1 497
Subscribers
+224 hours
+107 days
+2630 days
Posts Archive
ኢንጅነር ታከለ ፤ ያለ ባህር በር ባለቤትነት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ሙሉ ውጤታማ መሆን አይቻልም አሉ
ያለ ባህር በር ባለቤትነት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ውጤታማ አገር መሆን እንደማይቻል የኢትዮ ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ተናገሩ።
መንግሥት የሎጂስቲክስ ሰንሰለቱን ለማሳለጥ ወደቦች ማደራጀት፣ መርከቦችን መግዛት እና የየብስ ትራንስፖርት አውታሮችን ማስፋፋት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ታከለ ኡማ ጠቁመዋል። ሆኖም አገሪቱ እየተጠቀመችበት ያለው የሌላ አገር የባህር በርና ወደብ መሆኑ ትልቅ ፈተና እንደሆነ አስገንዝበዋል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
በቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን ጣቢያ የደረሰውን አደጋ ተከትሎ የልማት ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተቋረጡ
በለንደን የአክሲዮን ልውውጥ ገበያ የተመዘገበው “ከፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር” የተባለው የማዕድን ኩባንያ በኢትዮጵያ በዋናነት በሚያስተዳድረው የቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ላይ የነበሩትን ሁሉንም የልማት ስራዎች በድንገት አገደ።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ከሶስት ቀን በፊት በጸጥታ አስከባሪዎች እና በአካባቢው ማህበረሰብ መካከል በተከሰተ ከባድ የጸጥታ ችግር ሳቢያ በርካታ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን እና ቢያንስ አንድ የኩባንያው ሰራተኛ መሞቱን ተከትሎ ነው።
ኩባንያው ለሰራተኞች እና ለአካባቢው ማህበረሰብ አስተማማኝ ሰላም እስኪሰፍን ድረስ የመስክ ስራዎች እንዳቋረጠ አስታውቋል።
ምንም እንኳን የኢትዮጵያ እና የኦሮሚያ ክልል መንግስታት የፕሮጀክቱ አጋሮች በመሆን እየሰሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ወጪዎችን በጥብቅ ለመቆጣጠር እና የፋይናንስ እንቅስቃሴዎችን ለጊዜው ለማቆም ታቅዷል።
ኩባንያው በ2028 የመጀመሪያ አጋማሽ ወርቅ ማምረት ለመጀመር አቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን በተፈጠረው ጊዜያዊ እገዳ በጊዜ ሰሌዳው ላይ ስለሚኖረው ተጽዕኖ ለመናገር ገና መሆኑን ገልጿል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
አሜሪካ በአዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ላይ ትልቅ ኢንቨስትመንት ልታደርግ ነው
የዩናይትድ ስቴትስ ረዳት ሴክሬተሪ ጋርሲያ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰዉ ጋር በመሆን የሁለትዮሽ የንግድ አቪዬሽን ትብብርን እና ከአየር መንገዱ ጋር ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ለማጠናከር መወያየታቸው ታዉቋል።
አሜሪካ በአዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ የአሜሪካን ኢንቨስትመንት እና ቴክኖሎጂ መሰረት ለማድረግ ጠንካራ ቁርጠኝነት እንዳላት ገልጻለች።
የዩናይትድ ስቴትስ የልማት ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ይህንን እውን ለማድረግ ለአውሮፕላን ማረፊያው እና ለአካባቢው አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ትልቅ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ማቀዱ ተጠቁሟል።
ይህ ኢንቨስትመንት በሁለቱ ሀገራት መካከል እውነተኛ ቀጥተኛ በረራዎችን እውን በማድረግ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን እና የስራ እድሎችን ለመፍጠር ያስችላል ተብሎ ይጠበቃል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
