ትንቢተ ሕዝቅኤል 7
Open in Telegram
#ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። #ፍጻሜ መጥቶአል፥ ፍጻሜ መጥቶአል፥ ነቅቶብሻል፤ እነሆ፥ ደርሶአል። #በምድር የምትቀመጥ ሆይ፥ ተራህ ደርሶአል፥ ጊዜ መጥቶአል፥ ቀን ቀርቦአል፤ የሽብር ቀን ነው እንጂ በተራራ ላይ ያለ እልልታ አይደለም። #አሁን በቅርብ መዓቴን አፈስስብሻለሁ፥ ቍጣዬንም እፈጽምብሻለሁ፥ እንደ መንገድሽም መጠን እፈርድብሻለሁ፥ ጕስቍልናሽንም ሁሉ አመጣብሻለሁ። ትን.ሕዝ 7÷5-8
Show more705
Subscribers
+124 hours
-37 days
-1030 days
Posts Archive
705
#𝘽𝙍𝙀𝘼𝙆𝙄𝙉𝙂
" የአይሁዶች አገር በጦርነት ላይ ነች - በአደገኛ ጦርነት ዉስጥ ነዉ ያለነዉ - ነገር ግን እናሸንፋለን - ጠላት ፈጽሞ የማያውቀውን ልዩ ያህል ኃይል እሳት ለኩሶ ጠላቱን እንዲመልስ ትዕዛዝ አስተላልፌአለሁ - ጠላታችን ታይቶ የማይታወቅ ዋጋ ይከፍላል"
ቤንያሚን ኔታንያሁ
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር
Join👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va5lw25ATRSnWUnJpp1Y
705
#𝘽𝙍𝙀𝘼𝙆𝙄𝙉𝙂
❗️ 🇮🇱🇵🇸 የፍልስጤም ታጣቂዎች የእስራኤል ጦር ጄኔራል መያዛቸውን ተናገሩ !
የሃማስ ታጣቂዎች አንድ የእስራኤል ጦር ጄኔራል መያዙንና ጀነራሉ የከረም ሻሎም መሻገሪያውን ጥሶ ከገባ በኋላ ለማምለጥ ሲሞክር ተይዞ እርቃኑን ወደ ጋዛ የተወሰደ መሆኑን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል።
👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va5lw25ATRSnWUnJpp1Y
705
#𝘽𝙍𝙀𝘼𝙆𝙄𝙉𝙂
❗️ በእየሩሳሌም የመስጂድ ድምጽ ማጉያዎች ሙስሊሞች በአጠቃላይ እንዲነሱ እና በእስራኤል ላይ “የተቀደሰ ጦርነት” ጂሀድ እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረቡ !
Join👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va5lw25ATRSnWUnJpp1Y
705
ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 7
==================
#የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ።
#አንተ የሰው ልጅ ሆይ፥ ጌታ እግዚአብሔር ለእስራኤል(እስራኤል ማለት ኢትዮጵያ ናት።) ምድር እንዲህ ይላል። ፍጻሜ፥ በምድሪቱ በአራቱ ማዕዘን ላይ ፍጻሜ ደርሶአል።
#አሁን ፍጻሜ በአንቺ ላይ ነው፥ ቍጣዬንም እሰድድብሻለሁ፥ እንደ መንገድሽም መጠን እፈርድብሻለሁ፥ ጕስቍልናሽንም ሁሉ አመጣብሻለሁ።
#ዓይኔም አይራራልሽም እኔም አላዝንም፤ መንገድሽንም አመጣብሻለሁ ርኵሰትሽም በመካከልሽ ይሆናል፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።#ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ክፉ ነገር፥ አንድ ክፉ ነገር፥ እነሆ፥ ይመጣል።#ፍጻሜ መጥቶአል፥ ፍጻሜ መጥቶአል፥ ነቅቶብሻል፤ እነሆ፥ ደርሶአል።#በምድር የምትቀመጥ ሆይ፥ ተራህ ደርሶአል፥ ጊዜ መጥቶአል፥ ቀን ቀርቦአል፤ የሽብር ቀን ነው እንጂ በተራራ ላይ ያለ እልልታ አይደለም።#አሁን በቅርብ መዓቴን አፈስስብሻለሁ፥ ቍጣዬንም እፈጽምብሻለሁ፥ እንደ መንገድሽም መጠን እፈርድብሻለሁ፥ ጕስቍልናሽንም ሁሉ አመጣብሻለሁ።
