የግጥም ምሽት በቴሌግራም
Open in Telegram
ይህ ቻናል ከተለያዩ መጽሐፍት የተቀነጨቡ ግጥሞች የሚቀርቡበት እንዲሁም ወርሃዊ የግጥም ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው ግጥም ለምትወዱ ሁሉ...የራሳችሁን ሙከራም የምታቀርቡበት ነው ለማንኛውም አስታየት @Nirvana134 እንዲሁም @simba23 ላይ አለን ፧ @yegetem32
Show more5 931
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-4030 days
Posts Archive
5 931
5 931
ስምና ኩነኔ
"""""""""'''''''
ለውሸትሽ ድጋፍ፥
በ.ማ.በ.ል.ሽ አፋፍ፥
እውነትን ቀብተሽ
በማስመሰል አንባ፥መዝለቅሽ ቢሰምርም፤
ስም ያለው ሞኝ ነው
'ክህደት' ባልኩኝ ቁጥር፥"ወይታሽ" አይቀርም...
አይቀርም
አክብሩልኝ ካለው
ከአስርቱ ትዕዛዝ፥ህግጋት ተላልፎ፤
እንዳትነኩ ካለው
ገነት ከፀደቀው፥እፀ በለስ ቀጥፎ፤
የውሸት ቅኔ ዘርፎ...
የሰው ልጅ በድክመት
በህይወቱ ምላስ፥ኃጥያትን ቢቀስም፤
ዘላለም አለሙን
"እመት'' ሲል ይኖራል
ተደባልቀውበት፥መኮነኛው ከስም!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
ለሌሎች ምርጥ🤌👌 ግጥሞች join በሉ....👇👇👇
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
5 931
5 931
እምነት
""'''''''''''
የዓለም እሾህ ወግቶኝ
ከቤተ'ስቲያን ቅፅር፥መሬት ተንበርክኬ፤
ለጨነቀኝ ጭንቀት
ዕንባን አጎርፋለሁ፥መቅደሱን ታክኬ...
ፀልዬ ስነሳ
ያንኑ ጭንቀቴን አብሰለስላለሁ፤
አጉተመትማለሁ፤
አንስቼ ጥላለሁ፤
ድጋሚ ፈራለሁ፤
መቼም ሰው አይደለሁ!
ስሜትና ሀሳቤ፥አደብና ቀልቤ፤
ስክነቴን ሸክፈው
ሰቀቀን ሰዷቸው፥እርቀው ከበሬ፤
መልሶ ይወጋኛል
ለእምነቴ አለቅም፥የጭንቀቴን ፍሬ፤
የሞኝነት ነገር
"ባይችለውስ" ብዬ፥ፈጣሪን ጠርጥሬ...
አወይ ሰው መሆኔ!
አይ ፍርሃት፥
አይ ሸክም፥
አይ ጥረት፥
የህሊና ኡደት፥የመልፈስፈስ ዕዳ፤
ባይገባኝ ነው እንጂ
እምነቴ ቢጀግን
ግመል ጭንቄ ይሾልካል፥በመርፌ ቀዳዳ!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
join
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
5 931
5 931
5 931
5 931
# የተራዘመ_ውልደት
ጌታ ሆይ
ከአባትህ ቤት ወተህ ፥ ለኛ ስትቀጣ
ከሀጢአት ነፃነት ፥ ነፃ ስታወጣ
እንደ ድሮ መስሎ
ዳግም ለመወለድ ፥ ዘንድሮ ብትመጣ
አይ
አይ
አይ
እኚያ በትንፋሽ ፥ የሚያሞቁ ከብቶች
ግማሾቹ ታርደው ፥ ግማሾቹ በጥይት ተገለው
እስትንፋሳቸው ቆሟል ፥ ከሜዳ ላይ ወድቀው
አይ
አይ
አይ
ደሞ አህዮቹን
ያሞቁኛል ብለህ ፥ ብታስብ አሁንም
ብትፈልግ ብትፈልግ ፥ አይኖሩም ከግርግም
ካ..ገ..ኘ..ሃ..ቸ..ው..ም
ሲላላኩ ነው ሚውሉ ፥ በጦርነት ግድም
አይ
አይ
አይ
ሁሉ..ሁሉ..ሁሉ..ቀርቶ
ወገብ ማሳረፊያ ምናል ፥ ቢፈለግ ተገኝቶ
ሲታሰስ ሲታሰስ
ደጋግሞ ሲታሰስ
በእሳት ተበልቷል
አለ የተባለበት ፥ ምጣዱ ጋር ሳደርስ
ወዲያ ማዶ ከጋራው ላይ
አንዲት ጎጆ ዘንበል ያለች
እኔን ለመውለድ ከቶ ትበቃለች
ብለህ
ከቦታው ጋር ስደርስ ፥ ብታገኝም በረት
እሱም ተይዞ ፥ ጥይት ሆኗል፥ የሚከማችበት
እሱም ተይዞ ፥ ልጃገረድ አዛውንት ፥ ሆኗል የሚደፈርበት
ለዛ
ለዛ
ለዛ
ይኼን ሁሉ በደል
ይኼን ሁሉ ስቃይ
ይኼን ሁሉ ጭካኔ
ገና ሳትወለድ ፥ ከባሰ ከዛኔ
በቃ እንደውም እንደውም
በድሮ ውልደት ፥ እኛ ስንፃናና
ጊዜውን አራዝመኸ
አንተ አትወለድ ፥ በዘንድሮ ገ'ና
ይቅርብህ
ይቅርብህ
።።።።።።።።።።።።።።።።
✍ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
5 931
5 931
እ.ን.ደ.ራ.ጅ?
