en
Feedback
Admas

Admas

Open in Telegram

......@@በየቀኑ አስገራሚ እና የተለየያዩ(social Media) ፅሁፎች የምታገኙበት channel ነው.....@@

Show more
614
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1230 days
Posts Archive
ስምንተኛ ክፍል እያለን የሳይንስ ትምህርቶች በራሳችን ቋንቋ ይሰጡ ተባለ! እና ባዮሎጅ አስተማሪያችን ስለተክሎች ሲያስተምረን ዝንቡጤ፣ አምቡጤ ፣ ጉንቁሌ፣ ዘርጉጤ ጎጥጉጤ ምናምን ሲል ....እንዴ ይሄ ሰውየማ ድግምት ነው የሚያስተምረን አልን😀 ሰሞኑን አንዳንድ የኢኮኖሚክስ ቃላትን አማርኛ ትርጉም ሰጠን ብለው ግራ የሚያጋቡን ባለሙያዎችና ጋዜጠኞችን ሳይ ተመሳሳይ ስሜት ነው የፈጠረብኝ!ዛሬ ረፍት ነኝ የሰሞኑን ብዢታ፣ ኑሮየንም ያስረዳኛል ብየ አንዱን ዮቲዮብ ላይ ብሰማው "ለስነ ምጣኒያዊ ብያኔ አስኳለ መርህ መሠረት የሆኑት መሻትና ችረት ሲወሳሰኩ...." አለ! እ? ተወው በቃ! ዘይት ቢወደድ ይሻለኛል! እንዴ በዚህ ኑሮ ላይ...

ድህነት ያወፈራቸው (አሌክስ አብርሃም) ከቲክቶክ መስፋፋት ጋር ተያይዞ አንድ ዘግናኝ ባህል እንደሰደድ እሳት እየተስፋፋ ነው። ሰውነትን ለእይታ በማቅረብ ብር ማግኘት። ይሄ ነገር በተለይ ሴቶች ላይ እንደትክክለኛ «ቢዝነስ»እየታየ ከሃይስኩል ተማሪዎች እስከባለትዳሮችና በእድሜ የገፉ እናቶች መቀመጫቸውን ፣ጡታቸውን ለገበያ በማቅረብ ቢቻል ትንሽ ሳንቲም ካልሆነም አድናቆት የመቃረም ባህል የተለመደ ሆኗል። አስር የሴቶች ቪዲዮ ብትመለከቱ ቢያንስ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የዚህ ወረርሽኝ ሰለባ ሆነው ታገኟቸዋላችሁ! በተለይ ትልቅ መቀመጫ እንደትልቅ የሐብት ምንጭ የሚታይበት ጊዜ ላይ ነን።ምንድነው ችግራችን? የሚያጠያይቅ አይደለም ገንዘብ ነው! አንዳንዶች እውቅና ፣አድናቆት ቢሉም እውቅናውም ሆነ ዝናው ገንዘብ ለማግኘት ለሚደረገው ሩጫ መንደርደሪያ ነው። ሰው በሶስት ምክንያት ሰውነቱ ሊጨምር (ሊወፍር ) ይችላል! በአመጋገብ፣ በጤና ችግር ወይም በተፈጥሮ ! አራተኛውና ብዙሀኑ ያስተዋለው ያልመሰለኝ የውፍረት መንሰኤ ግን በአገራችን በሰፊው የሚታየው ድህነት የሚያመጣው ውፍረት ነው። ትልቅ መቀመጫንና ጡትን የገቢ ምንጭ ሊያደርግ የሚችል ብቸኛ ምክንያት ድህነት ነው። የተረጋጋ ገቢ፣ ራስን ማስከበር የሚችል ስራና ሕይዎት ያለው ሰው ወደዚህ አሳዛኝ የሰውነት ሽያጭ ያውም የስንቱን ስድብና ፀያፍ ዘለፋ ተጋፍጦ የሚገባ አይመስለኝም። ድህነት ክፉ ነው ! ሰው የሚሸጠውን ነገር ገዡ በሚፈልገው ልክ በማሳመር ይጠመዳል ። የንግድ ህግ ነው! ዛሬ ላይ ዱባይ ቱርክና ሌሎችም አገራት አገራችንን ጨምሮ ከአፍሪካ በሚጎርፉ ፀጉር አስተካይ ወንዶችና ጡትና መቀመጫ «አበልፃጊ» ሴቶች የመሞላታቸው ሚስጥር ይሄው ነው። በየጭፈራ ቤቱ የማንም ሰካራምና መሃይም ፊት እንደከበት ሰውነታቸውን እያወዛወዙ ሲገመቱ የሚያመሹት፣ በየቲክቶኩ ያውም እዩን ከሚል ልመና ጋር ሲራቆቱና እየተገላበጡ ሳንቲም ሲቃርሙ የሚገኙት ድህነት ያወፈራቸው ከሲታ ነፍሶች ናቸው። ይህን በድህነት የሚመጣ ውፍረት የበለጠ ለመረዳት ጉዳዩን ወደወንዶች እናምጣው! በየመንደሩ ድድ ማስጫ በየማሳለጫው የሚቀመጡ፣ በየድራፍት ቤቱ የሚሰየሙ ፣ ማጅራት መችዎችና መሰል ወንዶችን ሰውነት ተመልከቱ ፤ ብዙዎቹ የገደል ስባሪ የሚያካክሉና ዝሆን ከነነፍሱ የዋጡ የሚመስሉ ጠረንገሎ ናቸው! ይሄ ድህነት ወለድ ውፍረት የሚኖሩለትም የሚሞቱለትም የመጨረሻ ዓላማ በልቶ ማደር በመሆኑ የመጣ በዓዕምሮ የማይታዘዝ የስጋና የጡንቻ ክምር ነው! ድህነት ያወፈራቸው! ያገኙትን ለነገየ የማይሉ ተሻምተው በልተው ስለቀጣዩ ምግብ ወይም ሱስ የሚያስቡ፣ቤሳቤስቲን የሌላቸው። ዋናው ነጥብ የሴቶቹ መቀመጫም ይሁን የወንዶቹ ቦርጭና ጡንቻ በራሱ ችግር አይደለም ፤ ችግሩ አሁን እንደምናየው መቀመጫና ጡንቻቸው አዕምሯቸውን ተክቶ መስራቱ ላይ ነው። አሳዛኙ ነገር ዘፋኞች፣ የቲቪ ፕሮግራም አዘጋጆች፣ ተዋናያን ይህን ውድቀት መቀላቀላቸውና ከመልእክታቸው ሰውነታቸው በራሱ የተመልካች ሲሳይ እንዲሆን መታተራቸው ነው!

