en
Feedback
Addis Ababa Education Bureau

Addis Ababa Education Bureau

Open in Telegram

ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Addis Ababa Education Bureau

Channel Addis Ababa Education Bureau (@wwwaddisababaeducationbureau) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 162 865 subscribers, ranking 667 in the Education category and 154 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 162 865 subscribers.

According to the latest data from 08 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 2 624 over the last 30 days and by 283 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.29%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.03% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 33 055 views. Within the first day, a publication typically gains 16 331 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 90.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

162 865
Subscribers
+28324 hours
+1147 days
+2 62430 days
Posts Archive
በመርሐ ግብሩ ላይ አቶ ሙሉጌታ ጉልማ የአዲስ አበባ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ሀላፊ ፣አቶ አከበረኝ ወጋገን የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ፤ክብርት ወ/ሮ ቦጋለች ተድላ የክፍለ ከተማው ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ፣አቶ ኢብራሒም መሀመድ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ምክትልና ፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ፣አቶ ገነነ ዘውዴ የትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች ሱፐር ቫይዘሮች መመህራን፣ ተማሪዎች፣ የተማሪ ወላጆች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።   ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት ጳጉሜ 4 "የህብር ቀንን" አስመልክቶ የጥያቄና መልስ ውድድርና የግብዓት ስርጭት መርሀ ግብር አካሄደ። (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) በክፍለ ከተማው ጳጉሜ 4 የህ
+8
የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት ጳጉሜ 4 "የህብር ቀንን" አስመልክቶ የጥያቄና መልስ ውድድርና የግብዓት ስርጭት መርሀ ግብር አካሄደ።     (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) በክፍለ ከተማው ጳጉሜ 4 የህብር ቀንን ምክንያት በማድረግ በድምቀትና የተለያዩ ሀገራዊ አንድነትንና ህብረትን በሚያንፀባርቁ መርሐ ግብሮች እየተከበረ ሲሆን በዛሬው እለትም ሀገራዊ አንድነትን የሚያጎሉና የሚያሰርፁ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድሮች ተካሔዷል።   በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አከበረኝ ወጋገን ኢትዮጲያዊያን ከዓለም የምንለይበት የራሳችን የቀን መቁጠሪያ እና ከ80 በላይ ብሔር ብሔረሰቦች በተለያየ የባህል፣የአልባሳት የአመጋገብ እሴት ያለን በህብር የሚቆምና የሚደመር ህብራዊነት ድንቅ ህዝቦች ነን ብለዋል። አቶ ገነነ ዘውዴ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ በበኩላቸው ህብረትና አንድነትን በማስረፅ የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን ለመገንባት ዛሬ ላይ መስራት ተገቢ ነው ብለዋል።   በጥያቄና መልስ ውድድሩ ላይ ለአሸናፊዎች ሽልማት የተበረከተ ሲሆን ለሴት ተማሪዎች ደግሞ የንፅህና መጠበቂያ ግብአቶችን ተበርክቷል።

የኅብር ቀንን በማስመልከት ለተማሪዎች የተለያዩ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ። (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጳጉሜ 4 የኅብር ቀንን በማስመልከት ከተለያዩ
+9
የኅብር ቀንን በማስመልከት ለተማሪዎች የተለያዩ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ። (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጳጉሜ 4 የኅብር ቀንን በማስመልከት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ተቋማት የተሰበሰቡ የመማሪያ ቁሳቁሶችን ለተማሪዎች አስረከበ። በቦሌ ራዕይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በነበረው ርክክብ ከቦሌ ህብረተሰብ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች የቀረቡ 20 ላፕቶፖች ፣ ከአብሮህት ቤተ መጽሀፍት ከምቹ ትሬዲንግ ጋር በጋራ በመሆን 5ሺ የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ ሞዴሶች ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተበረከቱ ደብተሮች ፣ እስክሪብቶዎች ፣ እርሳሶች እንዲሁም ቦርሳዎችና የደንብ ልብሶች ለተማሪዎች ተሰጥቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሳምሶን መለሰ በዛሬው እለት የኅብር ቀንን ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ ይህብረተሰብ ክፍሎችና ተቋማት ተሰብስበው ለተማሪዎች ድጋፍ የተደረጉ ቁሳቁሶች በከተማ አስተዳደሩ እድገት እያሳየ የሚገኘው የተማሪዎች ውጤት የበለጠ እንዲሻሻል የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው ድጋፉን ላደረጉት የቦሌ ህብረተሰብ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች ፣ ከአብሮህት ቤተ መጽሀፍትና ለምቹ ትሬዲንግ እንዲሁም ለስራና ክህሎት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል። የቦሌ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ማስተዋል ፋንታሁን በበኩላቸው የዛሬው ድጋፍ አብሮነታችንን የምናረጋግጥበት መሆኑን በመግለጽ ድጋፉ ለነገ የሀገር ተረካቢ ዜጎች ለሆኑ ተማሪዎች መደረጉ እጅግ የሚያበረታታ ተግባር መሆኑን አመላክተዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