""""""""""""""
አሳማና ዶሮ ቡና ተጠራሩ፤
በቡና ቁርስ ወሬ
የባጡን የቆጡን ሁሉንም አወሩ...
አውርተው፥
አውርተው፥
ለህይወታቸው ለውጥ፥ለመድረስ ለስኬት፤
ዶሮ "እንክፈት" አለች
"አለ የተባለ ታዋቂ ምግብ ቤት"
"እሺ" ተባባሉ፤
በሀሳብም አልቀሩ፤
በአንድ ተደራጅተው ምግብ ቤት አቆሙ፤
ታ.ት.ረ.ው ለመስራት በአንድ ልብ ተስማሙ፤
አውጥተው አውርደው
ለሬስቱራንቷ ስም ለመስጠት አጤኑ፤
በሀሳባቸው ማምሻ
"ያ'ሳማ ስጋና እንቁላል ምግብ ቤት"በሚለው አፀኑ
ከዛማ
ከዕለት ወደዕለት
ከዓመት ወደ ዓመት ደንበኛቸው በዛ፤
እጅ ያስቆረጥማል
የአሳማ ስጋ አልሆነም የዋዛ...
በዝና ተሰምቶ
የሩቅ እንግዳዎች
ምግቡን ለመቅመስ ይመጡ ጀመረ፤
የዶሮ እንቁላልም
እንደአሳማ ስጋ ይጣፍጥ ነበረ።
እንዲህ ነው እንግዲህ
የአንዳንድ ምክክሮች የተግባር መቋጮ፤
የህብረት ተብሎ
ለአንዱ መሰዋት ነው ለአንደኛው መዋጮ..!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
join👇
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ሁለት ገፅ
"""""""""""
የደሀ የህልሙን ቅቤ
ሀብታም በእውን ቀመሰው፤
ደም ግባቱን አ.ሻ.ቅ.ቦ
መልኩን ወዝ አለበሰው፤
የደሀ የሰማዩን ላም
ቱጃር አልቦ ጨረሰው፤
ምስኪን ተስፋው ነጠፈ
ደሀ ጠኔ ወረሰው..!
አዬዬ.. ሰው........አዬዬ..ሰው
የክፋት ዓለም ንውዘት
የክፋት ህይወት መንጠቆ፤
እውነት ወዲያ ተሽቀንጥራ
ሁሉም ውሸትን ታጥቆ፤
የሰው ላብ ከማር ጣፍጦ
የስርቆሽ ሀሳብ ሰንቆ፤
በግ በአንድ ብር ይስቃል
በፍየል መቶው ተነጥቆ..!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
join and share
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
5 931
ትሁኔ....ይሁኔ
""""""""""""""""
ትሁኔ
በአንድ ሰሞን ቀን አንግሶ፤
ደም ግባቷን አሞግሶ፤
በውበት ልክ የምትቃኝ፤
ሁሌ የምትል መልኬ በቃኝ...
በፊት ልቧን ያኮፈሰች
ሁሉ ሲላት ቆንጆ ብቻ፤
አሁን ስጋት ያናወዛት
የምትመኝ ሶስት ጉልቻ..!
