cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Mohammed Ahmed Official

ዩቲዩብ 👇 youtube.com/@gharuhira በግል ጥያቄ እና አስተያየት ካለዎ 👇 @afhasmen

Show more
Advertising posts
4 537Subscribers
No data24 hours
-137 days
+4730 days
Posts Archive
ከወራት በፊት ለኬሚስትሪ መምህሩ አብዱ ኢድሪስ ሐሰን በአገር ውስጥ ለሚያከናውነው የኩላሊት ንቅለ ተከላ 600,000 ብር የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልገው ጥሪ ስናቀርብላችሁ በስድስት ቀናት ውስጥ 850,000 ብር ወደ አካውንቱ ገቢ በማድረግ የተለመደ ትብብራችሁን አሳይታችኋል። እንደናንተ አይነት መልካም ሰዎች ሲበዙ ጠያቂ አጥተው የነበሩ ግለሰቦች ጆሮ የሚሰጣቸው ወገን ያገኛሉ። አልጋ ላይ ወድቀው የሞታቸውን ቀን ይጠባበቁ የነበሩ ህሙማን ከተኙበት አልጋ ላይ በተስፋ ይነሳሉ። ህይወት ጀርባዋን አዙራባቸው ተስፋ የቆረጡ ሰዎች የመከራ ዳገቱን የሚሻገሩበት ምርኩዝ ያገኛሉ።   ወንድማችን መምህር አብዱ ኢድሪስ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ ከላይ በተያያዘው ቪዲዮ መመልከት ይችላሉ።                   ምሥጋና                  🍁🍁🍁 🚩 የገቢ ማሰባሰቢያውን ለማከናወን የመጀመሪያውን የምስልና ድምፅ ቀረጻ እንዲሁም የኤዲትንግ ሥራ በመስራት ከጎኔ ለነበሩት ወንድሞቼ ኢስማዒል ሰዒድ ፣ ሙሐጅሩ መሃመድ አቡ ከውሰር እና አሕመድ ኢብራሂም ሙሐመድ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ። 🚩 ንቅለ ተከላውን በተሳካ ሁኔታ ላከናወኑት የ St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC ሐኪሞችና የጤና ባለሙያዎች ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
Show all...
16👍 3
21
15😢 3
ቁርኣን በወረደበት ወርሃ ረመዷን የአላህን (ﷻ) ቤት በመገንባት ሂደት ላይ የበኩላቸውን አሻራ ለማሳረፍ ቃል የገቡ ደጋግ ወገኖቻችን ቃላቸውን ለመፈፀም የተለያዩ ምክኒያቶች ወደ ኋላ ያስቀሯቸው ይሆናል እንጂ ቃላቸውን እንደሚሞሉ ቅንጣት አንጠራጠርም። ምናልባት የዘነጉ ካሉ ለማስታወስና በመስጂዱ የሒሳብ ቁጥሮች እየገቡ ያሉ ገንዘቦችን አጠቃላይ ድምር ለማሳወቅ አልፎ አልፎ ብቅ እያልን ሪፖርት እናደርጋለን። በዚህም መሠረት በረመዷን በቀጥታ ሥርጭት ከተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በኋላ እስካሁን ድረስ በሁሉም የአዲሱ ሰፈር ኑር መስጂድ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች አጠቃላይ ሁለት ሚሊዬን አምሥት መቶ ሀምሳ ሰባት ሺህ አንድ መቶ ስድሳ አምሥት ብር ገቢ ሆኗል (2,557,165) በታላቁ ወር ለአላህ የገባችሁትን ቃል እየሞላችሁ ያላችሁ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ሁሉ ፣ ቃሉን የማያጥፈው አላህ ጀነትን ለመውረስ ከወዲሁ የሽልማቱ ትኬት ከተቆረጠላቸው ደጋግ ባሮቹ ተርታ ያሰልፋችሁ። ሌሎቻችሁም ለመስጂዱ ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገባችሁትን ገንዘብ እንደምታስገቡ በማመን በጉጉት እየጠበቅናችሁ ነው። http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
