en
Feedback
Paster Endriyas Eshetu

Paster Endriyas Eshetu

Open in Telegram
398
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-830 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '24
September '240
in 0 channels
August '24
+3
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '23
+455
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
17 September0
16 September0
15 September0
14 September0
13 September0
12 September0
11 September0
10 September0
09 September0
08 September0
07 September0
06 September0
05 September0
04 September0
03 September0
02 September0
01 September0
Channel Posts
አትረበሹ (1).m4a14.78 MB

2
ከእርብቃ ህይወት ምን እንማራለን!
302
3
ኢየሱስ የእኛ የሰላም አለቃ ነው። ሕፃን ተወልዶልናልና ፣ወንድ ልጅም ተሰ ጥቶናል አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆ ናል ስሙም ድንቅ መካር፣ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት ፣የሰላም አለቃ ተብሎ ይ ጠራል።(ኢሳይያስ 9÷6) ምንም ያል ብትሞክሩ ከክርስቶስ ኢየሱስ ውጪ፣በየትኛውም ስፍራ ሰላምን አታገኙ ም።በዮሐንስ 14÷27 እርሱ እንዲህ ብሏ ል፦ሰላሜን እሰጣችኋለሁ እኔ የምሰጣች ሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም ።ልባችሁ አይታወክ አይፍራም። ከላይ ኢየሱስ የተናገረው ቃል እንዴት የ ሚያጽናና ነው! በምንምሁኔታ ውስጥ ል ባችሁ እንዲረበሽ መፍቀድ እንደሌለባች ሁ ግልጽ አድርጎታል ፤ምክኒያቱም ህይወ ታችሁን በእርሱ ሰላም ሞልቶታል። አሁን  የእርሱ ሰላም አላችሁ።የዚህ ዓለም መንግስታት ሊሰጡን የማይችሉት ነገር አ ላችሁ፤ ቤተሰባችሁና ፤ጓደኞቻችሁ እንኳን ቋሚ የሆነ ሰላም ሊሰጧችሁ አይችሉም ኢየሱስ ብቻ ይችላል ። በህይወትችሁ ውስጥ ምንም ነገር ቢከሰ ት አትረበሹ፤በራስ መተማመን ይኑራችሁ ፤ምክኒያቱም የሰላም አሽናፊ በህይወታች ሁ ውስጥ አለ።በዙርያችሁ እየሆነ ባለው ማንኛውም ነገር ግራ አትጋቡ ፤እናንተ በ ልባችሁ የኢየሱስክርስቶስ ሰላም አላችሁ ። ፈልጵሱዮስ 4÷6-7  2ኛ ቆሮንጦስ 4÷16-18  የዮሐንስ ወንጌል 16÷33
344
4
"እግዚአብሔር ተዋጊ ነው""" “ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ተዋጊ ነው፤ ስሙም እግዚአብሔር (ያህዌ) ነው።” — ዘጸአት 15፥3 (አዲሱ መ.ት) እግዚአብሔር ጦረኛ ነው ።ዛሬም በመንገድህ ላይ ይዋጋልሀል ።ሙሴ ሲናገር ""ጠላቶቻቸሁ የምድሪ ቱን ፊት ሸፍነው ባያችሁ ጊዜ አትፍሩአቸው ።ለም ን ? ""ከእናንተ ጋር ያለው በሰልፍ ኃይለኛ የሆነው እግዚአብሔር በፊታችሁ ይወጣል ፤ስለህዝቡ እግ ዚአብሄር ይዋጋል ።""አለ ።ቀጥሎ ሲናገር ደግሞ ""ፈርዖን የእስራኤል ልጆች እያሳደደ ወደባህሩ ገባ " ይላል ።በዘጸአት 14÷ ላይ ሲናገር ""እግዚአብሔ ር ባህሩን ከፍሎ .....""ነበር ያሻገራቸው !ፈርኦን ወደ ባህሩ መግባትን በጀመረ ጊዜ "በነጋም ጊዜ እግዚአብሔር በደመና ተቀምጦ ፈርኦንንና ሰረገላ ውን በባህር አየ"""ይላል ። ""እግዚአብሔር አምላክም የፈርኦንን ሰረገላ አስረ ው።""