የግጥም ምሽት በቴሌግራም
Open in Telegram
ይህ ቻናል ከተለያዩ መጽሐፍት የተቀነጨቡ ግጥሞች የሚቀርቡበት እንዲሁም ወርሃዊ የግጥም ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው ግጥም ለምትወዱ ሁሉ...የራሳችሁን ሙከራም የምታቀርቡበት ነው ለማንኛውም አስታየት @Nirvana134 እንዲሁም @simba23 ላይ አለን ፧ @yegetem32
Show more5 931
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-4030 days
Posts Archive
5 931
ገላዬ....
ከመስኩ ላይ ቆሜ ፥ እምባን ባረገዘ
በናፍቆት ወይቦ ፥ በተድበዘበዘ
በዚያ መንታ አይኔ...
የመራቤን ጅራፍ ፥ የምኞቴን ጩኸት
ላንቀላፋው ጤዛ ፥ ለወፍ ጎጆው ምልዓት
ዘምሬ
ዘምሬ
ደስኩሬ
ደስኩሬ
ህቅ ባለው መንፈስ ፥ ምሬት ባየው ልሳን
ብናገር ለእነሱ ፥ የኔን እንዲህ መሆን
የአንቺ ወዲያ መቅረት ፥ የንጋት ሰቀቀን
በጉድ ወጣ እያሉ ፥ ለሰማይ ለምድሩ
ለሰው ላራዊቱ ፥ ለቀየው መንደሩ
መስቀሉ ናት ብለው ፥ ናፍቆት ወለፈንዴ
ተሸነፈ ብለው ፥ ያሙኝ ይሆን እንዴ?
.................. / / .....................
© ሲራክ ወንድሙ
@yegetem32
@yegetem32
5 931
የደጋ በረከት
.
©ሲራክ ወንድሙ @siraaq
.
የተስፋ ሀገር ወዲያ ፥ የሀሳብ ሀገር ወዲህ ፣
ፋኖሱ ተሰዷል ፥ ሊመሽ ነው እንግዲህ ፤
ዶሮ ከቆጥ ሰፍሮ ፥ ሊኮኩል ሲቀጥር ፣
ይሄንን እያየ ፥ ልቤ ሲለኝ ጠርጥር ፣
በምናልባት መናጥ ፥ የቀን ድግግሞሽ ፣
እንዳሞራው ፍጥነት ፥ አክናፍ እሽክርክሮሽ ፤
ከቀየዋ ሳልሄድ ፥ በሯም ሳይዘጋ ፣
አድማስ ሲደማምን ፥ ምሽት ሲዘረጋ ፣
ባዶ እጄን ወጣለሁ ፥ ውብ አይኗን ፍለጋ።
__°°° _
የደጋ በረከት
መስከረም ፳፻፲፬ ዓ.ም
@yegetem32
@yegetem32
5 931
እኔና ደመራ
""""""""""""""
አየሽው ህይወቴን...?
አንድ ግዜ እየገራ አንድ ግዜ እየከፋ፤
ስንት ግዜ በርቶ ስንት ግዜ እንደጠፋ...
አየሽው
አየሽው ህይወቴን?
በውሸት ተወግቶ ሲደማ ሲቆስል፤
በተስፋ እሳት ነዶ በአንድ አፍታ ሲከስም፤
ግንዱ ተለብልቦ
ሲገነደስ ዘሞ፥ደመራን ይመስል...
አየሽው
አየሽው ህይወቴን?
በሆታ ተሰቅሎ በሆታ ተገፍቶ፤
የእንቧይ ካብ ሆኖ እውነቴ ተንዶ፤
አመድ እንደሚሆን እኔነቴ ነዶ...
አየሽው
አየሽው?
መንፈቅም አመትም
ቀን እየቆጠረ ሲጨልም ሲበራ፤
ውል እያዋዋለ ህልሜን እያደራ፤
እረመጥ ላይ ቆሞ
ፅዱን ተከናንቦ በእሳት የሚገራ፤
የምኖረው ኑሮ አይመስልም ደመራ?
ይመስላል?
ይመስላል አለሜ?
ያሳለፍኩት ዘመን የቆጠርኩት ዕድሜ...
ይመስላል?🤔
አይ......አይ
ቆም ብዬ ሳስብ
አይመስልም......አይመስልም
ደመራ ትልቅ ነው
ቢቃጠል ቢወድቅም መስቀሉን አግኝቶ፤
ይብላኝ ለኔነቴ
እሳቱን ታቅፎ
ሲቃጠል ለሚኖር ፍላጎቱ ጠፍቶ...!
