en
Feedback
የግጥም ምሽት በቴሌግራም

የግጥም ምሽት በቴሌግራም

Open in Telegram

ይህ ቻናል ከተለያዩ መጽሐፍት የተቀነጨቡ ግጥሞች የሚቀርቡበት እንዲሁም ወርሃዊ የግጥም ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው ግጥም ለምትወዱ ሁሉ...የራሳችሁን ሙከራም የምታቀርቡበት ነው ለማንኛውም አስታየት @Nirvana134 እንዲሁም @simba23 ላይ አለን ፧ @yegetem32

Show more
5 931
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-4030 days
Posts Archive
ትዝብት """"""""""" ከማዕዱ ከለከሉኝ፥ በዓይኔ አይቼው እየገፉኝ... ተገባብዘው በሉ እነሱ፥ ቁራሽዋን ግን ለኔ ነሱ... በልተው ጠግበው ከምግቡ ያንን ሁሉ ሊያስተርፉ፤ ዓይናቸውን ቢርባቸው፥ከኔ ትዝብት አተረፉ!!! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

እፉ - ዬ - ገላ
``````````````
©ሲራክ ወንድሙ . ከጊዜ የዛፍ ጥላ ከቀን ቤልጅግ ቀላ' ቃታ ሳይታከል ሳይጠለል አካል ያቺ እፉ - ዬ - ገላ ፥ ያቺ እኔ የምወዳት መውደድ ነፋስ ገፍቶ ፥ ከእኔው ዳር አቆማት ወደ እኔው አመጣት። ግና ... ነፋስ ያደቆናት ምታቃጥል ገላ ፣ ደብር የለሽ ቀዳሽ ፥ የልቦራ ጥላ ፤ የመምጣቷ ሸማ ፥ ሞቆ ሳያሞቀኝ ፣ የመሄዷ ጨንገር ፥ ሸንቁጦ ሳይገርፈኝ ፤ መምጣቷ ሳይደላ ፥ መሄዷም ሳይከፋ ፣ ወረት 'ሚባል ነፋስ ፥ ድንገት ይዟት ጠፋ። .............. © ሲራክ ወንድሙ @yegetem32 @yegetem32

የሞት ብስራት (ኩኩሉ) """""""""""""""""" ዓለም ሳታባባው፥ ለነፍስና ስጋው፥ ለሰዎች ሆድ ጥጋብ፥መሰዋቱ አንሶ፤ አንዱ የዋህ ዶሮ "ሞት ወዴት ነህ?" አለ "ኩኩሉ" በማለት፥ ካሸለበው ዕንቅልፍ ፥አራጁን ቀስቅሶ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

ጉዞ """" ሀሳብሽን መርምሪ፤ ቀልብሽን መትሪ... ልብሽና እግርሽ፤ ይገጣጠሙልሽ... እንኳን ከአድማስ ማዶ፤ ልትርቂ ከቶ... ስንዝር አትሂጂ፥አስቢበት ፍቅሬ፤ መድረሻን ማወቅ ነው፥የመሄድ ጅማሬ...! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

ልንገርሽ ##### ልንገርሽ አንቺዬ ትንሽ ካሰብኩበት፥ነገር በኔ ይብሳል፤ ገጣሚ ደንቡ ነው ከአንገቱ ጎንብሶ፥ስንኝ ይቀልሳል። ስንኝ ሌላ አይደለም አንቺው ነሽ ስንኟ፥በኔ ድርሰት ዓለም፥ እሩቅ አታስቢ ይኸው ካንቺ ውጪ፥ሌላ ማንም የለም። ቢሆንም......ቢሆንም ልንገርሽ አንቺዬ ልብ ብለሽ ስሚኝ፥ብትሰሚ ይበጅሻል፣ አንቺ ካነሽበት ብዕሬ ክፉ ነው፥አሳንሶ ያይሻል፤ ከስንኝ ወደ ሀረግ ከሀረግ ወደ ቃል ከቃል ወደ ፊደል ቁልቁል ያ ወ ር ድ ሻ ል። አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

እያነቡ እስክስታ """""""""""""""""" የድል ፍሬ ተብሎ፥ ሰው ወንድሙን ገሎ፥ የእናት የጭንቅ እንባ፥ ሰርክ እየዋለለ፤ ለበርጩማ ሽሚያ እጅን እጅ በልቶ፥ሽለላ ፉከራ ቀረርቶ ካማረ፤ መፀፀቱን ትቶ በወንድሙ ሬሳ "ተጋዳላይ" ብሎ፥ድሉን ካከበረ፤ ከቶ መች አጠፋ? ያኔ...ያኔ....ያኔ ቃዬል በአቤል ላይ፥ ጀግንኖ ነበረ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

ልማዳዊ እምነት """"""""""""""""""" እንገናኝ ነበር ካሞቀችው ቤቷ ባጥር ተ.ዛ.ል.ዬ፤ ፍቅር የምሰጣት ፍቅር የምትሰጠኝ ውዷ ውሽማዬ። . . (ዛሬ አስከፋችኝ) . . ዛሬ አስከፋችኝ በለመድኩት ሰዓት በአጥር ተንጠልጥዬ፤ እየተክለፈለፍኩ በናፍቆት ወላፈን እሳት ተንቀልቅዬ፤ ሸፈን ሸሸግ ብዬ እንዳልዋረድም ባኖርኩበት ቀዬ...! . . (በእርምጃም በሩጫም) . . በእርምጃም በሩጫም ፈጥኜ በቻልኩት ብታደም ከቤቷ፤ የቀን ቀን ድርጎዬን የጭኗን ስር ሙቀት እንቅር አርጋ ተፍታ፤ የታመነላትን ሰርክ የፍቅሬን ፅናት አሽቀንጥራ ትታ፤ ልቤ ሰበረችው በለመድኩት ሰዓት እያመነዘረች ከባሏ ተኝታ! 😊😊😊 ተማኙ ውሽማ የግጥሙ ሀሳብ... #abrham_mulu_sew የግጥሙ ፀሀፊ አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

sticker.webp0.26 KB

የቁራ መልእክተኛ """"""""""""""""""""" ዓለም ስትሞላ፥ በጥፋቱ ውሃ...፤ ከኖህ መርከብ በቀር፥ ሁሉም ከተበላ! የታላከ ጊዜ ...፥ ከመርከቡ ወጥተህ ፥ተመልከት ተብሎ፤ ያ በራሪ ቁራ... ምን አማሎት ቀረ፥ከእምነት አስጎድሎ? አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

የሞት መልዕክት """"""""""""""""""""""" በሉ እንጓዝ ወደ ሰማይ ነፍሳችሁን አንጠልጥሉ፤ ተራ ተራ ይዛችሁ በጊዜ እስር ተቅጠልጠሉ፤ የስጋ ፍቅር ይለፋችሁ ንዋይ ብሩን በሉ ጣሉ፤ እግዜር ጉቦ ከቶ አይሻም ሀቂቃ ነው ብቻ ውሉ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

ናፈቀኝ ሀገሬ """"""""""""""" ብዕሬን ሸክፌ ሀሳብ አጠንፍፌ ቃላት አጣልፌ ሄድኩኝ ከወረቀት፤ ቅኔ ልደረድር ግጥሜን ልሰድር ከመድብሌ ልከት! ሀገር ብዬ ጀመርኩ ሀገሬን ላልጨርስ ጦማሬን ከትቤ፤ ዋ ብሎ አስፈራራኝ ከራሴ እያጣላ አመንትቶ ቀልቤ! . . ለምን አልሽ አለሜ? . . እንደምን ይፃፋል ስለሀገር ግጥም ጦቢያ ይሉት ቅኔ፤ ሁሉም አስሮ ይዞት ዘር የሚሉት ብሂል የአስተሳሰብ ጠኔ፤ የአባ ጃርሶ ቁጣ የአቶ መርዕድ ዱላ የት አለና? ዛሬ፤ የፅዮን ስፍስፍ ልብ የከድጃ ገር ነፍስ ርቆ ሄዶ ከኔ፤ የትርንጎ ውበት የአለሚቱ ምክር ጠፍቶ ከዘመኔ፤ እንደምን ይፃፋል ሀገር ይሉት ግጥም ሀገር ይሉት ቅኔ! . . ጉድ አለ በሀገሬ . . አዬ ጉድ ነው መርዶ ሰው ከራስ ተሰዶ ከእምነቱ እረክሶ፤ እሩቅ እሩቅ ሲሄድ እሳትን ሲላመድ እያደር ተናንሶ፤ ስክነት ይሉት ጠፍቶ ሰው እብሪትን ሽቶ እሳትን ተላብሶ፤ አባት አንገት ደፍቶ እናትን ሆድ ብሷት አይኖቿ አልቅሶ፤ እህት በእህቷ ወንድም በወንድሙ ጦር ሰይፍ ተማዞ፤ መከባበር ጠፍቶ ልጂት እናት ንቃ ልጅ አባቱን አ'ዞ! ሰው በቁም ታርዞ ሲሄድ ሲፈረጥጥ ቁልቁሉን እሩጫ የእውር ድንብር፤ እንዴት ከግጥሜ ላይ ጎላ ብላ ትፃፍ ቅኔ ያላት ሀገር? . . እንዴት? .....እንዴት? . . ወገን ተከፋፍሎ እገደል ተምሎ በዘርና በጎጥ፤ በነጮች ሰበካ ከሀገር ተሰዶ በድኑን ሲቀመጥ፤ በዳንኪራ ፈዞ ቁሙን ተገንዞ ከሀገር ሲፈረጥጥ፤ እና እንዴት ተብሎ ስለ ሀገር ይፃፍ ሀገር ትቆላመጥ? . . ተመልከች ዓለሜ . . ሀገር ማለት ሰው ነው ሰው ነው ሰው ነው ሀገር፤ ሰው ከሌለ የለም ሀገር ይሉት ወሬ ሀገር ይሉት ነገር! ሰብዕና ጎድሎ በሌላ ተደልሎ በቁም ተቀምጦ እሩቅ ከከነፈ፤ ምን ተብሎ ቅኔ ምን ተብሎ ግጥም ስለ ሀገር ተፃፈ? . . (እናማ) . . ስለሀገር ያሰብኩት ብዙ የተለምኩት ባሸተው ሰንፍጦ ብቀምስ ጎመዘዘኝ፤ ከእውነቱ ተውኩና ከተስፋ አጠቀስኩኝ ብዕሬን አነሳሁ ከወረቀት ልቀኝ፤ ሀሳቤን ሳሰፍር የሚል ግጥም ፃፍኩኝ ሀገሬ ላይ ቆሜ ሀገሬ ናፈቀኝ! (ሀገሬ ናፈቀኝ) አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

በእኔና በአንቺ """"""""""""""""" በፍቅር ቋጠሮ፤ ውስጣችን ተፋቅሮ! አንቺ እኔን ከጅለሽ እኔ አንቺን ከጅዬሽ፥ የተማመንን ቀን፤ ልባችንን አይቶ ልኬቱን ተረድቶ፥ ፍቅር ስቆ ነበር! ውሎ አድሮ . . ውሎ አድሮ ውዴታ ከራርሞ፤ ነገራችን ጠሞ፤ እምነታችን ቀሎ! ጥርጣሬ ሲያይል፤ እውነታችን ሲቀል! ከቆምንበት ገደል ሽብርክርክ እያለ ሳይሻገር ሲቀር፥ ፍ.ቅ.ራ.ች.ን ዘሎ፤ ይገርምሻል ውዴ ጥላቻ በኛ ላይ፥ ተሳለቀ ቆሞ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

ለጥጥጥ በይ ሀገሬ """"""""""""""""""""""""" ጎዳና ቢወጡት የሰው ፊት ይጠብሳል፤ እሰው ቤት ቢሄዱት መጡብኝ ይተርፋል፤ ተከናንበሽ ተኚ ችግር በዕንቅልፍ ያልፋል! ለሽሽሽ... ተኚ ሀገሬ . . በገሀዱ ዓለም በህይወት ረመጥ እሳት አትፈጂ፤ በነፍስ አውጪኝ ኑሮ በኑሮ ስንክሳር ልምጭ አትቀጪ፤ ላይሞላ ላይጎድል እግር ላያወጣ ዝም ብለሽ አትሩጪ፤ ስንፍና አይደለም የድካም ዕድሜሽን በዕንቅልፍሽ ፍጂ! ተኚ ሀገሬ ለሽሽሽሽ.... . . ለምን? አትበይኝ ተኚ ዓለምሽን ዝም ብለሽ አትሩጪ፤ በይ ተኚ የምልሽ ስንፍና አይደለም የድካም ዕድሜሽን በእንቅልፍሽ ፍጂ፤ ሽሮ ሲጠርብሽ በዕንቅልፍሽ ተኝተሽ በህልም ቅቤ ጠጪ፤ ደም ግባትሽ ይሙላ አመድሽ ይራገፍ ወዘናሽን አምጪ፤ ልጅሽ ሲሞትብሽ በዕንቅልፍሽ ሜዳ ሙሾሽን ተይና እልልታ አቅልጪ! ተኚ......አትሩጪ ለሽሽሽ.....እረፊ ሀገሬ.......እረፊ፤ በህልም አለም ጉዞ በዕንቅልፍሽ ኬላ ከእውነታው ጥፊ፤ ሰው ለምድር ሲሮጥ አንቺ ጋደም ብለሽ ከሰላም ክነፊ፤ ትተሽ አንኮራፊ! (ተኚ ሀገሬ ተኚ) (እኔ ልሙት ስልሽ) ቀልብን አሳምኖ ከሰው ጓዳ ደርሶ የምን መቀላወጥ፤ ለቀንድ አውጣ ኑሮ ብዥታ ለሞላው ደርሶ የምን ማማጥ፤ ሸውዶ አታሎ በዕንቅልፍ ነው ማምለጥ፤ ለጥጥጥጥ.....! (ተኚ ሀገሬ ተኚ) ጎዳና ቢወጡት የሰው ፊት ይጠብሳል፤ እሰው ቤት ቢሄዱት መጡብኝ ይተርፋል፤ ተከናንበሽ ተኚ ችግር በዕንቅልፍ ያልፋል! ችግርሽን በዘዴ በብልሃት ማለፉ አያስብል ዕንቅልፋም፤ ስጡኝ ስጡኝ ብለሽ እንደ የኔ ቢጤ የሰው ቤት ከመሳም፤ ተኝተሽ ማርፈድሽ ተኝተሽ መዋልሽ ተኝተሽ ማደርሽ ከሰው ዘንድ ቢጠላም፤ እኔን አምነሽ ተኚ የምልሽን ስሚ ጭንቅ ሀሳብሽ እንጂ ዕድሜሽ አይበላም! ለጥጥጥጥ ተኚ.... የሰው ልጅ ነው እንጂ አጉል ተሽኮርማሚ ለዕንቅልፍ የሚገደር፤ ለችግር ብልሃት ከዕንቅልፍ የበለጠ ምንስ ሌላ ነበር? . . ሀገሬ . . እኔን አምነሽ ተኚ የምልሽን ስሚ አንድ ታሪክ ልንገርሽ፤ መተኛት ብሂሉን ስሩን ላስረግጥሽ! በአንድ ዘመን ታሪክ በእስራኤል ምድር እግዚአብሄር ተረሳ፤ ሆነ እንደ ዋዛ! ክፋትና ተንኮል ደባ ምቀኝነት በአንድ ላይ ገነነ፤ ደግነት ቅጥ አጥቶ ሴራ ተቆነነ! አተርፍ ባይ ናኘ፤ ከዛ ህዝብ መሀል 3 