ይላል ።ሰረገላውንና ፈረሶቻቸውን ሲያስራቸ ው እየሮጡ ባሉበት ነው የሚሮጡት ፣እየሮጡ መ ድረሻ የላቸውም ።መፀሀፍ ሲናገር ""አሰራቸው"" ይላል ።ዛሬም እግዚአብሔር አምላክ ስለ አንተ( ስለአንቺ ) እየተዋጋ ስለሆነ ጠላቶችህ ታስረዋል። ፈረሳቸው ታስሯል፣አይደርስም ፣በእኛና በጠላታች ን መካከል እግዚአብሔር ገብቷል ።እግዚአብሔር በውጊያ መንፈስ ወደ እናንተ ወርዷል ።ከዚህ የተነ ሳ የጠላቶቻችሁ ሰረገላዎች ታስረዋል።ይፎክራሉ! ነገር ግን ምንም ሊያደርጉባችሁ አይችሉም ።ከጥ ቂት ደቂቃ በኃላ እግዚአብሔር አምላክ ውኃውን በ ላያቸው ይመልሳል ።የግብፅም ልጆች እንዲህ አ ሉ ይላል """እግዚአብሔር ስለ እስራኤል ይዋጋል ና ኑ እንመለስ ብለው ወደኃላ መመለስ ጀመሩ "" እግዚአብሔር ስለእናንተ ይዋጋል ።በኢዮብ መፀሀ ፍ 36÷32 ላይ ""እግዚአብሔር በብርሃን ውስጥ እጁን ሰውሯል፣በጠላቱ ላይ ይወጣ ዘንድ ያዘዋል ""ይላል ።ለታሰሩ መፈታት ፣ለተጠቁት ነጻ መውጣ ት ፣ለእውሮች ማየት ፣የተወደደውን የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ፣ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ፣ እግዚአብሔር ቀብቶኛል ፤ስላለ እስረኞች ዛሬም ይ ፈታሉ፤የአለቆች ዘንግ ይሰበራል ፤የስልጣን ኃይል ይዋረዳል ፤በኃይለኛው በእግዚአብሔር ፊት ይዋረ ዳሉ።በመጨረሻም ምርኮን ትበዘብዛላችሁ፤ጠላቶ ቻችሁን ትማርካላችሁ ።ምክኒያቱም እግዚአብሔር ስለእናንተ ሊዋጋ በፊታችሁ ወጥቷል ። “እግዚአብሔር ጦረኛ ነው""
298
5
_የለበትም_ዘማሪት_መአዛ_singer_meaza_@yonatanakliluofficial_@MARSILTVWORLDWIDE128k.m4a
210
6
"እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ፧ ያበጃትም      ይጠብቃትም ፣ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው ።               ( ዘፍጥረት 2÷15 )  ። እያንዳንዱ ሠው በህይወቱ ላይ የሚያበጀውና ፣የ የሚጠብቀው ነገር አለው ።በእግዚአብሔር ቃል መሠረት ። -  መንፈሳዊ ህይወትን ማበጀትና ፥መጠበቅ ። - ትዳርን ማበጀትና ፥መጠበቅ ።የልጆች ፍፃሜ ማ   በጀትና መጠበቅ ። -ቤተክርስቲያንን ማበጀትና ፥መጠበቅ ። -ንግዶችን ማበጀትና ፣መጠበቅ ። - ሥራዎቻችንን ማበጀትና፣መጠበቅ ። ህይወታችንን በቃሉ መሠረት ማበጀት ወይም እግ ዚአብሄር በሚፈልገው ቅርጽ ይዞ እንዲያድግና ተ ዕኖን የሚያመጣ እንዲሆን መገንባት ። የእያንዳንዱ ሠው ሀላፊነት ነው ።ማንም ሠው ህ ይወቱን እንደፈለገው መምራት አይችልም ።ህይወ ት ከእግዚአብሔር የተቀበልነው አደራ ነው ። ቃሉ በሚለው መሠረት ህይወታችንን መምራት አ ለብን። -
229
7
""ድል ለማግኘት የምንሄድበት መንገድ "" 1ኛ -ለጌታ ታማኝነታችን እንግለፀ “እግዚአብሔርንም ማምለክ ክፉ መስሎ ቢታያችሁ፥ አባቶቻችሁ በወንዝ ማዶ ሳሉ ያመለኩአቸውን አማልክት ወይም በምድራቸው ያላችሁባቸውን የአሞራውያንን አማልክት ታመልኩ እንደ ሆነ፥ የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።” — ኢያሱ 24፥15 2ኛ -ዐለት ዕለት ለጌታ ራሳችን አሳልፋ መስጠት ሮሜ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። ² የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። 3ኛ -እግዚአብሔር የሚያስቀድመውን እናስቀድም “ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።” — ማቴዎስ 6፥33
