en
Feedback
አዋሬ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ - AFG

አዋሬ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ - AFG

Open in Telegram

ይህ ቻናል የአዋሬ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤ/ክ ሲሆን የቤተ ክርስቲያንን መልዕክት የምናስተላልፍበት ነው፡፡

Show more
303
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+930 days
Posts Archive
+2
ዝማሬ በልጆች.mp36.06 MB

በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ! ትናትና ዕሁድ (ታህሳስ 21 ቀን 2016ዓ.ም) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን የጌታችንን እና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የቤተ ክርስቲያናችን የልጆች አገልግሎት ክፍል ልዩ ፕሮግራም የዘጋጀ ሲሆን በዕለቱ “ወንጌልና ተልዕኮን” ማዕከል ያደረገ በህፃናት እና በታዳጊዎች በሚጣፍጠው አንደበታቸው ዝማሬ÷ድራማ እና ኬሮግራፊ በግሩም ሁኔታ አቅርበዋል፡፡ ታዳጊ አቤኔዘር የእግዚአብሔርን ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን አምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት አገልግለውናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂዎች እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!

+1
አምልኮና ዝማሬ አገልግሎት.mp384.21 MB

የተወደዳችሁ ቅዱሳን: የጌታ ሠላምና ጸጋ ይብዛላችሁ! ባለፈው ዕሁድ (ታህሳስ 14 ቀን 2016ዓ.ም) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ መጋቢ ምህረት ከበደ ከእግዚአብሔር ቃል "ስለ ትንሳኤና ምላሻችን" በሚል ርዕስ ለሁለተኛ ሳምንት ያገለገለን ሲሆን ፤ በአ/አ በሚገኙ የሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤ/ክናት ያሉ ኢዮሳፍጥ መዘምራን ቡድን አባላት በአንድነት አምልኮ በመምራትና በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂዎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!

+1
የዝማሬ_አገልግሎት_እና_አምልኮ_ታህሳስ_7_2016_ዓ_ም_.mp353.45 MB

በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ! ባለፈው ዕሁድ (ታህሳስ 07 ቀን 2016ዓ.ም) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን " ስለ ጌታ ትንሳኤ" የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ መጋቢ ምህረት ከበደ ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት እንዲሁም የሙሉ ወንጌል የ ለ መዘምራን ቡድን በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂዎች እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!

+1
አምልኮ ህዳር 30 2016 ዓ. ም.mp336.66 MB

የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ ! ✍🏽ባሳለፍነው ዕሁድ (ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ) ማለዳ የነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን የያዕቆብ 1፡27 የእግዚአብሔርን ቃል መሰረት ያደረገ በቤተ ክርሰቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት ክፍል አስተባባሪነት የተደረገ ሲሆን በአገልግሎት ክፍሉ በ2015 ዓ.ም ስለተሰሩ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ አገልግሎቱን በተጠናከረ መንገድ ለማከናወን እና ለመደገፍ ከምዕመናን ለአገልግሎቱ የሚሆን የአልባሳትና የገንዘብ ስጦታዎች ተበርክቷል፡፡ በዕለቱም "ምን ልታደርጉ መጣችሁ?" በሚል ሀሳብ የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ ወንድም ቴዎድሮስ ዘውዱ ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ የዕለቱን የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂ እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው! ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!

+1
የመንፈስ_ቅዱስ_ኃይል_ለተልዕኮ_በመጋቢ_ዜናነህ_ማሞ_ህዳር_23_2016_ዓ_ም.mp325.10 MB

በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ! ትናትና ዕሁድ (ህዳር 23 ቀን 2016ዓ.ም) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ለተልዕኮ አስፈላጊነቱን የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ መጋቢ ዜናነህ ማሞ ከእግዚአብሔር ቃል ካካፈለ በኃላ ለመንፈስ ቅዱስ ሙላት እና ኃይል በቤተ ክርስቲያናችን የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች እና መሪዎች ፀሎት የተደረገ ሲሆን የቤተ ክርሰቲያናችን አምልኮ መሪዎች እና የፋሬስ መዘምራን አምልኮ በመምራትና በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ አምልኮ በመምራት ሲያገለግለን የነበው የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ ወንድማችን ዮናታን ወደ ውጭ ባለቤቱ ጋ ስለሚሄድ በጉባኤ በፀሎት ተሸኝቷል፡፡ በዕለቱ አንድ እህት ወደ እግዚአብሔር መንግስት የተጨመረች ሲሆን በዚህም ጌታን አክብረናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂዎች እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!

+1
ወንጌልን_ላልሰሙ_የምናደረስበት_ስልቶች_በመጋቢ_ዜናነህ_ማሞ_ህዳር_16_2016_ዓ_ም.mp361.10 MB

በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የጌታ ሠላም ይብዛላችሁ! ባሳለፍነው ዕሁድ (ህዳር 16 ቀን 2016ዓ.ም) ማለዳ በነበረው መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራማችን የቤተ ክርስቲያናችን የዓመቱ መሪ ሀሳብ ስለሆነው እና በተለየ መልኩ ተልዕኮ ተኮር በሆነ ሀሳብ ቅዱሳንን የወንጌል ማህበርተኛ በማድረግ ወንጌል ላልሰሙ ያማህረሰብ ክፍሎች በፀሎት እና በገንዘብ ለመድረስ ታላቁን ተልዕኮ ለማድረስ "ወንጌልን ላልሰሙ በዙሪያችን ላሉት የምናደርስበት ስልቶች" በሚል ሀሳብ የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ መጋቢ ዜናነህ ማሞ ከእግዚአብሔር ቃል ያገለገለ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን አምልኮ መሪዎች አምልኮ በመምራት እና በዝማሬ አገልግለውናል፡፡ በዕለቱ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ላመጡና ወደ ተለያየ ዩኒቨርስቲዎች ለተመደቡ የቤተ ክርሰቲያናችን ወጣቶች በፀሎት ሽኝ ት ተደርጎላቸዋል ፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት እና የዝማሬ አገልግሎት የድምፅ ቅጂዎች እና ምስሎች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል። በዕለቱ በተለያየ መልኩ ያገለገሉትን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!