en
Feedback
Apostolic generation evangelize

Apostolic generation evangelize

Open in Telegram

Mark16÷15 And he said unto them, Go ye into all the world, and preach the Gospel to every creature. ማር 16÷15 እንዲህም አላቸው።ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱና ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። for any comment @ApoGenEvaBot @rob_apo

Show more
968
Subscribers
No data24 hours
+67 days
+3230 days
Posts Archive
🎤 HOLETA MASS CHOIR🎤 🎼telegram Group 🎼 🎸 የሆለታ መዘምራን ቴሌግራም ግሩፕ🎸 🎧Garee telegiram Faarfattoota Holotaa 👉 https://t.me/h
+1
🎤 HOLETA MASS CHOIR🎤 🎼telegram Group 🎼 🎸 የሆለታ መዘምራን ቴሌግራም ግሩፕ🎸 🎧Garee telegiram Faarfattoota Holotaa 👉 https://t.me/holetaapostolicchurch1 👉https://t.me/holetaapostolicchurch1

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን በጎሮ ዶላ ወረዳ በድርቅ ምክኒያት ለተጎዱ መህበረሰብ የእህል እርዳታ አደረገች። በእርዳታ ርክክብ ስነሥርዓት ላይም የቤተክርትያንቷ ምክትል አስተዳዳር ቢሾፕ ኢሳያስ አሻ እንደተናገሩት የእርዳታው ምንጭ ከምዕመናን የተሰበሰበ ገንዘብ ነው። በተጨማሪም፣ የድርቅ መፍትሄው ወደ እግዝአብሔር ማልቀስ እና ንስሃ መግባት ብቻ መሆኑን ጠቅሰው እስከዚያ ግን የተቸገሩትን እንድንረዳ የእግዝአብሔር ቃል ስለሚያዘን ይህንን ድጋፍ አድርገናል ያሉት የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ሰባኪ ወንጌላዊ ደረጄ ከበዴ ናቸው። ቢሾፕ አዲሱ በሪሶ እንዳሉት ቤተክርስትያንቷ ለተቸገሩ ማህበረሰብ ድጋፍ ስታደርግ ይህ የመጀመርያዋ ሳይሆን ከዝህም በፊት ስታደርግ ቆይታለች። ህዝቡም በተደረገላቸው ድጋፍ ተደስተው ድጋፍ ያደረገላቸውን አካል አመስግኗል።

የወደደኝ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በታሪኬ/በሰማይ በምድር እንዳንተ ያለ አላውቅም ጌታ

የመስቀሉ ጸጋ አንተ ምስጋናዬ ነህ 4x የሱስ ምስጋናዬ ነህ አንተ ምስጋናዬ ነህ ጌታ ምስጋናዬ ነህ አንተ ራስህ ምስጋናዬ ነህ እያሰብኩኝ ብቻ የማይቀዘቅዘውን የመስቀሉን ፍቅር እንደማያቋርጥ ምንጭ ይፈልቃል ከውስጤ ገና ብዙ መዝሙር በጨለማዬ ላይ ብርሃን ያበራ የፅድቅ ፀሐይ የደህንነቴ ምንጭ ሁሉ የፈለቀብህ ካህኔም ጌታዬ አንተ ብቻ ነህ ምክንያቴ ለምስጋና እንዲከፈት አንደበቴ 1) አሰላስላለሁ የመስቀሉን ፀጋ ባልተገባኝ መጠን ብዙ እንደሰጠኸኝ/ብዙ እንደሆንክልኝ/4* እኔ ጤና እንድሆን ደዌዮን መሸከምህን እኔ እንዳምርልህ ደም ግባት ማጣትህን እኔ እንድወደድ መጠላት መገፋትህን እኔ እንድከብር የተናቅክ መሆንህን እኔ ቀና እንድል አንገትህን መድፋትህን እኔን ለማፅደቅ ኃጢአቴን መሸከምህን የተወጋውን ጎንህን የፈሰሰውን ደምህን የጠጣኸውን መራራ ያሳለፍከውን መከራ አልረሳም ይኖራል በልቤ ታትሞ በአይኖቼ ፊት በጉልህ ተስሎ የነፍሴ ብርሃን ነህ እያት ስታበራ በነፍስህ ድካም ጸድቃለችና አሃሃሃሃ ሃሌሉያ ከዘመርኩኝ አይቀር ለዚህ ፍቅር ዘምራለሁ ከአመለኩኝ አይቀር ይህን ፍቅር ብቻ አመልካለው ከተገረምኩ አይቀር በዚህ ፍቅር እገረማለው ካወራሁኝ አይቀር ይህን ፍቅር ብቻ አወራለው የወደደኝ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በታሪኬ/በሰማይ በምድር እንዳንተ ያለ አላውቅም ጌታ