209
8
ዘዳግም 9 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እስራኤል ሆይ፣ ስማ፤ ሰማይ ጠቀስ ቅጥር ያላቸው ታላላቅ ከተሞች ያሏቸውን፣ ከአንተ ይልቅ ታላቅና ብርቱ የሆኑትን አሕዛብ አስለቅቀህ ለመግባት ዮርዳኖስን አሁን ትሻገራለህ። ² ዔናቃውያን ብርቱና ቁመተ ረጃጅም ሕዝቦች ናቸው፤ ስለ እነርሱ ታውቃለህ፤ “ዔናቃውያንን ማን ሊቋቋማቸው ይችላል?” ሲባልም ሰምተሃል። ³ ይሁን እንጂ እንደሚባላ እሳት ከፊትህ ቀድሞ የሚሻገረው አምላክህእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) መሆኑን ዛሬ እርግጠኛ ሁን፤ እነርሱን ያጠፋቸዋል፤ በፊትህም ድል ያደርጋቸዋል፤ አንተም እግዚአብሔር (ያህዌ) በሰጠህ ተስፋ መሠረት ታስወጣቸዋለህ፤ በፍጥነትም ትደመስሳቸዋለህ።
292
9
የሚመጣው ግፊት ሁሉ ወደ ትክ ክለኛዉ ቦታ ሊወስደንና ወደ እግ ዚአብሄር ሃሳብ ሙላት ዉስጥ ሊ ያስገባን እንጂ ሊያጠፋን አይደለ ም። " የመዉለጃዋ ወራት ደረሰ" ይላል ( ሉቃስ 1÷6 ) ለመዉለድ በምትዘጋጅበት ጊዜ ወደ ቤተልሔም እንዲሂዱ ትእዛዝ ወጣ። ማርያም ስለዚህ ሁኔታ ማ ጉረምረም ትችል ነበር። ለምን በ ዚህ ጊዜ ወደ ቤቴልሔም እንድሔ ድ አደረግህ ? ይኼ ትዕዛዝ ለምን ወጣ። ልትል ትችል ነበር። ነገር ግን ምንም አላለችም። እግ ዚአብሄር አንዳንድ ጊዜ ፅንሱን፣ ራእዩንና ሃሳቡን በዉስጣችን ካስ ቀመጠ በኃላ ግፊት ሊመጣ ይች ላል።ከቀኝም ከግራም ከኃላም፡ከ ፊትም ፣ከምንወዳቸዉም፣ከሩቅ፣ ወይም ከቅርብ ከተለያዩ አቅጣ ጫዎች ግፊት ሊመጣ ይችላል። ነገር ግን የእግዚአብሔር የሆነው ን ተቀብለን አሜን ብለን እንደ ፈቃ ዱ የምንኖር ከሆነ ፣የሚመጣው ግፊት ሁሉ በዉስጣችን ያለዉን ፍሬ ሊገል አይችልም። ይልቁንም ወደ ቤተልሔም ወደ ትክክለኛዉ ቦታ ይወስደናል። ጌታ ኢየሱስ መ ወለድ የነበረበት በቤቴልሔም ወ ስጥ ነበር። ለዚህ ነበር ትዕዛዙ የወጣው።ማ ርያምና ዮሴፍ ባይገባችዉም እግ ዚአብሄር እነዚያን የፖለቲካ መሪ ዎችን ተጠቅሞ ወደ ቤቴልሔም ወደ ትክክለኛዉ ቦታ በሰዓቱ ወ ሰዳቸዉ ። የእግዚአብሔር ቃል በ ሕይወታችን የሚሆነዉ ነገር ሁሉ ለበጎ ነው የሚባለው በዚህ ምክ ኒያት ነው። እንግዲህ እኛ ማየት የሚገባን እንደ ፈቃዱ መጠራታች ንንና እግዚአብሄርን መዉደዳችን ን ነው። ይህንን ካረጋገጥን እርሱ ነገርን ሁሉ ለበጎ ያደረጋል። "" እዚያዉ ሳሉ የመዉለጃዋ ወራ ት ደረሰ "" ይላል።ይህ ዘመን የእግ ዚአብሄርን ሃሳብ የምንወልድበት ዘመን ነው።በዚህ ምክኒያት እንግ ዲህ ከመዉለድ ጋር ግፊት ሊበዛ ይችላል።ለመዉለድ ምጥ፤ መጨ ነቅና መጠበብ አለ ። ሁኔታዎች ሊከብዱ ይችላሉ፤ነገር ግን የእግዚአብሔር የሆነው ነገር ይወለዳል። የእርሱ የሆነው ሲወ ድ ትልቁ ቁም ነገር የት እንደተወለ ደ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ሆኖ መወለዱ ነው።ከእግዚአብሔር የ ሆነ በዝቅተኛ ቦታ ሊወለድ ይችላ ል። በትንሽ ሥፍራ ሊወለድ ይችላ ል፤በበረከት ዉስጥ ሊወለድ ይች ላል።ከእግዚአብሔር ከተወለደ ግ ን ይወጣል።ትልቅ ዛፍ ከትንሽ ፍሬ ውስጥ ነው የሚወጣው። ከእግዚአብሔርም የሚመጣው ነ ገር ብዙ ጊዜ ትልቅ መስሎ አይደ ለም የሚጀምረው ። ኤልሳዕም የድርቁ ዘመን እንዳበቃ ሲተነቢይ ያየው ደመና በጣም ት ንሽ ነበር። የሰውን እጅ የሚያክል ነበር።ነገር ግን ያ ትንሽ ደመና ነበር ሰማይን ሁሉ ሊሽፍን የቻለው።ታላቅም ዝና ብ እንዲመጣ ያደረገዉ። የእግዚአብሔር የሆነ ዝቅ ብሎ ሊ ጀምር ይችላል ነገር ግን ፍጻሜው ትልቅ ነው። "" ጅማሬህም ታናሸ ቢሆንም እን ኳ ፍፃሜህ እጅግ ይበዛል""። ተብሎ በእግዚአብሔር ቃል የተጻ ፈዉ ከዚህ የተነሣ ነው።( ኢዮብ 8÷7) ይህን በደንብ መገንዘብ አ ለብን።