ዛሬ "በኅብር ቀን" ሀገር በቀል እሴቶቻችንን በተግባር በመጠቀም አብሮነትን፣ መረዳዳትንና ሰው ተኮር ተግባራትን ባህል እያደረግን ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር በሁሉም ወረዳዎች፣ ክፍለከተሞች እና በ
+8
ዛሬ "በኅብር ቀን" ሀገር በቀል እሴቶቻችንን በተግባር በመጠቀም አብሮነትን፣ መረዳዳትንና ሰው ተኮር ተግባራትን ባህል እያደረግን ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር በሁሉም ወረዳዎች፣ ክፍለከተሞች እና በማዕከል ለከተማችን ነዋሪዎች ማዕድ አጋርተናል። ሁልጊዜ እንደምናደርገው ጧሪ ደጋፊ ለሌላቸው፣ ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ፣ ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞች፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሰራተኞችን ጨምሮ ከለውጡ ዘመን ጀምረን እርስ በእርስ በመረዳዳት ያለው ለሌለው እንዲያካፍል በማድረግ ማዕድ እናጋራለን ። ዛሬም ክረምቱን ሙሉ እና በበዓላት ስናጋራ እንደነበረው ሁሉ የማዕድ ብቻ ሳይሆን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ እንኳን አደረሳችሁ በማለት ፍቅራችንን፣ አብሮነታችንን እና አክብሮታችንን ለከተማችን ነዋሪዎች አጋርተናል። አዲሱን አመት የፍቅር፣ የሰላም፣ በትጋት ሰርተን የምንለወጥበት እንዲሆን እመኛለሁ። መስጠት አያጎድልም ብለው በከተማችን በሙሉ የምናደርገውን የማዕድ ማጋራት ካላቸው አካፍለው አስተዋፅኦ ላደረጉ ባለሃብቶች፣ ማህበራት፣ ልበቀናዎች ፈጣሪ አምላክ አብዝቶ ይስጣችሁ፤ ከልብ እናመሰግናለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

#EthiopiaPrevails   Guyyaa Waloomaa   Biyyi keenya Itophiyaan duudhaashee biyyaa maddeen, abdii ifaa egeree ishee ofiisheetiin bocaa jirti!   Duudhaalee ajaa’ibsiisaa biyyaa maddaniifi walrharkaa fuudhinsa dhalootaatiin arganne gabbisuufi falaasama Ida'amuutiin hogganamnee, tokkummaa keenya sab-daneessa cimaa ta'eef bu’uura hin raafamnerra keenyeerra. Boqonnaa seenaa haaraa marri biyaalessaa seena-qabeessa ta'e eegaluurraa kaanee, misooma kooriidarii nama giddu-galeessa godhatee jireenya lammiilee keenya hundaa jijjiiru, hojiiwwan keenya tola ooltummaa akkasumas Sagantaa Ashaaraa Magariisa qabatamaan hanga hojiirra oolchuutti, hundi keenya yoo waliin dhaabbannu seenessi keenya waloo gara milkaa’ina walootti akka nuceesisan agarsiifneerra.   Nuti kan ijaarru, biyya cimtuu haammattuu taate, diinagdeedhaan of dandeesse, aadaan waloomaafi wal-gargaarsaa itti dagaage qofa osoo hin taane, guddummaan waloofi humni kuufamaa Itoophiyaanota hundaa keessatti mul'atu gochaan mirkaneessaa jirra. Tokkummaadhaan imala badhaadhinaa keenyaa itti fufna.   Uummata tokko, biyya guddoo Itoophiyaa! #EthiopiaPrevails   ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) የኅብር ቀን ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች! በትውልድ
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት   (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) የኅብር ቀን ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች! በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል።     እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን።   አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ!