ግንቦት 3/2 ========= የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ማህበር በጉጂ ክልል ጎሮኦ ዶላ ወረዳ በረሃብ ለተጎዱ ማህበረሰቦች 670 ኩንታል እህል ለገሰ። ======================= በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የወረዳውን አመራር ወክለው የተገኙት የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ምክትል ሊቀ መንበር ቢሾፕ ኢሳይያስ አሻ እንደተናገሩት የእህል ዕርዳታው የተሰበሰበው ከሕብረተሰቡ ተከታዮች የበጀት ምንጭ 670 ኩንታል እህል በድምሩ በማኅበሩ የተበረከተ ነው። ከ2.6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ======================= እርዳታውን ያመጡት የቡድኑ አባልና የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ማኅበር የወንጌል ሰባኪ የሆኑት ቄስ ዳራጅ ከበደ እንደገለፁት አጠቃላይ የረሃብ ችግር መፍትሔው የሚገኘው ወደ እግዚአብሔር በማልቀስ/በጸሎት/ በመጸለይ ነው ቤተ ክርስቲያናችንም ከጎኗ ተቀምጣለች። የእግዚአብሄር ጸሎት ከወልድ አባላት በተሰበሰበው ገንዘብ የተቸገረውን ህዝብ ከመጎበኘት ይልቅ የምንችለውን መደገፍ አለብን በሚል ሀሳብ ሰብሉን ደገፉ። ======= የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ጳጳስ አዲሱ ባሪሶ ለኦቢኤን ሚዲያ እንደገለፁት ማህበሩ ከዚህ ቀደም በአማራ እና አፋር ክልሎች በተቀሰቀሰው ጦርነት ለተሰቃዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በድምሩ 6 ሚሊዮን ቀርሺይ ድጋፍ አድርጓል። የጎሮኦ ዶላ ወረዳ ነዋሪዎች እህሉን ገዝተው በማጓጓዝ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ======= በስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የጎሮኦ ዶላ አውራጃ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ሚስተር ጋዳኣ ሳአትቶ የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ማህበር ለማህበረሰቡ ላሳዩት ጉጉት አመስግነው ይህንንም በዲስትሪክቱ አስተዳደር ኢትዮጵያ /ሃዋሪያዊቲ/ ስም አመስግነዋል። የችግር ጊዜ እስኪያልፍ ድረስ በተቻለ መጠን ለህብረተሰቡ ብዙ ድጋፍ። =============== በስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የዲስትሪክቱ የጎኖፋ ልገሳ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሳፊያ ሁሴን የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ማኅበር ከአባላቶቻቸው ገንዘብ በመሰብሰቡ አመስግነው ህዝቡ ሁል ጊዜ የወቅቱን ዝናብና በቂ ውሃ በመጠቀም የሰነፍ ባህሉን ሊለውጥ ይገባል ብለዋል። ራሳቸውን ለመርዳት ጠንክረህ መስራት እና መስራት። ======================= ህዝቡ ባደረገው ድጋፍ በጣም ተደስተው ድጋፍ ላደረጋቸው አካል አመስግኗል። =========