334
10
Facebook.m4a
250
11
"""የምትወደውን አንድ ልጅህን ይዘህ ሂድ"" አለው ( ዘፍጥረት 22÷2 ) እግዚአብሔር "አሁን ሂድ ፣አሁን አድርግ ""ሲለን እኛ ግን ""ቆይ ነገ ፣ቆይ ከነገ ወዲያ """እንላለን ። ምንኛ ተከራካሪዎችና ምክኒያት ፈላጊዎች ነን ፥ አንድ ነገር ትክክል እንደሆነ ይገባናል ፣ያንን ነገር ላለማድረግ ግን የተለያዩ ሰበቦችን እናቀርባለን ። እግዚአብሔር ወደገለጸልን የላቀ ደረጃ እንድንደርስ ከተፈለገ ያንን ነገር ማድረግ ያለብን አሁን እንጂ ሌላ ቀን አይደለም ። አንድን መሥዋዕት ከማቅረባችን በፊት መሥዋዕ ቱ መጀመሪያ መቅረብ ያለበት ፈቃዳችን ውስጥ ነወ። <<አብርሃምም ተነስቶ ....እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሂደ >>( ዘፍ 22÷ 3 ) ።አብርሃም ምንኛ ትሑ ትና ቅን ነበር ።እግዚአብሔር ሲናገረው ""ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከረም >>( ገላ 1÷6 )።ከሥጋ ና ከደም ጋር "ወይም ደግሞ ከራስህ አመለካከት ና ጥበብ ጋር ድርድር እንዳናደርግ መጠንቀቅ ። የምናረገው ነገር ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ህ ብረት ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት ። የራሳችን ጥበብና አመለካከት እንዲሁም ሰዎች የ ሚሰጡን ምክር ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ሊጻረ ሩ ይችላሉ ፥እንዳትታዘዙ እንቅፋት ሊሆንብ ይችላ ል። አብርሃም ለመሥዋዕት የሚሆነውን ነገር አልመረ ጠም።ምንጊዜም ቢሆን በራሳችን ፍላጎትና ምኞት እግዚአብሔርን ከማገልገል ጥንቃቄ ልናደርግ ይገ ባል።የራሳችን ፍላጎትና ምኞት ንጹሑን አገልግሎታ ችን የሚበክል ሊሆን ይችላል ። አብርሃምም ፈጥኖ ታዘዘ እንጂ አልዘገየም ፥ወይ ም ተቃውሞ አላቀረበም ። ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ኀብረት ከሌለን ግን በቀላሉ እግዚአብሔርን ወደ መውቀስ ወይም ወደ ማማረር እናመራለን ። የራሳችን ውሳኔ ከመስጠታችን በፊት አስቸጋሪ ቢ ሆን እንኳ በእርሱ መንገድ መሄድ ፤በዚያ መንገድ ስንጓዝ በበለጠ ሁኔታ እግዚአብሔርን እናውቀዋለ ን። ላቅ ወዳለ ግብ ሊያደርሰን እግዚአብሔር በሕ ይወታችን ይሠራል ።ወደራሱ ግብ ካደረሰን በኃላ ም ዓላማው ዓላማችን ይሆናል ። ""የምትወደውን አንድ ልጅህን ይዘህ ሂድ "" ( ዘፍጥረት 22 ÷2 )
395
12
""""የፀሎት ጥያቄያችን ፣ሁሉ """ በምሥጋናችን ይመለሳል "" 2 ዜና 20 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²¹ ከሕዝቡም ጋር ተማክሮ በሠራዊቱ ፊት የሚሄዱትን፦ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ የሚሉትንም፥ ጌጠኛ ልብስም ለብሰው የሚያመሰግኑትን፥ ለእግዚአብሔርም የሚዘምሩትን መዘምራን አቆመ። ²² ዝማሬውንና ምስጋናውንም በጀመሩ ጊዜ ይሁዳን ሊወጉ በመጡት በአሞንና በሞዓብ ልጆች በሴይርም ተራራ ሰዎች ላይ እግዚአብሔር ድብቅ ጦርን አመጣባቸው፤ እነርሱም ተመቱ። ኤፌሶን 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁹ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤ ²⁰ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።
