Eyerusalem (Jerri) Negiya official channel
Open in Telegram
" ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜም ምስጋናህን ይናገራል።" (መዝሙረ ዳዊት 35:28) ይሄ የዘማሪት ኢየሩሳሌም ነጊያ telegram channel ነው። በዚህ ቻናል ፣ ነባርና አዳዲስ፣ እንዲሁም አልበም ላይ ያልተካተቱ ዝማሬዎቼን፣ ጽሑፎቼን ያገኛሉ። በተጨማሪም ከታች ባለው ሊንክ አዳዲስ ቪዲዮዎ ያገኛሉ https://www.youtube.com/channel/UCfDm9KT5NCiY9X_scwSqP_A
Show more2 032
Subscribers
No data24 hours
-37 days
+5030 days
Posts Archive
በዚያን ጊዜ፡— እንኪያስ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ፡ አላቸው። ማቴ 22:21
እንኳን ለጌታችን ለመድኅኒታችን ለኢየ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል መታሰቢያ አደረሳቹ ✝️🙌🏻😇🙏 Happy Resurrection Day
እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ።ኢሳ 41:10
ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም። 1 ዮሐ 4:10
Next time you see the couple with house, car and a dog on your feed remind yourself: ሁሉ ቀሪ፥ ሁሉ አላፊ ጠፊ ነው። ይዘነው ምንሄደው ሀብታችን በሰማይ ያከማቸነው መዝገብ ኢየሱስ ብቻ ነው።እንደተላላ 80 አመት እንፋሎት በማሳደድ አባክነን በእድሜያችን ማምሻ "ለካስ ኢየሱስ ነበር የመንፈስ ፍስሀ" ብሎ ከመፀፀት treasure Jesus wholeheartedly today.
“በሰማይ ከአንተ በቀር ማን አለኝ? በምድርም ከአንተ ሌላ የምሻው የለኝም።” መዝ 73፥25
ይህን መጣጥፍ አንድ ሰው በቴሌግራም አጋራኝና ውደድኩ : ከዛ ላጋራቹ ፈለገሁ ፀሀፌዋ ናርዶስ (Nana) ትባላለች በግልም አላውቃትም :
ነፍሴ በዚህ ዓለም አሰልቺ ድግግሞሽ በዛለችብኝ ጊዜ ኸረ ወዲያ እስከመቼ ብዬ የአምላኬፍ ፊት በመናፈቅ ውስጥ ሆኜ የተቀበልኩትን መዝሙር በሚገርም ሁኔታ አብራኝ የፃፈች እስኪመስለኝ ድረስ በሚገርም ሁኔታ ተንትናዋለች ፁፋ ካልረዘመባቹ እስከመጨረሻው እንድታነቡት አበረታታዋለሁ ናርዶስ ጌታይባርክሽ 🙌🏻😇
ገነቴ ነህ
ባለብሰው ገላዬ አዲሱ ያረጃል
የተጫሙ እግሮቼ ሌላ ያምራቸዋል
ደግሞ ይርበዋል ያበላሁት ሆዴ
ጥሜ ቆረጠ ስል ውሀ ጠማው አፌ
የኑሮዬ ቋጡ ገደቡ ላይሞላ
ስባክን ስዳክር ብዬ እንዳልቀር ኋላ
ሰማዩን ረስቼ ምድሩን ቆንጥጬ
አብላኝ አጠጣኝ ስል ለስጋዬ ሮጬ
አይጠረቃ ህይወቴ አይሞላ ክፍተቴ
መቼ በቃኝ ያውቃል ይሄ ማንነቴ
በምድራዊው አይደል በእህልና ውሀ
ለካስ ኢየሱስ ነው የመንፈስ ፍስሀ
ለካስ ኢየሱስ ነው የነፍሴ ፍስሀ
ሰለሞን በክብሩ ከለበሰው በላይ የምታስጌጣቸው አበቦች ጋር ፉክክር ገጥሜ ዘወትር recycle የሚደረገውን ፋሽን በማሳደድ እንድሽቀረቀር ብዙ ግፊት አለ። The 'geniuses' have convinced us that wearing brands with their name on it elevates our value..ግን ይሄ ሁሉ ልፋት ከንቱ ነው። ምክኒያቱም የማይወይብ ቀለም የማይነትብ ድሪቶ የለም።No matter how hard I try to keep up አዲስ ትሬንድ ሲመጣ ወይ ወቅቱ ሲቀየር ፍላጎቴም አብሮ ይለወጣል።
መክብብ ላይ ከተዘረዘሩት እግዚአብሔር ለሚሰራ ሰው መደሰቻ እንዲሆን ከሰጣቸው ስጦታዎች መሀል አንዱ (በተደጋጋሚ የተጠቀሰውም 😊) ምግብ ነው። እንደዚህ ሀገር ሰው መቼም ብዙዎቻችን ምግብን ለመሰንበት እንጂ ለመደሰት እያሰብን ላንበላ እንችል ይሆናል። ብቻ ግን እግዚአብሔር ዲዛይን ሲያደርገን ራሱ በየዕለቱ እንዲያስፈልገን አድርጎ ስለሆነ ለመብላት እንደምንኖር ሁሉ ዘወትር መደሰቻችንና ቁምነገራችን ሆኗል። Our social life and celebrations revolves around it.
