en
Feedback
የግጥም ምሽት በቴሌግራም

የግጥም ምሽት በቴሌግራም

Open in Telegram

ይህ ቻናል ከተለያዩ መጽሐፍት የተቀነጨቡ ግጥሞች የሚቀርቡበት እንዲሁም ወርሃዊ የግጥም ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው ግጥም ለምትወዱ ሁሉ...የራሳችሁን ሙከራም የምታቀርቡበት ነው ለማንኛውም አስታየት @Nirvana134 እንዲሁም @simba23 ላይ አለን ፧ @yegetem32

Show more
5 931
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-4030 days
Posts Archive
#የነፍስ_እሪታ ገጣሚ ፦ ኢዛና መስፍን አንባቢ ፦ ሲራክ ወንድሙ @siraaq @yegetem32 @yegetem32

#የሌት_ማህሌት . ገጣሚ ፦ በዕውቀቱ ስዩም አንባቢ ፦ ሲራክ ወንድሙ @siraaq @yegetem32 @yegetem32

............. ስንቅና ማህሌት ............. _ © ሲራክ ወንድሙ _ . እኩለ ሌሊት ላይ - መርዶ እንዳባተተው ፥ እኩይ ዜና ሰምቶ - ቀልቡ እንዳቃተተው ፥ በሀሳብ ናውዤ...... በምናብ ተጉዤ..... ሽሚያ እንደበዛበት የሰንበቴ መና ፥ በናፍቆትሽ ሳሳው ፥ በትዝታሽ ጠናው ዘንድሮም እንዳ'ምና። # እንደኮከብ ድምቀት - እንደጥቢ ፍካት ፥ እንደብርሃን ዥረት - እንደሞገድ ንጣት ፥ የሚያበራ አይንሽን - የተራበ አይኔ ፥ ከስጋው ተኳርፎ - ገብቶ ከምናኔ ፥ አለም እንደናቀው - አለም እንደናቃት ፥ እንቅልፍም በኔ ላይ - መሪር ኩርፊያ አላት። . ኦኦኦኦኦ!.. . ሰማኒያ አሀዱ ፥ የቅዱሳን መፅሀፍ - አንዱ ሆኖ በአንዱ ፥ ከመስኮቱ ምዕራብ - ከማዕዘኑ ቀዬ ፥ ይታየኛል ድርድር - ከወደ ግርጌዬ ። . አሁን.... ዘራሰብ በልማድ ከትንሽ ሞቱ ጋር ግብግብ ገጥሟል። እኔ... ትንሽ ህመም አማኝ ፥ ትንሽ ሞት ረስታኝ ፥ ፍቅርሽን እያልኩኝ - እምከነከናለሁ፥ በዚህ ድኩም ሌሊት - አንቺን አስባለሁ። . ኤዲያ! . የትዝታን ክቡድ - ቀንበር ፣ የናፍቆትን ግዙፍ - ሞፈር ፣ አጥምጄ በላዬ - በምኞት ቤት ድግር፣ በኑረት ክንዴ ላይ - እየወዘወዝኩት ፣ የእምባዬን ስል ጅራፍ - እያወናጨፍኩት፣ የነብሴን ውብ ጋራ - ብራብሽ አረስኩት ። . እህ.... . እኔ ቀድሶ አዳሪ - የደብር ሲምቢሮ ፣ አንች የባላባት ጭራ - የከበርቴ ሮሮ፣ እንደ የኔታ ጋቢ - ውብ ገፅሽ ሳያድፍ፣ በሳቅሽ ቅላፄ ቅኔ ሳይዘረፍ፣ ምንጯ ስር ብቅ በይ - እኔም ከዛው አለው፣ ለሀሴትሽ ጉቦም - ዋሽንቴን ይዣለሁ። . እምም... ኩርማን ለማደሪያ - ሰው አጥር ታክኬ ፣ እንደ ፀሎት ምልጃ - አይኔን ወዲያ ልኬ፣ የህዝቡን መማረር - ይሁን ብዬ ድኬ፣ እንደ በላኝ ቅማል - በደል ሲያሳክከኝ፣ ቀስሳለሁ ብሎ ደብር መቀላወጥ እንደ ውርደት ታየኝ። . ኦኦኦኦ!.. . ያቺ ከሲታዋ - ውብ አኩፋዳዬ... ግብር እንደጠሩት - እንደ ሆዳም እረኛ፣ ፍርፋሪ ሞልቷት - ጠጋግባ በማኛ፣ ጀምበር ስታቅላላ - ከደብር ብትደርስም፣ ለሚያያት ነው እንጂ - እንደእኔ ለኖራት .. በጭራሽ አትደንቅም። . ለምን?? . እንደጭን ስር ቅማል ፣ ሀሜት ያሳክካል ። አሽሙር ያሳምማል። . አምና በዚህ ጊዜ - ከዚያ ከአረን-ጓዴ፣ ግራሩ ስር ቆሜ - በአርባ ጦም ሁዳዴ፣ እህል ውሃ ሳልል - አይቼሽ ለመግደፍ፣ ከእግዜር ጋር ቅያሜ - ለመያዝ ስጣደፍ፣ ለውብ አይንሽ ብዬ - በሀፂያት ታምሜ ፣ ከእርኩስ ሀሳብ ዳራ - ምልዋጤን ደግሜ፣ እባብ ሆኜ መጣው .... አባትሽ ገደሉኝ - አፈር ልሼ ነቃው። . ደግሞም በነጋታው.... . ሰው መሆን ውበቴን - ፍቅርሽ ሲያስመንነው ዳግም እርግብ ሆኜ አጥርሽ ላይ ብቆም የእረኞች ወንጭፍ - ቃታው የከረረ ፣ ጠጠር ተወርውሮ - አክናፌን ሰበረ። . ኦኦኦኦ.....! . ሰማኒያ አሀዱ ፣ የቅዱሳን መፅሀፍ - አንዱ ሆኖ በአንዱ ፣ ከመስኮቱ ምዕራብ - ከማዕዘኑ ቀዬ፣ ይታየኛል ድርድር - ከወደ ግርጌዬ። . አሁን..... . ወዲያ ወዲያ ወዲያ ወዲያ ከአምባው ላይ፣ ወዲያ ከደብሩ ላይ፣ ወረብ አሰካክሮት - ደወል አስደንግጦት ፣ ከቤተ መቅደሱ - ደርሶ የሚሸፍት፣ ይሰማኛል ለእኔ - የሌ'ቱ ማህሌት፣ የዲያቆናት ዜማ - የካህናት ፀሎት። ዜማው ምጥን ያለ እንደድምፅሽ ቃና ፣ እንደወፍ ዝማሬ - እንደመላዕክት ዳና። ጥፍጥ ፣ እርግት ያለ - እንደ እንደአይንሽ ብርሃን ፣ ኑረትን የሚያሞቅ - የነብስ ሀሴት ኩርማን ። . እናልሽ.. . አሁን በዚህ ሰዓት.... አሁን በዚህ ቅፅበት... የምኩራቡ እጣን - በሰመመን ሸቶኝ፣ እጅብ ያለ ጉሙ - ሲንገዋለል ታይቶኝ፣ የወረቡ ስምረት - በቁሜ አስክሮኝ፣ የቅዳሴው ዜማ - በመዳፉ ዳሶኝ ፣ ከድኩም አልጋዬ - ፈገግታሽ አብርሮኝ ፣ ካልጠራሁት አለም ከኖርኩበት ቀዬ - አድማስ አሻገረኝ። . እና . ደብሬን ክጃለሁ - ደብር ነሽ ለነብሴ ፣ ቅዳሴም ትቻለሁ - አንቺው ነሽ ምላሴ። . እናም ..... . እንደየኔታ ጋቢ ውብ ገፅሽ ሳያድፍ ፣ የእድሜሽ ጀምበር ጠልቆ ውበትሽ ሳይረግፍ ፣ በሳቅሽ ቅላፄ ቅኔ ሳይዘረፍ ፣ ምንጯ ስር ብቅ በይ እኔም ከዛው አለው ፣ ለሀሴትሽ ጉቦም ዋሽንቴን ይዣለው። ////////////___ ስንቅና ማህሌት ////////// _ _ © ሲራክ ወንድሙ ____ ታህሳስ ፳፻፲፫ ዓ.ም @yegetem32 @yegetem32