ስትኮራ
ስትቆነን ውብነቷ የነጠፈ፤
የዕድሜ አለሟ
እንደ ድንገት በሆይ ሆይታ የከነፈ፤
ድንቅ ገፅዋ የረገፈ...
ት
ሁ
ኔ...
ይሁኔ
መሸታ ቤት ዘውትር ቤቱ፤
ወጣት መሳይ ዕድሜው የአንቱ...
ከዛች ከዚች ሲነካካ፤
ያልሰከነ ልቡ ያ'ረጋ...
በእድሜው ዘመን ወደ አመሻሽ፤
ብሎ የሚጮህ "የሚስት ያለሽ''...
ይ
ሁ
ኔ...
ይህን ያየ መንደርተኛ፤
ለሰው ኑሮ የማይተኛ...
ትሁኔንም አማከረ፤
ይሁኔንም መረመረ...
ቀረፃቸው በአንድ ጠርዝ
በራሱ ሀሳብ አድበልብሎ፤
ጊዜ ሄዷል ተፋቀሩ
"ይሁን" እና "ትሁን" ብሎ...
.
.
አንድ ጥያቄ አለኝ
በውስጤ ግር ያለኝ...
.
.
በዘመን ውርጅብኝ ታሪክ ሲለጣጠፍ፤
በውሸት የዳበረ የዘመኑን ጉድፍ...
በሁለት ፆታ ፍቅር
ህዝብ ተቅጠልጥሎ እያለ ሰለሜ፤
ዓላማና ፍቅር
በምን ተገናኙ እላለሁኝ ቆሜ..?
***
ያረፈደ ሁሉ
ካረፈደ ኃላ ዘመን ከጠገገ፤
መሰሉን መሰሉን
የረፈደበትን ሰርክ እየፈለገ...
መንደርተኛው ሁሉ
"ጊዜ ሄደባቸው" እያለ እያወጋ፤
በቡና ቁርስ ወሬ
"እከሌን ለእከሊት" ብሎ እያጋባ፤
ለዓላማ ሲደገስ
በሽሙጥ ጭብጫቦ በሽሙጥ ሀይሎጋ፤
ስሜት ሆነ ሞቱ
ፍቅር ገደል ገባ፤
ሰዉ ታቅፎ አደረ
ነፍስ የሌለው ስጋ..!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
join👇
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
እፎይ
""""""
አይቆረቁርህም፥
አይጎረብጥህም፥ደግሞ ለመቀመጥ፤
በሀሳብ እሩቅ አትሂድ፥ከመሬት ተዘርፈጥ፤
ሶፋና በርጩማ፥ብለህ ከቶ አትምረጥ፤
ምቾት ሲበዛ ነው፥እሳቤ የሚቀብጥ...
እመን
አይቆረቁርህም፥
አይጎረብጥህም፥
መቀመጫ ገር ነው፥አያውቅም አማሮ፤
አመል ከተገራ፥ከታጠበ አዕምሮ...
ተቀመጥ፥
አትቅበጥ፥
አትናቅ፥
አታማርጥ፥
ለምቾትህ አደልድል
አፈር ተፀይፈህ፥ፈፅሞ አትገደር፤
ህሊና ካልፀዳ
አይገጣጠሙም፥እፎይታና ወንበር..!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ፀሎቴን ባሰማ ፥ እንደሰው ዝም አለኝ
እሱንም ዘመቻ ፥ ወሰዱት መሰለኝ
.......
የእቴሜቴ ጀምበር
©ሲራክ ወንድሙ
.
እረኛ አይዘምርም ፥ ዝም ነው አድባሩ
ፋኖስ ክሩን አጥቷል ፥ መሸ ደህና እደሩ
ቡሬ መንደር ራቃት ፥ የለችም ከቤቷ
በሌት አልዘመረች ፥ ከፍቷታል ወፊቷ
ማልዶ ሌት ሚያነቃኝ ፥ ዶሮ በጉድ ወጣ
የሌት ድምፁን ሸጦ ፥ መውዜር ይዞ መጣ
ወዲያም ወደ ሰማይ
ከጎጆዬ በላይ
ፀሎቴን ባሰማ እንደሰው ዝም አለኝ
እሱንም ዘመቻ ወሰዱት መሰለኝ
.
