TheDeepThingsOfGod
Open in Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Show more1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 810
#SpiritOfWisdom
በሚስጥር የምናደርጋቸው ነገሮች በአደባባይ ከምናደርጋቸው ነገሮች መብለጥ አለባቸው፥ በአደባባይ ከስተማርናቸው፥ ከፈወስናቸው እና ነጻ ከወጣናቸው ሰዎች በስውር ያስተማርናቸው፥ የፈወስናቸው እና ነጻ ያወጣናቸው ሰዎች መብዛት አለባቸው።
በስውር የተደረጉ በዚህኛው ሕይወት ያልተነገሩና በሚመጣው ዓለም በአባቱና በመላእክቱ ፊት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወድሳቸው ስራዎች ሊኖሩን የግድ ነዉ።
1 810
"እውነትን ተጠቀሙ"
የምታነቡትን ተጠቀሙ : እውነትን ተጠቀሙ
በአእምሮአችሁ ውስጥ አጽኑት: አድራጊዎች ሁኑ: የጸሎታችሁ ክፍል አድርጉት: ሌሎችም እንዳገኙት እርግጠኛ ሁኑ : በራሳችሁ ሕይወት ተግባራዊ አድርጉት : ምን ያህል ተጨማሪ ብርሃን እንደሚያስፈልጋችሁ እወቁ።
ራሳችሁን እንደዚህ ብላችሁ ጠይቁ " በገባኝ እውነት ብርሃን እየተመላለስኩ ነዉ?" "ሕይወቴን እየለወጠው ነዉ?"
➤ወንጌላዊ ኢቫን ሮበርት
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
Yidnekachew Teka - NEW SONG 2016- "በእኔ ዘንድ ያለ ባንተ ዘንድ የሌለ" (ይድነቃቸው ተካ)
https://www.vidmateapp.com/subpub/yqh5/site?url=aHR0cHM6Ly9tLnlvdXR1YmUuY29tL3dhdGNoP3Y9emQ0TGFYbWVfbW8mZmVhdHVyZT15b3V0dS5i
ZQ==&f=sy
🔥Trending video shared via VidMate🔥
🎉Best downloader for video and image on YouTube, WhatsApp status, Facebook, Instagram...
🎉Platform for FREE latest movies🎥🎥
👇Download VidMate Now!👇
https://www.vidmateapp.com/?subpub=sharing
1 810
የተገለጠውን እግዚአብሔር ማወቅ!
ክፍል ሁለት~በልጅ ዳን
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Revival is a conditional promise, there will be revival if we meet the conditions.
1 810
እውነተኛና ቀጣይ የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ የምንፈልግ ከሆነ የግዴታ ወደ እግዚአብሔር እውነት እና የልብ ንጽሕና መመለስ አለብን።
-Victor
1 810
በአንድ ስፍራ ሳስተምር ከተቀዳ ድምጽ ተቆሮጦ የተወሰደ።
A very touching moment😭
The moment of truth!
መንፈስ ቅዱስ ለምን የሐዋሪያት ውጤት የለንም ብዬ ስጠይቀው የመለሰልኝ...
1 810
ልዩነቱ ግልጽ ነዉ!
ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆነ የፀጋ አስተምህሮ:- በፀጋ ድነናል፥ ስለዚህ ምንም አይነት መልካም ስራ መስራት አይጠበቅብንም፥ ምንም አይነት ኃጢአት ውስጥ ብንኖርም ዓለማዊ ኑሮም ቢኖረን እንድናል።
መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆነው የፀጋ አስተምህሮ:- በፀጋ ድነናል ይህም ያዳነን ፀጋ ኃጢአተኝነትን እና ዓለማዊ ምኞትን ክደን የኢየሱስን መምጣት እየተጠባበቅን እና መልካም ስራ ለማድረግ እየቀናን እንድንኖር በዚህ ሕይወት ያስተምረናል።
ቲቶ 2:11-14
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
1 810
የተገለጠውን እግዚአብሔር ማወቅ!