#ዓይኔም አይራራም እኔም አላዝንም፤ እንደ መንገድሽም መጠን አመጣብሻለሁ፥ ርኵሰትሽም በመካከልሽ ይሆናል፥ እኔም እግዚአብሔር የምቀሥፍ እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።
#እነሆ ቀኑ፥ እነሆ፥ መጥቶአል፤ ተራህ ወጥቶአል፤ ብትር አብቦአል፥ ትዕቢትም አጅብጅፎአል።#ግፍ ወደ ክፋት ብትር ተነስቶአል፤ ከእነርሱና ከብዛታቸው ከሀብታቸውም ምንም አይቀርም፥ የሚያለቅስላቸውም የለም።
#ጊዜው መጥቶአል፥ ቀኑ ቀርቦአል፤ መዓት በብዙዎች ሁሉ ላይ ነውና የሚገዛ ደስ አይበለው የሚሸጥም አያልቅስ።#የሚሸጥ ወደሸጠው ነገር አይመለስም፥ ሰውም በነፍሱ ኃጢአት አይጸናም።#መለከቱን ነፍተዋል ሁሉንም አዘጋጅተዋል፤ ነገር ግን መዓቴ በብዙዎች ሁሉ ላይ ነውና ወደ ሰልፍ የሚሄድ የለም።#ሰይፍ በውጭ ቸነፈርና ራብ በውስጥ አለ፤ በሜዳ ያለው በሰይፍ ይሞታል፥ በከተማም ያለውን ቸነፈርና ራብ ይፈጁታል።
#ከእነርሱም የሚሸሹ ይድናሉ በተራራም ላይ ይሆናሉ፤ እኔም በኃጢአታቸው ሁሉን እገድላለሁ።
#እጅ ሁሉ ትደክማለች ጕልበትም ሁሉ እንደ ውኃ ትቀልጣለች።
#ማቅም ይለብሳሉ ድንጋጤም ይሸፍናቸዋል፤ በፊትም ሁሉ ላይ እፈረት ይሆናል፥ ራሳቸውንም ሁሉ ይነጩታል።#ብራቸውን በጎዳናዎቹ ላይ ይጥላሉ ወርቃቸውም እንደ ጕድፍ ይሆናል፤ በእግዚአብሔር መዓት ቀን ብራቸውና ወርቃቸው ያድናቸው ዘንድ አይችልም። እርሱ የኃጢአታቸው ዕንቅፋት ሆኖአልና ሰውነታቸውን አያጠግቡም ሆዳቸውንም አይሞሉም።
#የክብሩንም ጌጥ ወደ ትዕቢት ለወጡ፥ የርኵስነታቸውንም ምስሎች አደረጉባት፤ ስለዚህ እኔ በእነርሱ ዘንድ ርኩስ አድርጌአታለሁ።#በባዕድም እጅ ለንጥቂያ፥ በምድር ኃጢአተኞችም እጅ ለብዝበዛ አሳልፌ እሰጣታለሁ፤ እነርሱም ያረክሱአታል።
#ፊቴን ከእነርሱ ዘንድ እመልሳለሁ፥ ምሥጢሬንም ያረክሳሉ፤ ወንበዴዎችም ይገቡባታል ያረክሱአትማል።
#ምድር ደም ባመጣው በደል፥ ከተማም በግፍ ተሞልታለችና ሰንሰለት ሥራ።#ከአሕዛብ ዘንድ ከሁሉ የሚከፉትን አመጣለሁ ቤቶቻቸውንም ይወርሳሉ፤ የኃያላንንም ትዕቢት አጠፋለሁ፥ መቅደሶቻቸውም ይረክሳሉ።
#ጥፋት መጥቶአል፤ ሰላምም ይሻሉ እርሱምአይገኝም።#ድንጋጤ በድንጋጤ ላይ ይመጣል፥ ወሬም ወሬውን ይከተላል፥ ከነቢዩም ዘንድ ራዕይን ይሻሉ፤ ከካህኑም ዘንድ ትምህርት፥ ከሽማግሌዎችም ዘንድ ምክር ይጠፋል። #ንጉሡም ያለቅሳል፥ አለቃም ውርደትን ይለብሳል፥ የምድርም ሕዝብ እጅ ትንቀጠቀጣለች፤ እንደ መንገዳቸውም መጠን አደርግባቸዋለሁ፥ በፍርዳቸውም መጠን እፈርድባቸዋለሁ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።
💚
💛
❤
✞
https://t.me/Abissiniyaworldlight
705
[ Album ]
" እውነቱን ለመናገር ነዋሪዎቹ እርቧቸዋል። እያለቀሱ ነው የተናገሩት። ድረሱልን እያሉ ነው " - አቶ ምሕረት መላኩ
የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋሰትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል የአማራ ክልል መንግሥት ድርቅ በተከሰተባቸው ቦታዎች የዕለት ድጋፍ ለማድረስ ቢስማማም በጸጥታ ችግር መድረስ እንዳልቻለ ገልጸዋል።