ራት የጋበዝካትን ልጅ ከነጋበዝካት ራት ፣ ከነአጎራረሷና ከነመሽቆጥቆጧ "በፍቅር ስም" አስር ፎቶ አንስተህ መለጠፍ ብዙም ዘመናዊነት አይመስለኝም! እንደውም ወደባሪያ ንግድ ይጠጋል! ደግሞ ፎቶ ባይለጠፍም ከእራት በኋላ በጨዋነት ወደቤቷ እንደምትሸኛት ብዙሀኑ ያውቃል! ካልሸኘሀትም አክስቷ ቤት ማደሯን እናውቃለን😀 በዚህ ሰዓት እንኳን የማይመለከተን እኛ ፣ አንዳንድ ወላጆች ራሳቸው ኑሮ የሚሉት ጣጣ አስመርሯቸዋል ....ልጃቸው አክስቷ ቤት ብታድር "በሰላም ደረሰች ወይ" ብለው አይደውሉም፤ አክስት ባይኖራትም ጭምር! እንደውም እነሱ ራሳቸው አክስታቸው ቤት ሂደው ቢኖሩ ደስታቸው ነው! ይሄ ማለት ግን የልጃቸው ዋጋ በእራት ሲተመን ደስ ይላቸዋል ማለት አይደለም! ምን ዋጋ አለው አንተ ይሄን የምታነበው ቁርስ ላይ ይሆናል! *ዋናው ነጥብ፦ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ፍቅር የሚመስል መታበይ አለ! ብዙም አደባባይ ላይ አትስቀሉት!