ክፍል አንድ ~በልጅ ዳን
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የአምላክ እውቀት
በዚህኛው ሕይወት ማትረፍ ከምትችሏቸው ነገሮች ሁሉ በላይ እጅግ የከበረ እና በሚቀጥለው ሕይወትና በሚመጣው ዓለም ትልቅ ዋጋ ያለው መዝገብ ነዉ።
የአምላክ እውቀት በዚህኛውም ዓለም እግዚአብሔርን በመፍራት፥ በመንፈስ ሕብረት በማድረግ እና እውነተኛ አምልኮን በማቅረብ፥ መገዛት ያለባቸውን ነገሮች ሁሉ በመግዛት የእግዚአብሔርን ሕይወት መኖር ያስችላል።
የአምላክን እውቀት ያገኘ ሰው ከመደበኛው ሰው የሚለየው ትልቁ ነገር ከዚህ ምድር ያለፈ ራዕይ ማየት መቻሉ ነዉ፥ ሐዋሪያው እንደተናገረ ክርስቶስን ለዚህኛው ሕይወት ብቻ ተስፋ የሚያደርጉ ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ናቸዉ።
ያገኘነው የአምላክ እውቀት በሚመጣው ዓለም የሚኖረንን ስም፥ ስልጣን እና ስፍራ ይወስናል፥ ይህ እስትንፋስን የሚወስድ አሳብ ነዉ(Breathtaking thought)፥ ስለሚመጣው ዓለም ሚስጥር እና ስርዓት ለመናገር አሁን አልወድም፥ ነገር ግን ይሄንን የሚያነበውን ሁሉ ጥያቄ እጠይቃለሁ፥ የአምላክን እውቀት ለማግኘት ምን እያደረክ ነዉ? በቀን ውስጥ ምን ያህል ጊዜ የአምላክን እውቀት ለማግኘት ትሰጣለህ? በመጨረሻ ላይ ዋጋ ያለው ይሄ ብቻ ነዉ፥ ይሄ ከሌለኝ ዋጋ የለኝም።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ከላይ ያለው የንባብ ክፍል ዛሬ እጅግ በጣም አስደንቆኛል፥ የአምላክ እውቀት/አምላክን ማወቅ የሚገኝበትን መንገድ ተግባራዊ በሆነ መልኩ ይገልጻል።🥰
ለብዙ ወራት የፈለኩት ተግባራዊ እውነት ነዉ፥ ዛሬ ግን ቃሉ ተገኝቷል እኔም በልቼዋለሁ፥ እግዚአብሔር ይመስገን።
1 810
ምሳሌ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ልጄ ሆይ፥ ቃሌን ብትቀበል፥ ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት፥
² ጆሮህ ጥበብን እንዲያደምጥ ታደርጋለህ፥ ልብህንም ወደ ማስተዋል ታዘነብላለህ።
³ ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት፥ ለማስተዋልም ድምፅህን ብታነሣ፥
⁴ እርስዋንም እንደ ብር ብትፈላልጋት፥ እርስዋንም እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት፤
⁵ የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን መፍራት ታውቃለህ፥ የአምላክንም እውቀት ታገኛለህ።
1 810
𝙧𝙚𝙘𝙤𝙜𝙣𝙞𝙯𝙚 𝙩𝙝𝙞𝙨!
...𝑖𝑓 𝑦𝑜𝑢𝑟 𝑒𝑦𝑒𝑠 𝑐𝑎𝑛 𝑠𝑒𝑒 #𝑠𝑝𝑖𝑟𝑖𝑡 𝑎𝑛𝑑 #𝑙𝑖𝑓𝑒 𝑎𝑠 𝑦𝑜𝑢 𝑠𝑡𝑢𝑑𝑦 𝑡ℎ𝑒 𝑤𝑜𝑟𝑑, 𝑦𝑜𝑢'𝑟𝑒 𝑒𝑥𝑝𝑒𝑟𝑖𝑒𝑛𝑐𝑖𝑛𝑔 𝑎 𝑚𝑖𝑟𝑎𝑐𝑙𝑒.