ኃላፊው ከ1.2 ሚሊዮን በላይ እንስሳት ወደ አጎራባች ወረዳዎች ለመፈናቀል እንደተገደዱ በሰሀላ ሰየምት ወረዳ ሂደው ማረጋገጣቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ግብረ ሰናይ ድርጅቶች በቦታው ገብተው ድጋፍ በማድረግ ችግሩን እንስኪጋሩ ድረስ የክልሉ መንግሥት የዕለት ምግብ አቀርባለሁ ብሎ ውሳኔ አሳልፏል " ያሉት አቶ ምህረት፣ " ነገር ግን ሰሞኑን በጎንደር መስመር የጸጥታ ችግር ስለነበረ የትራንስፓርት ተጫራቾቹ ችግር አለ #አንሄድም አሉኝ ነው ያለው " ብለዋል።
" መስከረም 18 እና ዛሬ መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም አንጻራዊ ሰላም ከሆነ ምግብ ይዘው እንዲገቡ ነው የተግባባነው " ሲሉ አክለዋል።
እስካሁን የተገኘ ድጋፍ እንዳለና እንደሌለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበላቸው ጥያቄም፣ " የሕጻናት አድን ድርጅት (ሴቭዘቺልድረን) 475 ቤት መሪዎች ለእያንዳንዳቸው 21,000 ብር ድጋፍ አደርጋለሁ ብሎ ዛሬ መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም የተጠቃሚ ልየታ ሊጀመር ነው " ብለዋል።
አክለውም፣ " ቅድመ ዝግጅት ነውና እያደረግን ያለነው ወደ ሕዝቡ በተጨባጭ የገባ ድጋፍ ይለም " ነው ያሉት።
ነዋሪዎች ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበላቸው ጥያቄም፣ " ነዋሪዎቹ እውነቱን ለመናገር እርቧቸዋል። እያለቀሱ ነው የተናገሩት። ድረሱልን እያሉ ነው " ሲሉ ድርቅ በተከሰተበት አካባቢ በአካል ተገኝተው ያረጋገጡትን አስረድተዋል።
" እንስሳትንም ለማየት ሞክረን ነበር" ያሉት አቶ ምህረት የጋማ ከብቶች፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየሎችን ጨምሮ 1.2 ሚላዮን እንስሳት ሳር ወዳለባቸው አጎራባች ቦታዎች መፈናቀላቸውን ገልጸዋል።
አክለውም ፣ " ተከዜን ተሻግሮ በሚገኙ የሰሀላ ሰየምት 13 ቀበሌዎች ከአንዱም ቀበሌ ለእንስሳት የሚሆን መኖ አላገኘነም። የእንስሳት ሞት ቁጥርም እየጨመረ ነው" ብለዋል።
ቀይ መስቀል በአካባቢው ላይ ገብቶ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥያቄ እንዳቀረቡም አቶ ምህረት ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
705
በአፋር ክልል በአራት ወረዳዎች አሳሳቢ ድርቅ መከሰቱ ተገለጸ
በአፋር ክልል ዞን ኹለት ውስጥ በሚገኙ አራት ወረዳዎች አሳሳቢ ድርቅ መከሰቱን የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል፡፡
የአፋር ክልል የመንግሥት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሙሃመድ አሊ ቢኢዶ፤ በክልሉ በብዛት አርብቶ አደሮች ባሉበት እና ከትግራይ ክልል ጋር አጎራባች በሆኑ ምስራቃዊ አፋር አካባቢዎች በክረምቱ ወቅት መዝነብ የነበረበት ዝናብ ባለመዝነቡ ድርቅ መከሰቱን ገልጸው፤ በዚህም በሰዎች እና በእንስሳት ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
ሥማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የክልሉ የግብርና ባለሙያ በበኩላቸው፤ በዞን ኹለት ውስጥ በሚገኙ አራት ወረዳዎች ከፍተኛ ድርቅ በመከሰቱ ከ3 ሺሕ 500 ሄክታር በላይ ሰብል ወድሟል ብለዋል፡፡
ባለሙያው አክለውም በአብኣላ፣ ብርሃሌ፣ ደሎል እና ቆነባ በተባሉ አራት ወረዳዎች ዝናብ የዘነበው በሚያዚያ እና ግንቦት ወር ብቻ መሆኑን ጠቁመው፤ "አርሶ አደሮች ዝናብ ይዘንባል በሚል ተስፋ የእርሻ ማሳቸውን በቆሎ እና ማሽላ የዘሩ ቢሆንም፣ ዝናቡ ሳይዘንብ በመቅረቱ ከ200 ሄክታር መሬት በላይ ሰብል ተዘርቶ ሳበቅል ቀርቷል።" ነው ያሉት።
በአራቱ ወረዳዎች በዝናብ እጥረት ታረሶ ያልተዘራ ከአንድ ሺሕ ሄክታር መሬት በላይ የእርሻ መሬት መኖሩንም ጠቁመዋል፡፡
በክልሉ ከተከሰተው ድርቅ በተጨማሪ ከነሐሴ 04 እስከ ነሐሴ 10/2015 ድረስ ተከስቶ በነበረው የአንበጣ መንጋ በአብአላ ወረዳ ብቻ ከ480 ሄክታር መሬት በላይ ሰብል መውደሙንም ተናግረዋል፡፡
አርሶ አደሮች ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች በብዛት የሚያመርቱት የበቆሎ እና የማሽላ ሰብል ቢሆንም፤ በአንበጣ መንጋ እና በድርቁ ምክንያት ሰብላቸው ከጥቅም ውጭ በመሆኑ ነዋሪዎች አስቸኳይ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ብለዋል፡፡
በሰው እና በእስንሳት ላይ የደረሰው አጠቃላይ ጉዳት ምን ያህል እንሆነ ጥናት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመውም፤ በክልሉም ይሁን በፌደራል መንግሥት በኩል እስካሁን ምንም ዓይነት ድጋፍ እንዳልተደረገ ገልጸዋል።
በድርቁ ምክንያት ችግር ላይ ለወደቁ ሰዎች አንዳንድ በጎ ፈቃደኞች በቤተክርስቲያን እና በመሰጂድ ገንዘብ በማሰባሰብ እንዲሰጣቸው እያደረጉ ቢሆንም፤ "ይህ በቂ ባለመሆኑ ችግሩ ሳይባባስ እርዳታ ሊደረግላቸው ይገባል።" ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በአፋር ክልል ከተከሰተው ድርቅ በተጨማሪ በትግራይ ክልል 27 ወረዳዎች እንዲሁም በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ጎንደር ዞኖች በተከሰተው አስከፊ ድርቅ የሰዎች ሕይወት እያለፈ ይገኛል።
705
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" የችግሩ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየከፋ ነው "
በአማራ ክልል ፣ በሰሜን ጎንደር 202 ሺህ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል።
በዞኑ በተከሰተው ድርቅ 452 ሺ ዜጎች መጎዳታቸው ተገልጿል።
የሰሜን ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና የምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት ይፋ እንዳደረገው ፤ በዞኑ ከግንቦት አጋማሽ ጀምሮ በተከሰተው ድርቅ 452 ሺህ ዜጎች ተጎድተዋል፤ 202 ሺህ ዜጎችም አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል፡፡
ከፅህፈት ቤቱ በተገኘው መረጃ ፦
- ጃናሞራ ፣ ጠለምት ፣ የበየዳ ወረዳዎችን ጨምሮ፣ ምሥራቅና ምዕራብ ጠለምትና የተወሰኑ የደባርቅ አካባቢዎች በድርቅ ተጎድተዋል፡፡
- ከግንቦት አጋማሽ ጀምሮ ዝናብ በወቅቱ ባለመዝነቡ ሳቢያ 6 ወረዳዎች ለድርቅ ተጋልጠዋል።
- በድርቁ ሳቢያ 19 ሺህ 500 ሄክታር ሰብል ጉዳት ደርሶበታል።
- በዝናብ እጥረት 103 ሺሕ እንስሳት ለድርቅ አደጋ የተጋለጡ ሲሆን 53 ሺሕ የሚደርሱ እንስሳት በድርቁ ሳቢያ #ሞተዋል።
- በጠለምትና ጃናሞራ ወረዳዎች በድርቁ ምክንያት ከ4 ሺሕ በላይ ዜጎች ከአካባቢያቸው ለቀው ወደ ወረዳ ማዕከላት ሄደዋል።
- ዞኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ድጋፍ ለማቅረብ ጥረት በማድረግ ላይ ነው ብለዋል፡፡
- በድርቁ አካባቢዎች ላይ ተላላፊ በሽታዎች በተለይም #የኮሌራ_በሽታ ተከስቷል።
- ድርቁ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ላይ ለሚገኙ ዜጎች አስቸኳይ የዕለት ምግብ፣ መድኃኒቶች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ውሃና የእንስሳት መኖ ድጋፍ አስፈላጊ ነው።
- የችግሩ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየከፋ ነው። በድርቁ ሳቢያ ዜጎች ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆኑ ሁሉም አካላት እንዲረባረቡ ፤ መንግሥት፣ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች፣ አጋር አካላት የተለያዩ ድጋፎችን እንዲያቀርቡ መልዕክት ተላልፏል።
እስካሁን ምን ድጋፍ ተደረገ ? ፅ/ቤቱ ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ክልሉ ከአንድ ሺሕ 500 ኩንታል በላይ የምግብ ድጋፍ ማድረጉንና ድጋፉን 14 ሺሕ ዜጎች ማድረስ እንደተቻለ ገልጿል።
Via EPA
@tikvahethiopia
705
#ALERT🚨
" ሰባ ሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም "
ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ በከባድ ድርቅ መመታቱ ተገልጿል።
በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ስር ያለው ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ 13 ቀበሌዎች አሉት።
ወረዳው የ2015/2016 የምርት ዘመን #ድርቅ ክፉኛ መትቶታል።
ወረዳው በከፊል አርብቶ አድር የሚታወቅ ሲሆን ከማሳው በሚያገኛት ጥቂት ኩንታል እህል በይበልጥ ለገለባው ዋጋ ሰጥቶ በእንሰሳቱ ኑሮውን የሚገፈ አርሶና አርብቶ አደር አካባቢ ነው።
በወረዳው ከፍተኛ የእንስሳት ሀብትም ይገኛል።
ጠቅላላ ካለው የእንስሳት ሀብት የዳልጋ ከብት 104,430፣ የጋማ ከብት 22,121 በግ እና ፍየል 465,428 ይገኙበታል።
ከዚህ ውስጥ ለድርቅ የተጋለጡ የዳልጋ ከብት 92,430፣ የጋማ ከብት 16,121፣ በግ እና ፍየል 396,760 ናቸው።
ወደአጎራባች ዞን የተሰደዱ የዳልጋ ከብት 20,328 ፣ በግ እና ፍየል 116,900 ሲሆኑ እስካሁን በድርቅ ምክንያት የሞተ የዳልጋ ከብት 1320 ፣ የጋማ ከብት 71 በግ እና ፍየል 2457 ናቸው።
በወረዳው ከ52 ሺህ በላይ ህዝብ የሚኖርበት ሲሆን 46ሺ የሚሆነው አፋጣኝ እርዳታ ካለገኘ አደጋ ውስጥ እንደሆነ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ብሩ ተናግረዋል።