#አትሟት © ሲራክ ወንድሙ . መሬት የሚጠርገው የቀሚሷ ጫፉ፣ በወንጌል ቢታሰር የሚቀድስ አፉ ፣ ምናልባት እዚህ ቤት... ፀሀይ ፈገግታዋን የተሻማ ሁሉ ፣ ከፈገግታ ጀርባ መከልከል እንዳለ የነገራት ውሉ ፣ ባይገባው ነው እንጂ... እስኪ አትሟት ይህቺን... ለቆረባት ሁሉ እህትነት ይዟት ከመጣው ብትቆርብም ፣ እሷ ቀሚሷን ነው ሳቋን አትሰስትም። ................... //////.................... ሲራክ @siraaq < የብርሃን መንገድ > @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

አጭሬ ፭ የአጫጭር ግጥሞች ስብስብ . የገጣሚ :- በዕውቀቱ ስዩም የገጣሚ :- በረከት በላይነህ የገጣሚ :- ዲበኩሉ ጌታ የገጣሚ :- ኤፍሬም ስዩም .......... #እና የገጣሚ :- መዘክር ግርማ ግጥሞች ተካተውበታል አንባቢ ሲራክ @siraaq @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

አጭሬ ፭ የአጫጭር ግጥሞች ስብስብ . የገጣሚ :- በዕውቀቱ ስዩም የገጣሚ :- በረከት በላይነህ የገጣሚ :- ዲበኩሉ ጌታ የገጣሚ :- ኤፍሬም ስዩም .......... #እና የገጣሚ :- መዘክር ግርማ ግጥሞች ተካተውበታል አንባቢ ሲራክ @siraaq @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

#የለም ገጣሚ ቴዎድሮስ ካሳ አንባቢ #ሲራክ @siraaq @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

#_እንግዳዬ ገጣሚ ሚኪያስ ሽፈራሁ አንባቢ #_c ራክ @siraaq @yegetem32 @yegetem32

ቶጳዝዮን የግጥም ምሽት መድረክ ጥር 29/2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በላምበረት መናኸሪያ በሚገኘው አራራት ሆቴል መጥተው ይታደሙ በብዙ መግቢያ 100 ብር ብቻ ትኬቱን ለማግኘት በ 0911697738 ወይም በ0991847559 አልያም በ0921659660 ይደውሉ። ለተጨማሪ መረጃ @Run_Viva_Run ያናግሩኝ። እናመሰግናለን!

ገጣሚ እና አንባቢ ሲራክ @siraaq # @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

#ላለፈ_ክረምት ገጣሚ:- ጋሽ አበራ ለማ አንባቢ:- ሲራክ ወንድሙ @siraaq ....... ብቻ እንዲያው ብቻ እንዲያው ድፍን ቅል ሰበራ፣ ውኃ ማንቀዳበት ጥሬ ማንሰፍርበት የልጅ ቢጤ ስራ መውደድም አንዴ ነው መጥላትም አንዴ ነው ሲያስለን የሚኖር ትዝብቱ ብቻ ነው። ..... @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