photo content

አፍንጫ የውበት ውሃ ልክ !! የፈለጋችሁትን ሰው ፊት ተመልከቱ "ቆንጆ" ከመሰሏችሁ የውበታቸው ሚስጥር 90 በመቶ አፍንጫቸው ነው! አፍንጫ የፊትን "ፕሮፖርሽን" ይጠብቃል፣ ፈገግታን የሚያሳምረው ጥርስ ይመስላችሁ ነበር አይደል? እኔም ይመስለኝ ነበር፤ ግን ተሳስተናል፤ አፍንጫ ነው! እየሳቀ የተቆጣ ፣እየተቆጣ የሳቀ የሚመስላችሁ ሰው ከገጠማችሁ አፍንጫውን ተመልከቱ! ጎራዳ ይሁን ስንደዶ ችግር የለውም፤ ብቻ አፍንጫ የተስተካከለ ከሆነ የፊት ውበት ውሃ ልክ ነው! "ቆንጆኮነች ግን ፊቷ ላይ የሆነ ነገር"....ብላችሁ ውበቷ ትንሽ ግራ ያጋባቻችሁ ሴት ካለች አፍንጫዋን አጥኑ፤ መልሱን ታገኙታላችሁ! ዓይን ፣ ጥርስ፣ ከንፈር ፣ እንደጉድ አምሮ አፍንጫ ላይ ሳት ካለ ውበት ውሃ በላው! ደራሲዎች ስለአፍንጫ ለምን ብዙ እንዳልፃፉልን አላውቅም! ስለአፍንጫ የተገጠመ ግጥምስ ይኖር ይሆን? ብቻ አፍንጫ የፊታችን ውበት ማዕከል ነው! ቀላል ግኝት እንዳይመስላችሁ .... ለምሳሌ ኮቪድ የተከሰተ ሰሞን ማስክ ብዙዎችን ሲያሳምር ብዙዎችን ደግሞ አጥፍቷቸው ነበር። ለምን? ማስኩ የውበትን መሰረታዊ ነጥብ ሸፍኖት ነበራ!! የሆነ ሆኖ ይህ "ጥልቅ መረዳት" በደንብ የሚገባችሁ የምታውቋት ቆንጆ ልጅ አፍንጫዋ ላይ በንብ ተነድፋ ስታይዋት ነው! በግጥም እንዝጋው! ኦ አፍንጫ የውበት መውረጃና መውጫ ሐምሌ 10/2016 አሌክስ አብርሃም!

ልጅቱን እቤቷ በር አድርሷት ሲመለስ ፤ የልጅቱ አባት ራሳቸው ሰፈር ውስጥ ጠብቀው መኪናውን አስቆሙትና "ስማ! ሽማግሌ ልከህ ይችን ልጅ አትወስዳትም ወይ? እስከመቸ ነው መንገድ ለመንገድ እየተጓተታችሁ በዕድሜ የምትጫዎቱት? ወይ ካልሆነልህ እቅጩን ንገረንና ሌላ 'የሚጦረን' ባል እንዳራት" ይታያችሁ በተደጋጋሚ የሚያደርሳት የራይድ ደንበኛዋ ብቻ ነው! ይሄ ኑሮ ግን ነገሮችን በጣም እያምታታቸው ነው😀