የማለዳ ትምህርት /223/ ቀን 02/09/2015 ዓ/ም 42ኛ ሳምንት ☞ ርቡዕ ርዕስ፦ #ትሔዳለህ_ወይስ_ትሸኛለህ?? ውድ ቅዱሳን! እንደ ምን አደራችሁ? ዛሬም የማለዳ ትምህርት #ትሔዳለህ_ወይስ_ትሸኛለህ በሚል ርዕስ አቀርባለሁ። በምድር ላይ እስካለን ድረስ ሁለት ነገሮች በኑሮአችን ላይ እየተከሰተ ይኖራል። አንድ ሰው ከሚኖርበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ስሄድ ቤተሰቡም ሆነ ጓደኞቹ እስከተወሰነ ቦታ ድረስ ያደርሱና ይመለሳሉ፤ ወይም የመክና መናኸሪያ እስካለበትም ይሁን ብቻ እስከተወሰነ ቦታ በእጅ የያዘውን ሻንጣውም ይሁን ዕቃውን ተሸክመው ያደርሱና በሠላም ግባ ብሎ ይመለሳሉ። ይህንን ድርግት በተለምዶ ቋንቋ #ሸኚና_ሐጂ ይባላል። 💃 የሚሔድ ሰው #ሐጂ ይባላል፤ 🚶‍♀የሚመለስ/ የሚቀር #ሰው ሸኚ ይባላል። በዛውም ልክ ለሰማይ ጉዞም ሐጂና ሸኚ አለ ማለት ነው። ታድያ ከእኛ ውስጥ ሸኚ ማነው፤ሐጂ ማነው? ዛሬ ብዙ ሰዎች በቤተክርስቲያን ውስጥ በአንድነት እያመለክን፣ እየዘመርን፣ እየጾምን.... እንገኛለን፤ ነገር ግን የኢየሱስ መምጫ/ ሙሽራው/ ስመጣ አንዳንዶቹ ይሄዳሉ አንዳንዶቹ ግን ሸኚዎች ሆኖ ይቀራሉ። አንተ ግን ሊትሔድ ነው ወይስ ሊትሸኚ ነው? በዚህ ዘመን በመሠዊያ የሚሰብክ፣ የሚመስክር ሰው ሁሉ የኢየሱስ መምጫ ቀርቧልና ተዘጋጁ፣ ሊንሔድ ነው፣ ሸኚዎች ሆነን እንዳንቀር፣ ሁላችንም እንድንሔድ እያለ ይሰብካል፤ ነገር ግን እኛስ ስንቶቻችን ተዘጋጅተናል? ✅ በሙሴ ዘመን እስራኤል ከግብጽ ስወጡ ከግማሽ ሚልዮን በላይ (600,000) የሆኑ ሰዎች ከግብፅ ወጥተው ነበሩ። በአርባ ዓመት ጉዞአቸው ውስጥ በመንገድ ላይ ተሰናክለው ቀሩ። ከእነርሱ ውስጥ ሁሉም ሰዎች ሸኚዎች ሆኑ፣ ሁለት ሰዎች ማለትም ኢያሱና ካሌብ ብቻ ሐጂ ሆኑ። ታድያ ያኔ ከ600,000 ሰዎች ውስጥ ሁለት ሰው ብቻ ከንዓን ከገቡ ዛሬ ከእኛ ስንት ሰው ሊገባ ይሁን? ሌላ ምሳሌ ደግሞ አሁን በዘመናችን ላይ በሜዳ ላይ ኳስ የሚጫወቱ ሰወች 12 ተጫዋቾች ብቻ ናቸው። ነገር ግን እነርሱን የሚደገፉ ግን ኳስ ሜዳ የማይገቡ በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰወች ናቸው። እንደዛውም እኛ ደጋፊዎች ሊንሆን ይሁን ወይስ ሜዳ የሚንገባ ነን? እስክ እራሳችንን እንመርምር። ይህንን ጽሁፍ የሚታነቡ ሁላችሁም አንድ ጸሎት ብትጸልዩ መልካም ይሆናል። "ጌታ ሆይ፦ እኔ ሊሔድ ነው ወይስ ሊሸኚ ነው? ከሔዱት ጋር አድርገኝ እንጅ ከሸኙት ጋር አታደርገኝ" እንበል። ✝ (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 9) 24፤ በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ። 25፤ የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን። 26፤ ስለዚህ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም፥ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፤ 27፤ ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ። የዚህን አለም ዋንጫ የሚወስዱ ተጫዋቾችና ሯጮች ምን ያህል እንደሚደክሙ ታውቃላችሁ፤ እኛ ግንየሰማዩን አክሊል ለመቀበል ምን ያህል መሮጥና መታገል መድከም እንዳለብን መግለጽ አልችልምና ለእናንተ ልተው። እናገኛለን ብለን ካልሮጥን አናገኝም ብለን ተቀምጠናል ማለት ነው። ለመሔድና ለመሸኘት የዛሬው ቀን ወሳኝ ነው። ዛሬ ከእግዚአብሔር ትዕዛዝና አላማ ወጥተን በራሳችን ፍላጎት የሚንውል ከሆነ በቃ ሸኚወች ነን፤ አንሔድም ብለን ወስነናል ማለት ነው። ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር ሀሳብ ለመዋል ወስነን ከሆነ እኔ እሔዳለሁ እያልን ነው ማለት ነው። ውድ ቅዱሳን! እችን ት/ት ለማቅረብ እንደፈለኩት አድርጌ አላቀረብኩም። ምክንያቱም ርዕሱን ስያስብ ብቻ በልቤ ውስጥ ትርታ በዛ፣ ሌላ ስሜት ተሰማኝ፣ ሀሳብ ተመታታብኝ.... እኔ ማን ነኝ የትኛው ወገን ነኝ በሚል ሀሳብ ውስጥ ገባሁ፤ ብሆንም ከእኔ ይልቅ ብዙ ፀጋ ስላላችሁ በፀጋችሁ ሰፋ አድርጋችሁ አስቡ። በማቴ 25፥1 ላይ ሙሽራ ለመቀበል የተዘጋጁ አስር ቆንጃጅቶች በመጨረሻቸው ምን እንደሆኑ ታውቃላችሁ። ዛሬ ሙሽራ ስመጣ እኛ ዬት ነን? ምን እየሠራን እየለን ይመጣ ይሁን? በአንድ ቤት የብረው ያገለግሉ፤ የበሉ፣ የጠጡ፣ አብረው የተኙ ሙሽሮች ሙሽራ ስመጣ ለሁለት ወገን ተከፈሉ። አንደኛ ወገን ልባሞች፣ ሁለተኛው ሰነፎች ተባሉ። ✅ ልባሞች ሐጂ ሆኑ፤ ❎ ሰነፎች ሸኚ ሆኑ። እኛስ ዛሬ የትኛው ወገን ነን? ከልባሞች ወይስ ከሰነፎች? አለም ይዞን ወደ ገሀነም ሊወስደን ነን ወይስ እየሱስ ይዞን ወደ ገነት ሊወስደን ነን? ✅ ኢየሱስ ስያባብል ወደ መንግሥት ያስገባል፤ ማቴ 25፥32 ❎ አለም ስያባብል ወደ ስኦል/እሳት ያስገባል፤ ማቴ 25፥41 ⁉️ ዛሬ ማነው እያባበለህ ያለው? በማን እጅ ነህ? ማቴ 22፥4 ላይ ለሠርግ የተጠሩት ነበሩ። ቁ.8 ... ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤... ይላል። እኛም ለበጉ ሠርግ ተጠርተን እንደለን ታውቃላችሁ። ነገር ግን ለሠርግ ብቁ ሆነን ካልተገኘን ምን ዋጋ አለን? የማይገባን እንዳንሆን እንጠነቀቅ። ደግሞም ተጠርተው ከመጡት ውስጥ አንዱ የሠርግ ልብስ ስይለብስ በራቁቱ እንደተገኘው ሳንለብስ መምጫው መጥቶ እንዳናፍር እንጠነቀቅ። ምናልባት በስሙ ተጠምቀን አንደ ኢየሱስን ለብሰናል ማለት እንችላለን፤ መለብሳችን አዎ ልክ ነው፤ ነገር ግን ከተጠመቅን ወዲህ በውሏችን መሀል የሚመጣው አለማዊ ምኞት እየሱስን እንደገና ከላያችን ሊያወልቅ ይችላል ወይንም ልብሳችንን አሳድፎን ከሆነ ዛሬ በፊቱ በመውደቅና ንስሐ በመግባት፣ በመራራ ለቅሶ እንደገና ልብሳችንን አጥበን ነጭ ለብሰን መምጫውን እንጠብቅ። አለዚያማ ቤ/ያን መግባታችን፣ ማምለካችን፣ መዘመራችን፣ መጸለያችን፣ መጾማችን፣ እጅ መጨብጨባችን.... ከንቱ ሆኖ የሚሔዱትን አጃቢዎች /ሸኚዎች/ አድርጎን ከመንገድ የሚንመለስ ያደርገናል /ሸኚ ወደ ቤት አያደርስም!/ እንደሚባለው እንዳንሆን እንጠነቀቅ። ማለት የፈለኩት ብዙ ነገር ብኖርም እኔም ለራሴ ብቁ ስላይደለሁ እቶዋለሁ፤ ነገር ግን እችን ጽሁፍ አምብቦ የጨረሰ ሰው አምብቤ ጨርሻለሁ ለማለት ለማሳወቅ ያህል በአስተያየት ላይ "ጌታ ሆይ፦ ሐጂኖ እንጅ ሸኚን አታርገኝ" የሚል ድምጽ ሳያሰማ እንዳያልፍ አደራ። 🌺 መልካም ቀን ይሁንላችሁ 🌺 🌼 የማለዳ ትምህርት በየማለዳ 🌼 🌻 የውሎአችን ስንቅ ከማራናታ 🌻 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH የአስተያየት ግሩፕ @marantawoch Inbox ለማዋራት @Taddyapostolic