ዓለም አቀፍ የባህር ማጓጓዣ ሥርዓት በጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ስጋት ውስጥ ወድቋል
የዓለም አቀፍ የባህር ማጓጓዣ ባለሥልጣናትና ከ18 አገራት የተውጣጡ የባህር ትራንስፖርት አካላት ጥምረት፣ እየጨመረ በመጣው የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና የንግድ ገደቦች ሳቢያ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ሊከፋፈል እንደሚችል አስጠነቀቁ።
በአሁኑ ወቅት ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው ዓለም አቀፍ ንግድ በባህር ማጓጓዣዎች የሚከናወን ሲሆን፤ ተፎካካሪ አገራት የሚዘረጉዋቸው ተቃራኒ ደንቦች እና ማዕቀቦች ዓለም አቀፍ አቅርቦት ሰንሰለትን ዋጋ እና አለመረጋጋት እያባባሱት መሆኑ ተገልጿል። ይህ ሁኔታ በባህር ላይ ያለውን ደኅንነትና አመኔታ ሊያሳጣው የሚችል የሁለትዮሽ ሥርዓት ሊፈጥር እንደሚችልም ተመላክቷል።
የባህር ማጓጓዣ ባለሥልጣናቱ የገበያ መረጋጋትን ለመጠበቅና የጋራ የባህር ማጓጓዣ ደረጃዎችን ለማስጠበቅ አገራት አፋጣኝ ዓለም አቀፍ ትብብር ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
ቅዳሜ ገበያን በቴሌግራም ያዳምጡ
ጷግሜ 2/13/2018
ርዕሰ ጉዳይ 👉 የቤት ችግር ይፈታል የተባለው እቅድ እውን ስኬታማ ይሆናል❓
👉 የቤቶች ገንዘብ አቅርቦት ኮርፖሬሽን እና የቤቶች ፈንድ መቋቋም ምን ይጠቅማል ሰፊና ልዩ ትንታኔ ይዘናል‼️
👉 ዩጋንዳ ነዳጅ ለውጭ ገበያ ልታቀርብ መሆኑን እወቁልኝ ብላለች‼️
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
የአፍሪካ ትልቁ አክሲዮን ሽያጭ፡
አሊኮ ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያውን ለአክሲዮን ሽያጭ የሚያበቃውን ሰነድ ፈረሙ
የአፍሪካ ቀዳሚዉ ባለጸጋ አሊኮ ዳንጎቴ የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ እና ፔትሮኬሚካል ኩባንያ የመጀመሪያ ደረጃ አክሲዮን ሽያጭ (IPO) የምዝገባ ሰነድ ተፈራረሙ። ይህ ሂደት አህጉሪቱ እስካሁን ካየቻቸው ትልልቅ የአክሲዮን ሽያጮች አንዱ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በተፈረመው የውል ስምምነት መሰረት ኩባንያው 4.1 ቢሊዮን አክሲዮኖችን በአንድ አክሲዮን 525 ናይራ (0.40 ዶላር) ዋጋ ለገበያ በማቅረብ 1.6 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ያለመ ሲሆን፣ ይህም የማጣሪያውን የገበያ ዋጋ 49 ቢሊዮን ዶላር ያደርሰዋል። የአክሲዮን ሽያጩ ከሴፕቴምበር 14 እስከ ኦክቶበር 13 ክፍት የሚሆን ሲሆን፣ በህዳር ወር አክሲዮኑ በገበያ ላይ ይሆናል ተብሏል።
ይህ የገበያ ዕድል አነስተኛ ባለሀብቶችን ጨምሮ በርካታ ተሳታፊዎችን ለመሳብ የታለመ ነው። ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ የተወሰነው ክፍል የማጣሪያውን ዕለታዊ የማምረት አቅም እስከ 2028 ዓ.ም ከነበረበት 700 ሺህ በርሜል ወደ 1.4 ሚሊዮን በርሜል ከፍ ለማድረግ ይውላል።
እንደ ኩባንያዉ ከሆነ ፤ ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የተደረገበት እና ለ11 ዓመታት የተገነባው ማጣሪያ ናይጄሪያ ከነዳጅ አስመጪነት ወደ ላኪነት እንዲሸጋገራት አስችሏል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
የአፍሪካ ትልቁ አክሲዮን ሽያጭ፡ አሊኮ ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያውን ለአክሲዮን ሽያጭ የሚያበቃውን ሰነድ ፈረሙ