ፍቅራችን ራሱ የጨበጣ ውጊያ! "እከሌም እከሊትን አወቃት ወንድ ልጅም ወለደች " ይላል መፅሐፉ ነገሩን በፍፁም ጨዋ ቃል ሲገልፀው! የእኛ አገር አገላለፅ ግን አወቃት ሳይሆን ወቃት አይነት ደመ ቁጡ ሞገደኛ ስሜት አለው! እንደሰውም እንደህዝብም ለምንወደው ነገር እንዴት ቆንጆ ቃል መምረጥ አቃተን? ይገርማችኋል ስለ ወንድና ሴት ግንኙነት ሲወራ የምንጠቀመው ቃል ዘግናኝ ከመሆኑ የተነሳ " ከዚህ ሁሉ ቢቀርብኝስ" የሚያስብል ነው! ግን ማንም ይቅርብኝ ብሎ አያውቅም! ስለሆነ አውዳሚ ጦርነት የምናወራኮነው የሚመስለው! ሴቶቹ ላይማ ገና ሲወለዱ ይጀምራል ! "እንዳትባልግ እንትኗን ገርዟት " አስባችሁታል ወንዱ እንዳይባልግ እንትኑን አጠር አድርጉለት ቢባል? ሲያጭበረብሩ ደግሞ "ወንድም ይገረዛልኮ" ይሉናል! ... ወንድ ሲመረቅ ራሱ "እንደፍየል ቀንድ ያቁምልህ ነው የሚሉት" አደግ ሲሉ አጎጠጎጠች ፣(ብዙ ሴቶች እጅ በደረት የመጀመሪያ ሰልፍ ድፌንሳቸው የሚሆነው ለዛ ነው፣ ከሰው አፍ) አጎነቆለች፣ ቆላት ፣ አንቀለቀላት፣ የሚያደርጋትን አሳጣት ሻፈ*ች...አለጠለጠች ! ኧረ ምኑን ሰጠሽ በዜማ ሁሉ.... ወንድ ጋር ገና ሲቀራረቡ ደግሞ ይቀጥላል... ገለፈጠች ፣ተዳራች፣ ተላፋች፣ ተጓተተች ...እግሯን አነሳች ..አሽኳለለች፣ እሽካነናት ፣ እዮኝ እዮኝ አለች ፣ በሽታዋን ይዛ እንዳትመጣ ፤ ዲቃላዋን እንዳትታቀፍ ፣ አምሯታል፣ እሳት አድርጓታል ፣ ተሸራ**ች....በስርዓት ብታገባ ወሲብ ፣ ግብረ ስጋ፣ ተራክቦ፣ ሩካቤ ስጋ ፣ አንሶላ መጋፈፍ፣ (መጋፈፍን ምን አመጣው? አንች ልበሽ አንተ ልበስ እያለ) መርፌና ክር! ሳታገባ ከሆነ መዳራት፣ ማመንዘር፣ የባለጌ ስራ፣ ከአልጋ መውደቅ ዘመነኛው አገላለፅማ ተውት የመጨረሻ ቀፋፊ ነው! የባሰበት ዘግናኝ! ከአባቶቹም የከፋ ትውልድ ተነስቷል! ከዛስ ክብረ ንፅህናዋን ገሰሰው፣(የሆነ ለመንገድ ስራ በደማሚት የሚፈርስ ተራራ ነው የሚታየኝ) ድንግልናዋን ወሰደው፣ (መቀበል መፈቃቀድ አይደለም የሆነ ነጥቆ መውሰድ) ብር አምባሯን ሰበረው እንደውም ሰበረለዎ ነው የሚባለው (የጠላትን አከርካሪውን ሰበርነው እንደሚሉት) በጧት ተነስተው አሳየው የደሙን ሻሽ... ይሄ ሁሉ ረብሻ የሆነ ቃል ሳያቆመን 130 ሚሊየን ሞላን! የሴቶቹ አቻቻል የወንዱ ጋሬጣ መሆን ምነው ለልማት እንዲህ በሆንን! ምናልባት "ልማቱን እንግሰሰው" ቢባል ይሄን አይበገሬነት ለልማት ማዋል ይቻል ይሆን? Alex abrham

ኮቪድ የገባ ሰሞን አንዲት ጋዜጠኛ የጦር መሳሪያ ሊሸምቱ የሆነ ስቶር በር ላይ የተሰለፉ ሰዎችን እየጠየቀች ነው! አንዱን ጎልማሳ ጠየቀችው! "መሳሪያ የምትገዛው ለምንድነው? " "ሁሉም ነገር ከተዘጋጋ የተራቡ ሰዎች ቤት ለቤት ዘረፋ ሊጀምሩ ይችላሉ! ቤተሰቤን መከላከል አለብኝ!" የገረመኝ ይሄ አይደለም! ሌላኛው ተጠያቂ ነበር! "ሐብታሞች ያከማቹትን ሲበሉ ቤተሰቦቸም ሆነ ራሴ በእርሃብ ስንሞት ዝም ብየ ላይ አልችልም" አለ! መሳሪያ የምገዛው ከተራብኩ ለመዝረፍ ነው ማለት ነው! ይታያችሁ ሟችና ገዳይ ከአንድ ሱቅ ሽጉጥ ሊገዙ ተሰልፈው ነበር ፤ ያውም "በሀያሏ" አሜሪካ! ርሃብ የመጨረሻው ማህበራዊ ቀውስ ነው! ርሃብ ባለበት ህግ ፣ ሰብዓዊነት ፣ መተዛዘን ዋጋ ያጣል! ሁልጊዜ ሰዎች ሲራቡ ወደቤተክርስቲያን ብቻ ላይሄዱ ይችላሉ! ወደላይ ሲያዮ ውለው መና ካልወረደ ወደጎን ማየት ይጀምራሉ!

photo content

ከሚስቱ ውጪ ሲወሰልት የነበረው ባል አፕል ኩባንያ ለትዳሬ መፍረስ ምክንያት ሆኗል ሲል ከሰሰ😁 ግለሰቡ ከሌሎች ሴቶች ጋር የተጻጻፋቸውን መልዕክቶች ሚስቱ እንድታገኛቸው ኩባንያው ተባብሯል ሲል ከሷል አፕል ሚስጥሬን ባለመጠበቁ ምክንያት የ20 ዓመት ትደሬ ፈርሷል በሚል ኩባንያው 5 ሚሊዮን ዶላር ካሳ እንዲከፍለው ጠይቋል(አል አይን) እዚጋ ደሞ ሌላ ትኩሳት🥵

አንድ የስራ ባልደረባችን እያጨበጨበ አስቸገረን! እንደሱ አይነት አጨብጫቢ የትም አልተፈጠረም! አለቃወቻችን ሲያስነጥሱ ሁሉ እጁ ያመልጠዋል! እውነቴን ነው ፤ ሳቅ ያመልጠናል እንደሚባለው እሱ ራሱ "እጀ ያመልጠኛል" ይላል! በቃ ስብሰባ ላይ "ደመዎዛችሁ ተቀንሷል" ቢባል እንኳን ያጨበጭባል! እሱ ካጨበጨበ ደግሞ "እንዳንጠቆር" እኛም እናጨበጭባለን! አንድ ቀን ግን ለወሳኝ ጉዳይ (ቅዳሜ ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ በደመወዛችን እንድንሰራ ለማሳመን) አለቃችን ሰበሰበን፣ እኛ ደግሞ ጉዳዮን ቀድመን ስለሰማን ለመቃወም ተዘጋጅተናል! ያንን አጨብጫቢ ደጋግመን አስጠነቀቅነው "እንዲች ብለህ አለቃችን ሲናገር ታጨበጭብና የመጨረሻችን ነው የሚሆነው ዋ!" "አይ እኔ አያስችለኝም! ጭብጨባ አስለምጃቸው ቀና እያሉ ሲያዮኝ 'ሸም' ይይዘኛል፤ ወይ አንድኛችሁ አጠገቤ ተቀመጡና ላጨበጭብ ስል እጀን ያዙኝ" አለ! ጥሩ ሀሳብ ብለን የሆነ ብረት ገፊ ሰራተኛ አጠገቡ ተቀምጦ ሊያጨበጭብ ሲል እጁን እንዲይዘው አደረግን ! ሀላፊያችን እንደለመደው በአፉ ሊደልለን ነገር አበዛ፣ አዘበዘበ፣ ተረት ጨመረ፣ ምሳሌ መሰለ ! ጭብጨባ ለምዶ በየመሀሉ ለጭብጨባ ፋታ ቢሰጠንም ጭጭ! የሆነ ቦታ ላይ በሞራል ተናግሮ ሲጨርስ ግን ያ አጨብጫቢ ሊያጨበጭብ ሞክሮ ለጥበቃ ያስቀመጥነው ጓድ እጁን እንቅ አድርጎ ይዞታል ለካ! እና የጭብጨባ ሱሰኛው ምን አደረገ? "እልልልልልልልልልልል" ብሎ ጭብጨባውን በእልልታ ተካው! ወንድ ልጅ እንደዛ እልል ሲል አይቸ አላውቅም! ጭብጨባ ከባድ ሱስ ነው!