#የጥያቄና_መልስ_ውድድር የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በጥያቄና መልስ በሚል መሪ ቃል የጥያቄና መልስ ውድድር አዘጋጅተናል። ስለዚህ ሁላችሁም እንድትሳተፉ እናሳስባችኋለን። ነገር ግን በዚህ ሳምንት ውስጥ ለ
#የጥያቄና_መልስ_ውድድር የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በጥያቄና መልስ በሚል መሪ ቃል የጥያቄና መልስ ውድድር አዘጋጅተናል። ስለዚህ ሁላችሁም እንድትሳተፉ እናሳስባችኋለን። ነገር ግን በዚህ ሳምንት ውስጥ ለእናንተ የሚመቻችሁ ቀንና ሰአቱን አሳወቁን። ደግሞም ጥያቄ የሚቀርበው ከዚህ በፊት በማራናታ ተለግራም ላይ በፅሁፍ ካስተማርነውና ከፖሰትነው ትምህርቶች ውስጥ ስለሆነ እያነበባችሁ እንድትጠብቁልን እናሳስባችኋለን። አብዘኛው ጥያቄ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠቃላይ እውቀት /Bible General knowledge/ የሚያመለክት ይሆናል፤ አንዳንድ ደግሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ ቀጥታ የሚመልስ ይሆናል። ስለዚህ በጥንቃቄ እያነበባችሁ እንድትቆዩና የፈተና ቀን fix እንድታደርጉልን አሳስባለሁ። ሀሳባችሁን በግሩፓችን ላይ ብቻ አስቀምጡልን። ግሩፓችን @marantawoch የሚል ስለሆነ ለሚያሳትፉ ወንድሞችና እህቶች #ሼር በማድረግ ሀላፍነታችሁንም ተወጡ። ማሳሰቢያ፦ ቀን 01-05/09/15 ዓ/ም ድረስ ባለው ቀናት ውስጥ ቀኑንና ሰአቱን ወስኑ። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH አስተያየት @maranathawoch group ላይ ስጡን

