234
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
✅የጥያቄና መልስ ውድድርን በተመለከተ
👉በክፍለ ከተማ ደረጃ የ6ኛ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል የጥያቄና መልስ ውድድር በ26/4/2016 ይካሄዳል::በመሆኑም የሁለተኛ ደረጃ እና በወረዳ ደረጃ የሚካሄዱ ውድድሮች እስከ 25/4/2016 መጠናቀቅ ይኖርባቸዋል::
✅የሞዴል ፈተና የሚሰጥበት ቀንን በተመለከተ
👉የ2016 ዓ.ም የ6ኛ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና በከተማ ደረጃ ከጥር 1-3/5/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል::
✅የሞዴል ፈተና የሚሸፍነውን በተመለከተ
👉የ6ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ከ6ኛ ክፍል የመጀመሪያ ሴሚስተር ብቻ ይሸፍናል
👉የ8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ከ8ኛ ክፍል የመጀመሪያ ሴሚስተር ብቻ ይሸፍናል
👉የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ከ9ኛ-11ኛ በነባሩ/በቀድሞው ስርዓተ ትምህርት እና የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ስርአተ ትምህርት የመጀመሪያ ወሰነ ት/ት የሚሸፍን ይሆናል::
📙በመሆኑም ይህንን መረጃ መሰረት በማድረግ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እና ለተማሪዎችን በቂ መረጃ መስጠት ከሁላችንም ይጠበቃል!!
የየካ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ታህሳስ 12//04/2016 ዓ.ም ሊሰጥ ለነበረው የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለመፈተን በስፍራው ለተገኛችሁ እና የከተማ አስተዳደሩን አቅጣጫ በፍፁም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በመቀበል ውሳኔውን ላከበራችሁ ሰራተኞች በሙሉ የላቀ ምስጋናውን እያቀረበ ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ ይጠይቃል።
በቀጣይም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑንም ቢሮው ያስታውቃል።
*******
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለአመራሮች ፣ ለባለሙያዎች እና ለሰራተኞች ፈተና እንዲሰጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊነት በመስጠት ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ቀን ማለትም በ 12/04/2016 ዓ.ም ፈተና ለመፈተን ሙሉ ዝግጅቱን ቢያጠናቅቅም ፈተናው የ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ባጋጠመው ቴክኒካል ችግር ምከንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ አይዘነጋም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በእለቱ ከረፋዱ 5:00-11:30 በፍጹም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እና በትእግስት የፈተናውን መሰጠት ስትጠባበቁ ለነበራችሁ የ ከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞች በሙሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የላቀ ምስጋናውን እያቀረበ ነገር ግን በእለቱ በሰራተኛው ላይ ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ ይቅርታ ይጠይቃል።
በተያያዘም ተፈታኞች በተረጋገጠ ሰላም አና በተረጋጋ ስሜት ፈተናውን እንዲወስዱ የተለመደ ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን ላሳየው እና የሰላም አርበኛ ለሆነው የመንግስት ሰራተኛ በሙሉ ቢሮው ምስጋናን ይቸራል።
በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩን አቅጣጫ በመቀበል የትራንስፖርት አቅርቦት በማመቻቸት፣የትራንስፖርት ፍሰቱን በማሳለጥ እና ሰላም እና ፀጥታን በማስጠበቅ ሙሉ ድጋፍ ላደረጋቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ቢሮ ከፍ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል።
በቀጣይም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን እያስታወቀ ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በ ኦረንቴሽን ወቅት የተቀመጡ መስፈርቶችን በሙሉ አሟልተው ለፈተና እንዲገኙ ቢሮው ጥሪ ያቀርባል።
በተመሳሳይም የተዘጋጀው ፈተና በቴክኒክ ችግር ምክንያት በመሰረዙ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይቅርታ መጠየቁም አይዘነጋም።
Repost from Yeka Education
👆👆👆👆👆👆
👆👆👆👆👆👆
ማስታወቂያ