እንዴት በቀስታ ወደዞምቢነት ተቀየርን? (አሌክስ አብርሃም) ፌስቡክ መጠቀም ከመጀመሬ በፊት ባሉት 10 ዓመታት ሁለት ሰዎች ጋር (አንዱ መልስ ሊያጭበረብረኝ የሞከረ የታክሲ ረዳት፣ ሌላኛው የቅርብ ቤተሰብ የሆነች ልጅ ያስቸገረ ጎረምሳ ጋር) ቀላል ፀብ ንጭንጭ ነገር ተጣልቻለሁ! ይሄን ነው የማስታውሰው! ፌስቡክ መጠቀም ከጀምርኩ በኋላ ግን 956,5568, 6568,656 5686,568,6868,1015555, 55656, 58556 8574,0000 (ብዙ እንደማለት) እንኳን ስማቸውን ፆታቸውን እንኳን የማላውቃቸው ሰዎች ጋር ተጣልቻለሁ! ተዝቶብኛል ፣ተፎክሮብኛል፣ የስድብ የእርግማን ቡፌ ተዘጋጅቶልኛል፣ እኔም ባልሳደብም ሰው ነኝና ልቤ ሌሎችን መጥላቱ አልቀረም! አስባችሁታል ግን? ይኑሩ ይሙቱ በህይዎታችሁ ምንም ለውጥ የማያመጡ ከነመፈጠራቸው የማታውቋቸው ሰዎች ጋር በመጣላት በመበሳጨት በመመላለስ በማስረዳት በማስተባበል ያሳለፋችሁት ጊዜ?! እስኪ ተመልሳችሁ አስታውሱ ከፌስቡክ በፊትና በኋላ ምን ያህል ሰዎች ጋር ተደባበራችሁ? ተሰዳደባችሁ? ብሎክ ተደራረጋችሁ? ብቻችሁን ተበሳጫችሁ ? እንቅልፍ አጣችሁ? ልባችሁ ተሰበረ? ሰው ጠላችሁ? በህይዎታችሁ ሰምታችሁ የማታውቁትን ፀያፍ ስድብ ሰማችሁ? ሁሉስ ምን ጠቀማችሁ? መራርኮነው ያደረገን! በጥላቻ በመናናቅ ነው የሞላን ፣ ወደዞምቢነት ነው በቀስታ የቀየረን ያገኘነውን መንከስ! ስንት ለስላሳ ትሁት ልጆች እያየናቸው ወደአስፈሪ የጥላቻ ማሽንነት ተቀየሩ? የተባሉትን ለማስተባበል ጋጠወጥ ሆኑ? ሲገፉ ላለመውደቅ የስንቱን ልብስና ስም ይዘው ወደቁ? ስንት ንፁሐን ተጨፈጨፉ ተሰደዱ ? ምን አተረፍን? የሚያሳዝነው አንዳንዶቹ ዛሬ በህይዎት የሉም የቀረነውም ምንም አንማርም! ትንሽም ቢሆን ፍቅር እንዴት አሪፍ ነገር ነው!

. ጂም ተስተካክሎ ለመታየት እንጂ አስተካክሎ ለማየት አይጠቅምም። (የመነፅር ቤት ጥቅስ)
. ጂም ተስተካክሎ ለመታየት እንጂ አስተካክሎ ለማየት አይጠቅምም። (የመነፅር ቤት ጥቅስ)

photo content

አሜሪካ በጥንቆላ ላይ ጥላው የነበረውን እገዳ አነሳች🥶 ሀገሪቱ እገዳውን ያነሳችው የጥንቆላ ተጠቃሚ ሰዎች በመብዛታቸው ነው ተብሏል ጥንቆላ በአሜሪካ ለ100 ሺህ ገደማ ዜጎች ስራ እድል ሲፈጥር 2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢም አስገኝቷል(አልዐይን) ወገን ተደፍረናል😂

አገር ምድሩ "ራስን መፈለግ " በሚል ስብከት ተሞልቷል! ሁሉም እየተነሳ "እራስን መፈለግ...ራስን ፈልጎ ማግኘት " ይላል! ቆይ ራሳችሁን ብታገኙት ምን ልታደርጉት ነው?😀 ምናልባትም አሁን ካላችሁበት ማንነት የባሰ ሁኔታም ላይ ልታገኙት ትችሉ ይሆናልኮ! የሆነ ጊዜ ከብዙ ዓመት በፊት በህፃንነቱ የጠፋ ልጃቸውን ተገኘ ብለዋቸው ኢቢ ኤስ ላይ የቀረቡት ሴትዮ ትዝ አሏችሁ? ገና ሲያገኙት "ውጭ አገር ነበርክ?" "አይ እዚሁ እህል በረንዳ ምናምን..." "እም...ለነገሩ ጆሮህ የጠፋውን ልጃችንን አይመስልም"😀