🙏🙏🙏 #እንኳን_ደስ_አላችሁ🙏🙏🙏 ዛሬ (ቀን 28-29/08/15 ዓ/ም) የአሰላ ሰበካ ዓመታዊ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ስለሆነ Online መከታተል የሚትፈልጉ ወንድሞችና እህቶች በማራናታ ተለግራም ላይ መከታተል እንድትችሉ እናሳስባችኋለን። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH GROUP @marantawoch

photo content
+2

photo content

የጧቱ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክትና የከሰአት ፕሮግራም ማታ ስለሚናቀርብ ከONLINE አትጥፉ። ለሌሎችም #ሼር በማድረግ ለበረከቱ ተካፋዮች አድርጉአቸው፤ እናንተም ተካፋዮች ሁኑ። #HAWASSA 01 እናት አጥቢያ ስመረቅ የሚተላለፉ መልዕክቶች ሁሉ ለማድረስ እንሞክራለን። እናንተም ለበረከቱ ተካፋይ ሁኑ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

🙏 ሰላም ለእናንተ ይሁን ውድ የማራናታ ተለግራም ቤተሰብ እና የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስትያን ወንድሞችና እህቶች በሙሉ፦ ባለፈው ሳምንት የማለዳ ትምህርት ከ121-200 ያለውን በpdf አዘጋጅተን እናቀርባለን ብለን ቃል በገባነው መሠረት ዝግጅቱን አጠናቀን ሊናቀርብ ስለሆነ ደስታችንንም እየገለጽን ከዚህ ጋርም በተጨማሪ ሌሎች pdfochnm ሊንልክላችሁ ወድደናል። ዛሬ ማታ " የትኛውን pdf ፈልገው አጥቷሉ" የሚል ፕሮግራም አዘጋጅተናል። ከዚህ በታች ያሉ pdfoch በእጃችን ስለሚገኝ የፈለጉትን pdf ስሙን በ @Taddyapostolic በመላክ መሳተፍ ይችላሉ። በጣም አስፈላጊ የሆኑትን ላኩልን። ነገር ግን pdfun የሚንለከው በ @MARANATHAWOCH ተለግራም በኩል ስለሆነ JOIN አድርጋችሁ ጠብቁን። ለሌሎችም #SHARE ማድረግን አትርሱ ፤ የፈለጋችሁትንም PDF ጽፋችሁ በ @Taddyapostolic ላይ ላኩልን። የpdf ስሞች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው። 1, ቃሉ ይናገር፦ በቢሾፕ ተክለማርያም የተጻፈ 2, Eschatology_ finale destiny፦ በቢሾፕ ጌታሁን ላምቤቦ 3, የአንድ አምላክ ልጆች ይለይ፦ በወ/ም ታደሰ ከWCU 4, የመዳን እውቀትን ተቀበል፦ በወ/ም ታደሰ ከWCU 5, ወደ መዳን የሚያደርስ እውነት፦ scanned by camera 6, ህይወት የሚገኝበት መንገድ፦ scanned by camera 7, የስላሴ አመጣጥ፦ በወ/ም ናቲ ከአረካ 8, ጥምቀት በእርግጥ ያድናል 9, የልደት በዓልን ስለ ማክበር መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? 10, እግዚአብሔር አንድ ነው። 11, የሥላሴ አማኞች ሊመለሱ የሚገባቸው ጥያቄዎች 12, የ666 ምልክቶች 13, የኢትዮጵያ ሐዋርያት ቤተክርስትያን አባላት መመሪያ 14, የማለዳ ትምህርት ከ1-60 15, እውነት እና ምህረት 16, አስተማሪ ትረካዎች 17, መንፈሳዊ ግጥም 18, መንፈሳዊ ወጣት 19, ዘጠኙ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች 20, ኢየሱስን ማን ይሉታል 21, የማለዳ ትምህርት ከ61-120 22, ONLY JESUS ( APK) 23, #የሥላሴ_አጠያየቅ_ምስጥር 24, #የዶክትርን_ትምህርት_እግዚአብሔር_አንድ_ነው 25, #አማላጅ_ማንነው? 26, የማለዳ_ትምህርት_121_200 ( #New ) . . . ከእነዚህ ከ1-26 ካሉት ውስጥ የፈለጉትን እስከ ቀጣዩ ሳምንት ላኩልን #join & #share 👉 @MARANATHAWOCH 👉 @MARANATHAWOCH የመወያያ ግሩፓችን @marantawoch ላይ እናወራ ጽሁፉን በ @Taddyapostolic ይላኩ