ይህንን እወቁ የእግዚአብሔርን ቃል ስታነቡ አይኖቻችሁ መንፈስ እና ሕይወት እየተመለከቱ ከሆነ ተዓምራት እየሆነ ነዉ።
-𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
1 810
ጸሎትና_የእግዚአብሔር_ቃል
አውቃለሁ ብዙ ጊዜ ጸልያችኋል: በጸሎት ክፍላችሁ ወይም የቤተክርስቲያን መሰብሰብያ ውስጥ አምርራችሁ አልቅሳችሁ ታውቃላችሁ: ነገር ግን የፈለጋችሁትን ውጤት ማግኘት አልቻላችሁም! ለምን ? “በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።”
— ዮሐንስ 15፥7
የእግዚአብሔር ቃል አለህ? የእግዚአብሔር ቃል አለሽ? በልባችሁ የእግዚአብሔር ቃል አላችሁ? ጸሎት እውነት ነዉ ትልቅ መንፈሳዊ መሳሪያ ነዉ፥ ነገር ግን እንዴት ነው የምንጸልየው? እንዴትስ ነዉ ይህንን መሳሪያ የምንጠቀመው??? ብዙ ሰዎች ጸሎቴ አልተመለሰም ይላሉ: ለዚህም ይጨነቃሉ ነገር ግን እነሱ የሚጸልዩበትን መንገድ በእግዚአብሔር ቃል አይፈትሹም።
የእግዚአብሔር ቃል በእናንተ ከሌላ ጸሎታችሁ ሁልጊዜ የተፈለገውን ውጤት አያመጣም።
በዚህ ጉዳይ ኢየሱስን እንስማው: የራሳችንን ስሜት ወይም ሰዎች አይደለም ኢየሱስን ራሱን እንስማው: "ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።” አለ! ይሄ ግልጽ ነዉ፥ አንድን ሰው ለትክክለኛ ጸሎት የሚያበቃው በውስጡ ያለ የኢየሱስ ቃል ነዉ።
የእግዚአብሔር ቃል የሌለው ሰው ጸሎትን በትክክለኛው መንገድ ማድረግ በፍጹም አይችልም፥ ለዚህም ጸሎቱ መልስ አይኖረውም፥ የእግዚአብሔርን ቃል እንውደድ።
የእግዚአብሔር ቃል በመንፈሳችን ስኖር የጠየቅነው ሁሉ ይሰጠናል፥ ምክንያቱም የምንጠይቀው በንጹሕ ልብና በቀና መንፈስ ነዉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መሆን ላይ እንጂ ማግኘት ላይ አትስሩ /Work on being not on having. -T.L Osborn
እግዚአብሔር በሃይል የሰራባቸውን አሁንም የሚሰራባቸውን ሰዎች ስትመለከቱ መመኘት ወይም መፈለግ ያለባችሁ እነርሱ ደርሰው የቆሙበትን መድረክ እና ያላቸውን የሚታይ ነገር ሁሉ ሰይሆን የማይታየውን በውስጣቸው ያለ ልባቸውን ነዉ፥ አእምሮአቸውን ነዉ። ምክንያቱም እግዚአብሔር አሁን ያለቸውን ሁሉ የሰጣቸው ለምኞቶቻቸው ብቻ ሰይሆን ተፈትኖ ላለፈ ልብና አእምሮአቸው ነዉ፥ አሁን ባላችሁ ልብና አእምሮ እነርሱ ያሉበት የመቆም እድል ብታገኙም ውጤቱ መበተንና ማፍረስ ነዉ የሚሆነው፥ አስተውሉ መበተን እና ማፍረስ እንደመሰብሰብ እና እንደመገንባት ከባድ አይደለም፥ የትኛውም መንግስት ሃላፊነት የሚሰጠው ሃላፊነቱን ተቀብሎ ለመከወን የበቃ ልብና አእምሮ ላለው ተመራጭ እንጂ ሃላፊነቱን አጥብቆ ለተመኘ ሁሉ አይደለም፥ የእግዚአብሔርም መንግስት ከዚህ የተለየ አይደለም።
-Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መሆን ላይ እንጂ ማግኘት ላይ አትስሩ /Work on being not on having. -T.L Osborn
እግዚአብሔር በሃይል የሰራባቸውን አሁንም የሚሰራባቸውን ሰዎች ስትመለከቱ መመኘት ወይም መፈለግ ያለባችሁ እነርሱ ደርሰው የቆሙበትን መድረክ እና ያላቸውን የሚታይ ነገር ሁሉ ሰይሆን የማይታየውን በውስጣቸው ያለ ልባቸውን ነዉ፥ አእምሮአቸውን ነዉ። ምክንያቱም እግዚአብሔር አሁን ያለቸውን ሁሉ የሰጣቸው ለምኞቶቻቸው ብቻ ሰይሆን ተፈትኖ ላለፈ ልብና አእምሮአቸው ነዉ፥ አሁን ባላችሁ ልብና አእምሮ እነርሱ ያሉበት የመቆም እድል ብታገኙም ውጤቱ መበተንና ማፍረስ ነዉ የሚሆነው፥ አስተውሉ መበተን እና ማፍረስ እንደመሰብሰብ እና እንደመገንባት ከባድ አይደለም፥ የትኛውም መንግስት ሃላፊነት የሚሰጠው ሃላፊነቱን ተቀብሎ ለመከወን የበቃ ልብና አእምሮ ላለው ተመራጭ እንጂ ሃላፊነቱን አጥብቆ ለተመኘ ሁሉ አይደለም፥ የእግዚአብሔርም መንግስት ከዚህ የተለየ አይደለም።
-Victor
1 810
“And you shall seek me, and find me, when you shall search for me with all your heart.”
— Jeremiah 29:13
“እናንተ ትፈልጉኛላችሁ፣ በፍጹም ልባችሁም ከፈለጋችሁኝ ታገኙኛላችሁ፤”
— ኤርምያስ 29:13