ቅዳሜ ለልማት ፈርሳለች! (አሌክስ አብርሃም) አንዳንዴ ቤትና አጥር ብቻ ሳይሆን ቀናትም "ለልማት" ይፈርሳሉ ይሆን? በድሮሮሮሮሮሮሮ ጊዜ (ከሰባት ዓመት በፊት) ቅዳሜ የሁሉም ሰው ሰርግ ትመስለኝ ነበር፣ ቅዳሜ በየሳምንቱ የምትፈካ አደይ ትመስለኝ ነበር፣ ቅዳሜ ከቡና የተሰራ ሽቶ የተነፋባት አበባ ጣል ጣል ያለበት የእፎይታ ቀሚስ የለበሰች ፣ አምስት መንቻካና አንድ ቀውላላ ወንድሞች ያሏት ውብ ሴት ትመስለኝ ነበር! ሰኞ ማክሰኞ የሚባሉ ....የቀን መንቻኮች! ቅዳሜን እንደበዓል የማከብራት አርብ ከስራ ስወጣ ጀምሮ ነበር! አርብ ሁለት ጓደኞቸ ጋር እንገናኝና ለገሀር አካባቢ ሁለተኛ ፎቅ ላይ ያለ ቤት አሪፍ ፒዛ እየበላን ወሬ እንሰልቃለን! ፒያሳ ሄደን አራዳ ህንፃ ላይ የማንኪራን ቡና እየጠጣን ወጋችን ይቀጥላል! ማንኪራ ስንሄድ ሁለት ወይም ሶስት ወይም አራት ወይም ብዙ ወዳጆቻችን ይቀላቀሉናል፤ የሚበዛው ወሪያችን ስለስነፅሁፍ ነበር። ክርክሩ ንትርኩ ሳቁ...እንደፈለግን አምሽተን ወደየቤታችን ወይም ወደአንድኛችን ቤት እንሄዳለን! ብዙ ጊዜ ወደእኔ ቤት! ቅዳሜ ረፈድ ሲል አንድ ስጋ ቤት ነበር ግርግሩ የሚገርመኝ! እንደገና እንታደማለን ! ጥሬ ስጋ ስለማልወድ ለእኔ ትንሽ ጥብስ ....ከዛ ወደብሄራዊ! ጋዜጣው ፣መፅሔቱ ፣ መፅሐፉ ...እነዛ ጠባብ ባለአንድ ፎቅ ቡና መሸጫዎች ...የስኒዎቹ ኳኳታ የቡናው ጠረን ... "የት ናችሁ ?" የሚሉ እህቶችም አሉ! እየተፍለቀቁ የሚቀላቀሉን! ኪሳችን ከኑሯችን አይጣላም ፤ የማናካልለው ቦታ አልነበረም! አራት ኪሎ ፣ መገናኛ፣ ቦሌ ... አንዳንዴ ከተማውን ጣጥለነው ወጥተን ሱሉልታ ሜዳው ላይ እንገኛለን ...ሌላ ሌላ ገጠር ነበር ፤እረኞቹ ፈገግ እያሉ ባዶ የሀይላንድ ኮዳ የሚለምኑን! ለምን ማሳችን ላይ ቆማችሁ የማይሉ..... ማናችሁ የማይሉ .... ዛሬ ላይ ሁለቱም ጓደኞቸ አግብተው ወልደው ቅዳሜ ሙሉ ቀን ይሰራሉ! አንዱ ምናለኝ? "ባክህ የድሮዋ ቅዳሜ ለልማት ፈርሳለች ሁሉም ቀን ሰኞ ሁኖብኛል!" ልማቱ መኖር መቻል ነው! ለመኖር ነው ከኑሮ ላይ ጠዓም የቀነስነው? አሁን ያለውን የኑሮ ጫና ሳስበው ስንት የአብሮነታችን መድረክ የነበሩ ቀናት ፈራርሰው ስንቶቻችን ባተሌ ሁነን ይሆን እላለሁ! ለፈረሱብን ቀናትስ ህይዎት ምን ካሳ ሰጠችን? ቢሆንም ቅዳሜ ውብ ናት! እንደዘር ቅንጣት በየትውልዱ የጊዜ ሁዳድ ላይ እንደአዲስ የምትፀድቅ የሳምንት አደይ!

እንደ ቫዮሊን ነበርኮ የሚያጫውቱት! የተበላ ዘመን ላይ ደርሰን ዛሬ ስጋ በጥፍር መቁረጫ ነው የምንቆርጠው😀
እንደ ቫዮሊን ነበርኮ የሚያጫውቱት! የተበላ ዘመን ላይ ደርሰን ዛሬ ስጋ በጥፍር መቁረጫ ነው የምንቆርጠው😀

ብዙሀኑ ከታዋቂ ሰዎች ጋር የተነሳው ፎቶ አለው፤ መዝረጥ አድርጎ ለመለጠፍ እስኪሞቱለት እየጠበቀ ነው😀 ቀዳሚውን አንድየ ነው የሚያውቀው በቁም ተደናነቁ ባካችሁ!

photo content