10👍 2
ሐቀል ሚልሕ ኦቶማን ቱርኮች ወደ ዓረቡ ዓለም ያስገቡት አንድ አስደናቂ ባህል አለ። «ሐቀል ሚልሕ» ይሰኛል። «ለጨዉ የሚገባ ሥጦታ» እንደማለት። ባል ከዒድ ሶላት ወደ ቤቱ ከመመለሱ በፊት ሚስት አቅሟ በፈቀደ ልክ ቤቷን ምድራዊ ገነት አድርጋ ትጠብቀዋለች። በማራኪ አልባሳት ተውባ ፏ ብትን ትላለች። ሰውነቷ ላይ አፍንጫን የሚያውዱ ሽቶዎች አርከፍክፋ ለምለማማ መስክ ላይ እንደምትሸቀረቀር ጣውስ አይኖቿን በሩ ላይ ትወረውራለች። ባል ወደ ቤቱ እንደገባ አንድ ስኒ ቡና ይቀርብለታል። ቡናውን ይጠጣል። ግና ከጠጣ በኋላ ስኒውን ባዶ አድርጎ ወደ እሷ አይመልስም። በረመዷን ሙሉ ላሳለፈችው ድካም እና ልፋት እውቅና ለመስጠት በባዶው ስኒ ውስጥ የወርቅ አሊያም የብር ቀለበት ያስቀምጥላታል። እሷም የቀረበላትን ሥጦታ በፈገግታ ትቀበላለች። በጥንዶቹ መሃል የተመሰረተው ፍቅር በመሰል ስጦታዎች ድርና ማግ ሆኖ የመቀጠል ዕድሜው ይረዝማል። «ሐቀል ሚልሕ» የተሰኘውም ሚስት በወርሃ ረመዷን እሳት ላይ ተጥዳ የምታዘጋጃቸው ጣት የሚያስቆረጥሙ ምግቦች የጨው መጠናቸው ውኃ ልኩን የጠበቀ ስለነበር ነው። ♥♥♥ ጉዳዩን ወደ ሀገርኛ ስንገለብጠው ነገር ዓለሙ ሁሉ ይገለባበጣል። የቀረበላቸውን ምግብ ጠራርገው የበሉበትን ትሪ ብቻ የሚያስተርፉ ዘጠኝ ወጠምሻ ጓደኞቹን ለፊጥራ የጋበዘ አባወራ ሚስቱ ቀኑን ሙሉ ማጀት ውስጥ በመዋል እሱን ጨምሮ የአስር ወንዶች ከርስ ሚዛን የሚያስተካክል ጣፋጭ ምግብ አቅርባ ስትጨርስ ወርቁ ቀርቶባት ግንባሯን ስሞ ምስጋና ይቸራት ይሆን ??? ነው ወይስ ገንዘብ ሳያወጣ «የስጋ ሳንቡሳ ስሪ ብየሽ እንግዶቼን እንዴት በምስር ሳንቡሳ ትሸኛለሽ ?» እያለ በቁጣ ብዛት ጸጉሩ የቦነነ አነር ነው የሚመስለው ??? 😃 👉 http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
17👍 10
ለዒድ ሶላቶች መስገጃ ተብሎ ከተዘጋጀው የባቲ ብርሃናማው ተራራ (ጀበለኑር) ላይ በዱንያ ውስጥ አንድ ክፍለዘመን ከአምስት ዓመት ከቆዩት የዕድሜ ባለፀጋው ጋሽ ሙሐመድ አደም ጋር ዓይን ለዓይን ተገጣጠምን። ዳገት ሲወጣ ጭሱን እንደሚያንፎለፉል ፊያት መኪና እያማጥኩ የወጣሁትን ፈታኝ ተራራ እኝህ የዕድሜ ባለፀጋ እንዴት እንደወጡት አላሁ አዕለም !! ዒድ ሙባረክ http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
13👍 5
23👍 2
በቅርቡ በባቲ ከተማ በአዲሱ ሰፈር የሚገኘውን ኑር መስጂድ ለመገንባት በቀጥታ ሥርጭት በተከናወነ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ በተደረገ ድጋፍ በቃል፣ በዓይነት እና በጥሬ በጠቅላላ አራት ሚሊዬን አምስት መቶ ሺህ ብር (4,500,000) መሰብሰብ እንደተቻለ መግለፃችን ይታወሳል። በዚህም መሰረት የአላህን ቤት ለመገንባት ከአላህ ጋር ቃልኪዳን የገቡ ጀግና ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቃላቸውን እየሞሉ ይገኛሉ። የገቢ ማሰባሰቢያው ከተከናወነ በኋላ እስካሁን ድረስ በሁሉም የአዲሱ ሰፈር ኑር መስጂድ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች በድምሩ ሁለት ሚሊዬን ሁለት መቶ ሀምሳ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሥምንት ብር ገቢ ሆኗል (2,250,248) የገባችሁትን ቃል እየሞላችሁ ያላችሁ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ሁሉ ፣ ቃሉን የማያጥፈው አላህ ጀነትን ለመውረስ ከወዲሁ የሽልማቱ ትኬት ከተቆረጠላቸው ደጋግ ባሮቹ ተርታ ያሰልፋችሁ። ሌሎቻችሁም ቃል የገባችሁትን ድጋፍ እንድትፈፅሙ በጉጉት እየጠበቅናችሁ ነው 😍😍😍 http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
