cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Fasiledes Students የፋሲለደስ ተማሪዎች

ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም

Show more
Advertising posts
900Subscribers
No data24 hours
-37 days
-3230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የተቋረጠውን የ12ኛ ክፍል ፈተና ለመውሰድ መስከረም 9/2016ዓ.ም ዩኒቨርስቲ የምትገቡ በመሆኑ ከወዲሁ ተዘጋጁ
Show all...
New Curriculum Grade 11 Biology Text Book
Show all...
"በፀጥታና በሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ከ18 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመፈተን ዝግጅት ተደርጓል" የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት በፀጥታና በሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ከ18 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ።በጎንደር፣ በጋምቤላ፣ በተለያዩ ማረሚያ ቤቶች 17 ሺህ 753 ተማሪዎችና በውጭ ሀገራት 300 ተማሪዎች ይፈተናሉ። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በሁለት ዙሮች መሰጠቱ ይታወቃል።ሆኖም በአማራ ክልል እና በጋምቤላ ክልል ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ ለሙሉና በከፊል ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች መኖራቸውን የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ በተለይ ለኢዜአ ገልፀዋል። በተለይም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሦስት መፈተኛ ጣቢያዎች ሲፈተኑ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል ከ16 ሺህ 580 በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሁለት እስከ ሦስት የትምህርት ዓይነቶችን ሳይፈተኑ መቅረታቸውን ገልፀዋል።በጋምቤላ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ምክንያት ደግሞ ከ100 በላይ የማኅበራዊ ሳይንስና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን በከፊልና ሙሉ ለሙሉ አልወሰዱም ብለዋል። በሕግ ጥላ ሥር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 982 ተማሪዎችና በኢትዮጵያ ሥርዓተ-ትምህርት በውጭ ሀገራት የሚማሩ 300 ተማሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ከ18 ሺህ በላይ በከፊልና ሙሉ በሙሉ ፈተና ያልወሰዱ መሆኑን ገልፀዋል።በመሆኑም በፀጥታ ችግር ያቋረጡትን፣ በማረሚያ ቤት የሚገኙና በውጭ ሀገራት የሚማሩ ተማሪዎች ፈተናውን እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም የፈተና ህትመት፣ የሰው ኃይልና የበጀት ዝግጅት እየደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከየአካባቢው አስተዳደሮች፣ የትምህርት ቢሮዎች፣ ከወላጆችና ከተማሪዎች ጋር ውይይቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።ተማሪዎች ስነ-ልቦናቸው ለፈተና ዝግጁ ሲሆን እንዲሁም አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጫ ሲገኝ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈተኑ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል። በውጭ ሀገራት በኢትዮጵያ ሥርዓተ-ትምህርት የሚማሩ 300 ተማሪዎችም ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓ.ም የሚፈተኑ ይሆናል።ለዚህም የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች ከኢትዮጵያ ፈተናው ወደሚሰጥባቸው ሀገራት መጓዛቸውን ነው ያነሱት።በፀጥታና ሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች በአፋጣኝ የሚፈተኑበትና ውጤታቸው ሐምሌ ላይ ከተፈተኑ ሁሉም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር ውጤታቸውን ይፋ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል።
Show all...
እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 አዲሱ አመት የጤና ፣ የሠላም ፣  የዕድገትና የስኬት ይሁንልን! 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 መልካም አዲስ አመት!
Show all...
New Curriculum Grade 12 Geography Text Book
Show all...