234
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from N/a
የየካ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃ አቶ ብርሀኑ ረታ የወጣቶች ገነት ቅድመ-አንደኛ ት/ት ቤት የማስፉፊያ ግንባታ ያለበት ደረጃ ተዟዙረው ምልከታ አደረጉ ህዳር 26/2016፣
በየካ ክ/ከተማ አስተዳደር በሚገኙ ት/ቤቶች " ትምህር ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረውን የትምህርት ተቋማት ጥራት የማስጠበቅ እና በስታንዳርድ የማሳደግ መርህ የማስፉፊያ ስራ እንዲደረግባቸው በየካ ክ/ከተማ በተመረጡ የትምህርት ተቋማትን አሁናዊ ይዘት ተዟዙረው ምልከታ አድርገዋል፡፡
በዚሁ መሰረት በት/ት ቤታችን በመገኘት
በመስክ ምልከታው የየካ ክ/ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሀኑ ረታ፤የየካ ክ/ከተማ የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ መገርሳ ገላናን ጨምሮ የየካ ክ/ከተማ አመራሮች፣ እንዲሁም መምህራን እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
የት/ቤቶችን ደረጃ ለማስጠበቅ የተጀመሩ ስራዎች እንዲሳኩ ሁሉም የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ትምህርት ቤቶች የትውልድ አውቀት መገንብያና በአእምሮ የዳበረ ብቁ አገር ተረካቢ ዜጋ ማፍሪያ ማእከላት እንደመሆናቸው ጥራት ያለው የመማር ማስተማር ስርአት እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ማድረግ የጎላ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተዋል ።
የት/ቤቶቹን እድሳት በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅና የጎደሉትን መሰረታዊ ግብዓቶች በሟሟላት የትምህርት ጥራት በመፍጠር ለተማሪዎች ምቹ የመማር ማስተማር ሁኔታ እንደሚፈጠርም አቶ ብርሀኑ ረታ አክለው ገልፀዋል፡፡
Repost from N/a
በወረዳው ሳምንታዊ የፅዳት ፕሮግራም ተካሄደ
ወጣቶች ገነት ት/ት ቤት ህዳር 14/2016 ዓ/ም
===========================
በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር በወጣቶች ገነት ት/ቤት የፅዳት መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት አከናውኗል።
በፅዳት መርሀ ግብሩ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስቻለው በቀለ፣ የየካ ክ/ከተማ ወረዳ 08 ዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አራጌ ሰይድ፣የወረዳ 08 ፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ተወካይና የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ ሰይድ እንዲሁም የወጣቶች ገነት ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ መሃመድ ኢሳ፣ መምህራን እና ተማሪዎችና ተገኝው በፅዳቱ ተሳትፈዋል ።
በፅዳት መርሀ ግብሩ ንግግር ያደረጉት የወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚው አስቻለው በቀለ ፅዳት የስልጣኔ ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር የአንድ ንቁ ማህበረሰብ የዕለት ተዕለት ተግባሩ መሆን አለበት ብለዋል።ቆሻሻ በአግባቡ ከያዝነው ገንዘብ ነው በተቃራኒው ከሆነ ደግሞ በሽታ እና የጤና አክል የሚፈጥር አደገኛ ነገር ነው ያሉት ስራ አስፈፃሚው የቆሻሻን ገንዘብነት በተግባር ማሳየት አለብን ብለዋል።
ፅዳት ወቅት እና ጊዜ የማይፈልግ የዘወትር ተግባር ሆኖ መቀጠል ያለበት ተግባር ስለሆነ ከቀጠሮ ስራ ወጥተን መስራት አለብን በተጨማሪም ደረቅ ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ዘርፍ ሞዴል ለማድረግ የተለያዩ ስሪዋችን በመስራት ላይ ይገኛሉ ያሉት ደግሞ የወረዳው ፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ተወካይና የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ ሰይድ ናቸው።
በመጨረሻም የወጣቶች ገነት ቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ መሃመድ ኢሳ በንግግራቸው ለፅዳት ሳምንት ወር ብሎ ጊዜ መስጠት የለበትም አስፈላጊ ከሆነ በየጊዜው ዘመቻ ሳንጠብቅ በማፅዳት ፅዱ ት/ቤት፣ ፅዱ ወረዳ ፣ብሎም ፅዱ ከተማ መፍጠር አለብን በማለት የፅዳት መርሃ ግብሩን ከተማሪዎች ጋር አስጀምረዋል፡፡
Repost from N/a
የስራ ቅጠር ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ለ2016 የትምህርት ዘመን ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ክፍት የስራ መደቦች ላይ መምህራንን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
Repost from Yeka Education
የስራ ቅጠር ማስታወቂያ
👉የአዲስ አበባ ት/ቢሮ በመምህርነት የስራ ዘርፍ ያወጣው የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
👉ማስታወቂያው የሚቆይበት ጊዜ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት
👉ምዝገባው የሚካሄደው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅበት ድረስ ከጠዋቱ 2፡30 – 11፡30 ሰዓት ብቻ ይሆናል፡፡
👉የትምህርት ማስረጃና ከ 3/ሶስት/ ወር ያልበለጠ ስራ ልምድና ዋናውን ቴምፖራሪና ሱቱደንት ኮፒ ስካን ወይም ፎቶ በማንሳት በመመዝገቢያ ሊንኩ ላይ መያያዝ አለበት
👉ለ2ኛ ዲግሪ ተወዳዳሪዎች ትምህርት ሚኒስቴር ለ2ኛ ደረጃ መምህርነት ባዘጋጀው ስርዓተ ትምህርት ስልጠናውን ወስደው ያጠናቀቁ መሆን አለበት፡፡
👉ከግል፣ ከቤተክህነት እና ከሚሲዮን ትምህርት ቤቶች የሚቀርብ የስራ ልምድ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
👉ከግል የትምህርት ተቋም የሚቀርብ የትምህርት ማስረጃ ቀድሞ ትምህርት ሚኒስቴር በወጣው የመምህራን የቅጥር መመሪያ መሰረት ይሆናል፡፡
👉በመምህራን የደረጃ እድገት መሰላል መሰረት ከጀማሪ እስከ መምህር ደረጃ የምትወዳደሩ መምህራን መልቀቂያ በቅጥር ሰዓት ማቅረብ የግድ ሲሆን በ0 ዓመት ቅጥር ከተፈፀመ በኋላ አገልግሎት ይያዝልኝ ማለት አይቻልም፡፡
👉የስራ ቦታ፡- አዲስ አበባ(በ11ም ክፍለ ከተሞች ስር በሉ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትመህርት ቤቶች)
👉የተወዳዳሪዎች የቅጥር ዘመንና የአገልግሎት ዘመን ተመሳሳይ መሆን አለበት፡፡
የምዝገባ ቦታ
✅ቢሮው ባዘጋጀው የመመዝገቢያ ሊንክ መሰረት በኦነላይን ይሆናል፡፡
👇👇👇👇👇👇
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdxUL1wAfiSGg1hOhpblCLTOqFHFBu3Iu2nx-R401Opy8525g/viewform
ቻናላችን ይህ ነው ሸር!!
👇👇👇👇👇👇👇
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/dam76