................ይብላኝ............
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ተይ...
"""""""
ሽንቁርሽ ይበዛል
ስዘክርሽ ስመክርሽ፥ባክሽ አትፍዘዢ፤
እ'ውን ዓለም እያለ
በሰመመን ባህር፥በህልም አትቃዢ፤
እልፍ መስሎ ከታየሽ
ከሳር ክዳን ጎጆሽ፥ሰበዝ አትምዘዢ፤
እኔ እየነገርኩሽ
እንዲያው የለበጣ፥በምክሬ አታፊዢ...
...እረፊ...
በነፍስሽ ብራና
በዕድሜሽ ልክ ብዕር፥ስህተት አትፃፊ፤
ለፆም አስቀድሰሽ
ስጋሽን አስርበሽ፥በአመል አትግደፊ፤
ልክ ልኳን ኑሪ መስመር አትለፊ...
...እረፊ...
ተሞኝተሽ አትቅሪ
ልቤ እየመከረሽ፥ስናገር ሳወራ፤
አይገጣጠሙም
ብልሀት እያለ፥ብልጥና መከራ...!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ምን ነካሽ ?!
©ሲራክ ወንድሙ @siraaq
.
' ጥፋቱ የማን ነው? ' ፥ ብዬ እንዳልጠይቅሽ ፣
ቃልሽን ሳልሰማ ፥ እንባ ነው ሚቀድምሽ !
ምንድነው ገላዬ? ፥ ውስጥሽን በርዞ ፣
የልብሽን ደጀን ፥ መሻከር ወዝውዞ ፤
ቂም አይሉት እልህ ፥ በነፍስሽ ተረግዞ ፣
ዜማሽ ቅኝት አጥቶ ፥ በሀዘን እንጉርጉሮ ፣
' ተወኝ ! ' የሚያስብልሽ ፥ ለአይን እንኳን አቅሮ ?
ለምን ነው አካሌ ??....
ሰውነት እርስቱን ፥ ቀን ሲገፋው ማልዶ ፣
በእምነት የካቡት ቃል ይወድቃል ተንዶ ፤
ፍቅርን ባነፁበት ፥ በቀየዱት ቀዬ ፣
እንዴት መልስ ይሆናል ፥ ለየምን እዬዬ?
ድክምክም አድርጎ ፥ ፍዝዝ ትክዝ ትክዝ ፣
አዚም ተከናንቦሽ ፥ ቀንሽን ሲበርዝ ፣
በጣት ያልጠለቀ ፥ የልባችን ኪዳን ፣
' ምን ነካት? ' ይለኛል ፥ ገፅሽ ሲደማምን።
እውነትም ምን ነካሽ ? ፥ ምን አየሽ እርግቤ
የሀሴቴ ደንገል ፥ የነብስ ረሀቤ
ምን ነካሽ? ፥ የኔ ወርቅ
የህይወት ውቧ ሰንደቅ
የናፍቆት ዶሰኛ
የቀን አመለኛ
የአይኔ ስር መሀረብ
የትዝታ ቀለብ
የሳቅሽ መስክ ላይ ፥ መከፋት ሳር ግጦ ፣
አዛኝ አንጀትሽን ያ ጭካኔሽ በልጦ ፤
በአይንሽ ስትገርፊኝ ፣
በኩርፊያሽ ስታስሪኝ ፣
በእምባሽ ልቤ ወልቆ ፥ ዝምታሽ ሲያደቀኝ ፣
' ያቺ ሴት ናት! ' ብሎ ማመኑ ጨነቀኝ።
እናልሽ ገላዬ ፥ አንቺ የነፍሴ ኩሬ
ድክምክም አድርጎ ፥ ፍዝዝ ትክዝ ትክዝ ፣
አዚም በገባሩ ፥ ቀንሽን ሲበርዝ ፤
በጣት ያልጠለቀ ፥ የልባችን ኪዳን ፣
'ምን ነካት? 'ይለኛል ፥ ገፅሽ ሲደማምን ።
ምን ነካሽ በእኔ ሞት??
.
.................... //// ....................
መስከረም ፳፻፲፫ ዓ.ም
@yegetem32
@yegetem32
5 931
ጥላ
"""""
ከማጥ ውስጥ ተዘፍቀህ
ከጭንቀት አረንቋ፤
እህህን ስታዜም
በመከፋት ቋንቋ!
ንዋይ ሀብትህ ጠፍቶ
ጭለማነት ወርሶህ
ከዓለም ስትጣላ፤
ብርሃንህ ሲሸሽ
እንኳንስ የሰው ልጅ
ከጎንህ አይኖርም የአካልህ ጥላ!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ጅል ትዕግስት
""""""""""""""""'
ለምን ጊዜ ሰዓት
ዘመን እያዋጀን
ለብርሃን ስንሮጥ
እንደ እሳት እራት ብርሃኑ ፈጀን?
ብለን ስንጠይቅ....
እሳት ሲለቁብህ
በረመጡ መሀል ዝምብለህ ተጋገር
በነገር ሲጠብሱህ
አንተ ምድር ሆነህ በሆድ ችለህ እደር
እንረድህ ሲሉህ
ትንፋሽህን ውጠህ ከአንገትህ በል ሰበር
በጨለመ ጊዜ
ቤትህ ሆነህ አልም ወጋገናም ጀንበር
በመሞትህ ማግስት
እውነትና ንጋት ይፈካል እያደር
የሚል መልስ አለ እንዴ?
ለክፉም ለደጉም
እስቲ ከልብ ሆነን እናስብ አንዳንዴ....
ሰው አንደበት ኖሮት መናገርን ትቶ
እንጫንህ ሲሉት ትከሻውን ሰጥቶ
በሰፈሩት መጠን ልኬቱን አስልቶ
በጊዜ ዱብእዳ በዘመን ወረንጦ
ሰው እንዴት ይኖራል?
ቀን እንዴት ይገፋል?
በጅላጅል ትዕግስት አሙዋሙዋት ተመርጦ?
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ሰቀቀን
""""""""
(ዳግም...ደግሞ...ደግሞ)
በእሳት አይቃለድ
ረመጥ የጠበሰው፤
በእህል አይጫወት
እርሀብን ያየሰው!
እንዲህ ነው ሰቀቀን
ያለፈ ጠባሳ
ትዕቢትን የሚያቀልጥ፤
እባብን ያየ ሰው
በመንገዱ ሁሉ
ይሸበራል በልጥ!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
እኔ አንቺን ስወድሽ
""""""""""""""""""""""
እኔ አንቺን ስወድሽ
እንደ ባህር ዕንቁ
ከውስጥሽ ጠልቄ፤
ጭራሽ ላልንሳፈፍ
ሀሳብ አሸፍቶኝ
ከፍቅርሽ እርቄ፤
ሰርክ
ለልቤ አጥቢያ
ከቁርበት ደርቄ፤
አንድ አንቺን ሰንቄ!
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
ባስቀመጥሽኝ ቦታ
በፈቀድሽው ስፍራ
ሁሌ የምኖር ከቶ፤
ከአንድ ሀሳብ
ለአንድ እውነት
የተስፋ ቄጤማ በአንድነት ገምዶ፤
እስርስር
ጥፍንግንግ
ያ'ረገኝ ጎልቶ!
(ፍቅርሽ)
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
ለዓይን አልሞላ ብሎኝ
የቆንጆ ሴት መልኳ፤
ግለ ህሊናዬ
ባንቺ ልክ ተሰፍቶ
የሁሉም ወይዛዝርት መስፍርትና ልኳ!
.
.
አድርጎብኝ አንቺን
.
.
አድርጎብኝ አንቺን
የህይወቴ ቆራጭ
የህይወቴ ፈላጭ፤
የአንዷ ስጋ ለባሽ
ብቸኛዋ ነፍሴ
መንበር ላይ ተቀማጭ
ለፍቅርሽ ብስልስል
ውበትሽን ቀላዋጭ!
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
ለዳፍንት እውነቴ
ከፀዳልሽ ማሾ
ስር ስር የምቀመጥ፤
ለሻማ እኔነቴ
በደስታሽ ፈንድቄ
በሀዘንሽ የምቀልጥ፤
ለብስጭቶችሽ
በንዴትሽ እጥፍ
እኔ ተናድጄ ጨጓራ የምልጥ፤
ለአንድ ዘለላ እንባሽ
ደረት የምደቃ
ፊቴን የምቧጥጥ!
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
ከሰማይ ላይ ያሉ
ኮከብ እንደማርገፍ፤
ለጨረቃ መልክሽ
ድምቀት ተጋሪሽን
ውበት እንደመግፈፍ፤
አንድ አንቺን አንግሶ
ታዛዥ ሎሌሽ ሆኖ
ከእግርሽ እንደማረፍ፤
ዓይንሽን እያዩ
በውበትሽ ልምጭ
ሁሌ እንደመገረፍ፤
ፍቅርቅር
ውድድድ
ለነፍስሽ መንሰፍሰፍ፤
በውበትሽ ፀዳል
በትከሻሽ ግርማ
ዘላለሙን መክነፍ!
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
ልቤ ላይ ያ ልብሽ
እያገነገነ፤
ነፍሴ ለውዳሴሽ
በጥዑመ ዜማ
እያቀነቀነ፤
አይኔ ጎላ ብሎ
ካንቺ ላይ ተተክሎ
ሱረት ተጭሶበት
እንደመረቀነ፤
ሞቅታ ውስጠቴን
ችፍችፍ ላብ ግንባሬን
ሁሌ የሚያርሰው
አንድ አንቺን እየለ፤
ሁሌ እየዛበረ፤
እንደ አገው ዣንጥላ
ምድሪቱ ዞራብኝ
ልክ እንደ ሰከረ!
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
ሌቱ ብርሃን ሞልቶት
ቀኑ እንደ ጨለማ
እጅ ክንዴ ዝሎ
ጉልበቴ ቄጠማ
ውል እምነቴ ድንግር
አመሌ ገገማ
እኔ
አንቺን
ስወድሽ
ከውበትሽ ማማ
ሽቅብ የማንጋጥጥ
እፍኝ ልብ ይዤ
ተራራ የምሳፈጥ
እብሪት የከበበኝ
ባንቺ ለሚመጡ
ቢሉኝ የማልፈራ
9 ሞቶች መጡ
አንዱን ግባ ብዬ
ልሰጥ ከደረቴ
ህይወትሽ ኑሮዬ
ሞትሽ ሆኖ ሞቴ...!
እኔ
አንቺን
ስወድሽ...!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ሁሉ አገሩ
"""""""""""
ቀለብ ስንቁን ሳይሸካክፍ
እሩቅ መንገድ አሳንሶ
ምን ገጠመኝ ሳይጨነቅ
አራዊቱን በጎን አልፎ
አጥንተ ቢስ ልበ ሙሉ
ህንፃ ግንቡን ኬላ አፍርሶ
ተስለክልኮ ተወንጭፎ
ተራራውን ዱሩ ጥሶ
ሄዶ ይመጣል
እግር ባይሄድ ሁሉ አገሩ ምላስ ደርሶ!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
ሐውልት
ግርማ ሞገስ ያለው እጅግ የሚያኮራ
በእጅ ያልተቀረጸ በሰው ያልተሰራ።
በእስክንድር ምሰሶ በቁመት የላቀ
በአሰራርም ቢሆን ይበልጥ የረቀቀ።
ሐውልት አቁሜያለሁ ለመታሰቢያዬ
ለሚመጣው ትውልድ ለወደ ኋላዬ።
ወደዚህም ቦታ ሰዎች ይመጣሉ
የሐውልቱን መንገድ እየተከተሉ።
የማይፈርሰውና የማይበሰብሰው
ረቂቅ መንፈሴም ሥጋ የለበሰው።
እንደ መሰንቆ ምት ወይ እንደበገና
ይኖራል ወደፊት ብዙ ዘመን ገና።
ቅኔ አዋቂ እስካለም ከሰማይ በታች
የኔን ሰም ይጠራል ሰርክ ሳይሰለች።
ኩሩው ስላቭና ትዕቢተኛው ፊንም
አረመኔው ትንጉሰ ወኔያሙ ካልምክም።
ዝናዬ ተስፋፍቶ በሩሲያ ሙሉ
ሲነገር ... ሲዘመር.. ሁሉም ይሰማሉ።
የማይጠፋ ብርሃን ስለሰጠኋቸው
ስሜን ያነሳሉ በየበኩላቸው።
ልብ እንደሚነካ የሙዚቃ ቃና
በማነሳሳቴ በሰዎች ሕሊና
ሁሉም ይወዱኛል ያፈቅሩኛል ገና።
በዚያ በአሰቃቂው በክፉ ዘመን
የነፃነት ትግል እንዲያገኝ ብይን።
ለተበደሉና አቅም ላነሳቸው
ጠበቃቸው ሁኜ ስለቆምሁላቸው።
የማያስታውሰኝ የማይጠራኝ የለም
ነገም...ከነግ ወዲያም፣ ዛሬም. ..