የአፍሪካ ቀዳሚዉ ባለጸጋ አሊኮ ዳንጎቴ የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ እና ፔትሮኬሚካል ኩባንያ የመጀመሪያ ደረጃ አክሲዮን ሽያጭ (IPO) የምዝገባ ሰነድ ተፈራረሙ። ይህ ሂደት አህጉሪቱ እስካሁን ካየቻቸው ትልልቅ የአክሲዮን ሽያጮች አንዱ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በተፈረመው የውል ስምምነት መሰረት ኩባንያው 4.1 ቢሊዮን አክሲዮኖችን በአንድ አክሲዮን 525 ናይራ (0.40 ዶላር) ዋጋ ለገበያ በማቅረብ 1.6 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ያለመ ሲሆን፣ ይህም የማጣሪያውን የገበያ ዋጋ 49 ቢሊዮን ዶላር ያደርሰዋል። የአክሲዮን ሽያጩ ከሴፕቴምበር 14 እስከ ኦክቶበር 13 ክፍት የሚሆን ሲሆን፣ በህዳር ወር አክሲዮኑ በገበያ ላይ ይሆናል ተብሏል።
ይህ የገበያ ዕድል አነስተኛ ባለሀብቶችን ጨምሮ በርካታ ተሳታፊዎችን ለመሳብ የታለመ ነው። ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ የተወሰነው ክፍል የማጣሪያውን ዕለታዊ የማምረት አቅም እስከ 2028 ዓ.ም ከነበረበት 700 ሺህ በርሜል ወደ 1.4 ሚሊዮን በርሜል ከፍ ለማድረግ ይውላል።
እንደ ኩባንያዉ ከሆነ ፤ ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የተደረገበት እና ለ11 ዓመታት የተገነባው ማጣሪያ ናይጄሪያ ከነዳጅ አስመጪነት ወደ ላኪነት እንዲሸጋገራት አስችሏል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
+1
የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት 17.59 ቢሊዮን ብር ገቢ ማስመዝገቡን አስታወቀ
የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት 17.59 ቢሊዮን ብር ገቢ ማስመዝገቡን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸናፊ ዳባ ገለጹ።
ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ግምገማ ባደረገበት መድረኩ ላይ እንደተገለጸው ፣ የዘንድሮው የገቢ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ18 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፣ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት ተችሏል።
በተጨማሪም ኮርፖሬሽኑ የጥራት፣ የሥራ ቦታ እና የአካባቢ ደህንነት ISO ስታንዳርዶችን በማሟላት በሶስቱም የብቃት ማረጋገጫ ማግኘቱ፣ እንዲሁም ተሽከርካሪዎቹን በጂፒኤስ (GPS) በመቆጣጠር ቀልጣፋ እና ወጪ ቆጣቢ አሰራር መዘርጋቱ ተመላክቷል። ኮርፖሬሽኑ በመንገድ፣ በሕንፃ፣ በመጠጥ ውሃ እና በመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን፣ ከ3 ሺህ በላይ ቋሚና ጊዜያዊ ሰራተኞችን በመያዝ ለ51 ሺህ ወገኖች የስራ ዕድል መፍጠሩ ተገልጿል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
የእለቱ የውጭ ምንዛሬ ተመን (ጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም)
👉👉👉 በዓለም አቀፍ ገንዘብ አስተላላፊዎች ገንዘብ ሲላክልዎ ዳሸን ባንክ በእለቱ የምንዛሪ ተመን የሚሰላ የ10% የማበረታቻ ቦነስ ያበረክትልዎታል።
#𝐭𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦 #𝐛𝐚𝐧𝐤 #𝐝𝐚𝐢𝐥𝐲 #𝐜𝐮𝐫𝐫𝐞𝐧𝐜𝐲
የዓለም ባንክ ቡድን የ2.5 ትሪሊዮን ዶላር የንግድ ፋይናንስ ክፍተትን ለመሙላት የሚያስችሉ አዳዲስ ስልቶችን ይፋ አደረገ
በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈጠረው የ2.5 ትሪሊዮን ዶላር የንግድ ፋይናንስ ክፍተት በማደግ ላይ ባሉ ገበያዎች የሚገኙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ጥቃቅንና መካከለኛ ንግዶች ፋይናንስ እንዳያገኙ ማድረጉ ተገልጿል።
ይህንን ክፍተት መሙላትም በዛሬው ዕለት ትልቁ የልማት ፈተና መሆኑን የዓለም ባንክ ቡድን አዲስ ጥናት አመልክቷል።
በአፍሪካ 90 በመቶ የሚሆኑት ኩባንያዎች ትናንሽና መካከለኛ ድርጅቶች በመሆናቸው፣ የዚህን የፋይናንስ ክፍተት መዝጋት ተጨማሪ የስራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ለማጠናከር እና የፋይናንስ አካታችነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል። በተለይም ትንንሽ እና አዲስ የተቋቋሙ ንግዶችን ተደራሽ ማድረግ ትልልቅ ለውጦችን እንደሚያመጣ ጥናቱ አሳይቷል።