18
ለባቲ ኑር መስጂድ ግንባታ ከፍጡር እስከ ሱሑር በተከታታይ ለ2 ቀናት በተዘጋጀ የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ከወንድሞችና እህቶች ጋር ባደረግነው ርብርብ በአይነት እና በጥሬ ገንዘብ አራት ሚሊዬን አምስት መቶ ሺህ ብር (4,500,000) ለመሰብሰብ ተችሏል። ክስተቱም ለኸይር ሥራ ተርበው የአቅማቸውን በመለገስ ርሃባቸውን የሚያስታግሱ ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የሞሉባት ዓለም ውስጥ እንዳለን አሳይቶናል። የቀጥታ ስርጭቱን ሳይታክቱ ለሌሎች በማጋራት ውለታ የዋሉ እጆች እንዳሉም አስተውለናል። የሞቁ ቤቶቻቸውን ትተው ይህን ውጤት ለማስመዝገብ ሌት ተቀን እየፈጉ ከኛ ጋር የማይረሱ ቀናት በማሳለፍ ከብረት የጠነከሩ መሆናቸውን ያስመሰከሩ ወንድሞቼን እና እህቶቼን አደባባይ ላይ ማመስገን እፈልጋለሁ። 👇👇👇 https://www.facebook.com/share/p/gWouWob72Msz1waA/?mibextid=oFDknk
Show all...
22👍 7👏 3
የአዲሱ ሰፈር ኑር መስጂድ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች ADDISU SEFER NUR MOSQUE ✍ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) 1000260513102 ✍ አቢሲኒያ 160463977 ✍ አዋሽ ባንክ 01425579695000 ✍ ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ 226891 ✍ዘምዘም ባንክ 0020205120101 ✍ሂጅራ ባንክ 1002846670001 ✍አማራ ባንክ 8800000589344
Show all...
1
16
ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) ❝ ለአላህ ብሎ እንደ ድንቢጥ ጎጆ ወይም ከሱ ያነሰ መስጂድ የሰራ ሰው አላህ ለእርሱ በጀነት ውስጥ ቤት ይገነባለታል❞ ብለዋል። http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
19
በባቲ ከተማ አዲሱ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለሚገነባው ኑር መስጂድ ነገ ሰኞ ፣ መጋቢት 23/ 2016 ዓ.ል ከፉጡር እስከ ሱሑር በምናካሂደው የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ከኛ ጋር በመሳተፍ መስጂዶች የጋራ አርማዎቻችን እንደሆኑና በአንድነት ከቆምን የማንወጣው አቀበት እንደሌለ ለማሳየት የአቅማችሁን ድጋፍ እንድታደርጉ ስንል ከወዲሁ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
Show all...
10
ሰኞ መጋቢት 23/ 2016 ከፉጡር እስከ ሱሑር ባለው ጊዜ ቆይታዎን ከኛ ጋር ያድርጉ - ኢንሻአላህ 👇👇👇 https://www.facebook.com/share/v/xeKR4skVP4fvYhMt/?mibextid=oFDknk
Show all...