....
የኑሮ ቋጥ ቀዳዳ ነው። የ11 ክፍል ኢኮኖሚክስ መፅሀፍ እንደሚለው የሰው ፍላጎት ገደብ የለውም። ማንም ሳያስገድደን ( በፈቃዳችን በተፅዕኖው ስር ውለን) ራሳችንን በሆነ መንገድ ከቀደመን ሰው ጋር እያወዳደርን ኋላ መቅረታችን አስቆጭቶን እረፍትን ለራሳችን እንነፍጋለን። Social media ደግሞ ይሄን አባብሶታል.. በ21 አመታቸው ቤት- መኪና- ትዳር- ልጆችና የሳሎን ውሻ ያሟሉትን ሰዎች አልጎሪትሙ ይመግበናል።
አስቡት እስቲ... "ዛሬ officially ከስራ ተባረርኩ።" "ቤት ኪራይ መክፈል ከተሳነኝ 3 ወር ሆነኝ"። "ከጓደኛዬ ጋር ተጣላን" እያለ የሚለጥፍ የለም። ጥቂት ሰዎች የህይወታቸውን ፈካ ያለ እጅግ ጥቂት ክፍል ያሳዩናል። ከዚያም አብዛኛውን ህይወታችንን consume እንዲያደርግ የፈቀድነውን አለም በጄሪ አማርኛ ቆንጥጠን የሙጥኝ ይዘን ልናሸንፈው እንሯሯጣለን። As if life was all about this world – ያለንን አቅም፣ ጊዜ፣ ሀሳብ ፣ ገንዘብ ሁሉ እዚሁ ምድር ላይ invest እናደርጋለን።
የልቤ ሀሴት የውስጤ እርካታ
ኢየሱስ አንተ ነህ የነፍሴ ፋታ
ባንተ ደስ ይለኛል ሁልጊዜ ሀሴት አደርጋለው።
የሰጠኸኝ ደስታ ፍፁም ነው እፍለቀለቃለው
የሰጠኸኝ ተስፋ ፍፁም ነው እፈነድቃለው
ባልበላም ጠግቤ አድራለው
ባልጠጣም ረክቼ ኖራለው
አንተ ካለህ ምን ሆናለው?
በረሀው ላይ አስቀኸኛል። ገነቴ ነህ አርክተኸኛል
ፍቅርህ ብቻ ይበቃኛል። መገኘትህ ያረካኛል
አንተ ካለህ ምን ያሻኛል? ፊትህ ብቻ ይበቃኛል።
ኢየሱስ ግን ሁሉ በሁሉ ነው። የምር ባይገባን ነው እንጂ.. እርሱ የህይወት ውሀ ነው። በጥማት የተዝለፈለፉትን ሊያረካ በምድረበዳ ከዓለት ከፈለቀው ውሀ በላይ የውስጥን በረሀ የሚያለመልም ተዓምር ነው። የምትቅበዘበዝ ነፍሳችን ፋታን ለማግኘት ኢየሱስ ጋር እንጂ ሌላ ምን መሄጃ አላት? “
ነፍሴ ዕረፍት የምታገኘው በእግዚአብሔር ብቻ ነው”(መዝ 62፥1)
ደካሞችንና ሸክም የተጫናቸውን እረፍት ሊሰጥ በፍቅር የሚጠራ መልካም እረኛ ኢየሱስ ብቻ ነው። የህይወት እንጀራ ስለሆነ ስጋን ለብሶ ራሱን ሳይሰስት ስለኛ የቆረሰ መናችን የሆነ ..ያደፈ ቡትቷችንን አስወግዶ የክት ልብስ የሆነን አብ ፊት መታያችን ኢየሱስ ፤ ኢየሱስ ብቻ ነው።
I love that this song is not just a testimony of experience, it can also be sung with a conviction that declares a decision of how to live from this point forward. ምናልባት ከዚህ በፊት ደስታችሁ በኢየሱስ ሳይሆን በሁኔታዎች ሆኖ ሊሆን ይችላል። How is that working for you? ነገሮች በተዛነፉ ቁጥር ደስታን እያዘረፉ መኖር ያዋጣል?
