Eyerusalem (Jerri) Negiya official channel
Open in Telegram
" ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜም ምስጋናህን ይናገራል።" (መዝሙረ ዳዊት 35:28) ይሄ የዘማሪት ኢየሩሳሌም ነጊያ telegram channel ነው። በዚህ ቻናል ፣ ነባርና አዳዲስ፣ እንዲሁም አልበም ላይ ያልተካተቱ ዝማሬዎቼን፣ ጽሑፎቼን ያገኛሉ። በተጨማሪም ከታች ባለው ሊንክ አዳዲስ ቪዲዮዎ ያገኛሉ https://www.youtube.com/channel/UCfDm9KT5NCiY9X_scwSqP_A
Show more2 034
Subscribers
+324 hours
+37 days
+4930 days
Posts Archive
ነፍሴ በዛለችብኝ ጊዜ እግዚአብሔርን አሰብሁት፤ ጸሎቴም ወደ አንተ ወደ ቅዱስ መቅደስህ ገባች። ት ዮ 1:7
7 እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? ሉቃ 18:7
ታላቅ ተራራ ሆይ፥ አንተ ምንድር ነህ? በዘሩባቤል ፊት ደልዳላ ሜዳ ትሆናለህ፤ ሰዎችም፡— ሞገስ፥ ሞገስ ይሁንለት፥ ብለው እየጮኹ፥ እርሱ መደምደሚያውን ድንጋይ ያወጣል፥ ብሎ ተናገረኝ።
ዘካ 4:7
17 ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥
18 እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።
19 ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል። ት.ዕን3: 17-19
ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ጕበኞችን በቅጥርሽ ላይ አቁሜአለሁ፤ ቀንና ሌሊት ከቶ ዝም አይሉም፤ እናንተ እግዚአብሔርን የምታሳስቡ፥ ኢየሩሳሌምን እስኪያጸና በምድርም ላይ ምስጋና እስኪያደርጋት ድረስ አትረፉ ለእርሱም ዕረፍት አትስጡ። ኢሳ 62:6
በፍጹምም ልባቸው ምለዋልና፥ በፍጹምም ሕሊናቸው ፈልገውታልና፥ እርሱም ተገኝቶላቸዋልና ይሁዳ ሁሉ በመሐላው ደስ አላቸው፤ እግዚአብሔርም በዙሪያቸው ዕረፍት ሰጣቸው። 2 ዜና 15:15
እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ የሚያውቅ ልብ እሰጣቸዋለሁ፤ በፍጹምም ልባቸው ወደ እኔ ይመለሳሉና ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ።
ኤር 24:7
5 የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥ 2ቆሮ 10:5
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡— ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤
ነገር ግን የሚመካው፡— ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር።
ኤር 9;27-28