2
ከመሬት መነሳት ለከበደው ወንድማችን መታከሚያ የሚሆን የጠየቅኳችሁን 50,000 ብር አንዲት እህት ሙሉውን እኔ እሸፍናለሁ ብላ 50,000 ብሩን ወዲያው ገቢ ስታደርግ እስከ አሁን በአጠቃላይ 130,000 ብር ወደ አካውንቱ ገቢ ሆኗል። http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
15👍 2
ከመሬት መነሳት ለከበደው ወንድማችን መታከሚያ የሚሆን የጠየቅኳችሁን 50,000 ብር አንዲት እህት ሙሉውን እኔ እሸፍናለሁ ብላ 50,000 ብሩን ወዲያው ገቢ ስታደርግ በአጠቃላይ 80,000 ብር ወደ አካውንቱ ገቢ ሆኗል።
Show all...
12👍 3
ትላንት እንደልቡ ይታዘዙ የነበሩት የገዛ እግሮቹ ዛሬ ላይ ከዱት። በአፍላ ዕድሜው ለመሮጥ ቢመኝም ከመሬት መነሳት ተራራን የመግፋት ያህል ከበደው። እምብዛም ትኩረት የማንሰጠውና አላህ ለሰው ልጆች ከዋለላቸው ሥፍር ቁጥር የለሽ ፀጋዎች አንዱ ኩላሊት ያጣራውን ያልተፈለገ ፈሳሽ ከሰውነታችን የምናስወግድበት መንገድ ቢሆንም ለወንድማችን ግን መንገዱ ተዘግቷል። እንዲያም ሆኖ ከሁለት ዓመት በፊት የጀመረው ህክምና በጤናው ላይ የተሻለ ለውጥ ማምጣቱን አስተዋለ። እንዳሻው ሲያዛቸው የነበሩት እግሮቹ ሊንቀሳቀሱ እንደሚችሉ ውስጡ የተስፋ ጭላንጭል ፈነጠቀ። ምኞቱ እውን እንዲሆን ቢጓጓም እጅ አጠረው። በዚህ የፈተና ቀለበት እያለፈ ያለ ቢሆን እንጂ ለሰው ልጆች የተሰጠውን የጤና ፀጋ ማን ይረዳል !! ወንድማችን ከናንተ የሚፈልገው 50,000 ብር ብቻ ነው። ትላንት እራሳችሁ በቀላሉ የምታዙት የነበረው የሰውነት ክፍላችሁ ዛሬ ላይ በሰው እጅ የሚታዘዝ ሆኖ ከሚፈትን በሽታ አላህ ያርቃችሁና ለዚህ ወንድሜ ይህችን 50,000 ብር በባሌም በቦሌም ብላችሁ በሚከተሉት የወንድማችን ወላጅ እናት የባንክ አካውንት ቢ በማድረግ በረመዷኑ በሰዎች ቤትደስታን አከፋፍሉ። HALIMA ANWAR MOHAMMED CBE 1000491520829 0913272669 የታማሚው ሥልክ 0949956788 http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
😢 9
ትላንት በውስጥ መስመር ረመዳን «ከሪም» የሚል መልዕክት ከአንዲት የክርሥትና ኃይማኖት ተከታይ እህት ደረሰኝ። ሥሟን ከነገረችኝ በኋላ ፌስቡክ ላይ ረዘም ላለ ጊዜ እየተከታተለችኝ እንደሆነች አጫወተችኝ። « አሁን እስልምናን መቀበል ስለምፈልግ ወደ ኃይማኖቱ ለመግባት የሚጠበቅብኝን የምስክርነት ቃል በአንደበቴ መናገር እንድችል አግዘኝ» አለችኝ። የልቤ መረት ጨመረ። ሥልክ ቁጥሯን እንድታስቀምጥልኝ መልዕክት ላኩላት። ቁጥሯን ላከችልኝ። ከዚያ በተደጋጋሚ ሥደውል አላነሳችልኝም። እኔ መስመር ላይ ስሆን እሷ ባለመኖሯ እና እሷ መስመር ላይ ስትሆን እኔ ባለመኖሬ በመካከላችን የነበረው የመልዕክት ልውውጥ ወዲያው ባለመሆኑ የጊዜ ክፍተት ተፈጠረ። ዛሬ ከፊጥራ በኋላ «አመሰግናለሁ ፣ ወንድሜ ዛሬ ሸሀዳዬን ያዝኩኝ ፤ የለመንኩህ ለዚህ ነበር » የሚል መልዕክት ተቀምጦ አገኘሁ። በአቅራቢያዋ ከሚገኝ መስጂድ ጎራ ብላ የቃለ ተውሒድን የምስክርነት ቃል እንደሰጠች ነገረችኝ። ውስጤ በቁጭት እና በደስታ ተናጠ። ዕድሉ ስላመለጠኝ ተቆጨሁ። ወደ እስልምና ቅፅር በመምጣቷ ተደሰትሁ። «ትላንት ከምሽቱ 1:46 ላይ ስደውልልሽ ነበር። ስልክሽ ይጠራል ግን አይነሳም ነበር» አልኳት። «ይቅርታ አሁን ላይ ሲም እስክቀይር የማላውቀውን ሥልክ አላነሳምና ነው። ቁጥርህ ስንት ቤት ነው» አለችኝ። ነገርኳት። ከዚያ በኋላ 15 ደቂቃ ከ 38 ሴኮንዶች ስለ እስልምና አወራን። ነፍስ ወደ እስልምና ዓለም ስትገባ ከየትኛው ምንጭ እንደሚፈልቅ ምስጢር በሆነው የእንባ ጎርፍ  ያለፈ ኃጥያቷን ማፅዳቷ አይቀርምና እህታችንም ተራው ደረሳት።   «ወንድሜ አንድ ሀሳብ ግን ይዞኛል»አለች። ጆሮዬን ሰጠኋት። «ወንድሜ ወደ እስልምና ስገባ ሁሉንም ነገር መተው እንዳለብኝ እስባለሁ። ሥራ ቦታ ደግሞ የምለብሰው የደንብ ልብስ ሱሪ ነው። ያንን ነገር ደግሞ ምን እንደማደርግ ግራ ገብቶኛል። የተከለከልኩትን ተከልክዬ ፣ የታዘዝኩትን ፈጽሜ መኖር ነው የምፈልገው። ምን ትመክረኛለህ ?» አለችኝ። እኔም ከሸይኼ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ተመካክረን ልቧን የሚያረጋጋ ምላሽ ሰጠኋት።
Show all...
40👍 9😢 6🥰 2
በምድር ላይ የአላህን ቤት ለመገንባትና ለእርሱ መልካምን ብድር ለማበደር የእናተን ቸር እጆች እየጠበቅን እስካሁን ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሰላሳ ሺህ አንድ መቶ ሰላሳ አራት ብር (2,630,134) በመሰብሰብ መስጂዱ አሁን ላለበት ደረጃ እንዲደርስ የጋራ ጥረት አድርገናል። የረመዷን ድባብ ደግሞ መስጂዳችንን ልዩ ውበት አላብሶታል። እንደ ምኞታችን ቢሆን ኖሮ የመስጂዱ አንደኛው ፎቅ ግንባታ ተጠናቆ እናቶቻችን እና እህቶቻችንም እንደኛ በምቾት ሶላታቸውን እንዲሰግዱ ማስቻል ነበር። ነገር ግን እንዳትሰለቹን በሚል ከቀናት እና ከወራት ቆይታ በኋላ ብቅ እያልን የናንተን ድጋፍ ለመጠየቅ ተገደናል። መልካም ሥራዎች አየሩን በሚቆጣጠሩበት በዚህ ታላቅ ወር ለመስጂዱ ግንባታ ድጋፍ እንድታደርጉ በሚል ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን የምናነሳ ከሆነ ከወዲሁ እንዳትሰለቹን ስንል በትህትና እንጠይቃለን። ለመስጂዱ ግንባታ የድጋፍ እንቅስቃሴ ከመጀመራችን በፊት መስጂዱ ቀድሞ የነበረበትን ይዞታ ለመመልከት ይህን ሊንክ ጠቅ ያድርጉ 👉 https://t.ly/6zTfv የአላህን ቤት በኤሊ እርምጃ ገንብተንም ቢሆን የሲራጥን ጎዳና በአይን ብልጭታ ከሚሻገሩት ሙእሚኖች እንዲያሰልፈን በዚህ ታላቅ ወር ለኸይር ነገር እጆቻችንን እንዘርጋ። ከዘካ ገንዘቦቻችሁ የተወሰነውን ወደዚህ መስጂድ አካውንቶች በመላክ ዱንያን ከተሰናበታችሁ በኋላ ለዚያኛው ዓለም የሚጠቅም ስንቅ አስቀምጡ። አዲሱ ሰፈር ኑር መስጅድ ✍ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) 1000260513102 ✍ አዋሽ ባንክ 01425579695000 ✍ ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ 226891 ✍ሂጅራ ባንክ 1002846670001 ✍ዘምዘም ባንክ 0020205120101 ✍አማራ ባንክ 8800000589344 ✍ አቢሲኒያ 160463977 https://www.facebook.com/share/v/FtnCfaVYrcsdvydK/?mibextid=oFDknk
Show all...