ዘላቂ የሆነ ደስታ ከፈለግን በእርግጥም በኢየሱስ ከመደሰት ውጪ አማራጭ የለንም። Piper explains the famous westminister confession article that states the chief end of man is to glorify God by enjoying Him። የተፈጠርነው በእርሱ በመርካትና በመደሰት ልናከብረው ነው።
So seeking enjoyment /happiness isn't the problem. Its where we are seeking it. በእርሱ ለመደሰት ስለተፈጠርን ደስታን በእግዚአብሔር በመፈለግ ራስወዳድ pursuit አይደለም። ሐዋርያው ጳውሎስ ስለወገኖቹ መጥፋት ስለሚያስብ ብዙ ሀዘንና የማያቋርጥ ጭንቀት አለብኝ እያለ እየመሰከረ.. ሁልጊዜ በጌታ ደስ እንዲለን የሚፅፈው ለዚህ ነው። Sorrowful yet always rejoicing is the testimony of a christian. Sorrow is inevitable. But we shouldn't rob ourselves of joy that is freely available to us in Christ because the joy of the Lord is our strength we can't 'live' without it. (ነህሚያ 8)
ነገሮች ሲሞሉም ሲጎድሉም our attitude should be "አንተ ካለህ ምን ሆናለው?" ምክኒያቱም የተደገፍነው ምርኩዝ ሸንበቆ አይደለም። አስተማማኝ ነው። ደግሞም የፈራነው በረሀም ቢመጣ ኢየሱስ ባለበት በረሀ መሳቅ literally የትም ቦታ ካለ ደስታ አይወዳደርም። ይሄ ሳቅ በምንም አይኮረኮርም፤ አልተደጋገፈም። በምንም ያልተገኘ በምንም የማይታጣ ኢየሱስ በሚገኝበት በቀኙ ያለ ፍስሀ ነው።
የኢየሱስን አብሮነት፣ ፍቅሩንና ለእኛ ያለውን ልብ በዚህ ምድር experience ማድረግ is the closest thing to heaven we'll experience in this broken world. It doesn't get better than that. Don't buy into the lie that there's more to life than that. There really isn't.
እግዚአብሔርም ሙሴን፡— የአማሌቅን ዝክር ከሰማይ በታች ጨርሼ እደመስሳለሁና ይህን ለመታሰቢያ በመጽሐፍ ጻፈው፥ በኢያሱም ጆሮ ተናገር፡ አለው። ዘፀ 17:14
ዮሴፍ ትንሹ የፍሬ ዛፍ ነው፥ በምንጭ አጠገብ የሚያፈራ የፍሬ ዛፍ፤ አረጎቹ በቅጥር ላይ ያድጋሉ። ዘፍ 49:22
ታላቅም ድምፅ ከሰማይ፡— እነሆ፥ የእግዚአብሔር ድንኳን በሰዎች መካከል ነው ከእነርሱም ጋር ያድራል፥ እነርሱም ሕዝቡ ይሆናሉ እግዚአብሔርም እርሱ ራሱ ከእነርሱ ጋር ሆኖ አምላካቸው ይሆናል፤ የዮሐንስ ራዕይ 21:3
ልቤን ባሰፋኸው ጊዜ፥ በትእዛዝህ መንገድ ሮጥሁ።መዝ 119:32
I will run the course of your commandment for you shall enlarge my heart ❤️
Psalm 119:32
https://vm.tiktok.com/ZMDrDngPE
The other of me👩🍳pls follow 🙌🏻
ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፤ እግዚአብሔር ወስዶታልና።
ዘፍ 5:24