የዛች የእዝነት አርማ ፥ የህዋ ላይ ሰንደቅ
እንዴት ቀን ከፍቶባት ፥ ውብ ጀምበሯ ትጥለቅ
ከዛች ከገራገር ፥ ከደጊቱ ዳሴ
እንደምን ብርቅ ይሁን ፥ ሰላም ለእለት ጉርሴ
ኧረ እንደምን በምን
ኧረ እንደምን በምን
አምነን ያነገስነው ብራ ቀን ይዳምን
እኔን አፈር ይብላኝ ፥ ለእኔ ቀኑ ይክፋ
አንቺን ያሳጣችሽ ፥ ያች አለም ትደፋ
እስከ መች አስከ መች ፥ የአረር ሙዳይ ቋጥረን
እንደጃኖ ኩታ ፥ ዝናር ጥለት አርገን
ሀገር እያጠፋን ፥ ያልፋል እንላለን ?
እንዴት ነው መሰንበት ?
መውዜር እንደነዶ በሚመዘዝበት?
ኧረ እንደምን በምን
ኧረ እንደምን በምን
አምነን ያነገስነው ብራ ቀን ይዳምን?
.
ከጩኸትሽ ማዶ ፥ ካኮረፈው ሰማይ
ቄራ ከመሰለው ፥ ከአድማስሽ ሸራ ላይ
እብሪት ያጠላበት ፥ ምስል ድንገት ካየው
ለቸር አንመስለኝም ፥ ያን ጊዜ ፈራለሁ
አርብ አርቡን አመሻሽ
የሰማዩ ገላ ሲመስል የደም ሻሽ
ንትብ የለበሰ
ከወደ አንገቱ ዘሞ የተዘለሰ
ይሁዳሽን ባላይ ፥ ወድቆ ሲያንሰራራ
መስቀል ሆኗል ለሻጭ ፥ ገዢ ራሱን ያኩራ
ከክርስቶስ ይልቅ ፥ ይሁዳ ነውና ሚረከብ መከራ
ምክኒያቱም ......
ዘመን እያሰፉ
ትውልድ ለሚነቅፉ
ነገር ጠንቷል ዛሬ ፥ አውቀውት ይረፉ
ለሻጭ መስቀል ሊሆን ፥ ምሏልና ዛፉ
.
በኑረት ቀራንዮ ፥ በህይወት ጎለጎታ
ከገዳይሽ ቀዬ ፥ አንቺ ሆነሽ ጌታ
በሰማያ አኮርባጅ ፥ ወዲያ ስትላጊ
የመከራን መስቀል በሌት ተሸክመሽ ፥ መንገድ ስትፈልጊ
ጨረቃዋ ገባች ፥ ከደመና ጉያ
ከዋክቶች ሸሽተው ፥ እንደሰደድ ቋያ
ጠረንሽን ገፍተው ፥ ከገላሽ ሲርቁ
በንቄት ሸምቀው ፥ ሊጥሉሽ ዘለቁ
.
ዞር ብንል ወዲያ ፥ አራራይ መረዋ
ቀና ብንል ኦና ፥ የጠቆረ ህዋ
የፀሎትሽ ጩኸት ፥ ካልደረሰው ያ ' ቃል
እሱም እንደሰዉ ዘምቶልሽ ይሆናል።
..................... //// ..............
©ሲራክ ወንድሙ @siraaq
የእቴሜቴ ጀምበር
ህዳር ፳፻፲፬ ዓ.ም
https://t.me/yegetem32
5 931
ተጓዥ
"""""""
ሂዱ ከመከራው፥
ቢከብድም ተራራው፥
ሜዳ ብቻ አይደለም፥ህይወት ስንክሳሯ፤
ስኬት ጫፉ አይሆንም
ፈተና ነው ደስታው፥በልብ ለሚመራ...
ሂዱ በጭንቅ መንገድ
የጭቃ ማጥ ጥርጊያን፥መርገጡ ቢሰቅም፤
አልጋ በአልጋ ሆኖ
የሮጡበት ኮቴ፥ከአንጀት አያስቅም...
ሂዱ...ሂዱ...ሂዱ
ቢያስፈራም መንገዱ፥
አያል ሆኖ ጉዱ፥
ውጤት አልባ ሆኖ
የተጓዙት ዳና፥አፈር ደም ቢያቀምስም፤
ላደከመ እርምጃው
ብልህ እግሩን እንጂ፥መንገዱን አይወቅስም..!
#ይሄዳል
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
join
👇👇👇
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