306
13
ከትላንት ሃዘን መላቀቅ ራዕይ ሲኖረን በትናንትና ጊዜ ውስጥ ተቀምጠን ስለ ዛሬና ስለ ነገ በማሰብ አንታሰርም።ራዕይ ትል ቁ ጉልበቱ ከትላንትናችን ያፋታንና በዛሬ የእግዚአብ ሔር አዲስ እንቅስቃሴ ውስጥ አስገብቶ ካበረታን በኋላ ወደ ነገ ያሽጋግረናል። ይህን የምልበት ምክኒያት ብዙ ስዎች ራዕይ ኖሮአ ቸው እስከ አሁን ከትላንትናቸው ውስጥ መውጣት ስላልቻሉ በዛሬ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን አ ዲስ እንቅስቃሴ ባለማየት የህይወት ጉዳት ውስ ጥ ስለሚኖሩ ነው። ኢያሱንም ቢሆን እግዚአብሔር እንዲሁ አይደለም ፅና አይዞህ እጅግ በርታ ያለው ።ትላንትና ታላቁ መ ሪ ሙሴ ሞቶበታል።አሰልጣኙ መካሪውን ፊት መሪ ውን ታላቅ ሰው አጥቷል ።ስለዚህ ምናልባት ከዚህ በኋላ መሄድ አልችልም በሚል ተስፋ መቁረጥ ው ስጥ የሙሴን ሞት እያሰበ ወደ ዛሬ የእግዚአብሔር አዲስ ራዕይ እና አላማ ውስጥ መግባት ተስኖት ይ ሆናል። ሰይጣን ካሰራቸው ይልቅ ደግሞ የትላንት ታሪክ ያ ሰራቸው ሰንሰለታቸው ጠንካራ ነው።ለምን?  ትላን ት ለነበራቸው ታሪክ በአእምሮአቸው ውስጥ ዕውቅ ና ስለሚሰጡት ያንን እውቅና የሰጡትን ማንኛውን ም ሃሳብ ራሳቸው በፈቃዳቸው አውጥተው ካልጣ ሉት በቀር ማንም ስለማይረዳቸው ነው። ሰይጣን ያሰራቸውን  ግን በቀላሉ ከላያቸው ላይ ማባረር ይቻላል ። እግዚአብሔርም ታላላቅ ማፅናናቶችን በኢያሱ ላይ ያስቀመጠው ከትላንት ሃዘኑ እንዲላቀቅ ነው።ያለ ሙሴ አልችልም ብቻዬን አልችልም ራሴን በዚህ አ ይነት የመሪነት ቦታ ላይ አላውቀውም በሚል ፍርሃ ት ከታሰረበት ብርቱ ሰንሰለት አይዞህ አትፍራ እኔ ከ አንተ ጋር ነኝ እየደጋገመ ያለው ለዚህ ነው። እግዚአብሔርን ከትናንትና ማንኛውም ሰንሰለት እ ዲፈታችሁ ፀልዩ።እግዚአብሔር ይችላልና የተሰጣ ችሁን ራዕይ አስቡ እንጂ ትላንትና ላይ አትቀመጡ        <<ከትላንት ሃዘን መላቀቅ >>
339
14
1ኛ ጴጥሮስ 3 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ ውበታችሁ በውጫዊ ነገሮች በመሽሞንሞን ይኸውም ሹሩባ በመሠራት፣ በወርቅ በማጌጥና በልብስ አይሁን፤ ⁴ ነገር ግን ውበታችሁ በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ፣ ገርና ጭምት መንፈስ ያለበት፣ ምንጊዜም የማይጠፋ የውስጥ ሰውነት ውበት ይሁን።(1ጴጥ 3÷3-4) የውጭ ውበት መልካም ነው ዋጋም አለው ።ነገር ግን ከውጭው ውበት ጋር ሲነፃፀር የውስጡ ውበት ዋጋው እጅግ የከበረ ነው ። የውጭው ውበት ለሰው የእግዚአብ ሄር ሥጦታ ሲሆን ማንም ሊመካበት የማይችል ውበት ነው ። የውጭው ውበት አንዴ ተሰርተው የ ምናስደንቀው ሲሆን የውስጡ ውበት ግን የህይወት ዘመን ሁሉ ትጋትን የ ሚጠይቅ ዘለቄታዊ ውበት ነው ። ውበት ሐሰት ነው ደም ግባትም ከንቱ ነው ።እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዎ ትመሰገናለች።(ምሳሌ 31÷30) የውጭው ውበት እግዚአብሔርን አያ ስደንቀውም የውስጡ ውበት ግን እ ግዚአብሄር ከሰው የሚፈልገው ስለ ሆነ እግዚአብሔር ደስ ያሰኘዋል ። የውጭ ውበት እንደዛፍ ቅጠል ሲሆን የውስጡ ፍሬ ግን እንደ ዛፍ ፍሬ ነው ።