ኖረህ አሳይ!!! አልቃሻ ደካማ ትውልድ ላየው ሁሉ የሚያጎበድድ በሀጢያት ሞቶ እሁድ የሚወለድ ሳያረጅ ያረጀ ልፍስፍስ ውስጡ ኦና እላዩ ቅልስልስ ላገኘው ሁሉ እጅ የሚያነሳ አቅመ ቢስ እንደ ፈሳሽ ውኃ ሰው ባበጀው ቦይ ውስጥ ዝም ብሎ የሚፈስ ከኮንፍረንስ መልስ የኢየሱስ ወቶአደር ፃዲቅ ልበ ሙሉ የሚሸልል የሚፎክር አቀንቃኝ ይሆናል ደርሶ ስለ እግዚአብሔር የሁሉም ሰው ተመሳሳይ ነው ፕሮፋይል ፒክቸር ከሳምንት ቦሀላ አቋም ይቀየራል ቀንደኛ ተሟጋች ወላይታ ነኝ ይላል ይፅፋል ይለጥፋል ይታገላል ያታግላል አዳምን ማውለቁን ጭራሽ ይዘነጋል ደግሞ ሌላኛው መብታችን ይከበር ድምፃችን ይሰማ ፍቼ ጫምባላላ አለን ለእኛ ለሲዳማ ተሸክሟል መፈክር በአንዱ እጁ ለሲዳማ በሌላኛው ለእግዚአብሔር ደግሞ ሌላኛው ኦሮሞ ነኝ እኔማ ዝም አልልም መሬታችን ሲቀማ ህዝባችን ሲጎዳ ሲፈናቀል እንታገል ዝም አንበል እያለ ይደራጃል ዘር ለመቀየር መጠመቁን ይዘነጋል ደግሞ ሌላኛው ሌላው አይኑር ከእኔ በቀር የአባይ ልጅ የበላይ ዘር ዋልታ ነኝ ይላል ለዚህች አገር ቆይቶ ትሰማለህ ሲዘምር እያለ ሰማይ ነው የኔ ሀገር ብኩን ትውልድ ዳተኛ ሰነፍ ትውልድ ዘረኛ ብቻ ኮንፍረንስ ይድረስ ንስሀ የሚገባ የለም እንደሱ የሚያለቅስ መለጠፍ አይበቃም ፕሮፋይልህ ላይ የተማርከውን ነገር አኑር በልብህ ላይ በሕይወትህ ተግብረው ለሁሉ እንዲታይ ኖረህ አሳይ ☞LINK ☞☞ https://t.me/MARANATHAWOCH Comment☞☞ https://t.me/Taddyapostolic