ለዘለዓለም።
አሌክሳንደር ፑሽኪን
ትርጉም አያልነህ ሙላቱ
@sabawiyan_gtim
@sabawiyan_gtim
@sabawiyan_gtim
@sabawiyan_gtim
@join & share
@join & share
@join & share
@join & share
5 931
ፈጣሪና ምኞት
"""""""""""""""""
"ካንቺ ጋር አድሬ ሲነጋ ልሙት
ለሞት አይደለም ወይ የተፈጠርኩት"
ብሎ የተመኘው ያአፍላ ወጣት
እግዜር በጥበቡ
ምኞቱን ሰማና ካንቺ ጋራ አድሮ
ጠዋት ሞት ቢመጣ ሊገለው ከጅሎ
"ና በል ልገልህ ነው" ሞት ሲለው በቁጣ
ከጭንሽ ውስጥ ገብቶ
"አልነጋም" አያለ እስካሁን አልወጣ!
ምነው ባልተመኘ
ጭንሽ ጭንቅላቱን ፈፅሞ ባይበልጠው፤
ላንቺ ልሙት ብሎ
ምላስ ባይዘረጋ ድንገት ባያደልጠው፤
ይኸው እዳ ገባ
ከጭንሽ ሲወጣ ሞት ነው 'ሚጠብቀው...!
አያድርስ
አያድርስ ነው እንጂ
መቼምአንዳንድቀን
ፈጣሪና ምኞት ይገጣጠሙና
በዋዛ ያወራናት
ገዝፋ ትገኛለች ፈጣሪ ያደምጥና።
አያድርስ
አያድርስ ነው እንጂ
በምላስ ወለምታ
እጅግ ተቀይሞ ከጠመመ እግዜሩ
በቁጭ የሰቀሉት
ማውረድ ይዳግታል ቆመው ቢንጠራሩ...!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
#ወዲያ_ሽሽ_ይለኛል!
© ሲራክ ወንድሙ @siraaq
.
ኑረት ሲረክስብኝ ፥ ሲሆን እንደ እቃ 'ቃ ፣
አዎን ያስፈራኛል ፥ የዘመን አታሞ
.................... ፥ የዘመን ድለቃ ፤
የድግግሞሽ ሰልፍ ፥ የእሽ ፡ ክርክሪት ምልዓት ፣
ሰው ሆኖ ተኝቶ ፥ ትል ሆኖ እንደመንቃት ።
ንጋት አድባር ሆኖ ፥ የሀገር ጌጥ የሀገር ዳስ ፣
ጀምበር በሰረቀ በአመሻሹ ፈለግ ፥ እንደካህን መርከስ ፤
እንደምኩራብ ከብሮ ፥ እንደ እንትን መንኳሰስ ።
አዎን ያስፈራኛል...
ወዲያ ሽሽ ይለኛል...
ወዲህ ግድም እሩጥ ፣
ወዲህ ግድም አምልጥ ፤
ወዲያ ጥግህን ያዝ ፥ ይለኛል ይለኛል ፤
የዘመኑ ቅኔ የዘመኑ መንፈስ ፥ መንን ያሰኘኛል ፤
ወዲያ ሽሽ ይለኛል ።
.............. | ። | ...............
ነሐሴ ፳፻፲፫ ዓ.ም
@yegetem32
@yegetem32
5 931
የኔ'ነት ሲጠፋ
""""""""""""""""""
ባለሁበት ህይወት
በቆምኩባት ምድር ፥በኖርኩባት ዓለም፤
ሁሉም የፈጣሪ
የኔ ነው የምለው፥ አንድ ስንጥር የለም!
ነፍሴ የፈጣሪ፤
አካሌ የፈጣሪ፤
ዕድሌ የፈጣሪ፤
አፈር የሚበላኝ ፥እኔ እንደሆንኩ ቀሪ!
(እናማ...)
እናማ ብታመም
ክፉኛ ክፉኛ ፥አጊንቶኝ እንቅፋት፤
ልቤ ሰተት ስትል
በአውራ ጣቴ ልክፍት፥ በህመሙ ብዛት፤
ለነፍሴ ብላችሁ
ፀሎት ስታሰሙ ፥ለደዌዬ ጥሪ፤
"እግርህ ታሟል" በሉት
እያሳሰባችሁ ፥ለዛ ለፈጣሪ!