---- ምኞተ-አዳም ---- °°°°°° © ሲራክ ወንድሙ. 'አርብን ተደግፎ ፥ ያ ታላቅ ደራሲ ፣ ከተረጋጭ አፈር ...... ............. ጠፍጥፎ ቀራርፆ ትንፋሹን ለግሶ ፥ ለነብሴ ነጋሲ ፣ ባይሰጣት ህላዌ ...... ........... ቢገደው ፅማዌ እንደ ፅጌሽ ቅጠል ፥ ዳሰሳሽን ለምደው ፣ ንጋትን በማምለክ ........... ............ አለንጋ ጣትሽን እንደሚናፍቀው ፣ በርሽ ላይ ነበረ - መብቀል የምመኘው። አዬዬዬ.....አለ 'አዳም ! -------- //// //// //// /// ......... ሲራክ @siraaq . @yegetem32 @yegetem32

_ ይኸው ነው _ © ሲራክ ወንድሙ . ያ ክፉ አመሏ ከሰው .... ከባህል ልማዷ ባራራቃት ማግስት እሷ እሷን ሳትሸት በሚወስዳት ወሃ ልጫወት ያለች 'ለት ኒሻን የመሰላት ትንፋሽ ቆራጭ ቀላድ ወዲያ ሲሸመቀቅ እውር እድል አምና ገባች ከመቀመቅ ////////________////////// © ሲራክ @siraaq @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

#መሸ_ደሞ_አምባ_ልውጣ ግጥም :- ከብላቴን ጌታ አብዬ ፀጋዬ ገ/መድህን አንባቢ :- ሲራክ ወንድሙ @siraaq @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

ይድረስ ለውዳጄ ------------------ በማዶ ያለኸው ወዳጄ እንዴት ነህ? ሀቁን ለመናገር የመገናኛችን ጊዜው ርቆኛል በላከው ደብዳቤ መልዕክትህ ደርሶኛል ሀገር እንደምን ነው ብለህ ለጠየከኝ እ ብለህ አድምጠኝ ከወሬ ያለፈ የምነግርህ አ'ኝ ሠው ጨካኝ ሆኗል ከጥቂቱ በቀር ሳይደክም ይሰላራ ወንድሙ ለመቅ'ር ህሊናውን ስጯል ምኞቱን ለመሸመት የቃ ቅራቅቦ ዛሬም ሆዱው ይጮሀል ብፌ ሙሉ ቀርቦ በጥልቁ የማሰው የምኞቱ ዋሻ መዳኒት ታጣለት ክፋቱን ማርከሻ ፍቅር ለተባለው እሬት አብልተውት ካገር ሊወጣ ሲል ከድንበር ላይ ያዙት ፀሀይ እንደ ወትሮው እስራ ላይ አለችደና ሀኪም ሳታማክር መርፌ ትወጋለች ጨረቃም ጤናዋን እጂግውን ነች ኪዳንዋን ሳታፈርስ ወታ ትገባለች እናልህ ወዳጄ ሀሳቤን ስጨርስ መፀለይ ይሻላል እግዜር ቶሎ እንዲ'ርስ እናፍቅሀለሁ የልቤን ላዋይህ በል ደና ሁንልኝ ባካል እስካገኝህ!! ✍ ምህረት @yegetem32 @yegetem32