አቶ ሲሳይ፤ " ምንም እንኳን ድርቅ ቢሆንም ከዚህ በፊት ለእንስሳት የሚሆን ሳር አይጠፋም ነበር። ዛሬ ግን የተቃጠለ መሬት ብቻ ነው የሚታየው፤ ለጥርስ ስጋ ማውጫ የሚሆን የሳር ስንጥር እንኳን አይታይም፤ የወረዳው ነዋሪዎች እንደነገሩን እንደ ወረዳችን እንዲህ አይነት ድርቅ አይተን አናውቅም፤ ሰባሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም " በማለት የድርቁን አስከፊነት ገልጸዋል።
በወረዳው የአርሶ አደሩ ማሳ ርቃኑን ቀርቷል፣ እንስሳት ቆዳቸው ከስጋቸው መጣበቅ ብቻ ሳይሆን ነፍሳቸው በጣዕረሞት ላይ ናት፣ ህጻናት፣ እናቶችና አረጋውያን በርሀብ ተገርፈው ነፍሳቸው ከጉንጫቸው ተጣብቃ ይዛቸው ልትጠፋ አፋፍ ላይ ነች። ተሎ መድረስ ካልተቻለ አሳዛኝ ክስተት በሰሀላ ሰዬምት ወረዳ ሊከሰት ይቻላል።
የአስተዳደሩ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ጉዞ አዘጋጅቶ የነበረ ሲሆን የብሄረሰቡ ከፍተኛ አመራሮችና አንዳንድ ግብረሰናይ ድርጅቶች በወረዳው ተገኝተው ቀበሌዎቹን ጎብኝተው ከነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገው ነበር።
የቀበሌው ማህበረሰብ በውይይቱ ላይ " ከእግዚአብሄር በታች መንግስት ነበር ለሰው ልጅ ዋስትና፣ ዛሬ ግን መንግስትም ፊቱን አዞረብን " ብለዋል።
" በዚህ ሳምንት ውስጥ የሚበላ ካልቀረበ ልጆቻችን አናገኛቸውም ፤ አሁንም ቢሆን አንዲት እንጀራ ለ10 ሰው ነው የምንሻማው፤ ከዛ ውጭ ግን ጨው በውሀ በጥብጠን ነው የምንጠጣው " ብለዋል።
እስካሁንም በወረዳው በርሀብ ምክኒያት የ2 ሰዎች ሂይወት አልፏል ሲሉ አሳውቀዋል።
እንስሳትን በተመለከተ " በወረዳችን ትንሽ እህል ካገኘን እንሰሳ ስለምናረባ ከብት እና ፍየሎቻችንን ሸጠን እህል ስለምንሸምት ብዙም አያሳስበንም ነበር፤ ዘንድሮ ግን ለከብቶችም ሆነ ለፍየሎችና በጎች የሚሆን የሚጋጥ ሳር ስለሌለ ተስፋ አስቆርጦናል " ብለዋል።
የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ምህረት መላኩ፤ የተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ቃል ከመግባት የዘለለ በመንግስት በኩልም ምንም የቀረበ ነገር የለም።
ለክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ሪፖርት ከማድረግ ባለፈ የችግሩን አሳሳቢነት ብንገልጽም እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም ብለዋል።
#መረጃው የዋግኽምራ ኮሚኒኬሽን ነው።
😭😭😭😭
#ጭንቁ ቀን ደረሰ።
705
#Update
" ዳንኤል " የተባለው አውሎ ንፋስ በፈጠረው ከባድ ጎርፍ በሊቢያየሞቱ ሰዎች 20 ሺህ ገደማ ሊደርሱ እንደሚችሉ ቢቢሲ ዘግቧል።
በ10 ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ደግሞ እስካሁን ያሉበት አልታወቀም።
ደርና የተባለችው ከተማ ትልቁ ጉዳት የደረሰባት ሲሆን አብዛኛው የከተማዋ ክፍል በውሃ ተወስዷል።
በሌላ በኩል ፤ አርብ በሞሮኮ በደረሰው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱ ሰዎች 3000 ገደማ መድረሳቸው የተነገረ ሲሆን አሁንም ድረስ በህይወት ያሉ ሰዎች ካሉ በሚል ፍለጋ እየተደረገ ነው። በአደጋው ሰዎችን በህይወት የማግኘቱ ነገር እጅግ የመነመነ ነው ተብሏል።
