አዋሬ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ - AFG
Open in Telegram
ይህ ቻናል የአዋሬ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤ/ክ ሲሆን የቤተ ክርስቲያንን መልዕክት የምናስተላልፍበት ነው፡፡
Show more303
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+930 days
Posts Archive
የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ !
ዛሬ ዕሀድ (ህዳር 09 ቀን 2016 ዓ.ም ) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን "የተልዕኮ ሠው እና ገንዘቡ ምን ይመስላል ?" በሚል ሀሳብ የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ ወንድም ዳግማዊ ካሣሁን ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የጎተራ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን የE መዘምራን አምልኮ በመምራት በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ የነበረው ወ/ዊ ሽመልስ ከእግዚአብሔር ተቀብዬዋለሁ ወዳለው አገልግሎት ለመሄድ መልቀቂያ በማስገባቱ በጉባኤ ተፀልዮለት ተሸኝቷል። የዕለቱን የዝማሬ የአምልኮ እና የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት የድምፅ ቅጂ እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡
ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!
የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ !
ባሳለፍነው ዕሀድ ( ህዳር 02 ቀን 2016 ዓ.ም ) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን "በምፅዓቱ እና በንጥቀቱ ውስጥ መኖር" በሚል ሀሳብ የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ ወንድም ዳግማዊ ካሣሁን ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ በተፈጠረው የቴክኒክ ችግር ምክንያት የአምልኮውን የድምፅ ቅጂ ባለማቅረባችን ይቅርታ እየጠየቅን የዕለቱን የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት የድምፅ ቅጂ እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡
ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!
በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ!
ትናትና ዕሁድ (ጥቅምት 25 ቀን 2016ዓ.ም) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን የቤተ ክርስቲያናችን የዓመቱ መሪ ሀሳብ በሆነው የወንጌል ተልዕኮ ላይ ያተኮረ ልዩ ፕሮግራም የነበረ ሲሆን፤ በዕለቱ ቅዱሳንን የወንጌል ማህበረተኛ በማድረግ ወንጌል ላልደረሳቸው በሀራችን ለሚገኙ የማህረሰብ ክፍሎች እንዲደርስ ለማድረግ በፀሎት እና በገንዘብ ድጋፍ የሚያደርጉበትን ሥርዓት የማስተዋወቅ ስራ ተሰርቷል፡፡ በቤተክርስቲያናችን በዕቅድ በተያዘው መሠረት በየዓመቱ የተልዕኮ ቀን የሚኖር ሲሆን የዚህ ዓመታዊ ፕሮግራም ማስጀመሪያም እንዲሆን ተደርጓል፡፡ በዚህም መሠረት በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት አብዛኞቹ ተሳታፊዎች በሀገራችን ለሚገች በወንጌል ላልተደረሱ 36 የማህበረሰብ ክፍሎች በቋሚነት ለመጸለይ ቃል ገብተዋል፤ እንዲሁም የወንጌል ማህበረተኛ በመሆን ለሚሲዮናውያን ድጋፍ የሚሆን ገንዘብ አቅማቸው እንደፈቀደ በየወሩ ለማዋጣት ስማቸውን በመስጠት ተመዝግበዋል፡፡ በዕለቱ ለዚሁ ርዕሰ ጉዳይ በሚያነሳሳ መልኩ "እግዚአብሔር ከየት እንዳነሳን እና በእጃችን የሰጠንን ኃላፊነት ማየት " በሚል ርዕስ ወንድም ቢኒያም ሰለሞን ከሆርን ሆፍ አፍሪካ ኢቫንጀሊካል ሚሽን ኢንጌጀርስ ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን አምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት እና በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ በዕለቱ ሁለት ወገኖች ወደ እግዚአብሔር መንግስት የተጨመሩ ሲሆን በዚህም ጌታን አክብረናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂዎች እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡
ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!
የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ !
ዛሬ ዕሀድ ( ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን "ሰበብ የለንም" በሚል ሀሳብ የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ መጋቢ ሮማን ሳሙኤል ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለች ሲሆን የቤተክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ ልጆችን ለጌታ በፀሎት የመስጠት ጊዜ ነበር በዚህም ጌታን አክብረናል። የዕለቱን የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂ እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡
ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!
በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ!
ትናትና ዕሁድ (ጥቅምት 11 ቀን 2016ዓ.ም) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን "እግዚአብሔር ፍቅር ነው እግዚአብሔር አምላክህን ውደድ" በሚል ርዕስ ከባለፈው የቀጠለ ሀሳብ የቤተ ክርስቲያናችን መጋቢ ምህረት ከበደ ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋዮች፤ የአምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት እንዲሁም መጋቢ ሮማን እና ቤተሰብዋ በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂዎች እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡
ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!
የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ !
ባሳለፍነው ዕሀድ ( ጥቅምት 04 ቀን 2016 ዓ.ም ) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን "በወንጌል እንኑር" በሚል ሀሳብ የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ መጋቢ ምህረት ከበደ ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ በዕለቱ ሁለት ወገኖች ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተጨምረዋል በዚህም ጌታን አክብረናል።በተፈጠረው የቴክኒክ ችግር የመዝሙር አምልኮውን ሙሉውን የድምፅ ቅጂ ባለማቅረባችን ይቅርታ እየጠየቅን የዕለቱን የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት አገልግሎት የድምፅ ቅጂ እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡
ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!