የዓለም ባንክ ቡድን ይህንን ችግር ለመቅረፍ በባለሙያዎች እና በተለያዩ ተቋማት አማካኝነት ሰፊ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ኪሳራ ቢገጥመውም ከፍተኛ ትርፍ አስመዘገበ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከፍተኛ የትርፍ ዕድገት እና የንብረት ማስፋፋት ማሳየቱን የኦዲት ሪፖርቱ አመለከተ። በኦዲት አገልግሎት ኮርፖሬሽን የተካሄደው እና በቦርድ ሰብሳቢ አህመድ ሽዴ እና በባንኩ ፕሬዚዳንት አብይ ሳኖ የጸደቀው ይኸው የፋይናንስ ሪፖርተር ይፋ ሆኗል።
በሪፖርቱ መሠረት የባንኩ ከታክስ በኋላ የተጣራ oትርፍ 75.8 በመቶ በማደግ ከቀድሞው 22 ቢሊዮን ብር ወደ 38.71 ቢሊዮን ብር ከፍ ብሏል። አጠቃላይ የወለድ ገቢ 30.7 በመቶ ጭማሪ አሳይቶ 132.06 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ የወለድ ወጪዎች ግን በ1.8 በመቶ ብቻ አድገው 45.31 ቢሊዮን ብር ደርሰዋል።
ከወለድ ውጭ ያለው ገቢም 77.5 በመቶ በማደግ 60.52 ቢሊዮን ብር ደርሷል። ይሁን እንጂ የሰራተኞች እና ሌሎች የሥራ ማስኬጃ ወጪዎች በእጥፍ ጨምረው 113.71 ቢሊዮን ብር መድረሳቸው ተጠቁሟል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
አዲስ አበባ እና ዋሽንግተን የሁለትዮሽ ንግድን፣ ኢንቨስትመንትን እና የጸጥታ ትብብርን ለማጠናከር መከሩ
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሰክሬተሪ ፍራንክ ጋርሺያ ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። በውይይታቸው ሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነትን፣ ንግድን፣ ኢንቨስትመንትን እና አፍሪካ ቀንድ የጸጥታ ትብብር ዙሪያ መምከራቸው ነዉ የተገለጸው።
ግንኙነቱ ባለፈው ግንቦት 2026 በዋሽንግተን በተካሄደው የአሜሪካ-ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ የተዋቀረ ውይይት ቀጣይነት የተከናወነ ነው። በዚህም የንግድ ትስስርን ማስፋፋት እና ለግል ዘርፍ ኢንቨስትመንት ሰፊ ዕድሎችን መፍጠር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል። ረዳት ሰክሬተሪው የቀጠናውን ሰላም እና የኢኮኖሚ ዕድገት ማጠናከር ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተዋል።
በተጨማሪም በሂደቱ የጸጥታ ሁኔታዎች፣ የመከላከያ ትብብር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ተደርጓል። ረጅም ጊዜ የሚወስዱ ግጭቶች የኢኮኖሚ ልማትን እና የባለሀብቶችን መተማመን እንደሚጎዱ የገለጸው ወገን፣ ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የኢኮኖሚ ቅድሚያ ሰጪዎቻቸውን ከቀጠናዊ ጸጥታ ጋር ለማቀናጀት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
የእለቱ የውጭ ምንዛሬ ተመን (ጳጉሜን 2 ቀን 2018 ዓ.ም)
👉👉👉 በዓለም አቀፍ ገንዘብ አስተላላፊዎች ገንዘብ ሲላክልዎ ዳሸን ባንክ በእለቱ የምንዛሪ ተመን የሚሰላ የ10% የማበረታቻ ቦነስ ያበረክትልዎታል።
#𝐭𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦 #𝐛𝐚𝐧𝐤 #𝐝𝐚𝐢𝐥𝐲 #𝐜𝐮𝐫𝐫𝐞𝐧𝐜𝐲
የአሜሪካ የግሪን ካርድ ሎተሪ ዕድለኞች የፍርድ ቤት ድል እና አዲስ እገዳ
የአሜሪካ ፌዴራል ፍርድ ቤት በኢትዮጵያና በሌሎች አፍሪካ ሀገራት የዲቪ ሎተሪ ዕድለኞች ላይ ተጥሎ የነበረውን ገደብ ውድቅ በማድረግ ውሳኔ አሳለፈ።
በካሊፎርኒያ የፌዴራል ፍርድ ቤት ዳኛ ኤድዋርድ ዳቪላ የቪዛ ሂደቱን አግደው የነበሩ መመሪያዎችን በጊዜያዊነት እንዲቆሙ ወስነዋል።
ይህ ውሳኔ በዲቪ-2026 ፕሮግራም ከተመዘገቡት ከ53 ሺህ በላይ አፍሪካውያን መካከል ከ3 ሺህ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 41 ሺህ የሚጠጉ አመልካቾች ተስፋ የፈነጠቀ ነው።