ታላቁ የመስቀል ፍቅር እህት መክሊት ተሻለ

#አስደሳች_ዜና #COMMING_SOON #NEW_PDF #የማለዳ_ትምህርት_121-200 PDF ውድ የማራናታ ተለግራም ቤተሰብ እና የማለዳ ትምህርት ተከታዮች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን የማለዳ ትምህርት
#አስደሳች_ዜና #COMMING_SOON #NEW_PDF #የማለዳ_ትምህርት_121-200 PDF ውድ የማራናታ ተለግራም ቤተሰብ እና የማለዳ ትምህርት ተከታዮች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን የማለዳ ትምህርት 121-200 ያለውን በpdf ወደ እናንተ ለማደርስ ጥቅት ቀናት ብቻ እንደቀረ እናሳውቃችኋለን። ከዚህ በፊት ከ1-60 እና ከ61-120 ያለውን ወደ እናንተ አድርሰን ነበር አሁንም፦ ሰከንድ ሰከንድን ተክቶ ደቅቃ እየሆነ፥ ደቅቃ ደቂቃን ተክቶ ሳአት እየሆነ፣ ሰአት ሰአትን ተክቶ ቀን እየሆነ፣ ቀን ቀኑን ተክቶ ሳምንትን ወልዶ፣ ሳምንት ሳምንትን ተክቶ ወርን ወልዶ እስከ ዛሬ ድረስ ኢየሱስ ተሸክሞን አድርሶናል። ስለዚህ ከዚህ በፊት ያላነበባችሁም ከ1 ጀምራችሁ እንድታነቡና ውሎአችሁን እንድታሳምሩ ይህ ውድ ትምህርት በpdf ተዘጋጅቶላችኋል። አንምብባችሁ ተግባር እንድታደርጉና ፍሬ እንድታፈሩ መልካም ምኞታችን ነው። ተባረኩልን!! @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH አስተያየት ካላችሁ ☞ @marantawoch inbox አስተያየት @Taddyapostolic & @Uwillnverwalkalone