አንቺን ለመርሳት """"""""""""""""""" ጥለሽኝ ከጠፋሽ ከጠላሽኝ ኃላ ምን ያልሆንኩት አለ፤ ብዙ የለመደ መከረኛ ልቤ ሰርክ አንቺን እያለ፤ ከንፍስያዬ ጥግ ስቃይና ህመም እየጎነቆለ፤ ከእሸት እምነቴ ረመጥ እሳትን እየፈለፈለ፤ እንቺ ከሄድሽ ኃላ ምን ያልሆነው አለ? አንቺ ከሄድሽ ኃላ ጥለሽኝ ከጠፋሽ ጊዜው ከነጎደ፤ መከረኛ ልቤ እረሳሽ እያለ ብዙ ተላመደ፤ ሴቶችን ለመደ፥ ሲጋራን ወደደ፥ መጠጥን እያለ ባሰኘሽው ሰዓት ለትኩስ ስሜቱ ከጊዜ አረፈደ! ግና አንቺ የለሽም ሴቶቹን ብቀርብም እንዳንቺም አላገኝ፤ አልባብ እንሸት ብለው ከደረት የነፉት ሽቶ ሰነፈጠኝ! ኩላቸው አይደምቅም ሊፒስቲክ ቢቀቡ ካንቺ በልጦ የነሱ፤ ጭራሽ ያስጠላሉ አውሬ ያስንቃሉ መስለው ደም የላሱ፤ ያላንቺ ማን ሊገኝ ምድርን ቢያስሱ.. (ይገርምሻል ውዴ) አሁን በቀደም ለት ያስረሳኝ ይመስል እያጨስኩ ሲጋራ፤ አፌ በለሆሳስ ስላንቺ ውዳሴ ከራሱ እያወራ! ቁልቁል እየሄድኩኝ ጭሱን ስተነፍስ የማጉ'ት ትምባሆ፤ ከሰተሽ ከፊቴ በጭስ አንቺን ስሎ! ስትፍለቀለቂ፥ ስትፈነድቂ፥ ከኔ ስትቦርቂ! ጣልኳት ሲጋራዬን በእግሬም እረገጥኳት፤ መች በሱስ አጥምዳኝ ያጨስኩት ለመርሳት! (ይገርምሻል ውዴ) አሁን በቀደም ለት ዘው ብዬ ገባሁ ከገዳም ነሽ ጠላ፤ አንቅሬ ልተፋሽ መለኪያ ጨብጬ ልጋት ካቲካላ! መቼም እሳት አይደል አረቄ አወጣጧ ሙያ የገዳምነሽ፤ ከራሴ እርቄ በሁለት መለኪያ ከወኔዬ ስሸሽ! ልቤን እየሞቃት ነፍሴን እየሳትኩኝ አይኔ እየሰከረ የአንድ ያንቺ ሲገርመኝ ሁለት አንቺን አርጎ ያሳየኝ ጀመረ! ወጣሁ ስደናበር ብዙ ብትሆኚብኝ ከግድግዳው ሳፈጥ፤ የፍቅር አኩኩሉ ካንቺ ተደብቆ ወዴትስ ሊመለጥ? መች ሊያስጥለኝ ውዴ ድካም እንጂ ትርፉ ለሌላ መ.ጋ.በ.ዝ፤ ፍቅር ከገነነ መች ይስጥላል ሌላ? መች ያስጥላል ግዑዝ? አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