ሆኖም ይህን ፍትህ ተከትሎ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ከጸጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ የቪዛ አሰጣጡን በድጋሚ ማገዱ አዳዲስ ስጋቶችን ፈጥሯል። አመልካቾች ሰነዶችን ማቅረብ እና ቃለ መጠይቅ ማድረግ ቢችሉም፣ መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከመጠናቀቁ በፊት ቪዛ ካልተሰጣቸው እድሉ ሊባክን ይችላል የሚል ስጋት አለ። የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ህጋዊ እንቅፋቶችን ያስወገደ ቢሆንም፣ አዲሱ እገዳ ዕድለኞቹን ባለበት እንዲቆሙ አድርጓል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
#DiversityVisa
#DVapplicants
ኢትዮ ቴሌኮም ከ553 ሚሊዮን ብር በላይ የማህበራዊ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አስታወቀ
ካምፖኒው ለ50 የበጎ አድራጎት ተቋማት ድጋፍ አድርጓል
ካምፓኒው ነሐሴ 30 ቀን 2018 የበጎነት መርኃ ግብር በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚገኙ 50 የበጎ አድራጎት ተቋማት የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በዚህም ድጋፍ በእነዚህ የበጎ አድራጎት ማዕከላት ውስጥ ለሚገኙ 22 ሺህ 212 አረጋዊያን፣ ህጻናት፣ እናቶች፣ አቅመ ደካሞች እና አካል ጉዳተኞች ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
ካምፖኒው የዘንድሮውን ጨምሮ ባለፉት አምስት ተከታታይ ዓመታት በተመሳሳይ የበጎ አድራጎት መርኃ ግብሮችን በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚገኙ ከ117 በላይ ለሚሆኑ የበጎ አድራጎት ተቋማት መሰል ድጋፎችን አድርጓል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ኩባንያው በዘንድሮው "ለነገ ተስፋዎች" መርሃ ግብር በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ እና አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ያደረገ 113 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለመማር ማስተማሩ የሚያግዙ ድጋፎች ማድረጉን ገልጿል።
ኩባንው ዘላቂ እሴት በመፍጠርና ኃላፊነት የተሞላበት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ኩባንያነት ሚናውን ለማጠናከር አካባቢያዊ ማህበራዊና አስተዳደራዊ (ESG) መርሆዎችን መተግበሩን እንደሚቀጥል የተጠቆመ ሲሆን በአካባቢ ዘላቂነት (environmental sustainability)፣ በአረንጓዴ ኃይል፣ በኃይል ቆጣቢነትና በካርበን ልህቀት ቅነሳ ላይ እንደሚሰራ አስታውቋል።
በማህበራዊ ተጽዕኖ ዘርፍ ዲጂታል አካታችነት፣ ተመጣጣኝ አገልግሎቶች፣ የፋይናንስ አካታችነት፣ የሠራተኞች ልማትና የማህበረሰብ ኢኒሸቲቮች እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።
የካምፖኒው ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በተያዘው በጀት አመት ከ553 ሚሊዮን ብር በላይ የማህበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስችል ስራ እንደሚከናወን አስታውቀዋል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
#ethiotelecom
ኢትዮ ቴሌኮም ከ553 ሚሊዮን ብር በላይ የማህበራዊ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አስታወቀ
ካምፖኒው ለ50 የበጎ አድራጎት ተቋማት ድጋፍ አድርጓል
ካምፓኒው ነሐሴ 30 ቀን 2018 የበጎነት መርኃ ግብር በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚገኙ 50 የበጎ አድራጎት ተቋማት የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በዚህም ድጋፍ በእነዚህ የበጎ አድራጎት ማዕከላት ውስጥ ለሚገኙ 22 ሺህ 212 አረጋዊያን፣ ህጻናት፣ እናቶች፣ አቅመ ደካሞች እና አካል ጉዳተኞች ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