የውስጥ ውበት የሚለካባቸውን እግ ዚአብሄር ከእያንዳንዳችን የሚፈልጋቸ ውን ሁለት ወሳኝ ባህሪያትን እንመል ከት። 1ኛ ጴጥሮስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ ለእናንተም ጠጕርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ፥ ⁴ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ። 1ኛ- የዋህነት ፦የዋህነት ማለት ፦ክ ፉን በክፋ ለመመለስ ሙሉ ሃይል ይዞ ነገርግን ሃይልን ለክፉት ላለመጠቀ ም መወሰንና ራስን መግዛት ነው ። ሃይል እንዳለው እያወቀ ሃይሉን ለክፉ ት ሳይሆን ለመልካም ብቻ ለመጠቀ ም የወሰነ። 2ኛ -ዝግተኛ ፦ዝግተኛ ማለት ፦ -እግዚአብሔርን የማይቀድም - እግዚአብሔር የሚከተል -የእግዚአብሔር እርምጃ የሚታ ገስ። - በእግዚአብሔር የሚመራ ሠ ው ማለት ነው። ምሳሌ 3÷5
322
15
የሚረዳኝ_Yemirdagn_የፀሎት_ዝማሬ_Eyerusalem_Jerri_negiya_official_video128k.m4a
300
16
Word - Saturday at 4-12 PM.m4a
438
17
"""የአንደበት ቃል  """ ማቴዎስ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁶ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል፤ ³⁷ ከቃልህ የተነሣ ትጸድቃለህና ከቃልህም የተነሣ ትኰነናለህ። ብዙ ጊዜ አንደበታችን እንደመጣልን እንናገራለን ፤ አንዳንድ ጊዜም በመሰለኝ ስሜት በሰዎች ላይ የ ፈለግነውን አስተያየት እንሰጣለን ።ሌላም ጊዜ አ ፋችንን በከንቱና በማይረቡ ቃላት እንከፍታለን ።ከ ምሬትና ከሐዘን ወይም በቁጣ ተነሣስተን ""ይህ እ ንዲህ ነው ፤ያም እንዲያ ነው .....ማለታችን የተለ መደ ነገር ስለሆነ ስህተት እንደሠራን እንኳ ያን ያህ ል ላይሰማን ይችላል ። ለመሆኑ ስለምንናገራት ስለ እያንዳንዷ ቃል በክር ስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት በቀረብን ጊዜ መልስ እ ንደምንስጥ ምን ያህል እናስተውላለን ? በእርግጥ በዚያ ቀን የምንቆመው ዓይኖቹ እንደ እሳት ነበልባ ል በሆኑና ልብንና ኩላሊት ጠልቆ መመርመር በ ሚችል አምላክ ፊት ነው ፣እርሱን ደግሞ በአንደበ ት ፣ቅልጥፍና ወይም በንግግር ችሎታ ልንረታው አ ንችልም ።በመሆኑም በየትኛውም ጊዜ ስለምንም ጉዳይ ምን እንደምንናገር ብንጠነቀቅ ይበጃል ። ለምሳሌ በመግቢያው ላይ የተጠቀሰው ክፍል ኢየ ሱስ አንድ በአጋንንት ተይዞ ማየትና መናገር የማይ ችልን ሰው ከፈወሰ በኃላ ከሆነው ታሪክ ጋር የተያ ያዘ ነው ።በወቅቱ ኢየሱስ ስለፈወሰው ሰውየው ማየትና መናገር ችሎ ነበር ።ታዲያ ይኼን ያዩ አን ዳንድ ሰዎች ተደንቀው """ይህ ሰው የዳዊት ልጅ ይሆን ?...ተባባሉ ። ፈሪሳውያን ግን """አጋንንትን የሚያወጣው በአጋን ንት አለቃ ወይም በብዔልዜቡል ነው ""በማለት በ ድፍረት አስተያየታቸውን ይሰጡ ነበር ። በዚህ ጊዜ ጌታ ፤ለፈሪሳውያኑና በዚያ ለነበሩት ሁሉ አስቀድሞ ስለፈውስና የአጋንንት አስተዳደር ጥልቅ ትምህርት ካስተማረ በኃላ """ዛፍ ሁሉ በፍ ሬው ስለሚታወቅ ፣መልካም ፍሬ እንድታገኙ መል ካም ዛፍ ይኑራችሁ ፤መጥፎ ዛፍ ቢኖራችሁ ግን መጥፎ ፍሬ ታገኛላችሁ ።እናንት የእፋኝት ልጆች ፣ እናንተ ክፋዎች ስትሆኑ መልካም ነገር መናገር እ ንዴት ትችላላችሁ ?  በልብ ውስጥ የሞላውን አንደ በት ይናገራል ። መልካም ሰው በልቡ ካከማቸው መልካም ነገር ፣ በጎ ነገር ያወጣል ፤ክፋ ሰው በልቡ ካከማቸው ክ ፉ ነገር ፣መጥፎ ነገር ያወጣል ""በማለት የሰዎች ችግር ከልባቸው ውስጥ ካለው ክፋትና አለማመን የሚመነጭ እንደ ሆነ አስገነዘባቸው።