እዚጋ ደሞ ሌላ ትኩሳት """""""""""""""""""""""""""" ኧረ ጉድ ነው እናንተዬ......በስንቱ ጭንቅላታችን ስሜታችን ተነክቶ እንቻለው?.....የት እንሂድ?... ወዴት እንድረስ... ወይ አሰልፈው ይረሽኑን እና እንረፈው። ("ምን ሆንክ?" ትላላችሁ መቼም...) ኮሮናን ተዉት......ስራ መቀዝቀዙንም ተዉት.....ትምህርት መዘጋቱንም ተዉት.....የሀገር እረብሻውንም ተዉት.....ሰዉ በየክልሉ መሞቱንም ተዉት....አንበጣዉንም ተዉት!....እንደው ከላይ ከዘረዘርኳቸው አስጨናቂ ወሬዎች ትንሽ ፈታ ብንል ብለን የቲቪ ሪሞታችንን ይዘን ጋቢ ቢጤ ጣል አድርገን በየአልጋችን፣ በየሶፋችንና በየወንበራችን (ሰው ባለው ነው መቼም ) አረፍ ብለን ቲቪያችንን ስንከፍት ህሊናችንን እያገላበጠ የሚገርፍ ማስታወቂያዎች ጋ ገጭ እንላለን። አሁን የኔ አሙዋሙዋት አሙዋሙዋት ነው ወይ? ጉች ጉች ያለ ጡት አንድ ቀን ሳላይ.... ያለው ያገሬ ሰው እኮ በኛ ደርሶ ቁጭ አለ።(በእውነት)....የሪል ስቴቱ ብዛት ለጉድ ነው "ካሳንቺስ መሀል እንትን ሪል ስቴት ሌግዠሪ ህይወትን ይኑሩ ሺ አመት አይኖር....." ይላል አስተዋዋቂው ድምፁን ጎርነን ቀጠን እያደረገ።....ኧረ ወንድሜ 64ቱንም አመት እንዴት እንደሚያልቅ ጭንቆናል ዘረኛ ይድፋን፣ ኮሮና ይድፋን ገና አላወቅነውም። በቁማችን ግን ሰቀቀኑ እየገደለን ነው። ምን አይነት ቤት ነው የምታሳዩን እንቁልልጭ እያላችሁት ነው ደሀውን......ኧረ ተዉ ግፍ አለው ለኑሮዋችን ተዉን በGood morning ሻይ ቅጠል እና በዘኒት ቅባት ማስታወቂያዎች እኮ ነው የለመድነው ድንገት ምነው ሰቀላችሁን?....ቲቪ የገዛበትን ብር ብድር ሳይከፍል ህዝቤ ተሳቆ ....ለደስታ በገዛት ቲቪ ደሞ የባስ በእናንተ አፓርታማ እና ሪል ስቴት ይሳቀቅ እንዴ ሆኦኦ.... ወይ እዛው የናንተን ቅንጡ ኑሮ የምታሳዩበት ቻናል ለብቻችሁ ከፍታችሁ እዩ(ሀብታሞች)......እኛ ደሀዎቹን አታቁለጭልጩን ኑሮ የሚያቁለጨልጨን ይበቃል። አሁን በቀደም ጎረቤቴ የሆነ አንድ አባት ከህፃን ልጁ ጋ ሲያወሩ ጆሮዬን ጣል አድርጌ እሰማቸው ጀመር(ለነገሩ ጆሮዬን ጣልኩ አልጣልኩ የተፈሳችው የተገሳችውም ትሰማኛለች ኩታ ገጠም ከመሆኑ የተነሳ) ልጅ፦ አባቢ አባቢ ቦቦ ግዛልኝ.... አባት፦ አንተ ልጅ እንደገና ቁልቁል ሽንት ቤቱ ምን ሆነና አድገህ የለም እንዴ?(ፖፖ ያለው መስሎት ነበር እኔ እየሰማው በውስጤ በሳቅ ፍርስ) ልጅ፦ ኧረ አይደለም አባዬ ቦቦ ወተት ነው እነ ቸሬ...ቤቢ...ትርሲትም ተገዝቶላቸዋል አስቀምሰውኛል ይጣፍጣል አባት፦ ስንት ብር መሆኑ ነው? ልጅ፦ 15 ብር አባት ክው .....ስራ ሲሄድ ለትራንስፖርት አድርሳ የምትመልሰውን 15 ብር ልጁ ፉት ሲላት ታይቶት... አባት፦ በቃ የኔ ልጅ ለደሞዝ እገዛልሀለው ልጅ ሆዬ እንባው ዱብ ዱብ "ግዛልኝ ዛሬ ነው የምፈልገው..." አባትም ቆጣ ብሎ "ሂድልኝ አንተ ውሪ ...የምንም ጣፋጭ ለምዶ ሊባልግ ይፈልጋል እንዴ..." ሊመታው አርጩሜ ሲፈልግ ልጅ ፈርቶ ቁጭ ....አባት ውስጡ እያለቀሰ ላዩን ተቆጥቶ ልጁን አሳረፈው....ቢኖረውና ቢገዛለት ምንኛ ደስ ባለው ግን ዛሬ አንድ ወተት ቢያጠጣው ነገ ስራም መሄጃም አይኖረው፤ ስለዚህ የልጁን አምሮት በቁጣ ማብረድ ግድ ሆነበት። ስሰማቸው ስለነበር አቡሽ አሳዘነኝ ደሞዝ ሰሞኑን ስለተቀበልኩ ልገዛለት አሰብኩና አባቱ ፊት ብገዛለት አባትየው እንዳያፍር እንዳይናደድም ብዬ (መቼም ደሃ ብንሆንም ኩሩ አይደለን) እቅድ አቀድኩ.... አቡሽን ቤተ ክርስትያን ይዤው መሄድ እና ስንመለስ ያማረውን እገዛለታለሁ አልኩ። አባቱንም አስፈቅጄ ቅርባችን ወደአለው ሚካኤል ቤተ ክርስትያን ተያይዘን ሄድን ተሳልመን ገባንና ወደ ግንቡ ጠጋ ብዬ ፀሎቴን አድርሼ ጨረስኩ ወደ አንድ መቀመጫም ሄጄ አረፍ አልኩ። አቡሽ አሁንም ግንቡን ተለጥፎ ፀሎቱን ያደርሳል ካሰብኩት ደቂቃም ሲቆይብኝ ምን ብሎ እየፀለየ ይሆን የሚል ጥያቄ ፈጠረብኝ። ከዛ እሱም ጨረሰና ተያይዘን ወጣን ከዛ ጠየኩት"አቡሽዬ ምን ብለህ ፀለይክ?" በሚያሳዝን አይኑ ቀና ብሎ እያየኝ በቁምነገር እንዲህ ብሎ መለሰልኝ "እግዚአብሄር ወይ ቦቦ ግዛልኝ ነው ያልኩት" መንገድ ላይ እንደዛ ስቄ አላውቅም አቡሽም ቀና ብሎ እያየኝ ግራ ገብቶት ፈገግ እያለ"ምነው አብርሽ?" አለ። "ና ና ፈጣሪ ፀሎትህን ሰምቶሀል..." ወደ ሱቁ አመራን እዚጋ ደሞ ሌላ ትኩሳት ወገኔ አለቀ በጉጉት እሳት እሳት እሳት.....በሉልኝማ አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