ካምፖኒው የዘንድሮውን ጨምሮ ባለፉት አምስት ተከታታይ ዓመታት በተመሳሳይ የበጎ አድራጎት መርኃ ግብሮችን በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚገኙ ከ117 በላይ ለሚሆኑ የበጎ አድራጎት ተቋማት መሰል ድጋፎችን አድርጓል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ኩባንያው በዘንድሮው "ለነገ ተስፋዎች" መርሃ ግብር በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ እና አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ያደረገ 113 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለመማር ማስተማሩ የሚያግዙ ድጋፎች ማድረጉን ገልጿል።
ኩባንው ዘላቂ እሴት በመፍጠርና ኃላፊነት የተሞላበት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ኩባንያነት ሚናውን ለማጠናከር አካባቢያዊ ማህበራዊና አስተዳደራዊ (ESG) መርሆዎችን መተግበሩን እንደሚቀጥል የተጠቆመ ሲሆን በአካባቢ ዘላቂነት (environmental sustainability)፣ በአረንጓዴ ኃይል፣ በኃይል ቆጣቢነትና በካርበን ልህቀት ቅነሳ ላይ እንደሚሰራ አስታውቋል።
በማህበራዊ ተጽዕኖ ዘርፍ ዲጂታል አካታችነት፣ ተመጣጣኝ አገልግሎቶች፣ የፋይናንስ አካታችነት፣ የሠራተኞች ልማትና የማህበረሰብ ኢኒሸቲቮች እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።
የካምፖኒው ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በተያዘው በጀት አመት ከ553 ሚሊዮን ብር በላይ የማህበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስችል ስራ እንደሚከናወን አስታውቀዋል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
#ethiotelecom
ሲጠበቅ የነበረው የአኪር ኮንስትራክሽን የሃራጅ ጨረታ ታገደ!
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበለት የመቃወም አቤቱታ መሰረት ስመ ጥር የሆነው አኪር ኮንስትራክሽን ላይ እሮብ ነሀሴ 27 ቀን ሊደረግ የነበረው የሃራጅ ጨረታ ተሰርዟል፡፡
ዝርዝሩ በሊንኩ https://tinyurl.com/mr2bu62m
#etbusinessview #ቅዳሜገበያ #Ethiopia
+3
አገልግሎቴን በዲጂታል የታገዘ እያደረኩ ነው ሲል የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አስታወቀ
ተቋሙ Digital ESL ”የደንበኛ ራስ አገዝ ዲጂታል አገልግሎት (Customer Self Service Web & Mobile App) በይፋ አስመርቋል፡፡
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የአገልግሎት አሰጣጡን ሙሉ በሙሉ ዘመናዊና ፈጣን የሚያደርገውን ”Digital ESL”የደንበኛ ራስ አገዝ ዲጂታል አገልግሎት (Customer Self Service Web App) በይፋ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ ችሏል።
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ በፕሮግራሙ ላይ እንደተናገሩት መተግበሪያው ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው በሞባይል ስልካቸው ወይም በዌብ ፖርታሉ አማካኝነት ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን በፍጥነትና በሙሉ ግልጽነት ማግኘት የሚችሉበትን ዘመናዊ አሰራርን የዘረጋ ነው፡፡
መተግበሪያው ቀደም ሲል የነበረውን አላስፈላጊ የደንበኞች የጊዜ ብክነት እና ወጪ ሙሉ በሙሉ ያስቀራል ተብሎለታል ።
ከዚህም በተጨማሪ ተቋሙ የሚሰጠውን አገልግሎት ከሰው ንክኪ ነፃ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ያስችላል ነው የተባለው፡፡
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia
#EthiopianShippingandLogistics