የማለዳ ትምህርት /199/ ቀን 08/08/15 ዓ/ም ( 38ኛ ሳምንት ☞ እሁድ) ርዕስ፦ #በመብል_ምክንያት_የእግዚአብሔርን_ሥራ_አታፈርስ " NB:- የነገ ማለዳውን ዛሬ ለማካፈል የወደድኩት በየተለይ የዩኒቨርስቲ ተማርዎች በማለዳ ተነስተው ቁርሳቸውን ስለሚበሉ ምናልባት ከጣኦት ጋር ተካፋይ ይሆናሉና ቀድሜ ሊድረስላቸው በሚለው ግምት ነውና ተከታተሉ። ለሁሉም አድርሱአቸው። ውድ ቅዱሳን እንደምን አደራችሁ? ይህ ዘወትር ማለዳ ወደ እናንተ የሚናደርሰው የማለዳ ጸሎት ድምጽ ነው። አሁን በዚህ ሰአት የሚናስበው ነገር ለዛሬ ውሎአችን መሪ ቃል ይሆናል። ዛሬ የሚናደርገው ነገር ነው። እንደምታወቁት ዛሬ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ ቀን ይከበራል። አሁን ግን በዚህ አጋጣሚ አንድ ነገር ሊያሳስባችሁ ወደድኩ። ⭕️ የአንድ አምላክ ልጆች እናንተ ግን፦ " በመብል ምክንያት የእግዚአብሔርን ሥራ አታፈርሱ " ብዬ አጭር ማሳሰብያ ላሳስባችሁ። ይህንን ለማለት የወደድኩት የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሳኤ ቀን ምክንያት በማድረግ ሰው ሁሉ በየቤቱ፣ በየሰፈሩ፣ በየዩኒቨርስቲው ግብ...... ግብዣ አዘጋጅቶአል። 🆔 የእኛ ክርስትያን ግን ይህንን ከማድረግ ራሳቸውን የጠበቁ ናቸው። ምናልባት ግን አንዳንድ ሰዎች በአለማስተዋልም ይሁን እያወቁም የሰፈረ ሰዎች ይህንን ስያደርጉ እኔ እንዴት ከእነርሱ እለያለሁ በማለት እንዳይሰናከሉ ብዬ ይህንን ጽሁፍ ለማስታወስ ያህል ለመጻፍ ወደድኩ። 🕎 ሮሜ 14፥16-21 " እንግድህ ለእናንተ ያለው መልካም ነገር አይሰደብ። 17:- የእግዚአብሔር መንግስት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጅ #መብልና_መጠጥ_አይደለችምና። 18:- እንደዚህ አድርጎ ለክርስቶስ የሚገዛ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛልና፥ በሰውም ዘንድ የተመሰገነ ነው። 19:- እንግድያስ ሰላም የሚቆምበትን እርስ በርሳችንም የምንታነጽበትን እንከተል። 20:- " #በመብል_ምክንያት_የእግዚአብሔርን_ሥራ_አታፈርስ ሁሉ ንጹህ ነው፥ በመጠራጠር የተበላ እንደሆነ ግን ለዚያ ሰው ክፉ ነው" ይላል። ✝ ስለዚህ ይህንን በማድረግ ወንድሞቻችንን እንዳናሰናክል አደራ እላለሁ። በተለይ በተለይ በዩኒቨርሲቲ ግብ ውስጥ የሚትገኙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ዛሬ ልክ ጧት 12:00 ሰአት ጀምሮ የካፌ ምግብ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል። ይህ ለእናንተ ሳይሆን ለጣኦት የተዘጋጀ ምግብ ነው። አትረክሱ። መንፈሳችሁን ጠብቁ። 🕎 (በ1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 8፥4-13) 4፤ እንግዲህ ለጣዖት የተሠዋውን ሥጋ ስለ መብላት፥ ጣዖት ሁሉ በዓለም ከንቱ እንደ ሆነ ከአንዱም በቀር ማንም አምላክ እንደሌለ እናውቃለን። 5፤ መቼም ብዙ አማልክትና ብዙ ጌቶች አሉ፤ ነገር ግን በሰማይ ሆነ በምድርም ሆነ አማልክት የተባሉ ምንም ቢኖሩ፥ 6፤ ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን፥ ነገር ሁሉም በእርሱ በኩል የሆነ እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን። 7፤ ነገር ግን ይህ እውቀት በሁሉ ዘንድ አይገኝም፤ አንዳንዶች ግን ጣዖትን እስከ አሁን ድረስ ስለ ለመዱ። ለጣዖት የተሠዋ ነው ብለው ይበላሉና ሕሊናቸው ደካማ ስለ ሆነ ይረክሳል። 8፤ መብል ግን ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላም ምንም አይጎድለንም ብንበላም ምንም አይተርፈንም። 9፤ ዳሩ ግን ይህ መብታችሁ ለደካሞች ዕንቅፋት እንዳይሆንባቸው ተጠንቀቁ። 10፤ አንተ እውቀት ያለህ በጣዖት ቤት በማዕድ ስትቀመጥ አንድ ሰው ቢያይህ፥ ደካማ ሰው ቢሆን ለጣዖት የተሠዋውን ለመብላት ሕሊናው አይታነጽበትምን? 11፤ በአንተ እውቀትም ይህ ደካማ ይጠፋል፥ እርሱም ክርስቶስ የሞተለት ወንድም ነው። 12፤ እንዲህም ወንድሞችን እየበደላችሁ ደካማም የሆነውን ሕሊናቸውን እያቆሰላችሁ ክርስቶስን ትበድላላችሁ። 13፤ ስለዚህም መብል ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ፥ ወንድሜን እንዳላሰናክለው ለዘላለም ከቶ ሥጋ አልበላም" ይላል። ❇️ የአንድ አምላክ ልጆች፦ ከአለም ጋር አትደባለቁ። ✅ አሁንም ደግሜ ደጋግሜ በተለይ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለሚገኙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን አደራ እላለሁ። #ከቤተሰቦቻችሁ_ርቃችኋል_እንጅ_ከአምላካችሁ_አልራቃችሁም፤ ከቤተሰቤ ርቀአለሁ ማን ያቀኛል? ብለህ/ሽ ከአለም ጋር አትደባለቅ/ቂ፤ ቅድስናህን/ሽን ጠብቅ/ቂ። 🌺 ከቤተሰቦቻችን ርቀናል እንጅ ከአምላካችን አልራቀንም፤ ሁሌ ከእኛ ጋር ነው፤ እሱ እያየን ነው። እንጠነቀቅ!!! ⚛ ለዚህ ቀን ግን መብቴ/መውጫ ምንድ ነው? ነገ በየአጥቢያችን ቆንጆ የሆነ መንፈሳዊ ፕሮግራም ተዘጋጅቶላችኋል። የአለም ልጅች በብራና በየተለያዬ ነገር ስሰክሩ እናንተ ግን #በመንፈስ_ስከሩ። እንደምንም ሆናችሁ የነገ ቀን ውጭ ለመመገብ ሞክሩ። መልካም የፕሮግራም ሳምንት ተመኘንላችሁ🙏 በዚህ ማለዳ ትምህርት ላይ መስተካከል አለበት የምትሉት ሀሳብ ጥቆማ አስተያያት ካለ ከታች ባለ ቦት ላይ ማድረስ ትችላላችሁ። 👇👇👇👇👇👇 @Taddyapostolic @Uwillnverwalkalone አይ ኤሄ ይቅርብኝ የሚትሉት ከሆናችሁ እንደአማራጭ ያቀረብንላቸው የማራናታ Group አለ በእሱ ላይ commentachun ማድረስ ትችላላችሁ👇👇👇👇👇👇 @Marantawoch እግዚአብሔር የልመናችን ድምጽ ይስማልን አሜን!!! 🤷‍♂🤷‍♀በጸሎት ወጥታችሁ በምስጋና ግቡ🤷‍♂🤷‍♀ 🌻የማለዳ ትምህርት በየማለዳ🌻 🌸የውሎአችን ስንቅ ከማራናታ🌸 🌼መልካም ቀን!!!🌼 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH