234
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ጉዳዩ፡- የፈተና እና ዉጤት ትንተና የጊዜ ሰሌዳ ስለማሳወቅ፤
👉ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረዉ የ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ወደ ማጠቃለያዉ ምዕራፍ መድረሳችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም በከተማዉ አስተዳደሩ ዉስጥ የሚገኙ የመንግስትና የግል ት/ቤቶች በሙሉ ወጥ የሆነ የፈተና መርሐ ግብር ለማከናወን ያስልች ዘንድ ከዚህ በታች በቀረበዉ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንዲከናወኑ እያስታወቅን
👌 የጊዜ ሰሌዳዎቹ -
1️⃣ ከሰኔ 7-9/2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ይሰጣል፡፡
2️⃣ ከሰኔ 7-8/2015 ዓ.ም የ6 እና 8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ይሰጣል፡፡
3️⃣ ከሰኔ 12-16/2015 ዓ.ም የ2ኛ ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል፡፡
4️⃣ ከሰኔ 19- 20/2015 ዓ.ም የመልስ ወረቀት ለተማሪዎች የሚመለስበት ይሆናል፡፡
5️⃣ ከሰኔ 20- 23/2015 ዓ.ም የተማሪዎች የዉጤት ማጠቃለያ የሚሰራበት ይሆናል፡፡
6️⃣ ከሰኔ 26-27/2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡፡
7️⃣ ከሰኔ 28-30/2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡፡
8️⃣ ከሐምሌ 1-2/2015 ዓ.ም የተማሪዎች የዉጤት መግለጫ ካርድ መካን ሆናል፡፡
9️⃣ ከሐምሌ 3-5/2015 ዓ.ም የተማሪዎች የዉጤት ትንተና ለክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት ገቢ የሚደረግበት ይሆናል፡፡
🔟 ከሐምሌ 8-12/2015 ዓ.ም የተማሪዎች የዉጤት ትንተና የክ/ከተማ ት/ጽ/ቤቶች ለትምህርት ቢሮ ገቢ የሚያደርጉበት ይሆናል፡፡
➢1️⃣1️⃣ ከሐምሌ 19-30/2015 ዓ.ም የ12ተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የሚሰጥ መሆኑ ታዉቆ በወጣዉ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በማድረግ ተግባራቶቹ በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲከናወኑ እናሳስባለን፡፡
አዲስ አበባ ት/ት/ቢሮ
ጉዳዩ፡- የተማሪዎች የልደት ሰርተፍኬት ይመለከታል፣
👌ከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረዉ ዜጎች የልደት ምዝገባ ማከናወናቸዉ ለትምህርት ስራችን ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳለዉ ይታወቃል፡፡
👌በሴክተራችን ትክክለኛዉን የተማሪዎች እድሜ ማወቅ ትረጉሙ ከፍተኛ በመሆኑ ከባለፈዉ ዓመት ጀምሮ ተማሪዎች የልደት ምዝገባ በማከናወን የልደት ሰርተፍኬት እንዲያወጡ የተደረጉ ስራዎች አበረታች ቢሆንም አሁንም ካለን ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ተማሪ አንጻር ተግባሩን አጠናክሮ መስራት ያስፈልጋል፡፡
👌ስለሆነም አሁን በተጀመረዉ ንቅናቄ ላይ ተገቢዉን ትኩረት በመስጠት የት/ቤት ማህበረሰብና የተማሪ ወላጆች እንዲያዉቁት በማድረግ በሁሉም ት/ቤቶቻችን ላይ ያሉ ተማሪዎች የልደት ምዝገባ ሰርተፍኬት እንዲያወጡ እና ለቀጣይ የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤት ምዝገባ ሲከናወን ተመዝጋቢዎች የልደት ሰርተፍኬት እንዲያቀርቡ እንዲደረግ እናስታዉቃለን፡፡
Repost from Yeka Education
👌ጉዳዩ፡- የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተከለሰ ፕሮግራምን ይመለከታል☝️
👉የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በቁጥር 018/ፈ.8/2851/15 በቀን 08/07/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ፕሮግራም መላካችን ይታወቃል፡፡
👉ይሁን እንጂ በላክነው ፕሮግራምም ሆነ በተጣመሩ የትምህርት ዓይነቶች ላይ ክአብዛኛው ክልልና ከተማ አስተዳደር ጥያቄ በመቅረቡ የሁላችሁንም ፍላጎት በስልክ በተደረገ የሀሳብ ልውውጥ መሰረት እንደገና እንዲታይ አስፈላጊ አድርጎታል፡፡
👉ከዚህ በመነሳት መጋቢት 25/2015 ዓ.ም ከሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ክፍል ኃላፊዎች ጋር በበይነ መረብ በተደረገ የውይይት ሂደት ባገኘነውና አብዛኛው ሀሳብ አቅራቢ በተስማማው መሰረት የፕሮግራም ማስተካከያ በማድረግ ከሰኔ 19-20/2015 ዓ.ም ድረስ እንዲሆን ተወስኗል፡፡
👉በተጨማሪም የሁለተኛ ቋንቋን በተመለከተ የተወሰኑ ክልሎች እንደማይሰጡ ስላረጋገጥን ወደሁለተኛው ቀን ከሰዓት እንዲሆን በማድረግ የፕሮግራምም ሆነ የትምህርት መጣመሩን መከለስ አስፈልጓል፡፡
👉ስለሆነም የአብዛኛውን ሀሳብ ከግንዛቤ በመውሰድ የተከለሰውን ፕሮግራምና የተጣመሩ የትምህርት ዓይነቶችን የያዘ ፕሮግራም ከዚህ መሸኛ ደብዳቤ ጋር 1 ገጽ አባሪ በማድረግ አያይዘን የላክን ስለሆነ በተቀመጠው አግባብ በሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር በወጥነት እንዲተገብር እናሳስባለን፡፡
ከሠላምታ ጋር!