ያን ግዜ ነው የምሽር
እ.የ.ጠ.ዘ.ጠ.ዘ ፥ካሰቃየኝ ህመም፤
ሁሉም የሱ ናቸው
ከመላ አካላቴ፥ የእኔ ምንም የለም!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run @HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
5 931
#ስጋት_የገባው_ልብ
...................©ሲራክ ወንድሙ
እቱ የኔ ገላ ፥ የመንገዴ ማሾ ፣
የፍቅሬ ጥንስሱ ፥ ብቅልና ጌሾ ፤
እቱ የኔ ሰፈፍ ፥ የነብስ ወንዜ ቅጂ ፣
ናፍቆትሽ አስዳኸኝ ...
ፍቅርሽ አስለቀሰኝ ፥ እንደመንፈቅ ልጂ ።
.
ሚሻልም ቢመጣ ፥ አንድ አይስቴው ተኳሽ ፣
ፈሪ አይናቅም ፥ ውጭ ውጩን 'ማያመሽ ።
ተይማ ፥ ተይማ ፣
ተይማ ፥ ተይማ ፣
ጣል ጣል አታርጊኝ ፥ እንዳደፈ ሸማ።
................. // ................
@yegetem32
@yegetem32
5 931
#የግርጣት_ሰላምታ
© ሲራክ ወንድሙ @siraaq
.
ለደባ እሩቅ ናት - ዝምታ ነው ቤቷ - ሰቀላው ሰገነት ፣
ጅራፏ ውሽንፍር - ቁጣዋ ሞት ጠሪ - የዘላለም ግርጣት ።
የአድማስ ማዶው - ቅላት ምስሏን ዘዋሪ ፣
ግዛቷ ገመገም - የመብረቅ ስባሪ ።
ግልምጫዋ እቶን - የጉድ ቁና ሰፈፍ ፣
ሰማይ ከዋክብቱን - አጥምዶ ሚያረግፍ ።
የሸማዋ ጥለት - ቢሸመን በእግዜር እጅ ፣
ቢደወር ቢታጠብ - ቢሰጣ አርያም ደጅ ።
እሷ እንደው እሷ ናት - አይሞቃት አይደንቃት ፣
ዝም ነው አመሏ - አይዳዳትም ቅብጠት ፣
ጥለቷ ነውና -
ያ ቀስተ ደመና - የሰማይ መቀነት ።
"""""""""""""".........///////...... """"""""""""""""" #________ሲራክ_ወንድሙ
@yegetem32
@yegetem32
5 931
ጠይም ፀሀይ
"""""""""""""""""
አ
ያ
ች
ኃ
ት
ል
ኝ?
ለማይሞላ ቀኔ፥
ለማይጠግን ቅስሜ፤
ለማይሰምር ህልሜ፥
ለማይሽር ህመሜ...
ብዬ በደመደምኩ
እህህን አዚሜ ፥ተስፋዬ ቢረታ፤
አለሁልህ አለች
ዳመና ያልጋረዳት
ከሰማዩ ግድም፥ ጠይም ፀሀይ ወጥታ!
ጠየም...
ያለች...
ፀሀይ...
ዕንባዬን ልታደርቅ
የህመሜን ሲቃ፤
በተከዝኩበቱ
ከሀዘን ደዌዬ
በምስራቅ ፈንጥቃ፤
የዳመናውን በር
የጠቋቆረውን
በእጆቿ አላቃ....
በረጅም የእግዜር ጣት፥
የቁስሌን ቅ.ር.ፋ.ት፥
የእግሬን እንቅፋት፥
የህይወቴን ክርፋት፥
ልታሽረው ሽ...ታ ፥ በጨረሯ ብርታት!
ስትዳብሰው ልትውል
የህመሜን ቋንጃ፤
ወጣች ጠይም ፀሀይ
ፍልቅልቅ እያለች
ከአድማስ መጋረጃ፤
እሷ ስትፈነጥቅ
ቃኘሁ ጠረጠርኩት
የፈጣሪን መምጫ....
የዓለም
ዘላለም
የህመም መቋጫ...!
ጠየም...
ያለች...
ፀሀይ...
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@Run_Viva_Run
@HAKiKA1
@HAKiKA1
@HAKiKA1
