en
Feedback
Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Open in Telegram
888
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+230 days
Posts Archive
ቀስተ-ደመና ቅድመ-አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት "እያንዳንዱ ቤት ዩኒቨርስቲ ነው፤ወላጆችም መምህራን ናቸው።" በሚል መሪ ቃል የ2ኛ መንፈቀ-ዓመት የወላጅ ጉባኤ አካሔደ። ሠኔ
+1
ቀስተ-ደመና ቅድመ-አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት "እያንዳንዱ ቤት ዩኒቨርስቲ ነው፤ወላጆችም መምህራን ናቸው።" በሚል መሪ ቃል የ2ኛ መንፈቀ-ዓመት የወላጅ ጉባኤ አካሔደ።    ሠኔ 30/2016ዓ.ም) ከተወያየንባቸው አጀንዳዎች ውስጥ 1 ውጤት ትንተና እና የደረጃ ተማሪዎች እውቅና ሽልማት 2 ሠላማዊ መማር ማስተማር 3 መልካም አስተዳደርና ኪራይ ሰብሳቢነት 4 የህብረተሠብ ተሳትፎ እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በተመለከተ "ውይይት በማድረግ የተሳካ ተግባቦት ላይ ደርሠናል።

+1
Shared by One Read - an all-in-one file viewer: https://st.simplehealth.ltd/uAJjyu

በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ ወረዳ-09 ስር የሚገኘው ቀስተ-ደመና ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 124 ተማሪዎችን አስመረቀ። (23/10/2016ዓ.ም) በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ ወረዳ-09 ስር የ
+9
በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ ወረዳ-09 ስር የሚገኘው ቀስተ-ደመና ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 124 ተማሪዎችን አስመረቀ። (23/10/2016ዓ.ም) በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ ወረዳ-09 ስር የሚገኘው ቀስተ-ደመና ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው ዕለት ወንድ 71 ሴት 53 ድምር 124 ተማሪዎችን አስመረቀ። በዕለቱ በተመራቂ ተማሪዎች የተለያዩ ማራኪ ትዕይንቶች ቀርበዋል። ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ።

በ2017 የትምህርት ዘመን  ትምህርት ቤቶች ምዝገባ ሲያካሂዱ  የልደት ሰርተፍኬት መቀበል አስገዳጅ ሆነ የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ ስርዓት ዘመናዊ የትምህርት ስርዓት መዘርጋት እንዲቻል  እንዲሁም ያልተመዘገበ ልደት ክምችትን ሙሉ ለሙሉ ለማቅለል የልደት ምዝገባ ሰርተፍኬትን በከተማዋ ባሉ  ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ቅበላ የምዝገባ ቅድመ ሁኔታ አሰራር ስርዓት አስገዳጅ መሆኑን አስታውቋል። በመሆኑም እስካሁን የልደት ምዝገባ ያላከናወኑ ህፃናት እና ተማሪዎች በወረዳ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ቀርበው መመዝገብ እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ሲቪል ምዘገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዮናስ ዓለማየሁ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ከከተማው የትምህርት ቢሮ ጋር ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን ከመደበኛ ቀናት በተጨማሪ  ከሰኔ 22 ጀምሮ ዘወትር ቅዳሜ ሙሉ ቀን የዚህ ምዝገባ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑንም ሃላፊው ገልጸዋል።በምዝገባ ወቅት ወላጆች ነዋሪ የሆኑበት የወረዳ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት  የወላጆች ማንነትን የሚገልፅ የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ ወይም ፓስፖርት፣ ከወረዳው አስተዳደር መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ  የድጋፍ ደብዳቤ ወይም ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት ባልደረባነታቸው እና ዜግነት የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤና የመስሪያ ቤቱን መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል። የህፃኑ ወላጆች በህይወት ካሉ አባት እና እናት ሁለቱም በአካል መቅረብ ያለባቸው ሲሆን ልደቱን ለማስመዝገብ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከሁለት አንዳቸው ያልቻሉ ሲሆን አንዳቸው ለሌላቸው ልዩ የልደት ውክልና በመስጠት ማስመዝገብ ይቻላሉ።  ከወላጆቹ አንዱ በህይወት የሌለ ከሆነ ደግሞ  በህይወት ያለው ወላጅ የሟች ወላጅን ህጋዊ የሞት ማስረጃ ሲያቀርብ ልደቱ ይመዘገባል፡፡ ልደቱ ሲመዘገብ የህፃኑ አባት ያልታወቀ እንደሆነ የእናትየዋ አባት ስም የልጁ አባት ስም ሲሆን የእናትየዋ አያት ስም ደግሞ የልጁ አያት ስም ሆኖ ይመዘገባል፡፡  ከወላጆቹ አንዱ የውጪ አገር ዜጋ ከሆነ የህፃኑ ዜግነት በኢትዮጵያዊ ወላጅ ውሳኔ መሰረት የሚመዘገብ መሆኑም ተነግሯል። በመሆኑም ወላጆች ልጆቻቸውን  ለ2017 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ሲያካሂዱ  የልደት ሰርተፍኬት  አስገዳጅ  እንደሆነ ሊገነዘቡ  እንደሚገባ አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja

የ2017 የትምህርት ዘመን የተከለሰ የትምህርት ካላንደር (ሰኔ11/2016 ዓ.ም)