በአደጋው ከ5,530 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል።
@tikvahethiopia
705
#Update
በሊቢያ ባጋጠመው የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ወደ 5000 ሺህ ሳይጠጋ እንደማይቀር እየተነገረ ነው።
10 ሺህ ሰዎችም ያሉበት አይታወቅም ተብሏል።
የሊቢያ ቀይ ጨረቃ እስካሁን ባለው 2,084 ሰዎች መሞታቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።
በሊቢያ የሚገኘው ቀይ መስቀል በበኩሉ የገቡበት የማይታወቁ ሰዎች 10 ሺህ ደርሰዋል ሲል አሳውቋል።
መቀመጫውን በ ' ምስራቃዊ ሊቢያ ' ያደረገው አስተዳደር በአደጋው 5000 ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ገልጿል።
100 ሺህ ነዋሪ ባላት ደርና ከተማ ውስጥ የነበሩ ሁለት ግድቦች እና አራት ድልድዮች ከተደረመሱ በኋላ በከተማዋ ሙሉ ለሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ በውሃ ተውጣለች ብሏል።
" የሰዎች አስክሬን በየቦታው ወድቆ ይገኛል " ሲል ገልጿል።
የከተማዋ ሩብ ክፍል ሙሉ በሙሉ ጠፍቷልም ብሏል።
በከተማይቱ የሞቱ ሰዎች በጅምላ እየተቀበሩ እንደሆነ ተሰምቷል።
705
በምስራቅ ሊቢያ የጣለውን ከባድ ዝናብና አውሎ ነፋስ ተከትሎ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ቢያንስ ሁለት ሽህ ሰዎች ሲሞቱ፤ በሽህዎች የሚቆጠሩት ደግሞ የገቡበት አልታወቀም ተብሏል።
ምስራቅ ሊቢያን የሚቆጣጠረው የሀገሪቱ ጦር ቃል አቀባይ እንደተናገሩት አደጋው ደርና በተባለች ከተማ አቅራቢያ የነበረው ግድብ መደርመሱን ተከትሎ ደርሷል።
"ጎርፉ መንደሮችን ከነነዋሪዎች ጠራርግ ወስዷል" በማለት ስለ አደጋው ክብደት ተናግረዋል።
ቃል አቀባዩ የገቡበት ያልታወቁ ሰዎችን ቁጥር ከአምስት ሽህ እስከ ስድስት ሽህ መሆናቸውን ገልጸዋል።
705
በሞሮኮ የመሬት መንቀጥቀጥ ሟቾች ቁጥር ከ1 ሺህ አልፈ
ያልተለመደና እጅግ ክፉኛ የተባለው የሞሮኮ ርዕደ መሬት አርብ ምሽት ተከስቶ ከ1 ሽህ በላይ ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ ተነግሯል።
አደጋው በታሪካዊቷ ማራካሽ ከተማ ጥንታዊ ህንጻዎችን ዶግ አመድ ማድረጉ ታውቋል።
እስካሁን ድረስ የርዕደ መሬቱ ሙሉ የሟቾች ቁጥር ያልታወቀ ሲሆን፤ በአደጋው ክፉኛ በተጎዱ አካባቢዎች የነፍስ አድን ሰራተኞች መድረስ አለመቻላቸውን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል። 6.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በሞሮኮ ከ120 ዓመታት በኋላ በእጅጉ የከፋ ነው ተብሏል።
705
አስደንጋጩ የሞሮኮ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ
በሞሮኮ ማራካሽ ከተማ እና አካባቢዋ ላይ በሬክተር ስኬል 6.8 ማግኒትዩድ የሆነ ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከስቷል።
በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ800 መሻሩ ተነግሯል።