👍 4 1
የ 23,000 ብር የገንዘብ ድጋፍ ብናደርግላት ወደ ሥራ መግባት እንደምትችል ትላንት የጠቆምኳችሁ እህት የተጠቀሰው የብር መጠን ወደ አካውንቷ መግባቱን ባስተዋለች ጊዜ ማታ ደስታዋን አጋራችኝ። ረፋድ ላይ ደግሞ በአቅራቢያዋ ወዳለ የገበያ ማዕከል እየበረረች አቅንታ የድፎ መጋገሪያ እና የችብስ ማዘጋጃ መሳሪያዎቹን ገዝታ በፎቶና በድምፅ የታገዘ ቪዲዮ ቀርፃ ላከችልኝ። የረሳሁት 🍀🍀🍀 የድጋፍ እንቅስቃሴው ከተቋጨ በኋላ አንድ ነገር ትዝ አለኝ። እህታችን ማሽኖቹን የገዛችው ዳቦ እና ችብስ ልትሰራበት እንጂ ልትታቀፈው አለመሆኑን የበራልኝ የረመዷኑ ረሃብ ከወተወገደልኝ በኋላ ነበር። ሥለዚህ እህታችን ለሥራ ማስጀመሪያ የሚሆናት ለዘይት ፣ ለድንች እና ለዱቄት የሚሆን 5,000 ብር ማስወንጨፍ እችላለሁ የሚል ባለ ዕጣ በውስጥ መስመር ያናግረኝ። ለጨቅላ ልጇ በጉሮሮው የወተት ጠብታ መስደድ የተሳናትን እናት ደግፋችሁ የምታገኙትን ምንዳ አስቡት ...
Show all...
12👍 8
በናንተ በተደረገ ድጋፍ ደረሳዎቹ ቀሪ የረመዷን ቀናትን ተረጋግተው መፆም ጀምረዋል። የዕለት ጉርሳቸውን ለማግኘት ከከተማው ነዋሪዎች ደጃፎች ላይ ቆመው ❝ቀሪኣ❞ መጠየቅ ትተዋል። የረመዷንን ፆም የሚወጡበት እና ከፆሙም በኋላ የመስጂዱ ንብረት የሚሆኑ ውስን እና አስፈላጊ የሚባሉ እቃዎችን ገዝተን አስረክበናቸዋል። ምናልባት በስንት አንዴ የሚያጋጥማቸውን የምግብ ዓይነት ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲቀምሱ ድጋፍ ላደረጋችሁ ወንድሞች እና እህቶች ደረሳዎቹ ሌት ተቀን እያደረጉላችሁ ያለውን ዱዓ በአካል መጥታችሁ ብትሰሙ ኖሮ ለሚቀጥለው ረመዷን ሙሉ ወጪያቸውን እኔ እችላለሁ የሚያስብል ስሜት ውስጥ እንደሚያስገባችሁ አልጠራጠርም። ለማንኛውም ለናንተ ተብሎ ወደ ሰማይ እየተተኮሰ ያለው ዱዓ ኢላማውን እንደማይስት በአላህ ላይ ፅኑ እምነት አለኝ። የሚተርፋቸውን ገንዘብ ከእነሱ ጋር ቁጭ ብለን በመመካከር ፍላጎቶቻቸውን በማዳመጥ እና ለሚበጃቸው ነገር እንዲውል እንደምናደርግ ቃል እንገባለን።
Show all...
