፋር ክልሎች አዝምቷል። በዚህ ወረራ ወደር የሌለው ጭካኔ በመላበስ አማራን እስከወዲያኛው አንገት ለማስደፋት በየደረሰበት አካባቢ ሴቶችን በመድፈር፣ ንጹሐንን በመረሸን፣ መሰረተ ልማቶችን በማውደም፣ የመንግሥትና የግለሰብ ሀብቶችን በመዝረፍ፣ የቤት እንሰሳትን በጥይት በመግደል ሕዝብን እያሸበረ ከቀየው እንዲሰደድ በማድረግ ላይ ይገኛል። የትግራይ ወራሪ ኃይል ሀገርን የማፍረስና አማራን እንደ ሕዝብ የማጥፋት ዘመቻው ከመደበኛ ወታደራዊ አደረጃጀት በተጨማሪ በሕዝባዊ ማዕበል መቀልበስና መደምሰስ እንዳለበት ግድ የሚል ሁኔታ ስለተፈጠረ ሀገራዊ የመንግሥት ጥሪ መተላለፉ ይታወቃል። ይህ ሀገራዊ የመንግሥት ጥሪ እንደተጠበቀ ኾኖ በአማራ ክልል ደረጃ ፈጣንና የተደራጀ ሁሉ አቀፍ ሕዝባዊ ዘመቻ ማካሄድ ጊዜ የማይሰጠው እጅግ አጣዳፊ ጉዳይ ሆኗል። ስለሆነም እድሜውና አካላዊ ብቃቱ የፈቀደለት የክልላችን ሀገር ወዳድ ዜጋ ኹሉ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥቅምት 23/2014 ዓ.ም ድረስ ማንኛውንም መሳርያና ስንቅ በመያዝ ወደ ወረዳ ማዕከላት የክተት ጥሪውን ተቀብሎ እንዲገባ የክልሉ መንግሥት ታላቅ የሕልውና ዘመቻ ጥሪ አቅርቦልሃል። ሁሉ አቀፍ የሕልውና ዘመቻውን የተደራጀ አመራር፣ በሕዝባዊ ማዕበል ተመስርቶ በእልህና በወኔ ለማከናወን የሚያስችል ዝርዝር ማስፈፀሚያ መመርያ በየአካባቢው ይደርስሃል። የዚህ ክተት ዘመቻ ዋነኛ ኃይላችን ለመስዋእትነት የተዘጋጀ ሕዝባችን መሆኑን የክልላችን መንግሥት ያምናል። በመሆኑም አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኃይል የከፋ ምኞች ማምከን ብሎም የገባበት ገብቶ ለመደምሰስ የቀረበውን የጀግንነት ጥሪ በመቀበል ኢትዮጵያን ለማዳን እንዲሁም የአማራ ክልልን ሕዝብ ከውርደት ለመታደግ እንድንዘምት የክልሉ መንግሥት ጥሪውን በድጋሜ ያስተላልፋል። ህልውናችንን በትግላችን እናረጋግጣለን! እናሸንፋለን! የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጥቅምት 20/2014 ዓ.ም ባሕርዳር፣ ኢትዮጵያ

ሁሉም ነገር ሰላም ነው። ህዝባችን የማንም ደካማ መጫዎቻ የሆነበትን እንቆቅልሽ የግድ፣ የግድ እንፈታዋለን። ከአሁን በኋላ የማንንም ተኳሽና አስተኳሽ ታቅፈን እየቀለብንና በይሉኝታ ተቀፍድደን በመድፍ የምንደበደብበት አንዳች ምክንያት አይኖርም። ጋሻው መርሻንና እኔን ለመምታት ሶስት መድፍ ተተኩሷል። አንዱ መኪናችንን ስቷል፣ ሌላው የመኝታ ክፍላችንን አፍርሷል። ከተኳሹ አስተኳሹ! ከ30000 በላይ የትህነግ አስተኳሽ ታቅፎ የሚኖረው የደሴ ከተማ ህዝብ ከውስጥ ባይተኮስበት፣ በውዥንብር ባይፈታ ነበር የሚገርመው። ግን ይሄን ምስኪን ህዝብ የሚያስብለትና የሚያስተዳድረው ማን ነው? ደሴ ከተማ ለመግባት ከሞከረው ወራሪ ጋር መቀሌ እንደምንገናኝ ስነግራችሁ "የማይሰበር፣ የማይነጥፍ ቃል" መሆኑን በማረጋገጥ ነው። ከዚህ በኋላ በትግላችን እቀልዳለሁ ወይም አላግጣለሁ የሚል ካለ የብረት ገላ ካለው ብቻ ይሞክረው! እጅግ መራር በሆነ ምዕራፍ እንገናኝ!!! 📝የሱፍ_ኢብራሂም (ከደሴ) @warkatime

ከመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ! https://www.amharaweb.com/ከመንግሥት-ኮምዩኒኬሽን-አገልግሎት-የተ/ በሀገር መከላከያ ሠራዊት እየተመራ ወራሪውን የሽብር ቡድንና ያሰለፈውን መንጋ እየመከተ የሚገኘው መላው የፀጥታ ኀይላችን በፀረ ማጥቃት እርምጃው ቀጥሏል። በተለይ ደሴን ለመያዝ አሰፍስፎ የመጣውን ወራሪ ኀይል በመመከት አኩሪ ገድልን እየፈፀመ ይገኛል። ሌሊቱን ሙሉ ከተለያዩ ግንባሮች ጠጋግኖ በማሰባሰብ ደሴን ለመያዝ በኩታበር፣ ቦሩ ስላሴና በኀይቅ መስመር የመጣውን ወራሪ መንጋ የፀጥታ ኀይላችን በታላቅ ጀብዱ መክቶታል። አሁንም ደሴና አካባቢዋ በፀጥታ [...]

የብልጽግና ፓርቲ ጥሪ። https://www.amharaweb.com/የብልጽግና-ፓርቲ-ጥሪ።/ ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአሸባሪው ትሕነግ ኢትዮጵያን የማፈራረስ ከንቱ ምኞትን በሚገባው ቋንቋ አስረድተን እስከወዲያኛው ላይመለስ በአጠረ ጊዜ ልንሸኘው ይገባል ሲል ብልጽግና ፓርቲ ጥሪ አቀረበ፡፡ ፓርቲው በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባወጣው መረጃ አሸባሪው ሕወሓት ኢትዮጵያን በቅጥፈት እጆቹ ጠፍጥፎ የጋገራት ሕብስት አድርጎ በመቁጠር እሱ ባሻው ሰዓት የሚያቦካትና የሚፈረካክሳት ጡብ አድርጎ ይቆጥራታል ብሏል። ነገር ግን ኢትዮጵያዊያንን [...]