✅የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ለ2016 ትምህርት ዘመን መምህራንን አወዳድሮ ለመቅጠር በቀን 14/03/2016 ዓ.ም ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ መሰረት በONLINE ምዝገባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
✅በመሆኑም በመመረቂያ ነጥባችሁ የተመረጣችሁ የትምህርት ማስረጃችሁን ለማጣራትና ቅጥር ለመፈፀም _ ስም _ ዝርዝራችሁ በቴሌግራም የተለቀቀላችሁ በሙሉ የትምህርት ማስረጃችሁን በመያዝ በዳግማዊ ምኒሊክ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ከቀን 11/04/2016 ዓ.ም እስከ 12/04/2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡
👉ማሳሰቢያ፡- ማሟላት ያለባችሁ መስፈርት
1. የትምህርት ማስረጃ ኦርጂናልና ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ከ3 ወር ያልበለጠ አገልግሎት በማፃፍና
2. በስራ ልምድ የተመዘገባችሁ የቅጥር ዘመን ከ2010 ዓ.ም እስከ 2016 ዓ.ም ብቻ ሆኖ ከ3 ወር ያልበለጠ የአገልግሎት ልምድ በማፃፍ ይዛችሁ መቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡
3. PGDT ኮርስ የወሰዳችሁ ኦርጂናልና ፎቶ ኮፒ ማቅረብ
4. በመንግስት ትምህርት ተቋም የተማራችሁ ብቻ መሆን አለባችሁ፡፡
ጉዳዩ፡- ለጤናና ሰ/ማጎልመሻ ትምህርት የሜዳ ላይ የተግባር ትምህርት ዕቅድ ናሙና መላክን ይመለከታል
✅መምህራን ወደ ክፍል ዉስጥ ገብተዉ ከማስተማራቸዉ በፊት ዕለታዊ ዕቅድ ከዓመታዊ ዕቅድ ጋር በሚጣጣም ሁኔታ አዘጋጅተዉ ማስተማር ከሙያዊ ስነ-ምግባር አንዱ በመሆኑ የሁሉም ትምህርት ክፍል መምህራን ተመሳሳይነት ያለዉን ዕለታዊ ዕቅድ በማዘጋጀት የዕለት ሥራቸዉን እንዲተገብሩ የዕቅድ አዘገጃጀት ናሙና ከዚህ በፊት መላካችን ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን የጤናና ሰዉነት ማጎልመሻ ትምህርት የሜዳ ላይ የተግባር ትምህርት ዕቅድ ክፍል ዉስጥ ከሚሰጥ ዕቅድ በባህሪዉ የተለየ በመሆኑ ከተግባር ትምህርት አሰጣጥ ጋር የሚጣጣም ዕለታዊ ዕቅድ ናሙና መላክ አስፈልጓል፡፡
✅ስለሆነም ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ በተደረገዉ ዕለታዊ የዕቅድ ናሙና መሰረት ከ1ኛ-6ኛ ክፍል የሚያስተምሩ መምህራን በአማርኛ የተዘጋጀዉን እንዲጠቀሙ፣ ከ7ኛ-10ኛ ክፍል የሚያስተምሩ መምህራን በእንግሊዘኛ የተዘጋጀዉን ዕለታዊ የዕቅድ ናሙና በማዘጋጀት እንዲያስተምሩ አያይዘን የላክን ሲሆን ለት/ቤቶች በእናንተ በኩል በማዉረድ ተግራዊ እንዲሆን እናሳስባለን::
Repost from ወቅታዊና ትክክለኛ የትምህርት መረጃ መለዋወጫ
የ6ኛ ክፍል የመለማመ ጥያቄዎች
አዘጋጅ
በአብዮት እና በክላስተሩ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀ
ተማሪዎች በዚህ ወር የሚፈተኑትን content ብቻ ማሰራት ተገቢ ነው
✅በት/ቤቶቻችን በቀጣይ ትኩረት ልንሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮች
👉የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት የትምህርት ይዘት ሽፋን (Portion covarage) ያለበትን ደረጃ መከተታል
👉 ሰላማዊ መማር መስተማሩ ባለበት እንዲቀጥል እና ምንም አይነት ክፍተት እንዳይፈጠር ትኩረት መስጠት
👉 ክበባት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መግባታቸውን በቂ ድጋፍና ክትትል ማድረግ
👉 ተከታታይ ምዘና በአግባቡ እየተከናወነ መሆኑን መከታተል
👉ጥያቄና መልስ ውድድር በእቅድ እና በፕሮግራም በሁሉንም የክፍል ደረጃዎች እየተካሄደ መሆኑን ማረጋገጥ
👉ለ6ኛ፣8ኛእና12ኛ ክፍል ተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በት/ቤት እና በወረዳ ደረጃ በማድረግ በክፍለ ከተማ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር በቂ ዝግጀት ማድረግ
👉 በት/ቤታችን የመጽሀፍ ግምገማ በወረደው ቅጽ መሰረት በሁሉም የት/ት አይነቶች መካሄዱን ማረጋገጥና ለክ/ከተማ ማሳወቅ
👉 የተቋቋሙ ክበባት ተጨባጭ ስራ እየሰሩ ስለመሆኑና መረጃ መያዙን ማረጋገጥ
👉 ቤተ ሙከራ ፣ቤተ መጽሀፍት፣አይሲቲ ላብ እና የት/ት ማበልጸጊያን በአግባቡ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ማረጋገጥ
👉 ለሱፐርቪዥን ስራዎችና ችግር ፈች ጥናትና ምርምር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ማረጋገጥ
👉የከተማ ግብርናን ትኩረት በመስጠት ከነበረት በተሻለ ሁኔታ ማስቀጠል
👉የመምህራንና ተማሪዎች ሳይንስና ፈጠራ ስራ ልዩ ትኩረት በመስጠት በሁለቱም ስርአተ ት/ት አቅዶ እና በቂ ግብአት አሟልቶ መስራት
👉 የት/ት ክፍለ ጊዜ ብክነት እንዳይፈጠር ጥረት እየተደረገ ስለመሆኑና የባከነ ክ/ጊዜ በፍጥነት እንዲካካስ ማድረግ
👉 በቅዳሜ ትምህርት ለ6ኛ፣8ኛ እና12ኛ ክፍል ተማሪዎች እገዛ እየተደረገ ስለመሆኑ
👉 የማታ ትምህርት(ላላቸው) እና የሬዲዮ ትምህርት በአግባቡ እየተተገበረ መሆኑን ማረጋገጥ