580
18
"""ደህና ነው አለች ""( 2ኛ ነገስት 4÷23 ) የሞተ እሬሳን ቤት አስተኝቶ ደህና ነው ማለት አይቻልም ።ደህና ነው የሚለው ከአፋ የወጣው ቃል ያለ ምንም ጥርጥር ይህች ሴት አንድ መንፈ ሳዊ ጥንካሬ በውስጧ እንደገነባች አመልካች ነው ።የሚታየው ነገር እንደሚታየው መናገር ይቻላል ። የሞተ አይቶ ሞቷል ማለት የተለመደ የሰው ህይወ ት አኗኗር ልምድ ነው ።ጨለማን አይቶ ጨለማ ች ግርን አይቶ ችግር ማውራት ያንኑ ማስተጋባት የ ሚታየው ነገር ሁሉ እንደሚታየው አይደለም ብሎ ማመንና ማሰብም ይቻላል ። ሁኔታውና ፍጥረታዊው አለም የሰጠውን ልምድ አ ለማስተጋባትም ይቻላል ።ዋናው ነገሩን ወይም ሁ ኔታውን ካየን በኃላ የእግዚአብሔርስ ዓይን ይህን እንዴት ያየዋል ? ብለን አእምሮአችንን ለመንፈሳዊ ው ዓለም አቆጣጠርና አመለካከት የመክፈታችን( የማዘጋጀታችን ) ጉዳይ ነው ። ይህች ሴት በየመንገዱ ሞቷል ብትል ኖሮ በየመን ገዱ የሚያገኛት ሁሉ ከሞተ ምን ትጠብቂያለሽ ? እንቅበረው ብለው የቀብር ስነ ሥርዓቱን ለማፍጠ ንና ለማስተባበር ይሯሯጡ ነበር ።ስለዚህ አንዳን ድ ነገራችን ሰውረን ወደሚመለከተው አካል ብቻ መሮጥ የነገረንን ትንሣኤ ሊያመጣና እኛንም ተገ ፋፍቶ ከመቅበር ታላቅ ኪሳራ ሊያድነን ይችላል ። በየትኛውም ጊዜ ወደ ማን እንደምንሄድ ማወቅ መንፈሳዊነት ነው ። ነገር ግን ደሴቲቱ ወደ እግዚአብሔር ሰው ብቻ እየ ሮጠች ።2ኛ ነገስት 4÷26 እንዲህ ይላል ግያዝ ባ ገኛት ግዜ ደህና ነው ብላው አለፈች ።ይህምሰው ነገሩ አይመለከተውም ማለት ነው ።በዚህ ሁሉ ው ስጥ ግን የምትፈልገውን የእግዚአብሔር ሰው እስ ክታገኝ ድረስ ደህና ነው አለች ። የዚህች ሴት ታሪክ በ2ኛ ነገስት 4÷14 ላይ ታሪኳን ብትመለከቱ ልጅ ያልነበራት መካን ነበረች ።በእድ ሜዋም ልጅን ከማግኘት አልፋለች ።ባሏም ሸምግ ሏል።በግራና በቀኝ ተስፋ በሌለው ሁኔታ ውስጥ የተቀመጠችና አለመውለድን በህይወት ከመለማ መዷ የተነሳ አለመውለድን ተቀብላዋለች።የዛሬ አ መት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ ባላት ጊዜ ባሪያህን እንዳትዋሻት ተጠንቀቅ ብላዋለች።ያ ማለት ያለችበ ት የሁኔታ ክብደት የመጣውን ትንቢት በፍጥነት ተ ቀብሎ ለማስተናገድ በምትችልበት ሁኔታ ውስጥ አለመኖሯን ያስረዳል ።ይሁን እንጂ የእግዚአብሔ ር ሰው ኤልሳዕ ትንቢትን ከተናገረ በኃላ በትንቢታ ዊ የአዋጅ ቃል መካንነት ተሰብሯል ፤የተፈጥሮ ስር ዓት ተቀይሯል ፤የሸመገለውና ያበቃለት ሰው ዘር በ ውስጡ ተገኝቶ አባት መሆን ችሏል ።
336
19
""እግዚአብሔር ለኢያሱ የሰጠው ራዕይ ምንድን ነው ? ኢያሱ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደ ሆንሁ እንዲሁ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፥ አልተውህም። ⁶ ለአባቶቻቸው፦ እሰጣችኋለሁ ብዬ የማልሁላቸውን ምድር ለዚህ ሕዝብ ታወርሳለህና ጽና፥ አይዞህ። ⁷ ነገር ግን ጽና፥ እጅግ በርታ፤ ባሪያዬ ሙሴ ያዘዘህን ሕግ ሁሉ ጠብቅ፥ አድርገውም፤ በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል። ⁸ የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። ⁹ በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን? ታላቁ መሪ ሙሴ ከሞተ በኃላ የተተካው መሪ የተ ቀበለውን ራዕይ የተሰጠው ተስፋ እንዲሁም የተሰ ጠውን ራዕይና ተስፋ መጠበቂያ መፍትሄና ማስ ጠንቀቂያ እንመልከት ! እግዚአብሔር ለኢያሱ የሰጠው ራዕይ ምንድን ነበር ። ኢያሱ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ ለሙሴ እንደ ነገርሁት የእግራችሁ ጫማ የሚረግጠውን ቦታ ሁሉ ለእናንተ ሰጥቼአለሁ። ⁴ ከምድረ በዳው ከዚህም ከሊባኖስ ጀምሮ እስከ ታላቁ ወንዝ እስከ ኤፍራጥስ ድረስ የኬጢያውያን ምድር ሁሉ እስከ ፀሐይ መግቢያ እስከ ታላቁ ባሕር ድረስ ዳርቻችሁ ይሆናል...........ጥቁር 6 ለአባቶቻችሁ እሰጣችኋለሁ ብዬ የማልሁላቸውን ምድር ለዚህ ህዝብ ታወርሳለህና ፦ ራዕይ ከላይ የተጠቀሰውን ለአባቶቻቸው የተማለ ውን ምድር ለሚቀጥለው ህዝብ ማውረስ ነው ።በ ምድር ላይ ደስተኛና የታደለ ሰው ቢኖር ራዕይ ያለ ው ሰው ነው ።ራዕይ ሲኖረን የምንኖርለት ዓላማ ስ ላለን ብቻ ህይወት ትጣፍጠናለች።ራዕይ ሲኖረን የ ህይወት ውጣ ውረዶች አድካሚና አታካች ሁኔታ ዎች ከፊታችን ቢጋረጡም እንኳን ራዕያችን የውስ ጥ ጉልበታችንን እያደሰው ወደ ፊት ያስፈነጥረናል ።ራዕይ ከሰው ሁሉ ለየት ያደርገናል ምክኒያቱም በምድር ላይ የምንኖርለትና የምንሞትለትን ጉዳይ አውቀናል ።እግዚአብሔር ኖረን እንድንሞት ሳይሆ ን ፣ሰርተን እንድናልፍ ፈጥሮናል። የእግዚአብሔር ቃል በኤፌሶን 2÷10 “እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” እግዚአብሔር አስቀድሞ ስላዘጋጀው መለኮታዊ አ ጀንዳ ስራ ፈጥሮልናል።እርሱ ደግሞ መልካሙን ስ ራ ተብሎ ተፅፏል ።እንዲሁ አልተፈጠርንም የመ ጣንለት የተፈጠርንለትና የምናከናውነው መለኮታ ዊ የእግዚአብሔር ሃሳብ አለ ። ይህ ሲገባንና ይህንንም ለመስራት በምንነሳበት ጊዜ ህይወታችን በደስታ ይሞላል ። ደስታን ከምናገኝበት ታላቅ ስጦታ መካከል ዋነኛ ው በራዕይ ወይም በአላማ እንደምንኖር ለራሳችን ሲገባን ነው ።
366
20
"""ገስጽ ነገር ግን ትችት አትሰንዝር """ “ወንድምህን በልብህ አትጥላው፤ በባልንጀራህ ምክንያት ኃጢአት እንዳይሆንብህ ገሥጸው።” — ዘሌዋውያን 19፥17 “ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፦ ወንድምህ ቢበድልህ ገሥጸው፥ ቢጸጸትም ይቅር በለው።” — ሉቃስ 17፥3 ለጥፋት በር ከምከፍትላቸው መካከል እጅግ አደገ ኛ ከሆኑት አንዱ ትችት መሰንዘር ነው ። የሚሰብሩ ፥የሚያንቋሽሹ ፥አስተያየቶችን በግንኙነ ት ውስጥ ያለውን ህብረት የሚያበላሹ ነገሮች ናቸ ው።ከትችት የሚጠቀም ማንም የለም ። የሚተቸው ሰው ( ትችት የሚቀርብበት እንዲሁም ትችቱን መስማት በሚችልበት ርቀት ውስጥ ያለ ማንም ሰው ቢሆን ከዚህ ተጠቃሚ አይሆንም ።የ ማያባራ ትችት የሰውን መንፈስ ያወድማል ።ነቀፌ ታ፤ስብራትን፤መራራነትን፣ሞገደኝነትንና ጥላቻንም እንኳን ያፈራል ።ነቀፌታ ግልጽነትንና ሀቀኝነትን አያ በረታታም ፤ያለ እነዚህ ነገሮች ደግሞ ማንኛውም ግንኙነት ጤናማ ሊሆን አይችልም ።ነቀፊታ በባህ ሪው ራሱ አውዳሚ ነው ፤ምክኒያቱም መፍትሄ ፈላ ጊ ከመሆን ይልቅ ችግሮችን አነፍንፎ በመፈለግ ጉዳት ለማስከተል ታስቦ የሚደረግ በመሆኑ ነው። አዘውትረው ትችቶችን የሚሰነዝሩ ሰዎች ብዙውን ጊዜ በራሳቸው ህይወት ምላሽ ያላገኙ ፣ፍላጎት ወይም መፍትሔ ያላገኘ ጉዳይ ያላቸው ሲሆኑ፤እነ ዚህ ችግሮችም በነቀፌታ መንፈስ ራሳቸውን ይገል ጣሉ ።
417