#ከነዓኑ_ልብሽ ........ ....... ልቤ እግሬን ሾሞ ግዳጁን ሊፈፅም ወዳንቺ ይጓዛል ደረስኩኝ ስል ጊዜ ለምን እንደው እንጃ መንገዱ ይረዝማል ።።።።።።።። ማይታክተው እግሬ እንደው ብታይ ከአንድ ጥግ ቆሞ እረፍት ፍለጋ እንጂ ዘንግቶኛል ብለሽ አስቢ አሉሽ ደሞ ።።።።።።።።።።።። ባንቺ ሀሳብ ስሸሸግ በረፍቱ አ'ሳብቤ ያደረግነውን ነገር አንድ እንኳ ሳላስቀር በትዝታ ፈረስ የኋሊት ጋ..ል..ቤ ፀሀይዋን ሳስታውስ በዝምታ ስንቃጠል እንደ ቀትር ፀሀይ ዝናቡን ሳስታውስ ፊቴ ድቅን ይላል በእንባ ስንለያይ ።።።።።።።።።።። የትዝታው ፈረስ ሲመልሰኝ ጨክኖ በግዳጄ መሀል እረፍቴ አንድ ሆኖ በመንገዱ ርቀት በእግሬ ዝለት እረፍቱን ፈልጌ ምክንያት ብፈጥርም ዳግም ለመጋለብ ስሻ ፈረሱ ግን የለም ።።።።።።።።።።።።።።።።።። ለካስ እውነት አለ ተፃፎ ያደረ ተፃፎ የዋለ ልክ እንደ ሙሴ፤ ትዛዙን ተላልፎ፤ ከበረሃው ሲቀር ከነዓኑ ልብ'ሽን፤ መርገጥ አይቻልም፤ ከማየት በስተቀር ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። @yegetem32 @yegetem32