ንፁህ ተገኘ! ጊዜ ብሎ ብሎ ተግሳፅና ቁጣ ሲመጣ ከእግዚአብሄር፤ በባቢሎን ነገድ በሰራችው ሀጥያት ተቀጣሽ እስራኤል! ናቡከደነጾር ህዝቡን ምርኮኛ አ'ርጎ ብዙዎች ሲጠፉ፤ ነብዩ ኤርሚያስ ባሮክ፣ አቤሜሌክ በንፁህ ልባቸው ከጥፋት ተረፉ! "እንደምን ተረፉ?" ለምትይኝ ነገር፤ መላዋ እስራኤል በፈጣሪ ተግሳፅ ጥፋት ስትበጠር፤ ባሮክ አቤሜሌክ ከዚህ ያዳናቸው ግማሽ ክፍለ ዘመን ዕንቅልፋቸው ነበር። 66 ዓመት የክፋቱን ዘመን በዕንቅልፋቸው ፈጁ፤ ከዕንቅልፍ ሲባንኑ እንደዛው ነበሩ ቅንጣት አልገረጁ! አየሽው ሀገሬ የቀን ጅብ አጅቦሽ ጥርሶቹን አስሎ ደንግጠሽ ብታዪ፤ ፈጣሪን ተማምነሽ ለእንቅልፍ... ቅዥትሽ ጎንሽን ከመደብ አ'ርገሽ ብትተኚ! የተማመንሽበት ፈጣሪ ለአመሉ እንደ በቆሎ እሸት ሽፍን ሽክፍ አ'ርጎ ዙሪያ ከቦ ሲያጅብ፤ ከእንቅልፍሽ ስትነቂ ለጋ ሆነሽ እንጂ ዕድሜሽ ከቶ አይጃጅም! ተኚ ተኚ ተኚ አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

ሰቀቀን """""""" (ዳግም...ደግሞ...ደግሞ) በእሳት አይቃለድ ረመጥ የጠበሰው፤ በእህል አይጫወት እርሀብን ያየሰው! እንዲህ ነው ሰቀቀን ያለፈ ጠባሳ ትዕቢትን የሚያቀልጥ፤ እባብን ያየ ሰው በመንገዱ ሁሉ ይሸበራል በልጥ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

ርክም ራግ """""""""""""" አይገርምሽም እቴ "ብልህ ሁን!" ብለውኝ የሚያስብ አርቆ፤ ሀሳቤ ሁሉ መጥቆ፤ አያያዜ ረቆ....! ሄዶ .... ሄዶ .... ሄዶ .... ቂላቂል ሆነና ይህ አጉል ዕድሌ፥የተሰጠኝ ዕጣ፤ መልሶ አስታዘበኝ የሩቁን ሳማትር፥የስር ስሩን ባጣ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

አሜን """"""" ለቆፈነ ገላው ከተንቀለቀለው ረመጥ እሳት ጭሬ፤ ጎኑ አድርጌለት ቆፈኑ ቢለቀው "እግዜር ይስጥሽ" ብሎ መረቀኝ አጅሬ... "አሜን" ብዬ ብለው መዳፌን ዘርግቼ ለምርቃት መልሱ፤ ይኸው ከዛ ወዲህ እሳት በእሳት ሆነ የዕድሌ ምሱ...! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) ለአስተያየትዎ @Run_Viva_Run @HAKiKA1 @HAKiKA1 @HAKiKA1

#አልሃምዱሊላሂ_ደህና_ናት . ገጣሚ ፦ አብርሃም ፍቅሬ አንባቢ ፦ ሲራክ ወንድሙ @siraaq @yegetem32 @yegetem32

#እርጥባን ገጣሚት ፦ አረጋሽ ሰይፉ አንባቢ ፦ ሲራክ ወንድሙ @siraaq @yegetem32 @yegetem32