5
19👍 8
የዛሬው መረጃችን ከአዲስ አበባ ነው። እህታችን በዐረቡ ዓለም የቤት ሰራተኛ በነበረችበት ወቅት በአገር ቤት ውስጥ ችግር ላይ የወደቁ ዜጎችን አቅሟ በፈቀደ መጠን ለመደገፍ ያላሰለሰ ጥረት ታደርግ ነበር። የብዙዎች ህይወት እንዲቃና በግል እና በቡድን የራሷን አስተዋፅዖ አበርክታለች።       እነዚያ ሰዎችን ለመደገፍ ያለ ስስት ይዘረጉ የነበሩ እጆች ዛሬ ላይ ከሰዎች ድጋፍ ፈልገው በተራቸው ለመዘርጋት ተገደዋል። ራሷን ይቅርና ጨቅላ ልጇን መመገብ የሚያስችላት አቅም አጥሯታል። ትላንት ለተቸገሩ እናቶች የወተት መግዣ ስትልክ የነበረችው እህት ዛሬ ለልጇ ወተት መግዣ አጥታለች። የረመዷን ድባብ ከጎጆዋ ገና አልገባም። በዙሪያዋ ለከበቧት ሦስት ልጆች የዕለት ጉርስ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የማትኳትንበት ጥግ አልነበረም። አሁን ግን የወጣችበት እና የወረደችበት ፈተና ጉልበቷን አመንምኖ ❝እባክህ በአላህ ሥሜን ደብቀህ በህይወት ድረስልኝ❞ ስትለኝ ወደናንተ ወዳጆቼ ጓዜን ተሸክሜ ብቅ ብያለሁ። ጉዳዩንም በደንብ አጣርቻለሁ። ብዙውን ሆድ ይፍጀው ብዬ ትቼዋለሁ።                      መፍትሔ                   🔴🔴🔴 እህታችን ጋር በሰፊው ተነጋግረናል። በሙያዋ እየሰራች የገቢ ምንጭ የሚፈጥርላት የሥራ ዘርፍ ካለ እንደምደግፋት ሃሳብ ሳቀርብላት ጉዳዩ አሁን የተሳካላት ያህል በደስታ ብዛት ፈንድቃለች። እጇ ላይ ከዓረብ አገር ስትመጣ ይዛ ከመጣችው የልብስ ማጠቢያ ማሽን ውጭ አንዳች ነገር የላትም። ❝ለአካባቢው ነዋሪዎች የልብስ ንፅህና መስጠት እችላለሁ። ነገርግን ማሽኑ ከቤት  ወደ ውጭ ከወጣ ለስርቆት ስለሚጋለጥ የብረት ላሜራ ቤት ይፈልጋል❞ አለችኝ። ሌሎችንም ሁለት ሥራዎች የመስራት ፍላጎት እንዳላት አሳውቃኛለች።     የብረት ላሜራ ቤት መስሪያ =  6,000 ብር የድፎ መጋገሪያ = 12,500 ብር የችብስ ማሽን = 4,500  አጠቃላይ የሚያስፈልጋት  23,000 ብር ነው። በዙሪያዋ ካሉ ብዙነ ፍሶች ጋር አብራ የተጨነቀችን ነፍስ ከገባችበት የጭንቅ ዓለም ለማውጣትና ከመጪው ዓለም አስፈሪ ጭንቀት ነፃ ናችሁ የሚል ሽልማት እንዲደርሳችሁ የምትመኙ ደጋጎች በሙሉ በውስጥ መስመር ልታናግሩኝ ትችላላችሁ። http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
👍 15
መግሪብ አካባቢ ለደረሶቹ የረመዷን ማፍጠሪያ የሚሆን ሙሉ ወጪ 50 ሺህ ብር ብንጠይቅም ከተራዊሕ ስመለስ እንደ ሀምሌ ወጨፎ አላባራ ብለው ጓዳዬን ያጨናነቁ እህትና ወንድሞች እስካሁን 200 ሺህ ብር ለግሰዋል። http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
18👍 11
መግሪብ አካባቢ ለደረሶቹ የረመዷን ማፍጠሪያ የሚሆን ሙሉ ወጪ 50 ሺህ ብር ብንጠይቅም ከተራዊሕ ስመለስ እንደ ሀምሌ ወጨፎ አላባራ ብለው ጓዳዬን ያጨናነቁ እህትና ወንድሞች እስካሁን 200 ሺህ ብር ለግሰዋል። http://t.me/abuafnanmoh
Show all...
8