ጳጉሜ 4 የህብር ቀን (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) ህብር ማለት የተለያዩ ሰዎች፣ ሀሳቦች፣ ባህሎችና አመለካከቶች ልዩነታቸውን እየጠበቁ በመከባበር፣ በመተባበርና በአንድ ዓላማ ዙሪያ ተሰባስበው አንድ የ
ጳጉሜ 4 የህብር ቀን (ጷግሜ 4/2018 ዓ.ም) ህብር ማለት የተለያዩ ሰዎች፣ ሀሳቦች፣ ባህሎችና አመለካከቶች ልዩነታቸውን እየጠበቁ በመከባበር፣ በመተባበርና በአንድ ዓላማ ዙሪያ ተሰባስበው አንድ የጋራ ኃይልና ውጤት መፍጠር ነው። ህብር ልዩነትን እንደ እንቅፋት ሳይሆን እንደ ጥንካሬ በመመልከት፣ የእያንዳንዱን አበርክቶ በማክበርና የጋራ ጥቅምን በማስቀደም የተሻለ ማህበረሰብና የተሻለ ነገን ለመገንባት የሚያስችል የአንድነት መርህ ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያ በህብር የተለያዩ ሕዝቦች፣ ቋንቋዎች፣ ባህሎች፣ ታሪኮችና አስተሳሰቦች በአንድ ሀገራዊ ማንነት የሚገናኙባትን ሀገር ናት። የኢትዮጵያ ልዩነቶቿን እንደ ጥንካሬና ሀብት በመቀበል በመከባበር፣ በመተሳሰብና በትብብር የጋራ እጣ ፈንታን መገንባት ችላለች፡፡ ኢትዮጵያ የብዝሃነቷን ቀለም አጥብቃ በመያዝ፣ የጋራ እሴቶቿን በማጎልበትና ሁሉም ዜጎቿ በእኩልነት የሚሳተፉበትን የጋራ ራዕይ በመገንባት ወደ ሰላም፣ አብሮነትና ዘላቂ ልማት የምትራመድ ሀገር ሆናለች። በዕለቱ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በሪፎርሙ የተገኙ የዘርፈ ብዙ አካታችነት ስኬቶችን፣ ሀገር በቀል እሴቶችንና የወል ትርክትን በማጎልበት ህብረብሔራዊ አንድነትን ማጽናት፣ እንዲሁም አብሮነትን፣ መረዳዳትንና ሰው ተኮር ተግባራት ባህል ያደረገ ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር፣ በከተማችን አዲስ አበባ የተሰሩ ሰው ተኮር ስራዎች እና የበጎ ፍቃደኞችን ተግባራት በማጉላት የሚያከበር ይሆናል፡፡ በህብር ደምቀን፣ የኢትዮጵያን አዲስ ከፍታ እናበስራለን! ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

መዲናችን አዲስ አበባ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ከአፍሪካ ቀዳሚ ፣ ከዓለም 2ኛ ከተማ ሆነች! ዘኒዮርክ ታይምስ (The New York Times) ይዞት በወጣው ዘገባ፣ የቦታዎች ስጋትየሚያጠናና
+4
መዲናችን አዲስ አበባ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ከአፍሪካ ቀዳሚ ፣ ከዓለም 2ኛ ከተማ ሆነች! ዘኒዮርክ ታይምስ (The New York Times) ይዞት በወጣው ዘገባ፣ የቦታዎች ስጋትየሚያጠናና የሚተነብይ (AlphaGeo) ጂኦስፓሻል ኩባንያ በዓለም ላይ ካሉ ትልልቅ ከተሞች የ72 ቱን የአየር ንብረት የመቋቋም አቅም (Resilience) ደረጃ መድቧል። በዚህ መሠረት የተቀመጠውን መስፈርት በሟሟላት፣ ከተማችን አዲስ አበባ ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለም ሁለተኛ ከተማ በሆን ተቀምጣለች ። ከተማችን አዲስ አበባ እንደስሟ ውብ፣ ንፁህ እና ለመኖር ምቹ ከተማ እናደርጋለን ብለን በገባነው ቃል መሠረት፣ የአፍሪካ ኩራት በአጭር ጊዜ የከተማ ልማት ለውጥ ተምሳሌት በመሆን ላይ ነች። ለመላዉ የከተማችን ነዋሪዎች እና አብራችሁን ተባብራችሁ የሰራችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ https://www.nytimes.com/2026/09/03/realestate/is-your-city-prepared-for-climate-disaster.html

በዚህ ወቅት ታዲያ አዲስ አበባ ያስመዘገበችው ይህ የላቀ ደረጃ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃ እና ዘላቂ የከተሞች ልማት ላይ የምታደርገው ጥረት ፍሬ ማፍራቱን የሚያሳይ ነው። መዲናችን ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ደኅንነቷ የተጠበቀ የጽናት ተምሳሌት መሆኗን እየኖሩባት ላሉት ሁሉ የየቀን እውነት ቢሆንም አሁን ደግሞ ለዓለም ሁሉ የታወጀ ታላቅ ብስራት ነው።

አዲስ አበባ የአየር ንብረት አደጋዎችን በመቋቋም በዓለም 2ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ የምሥራች አበሰረች ዓለም አቀፉ የጂኦስፓሻል አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም አልፋጂኦ (AlphaGeo) የዓለም ታላ
+8
አዲስ አበባ የአየር ንብረት አደጋዎችን በመቋቋም በዓለም 2ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ የምሥራች አበሰረች ዓለም አቀፉ የጂኦስፓሻል አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም አልፋጂኦ (AlphaGeo) የዓለም ታላላቅ 72 ከተሞችን የአየር ንብረት አደጋ የመቋቋም አቅም (Climate Resilience) አመላካች ይፋ አድርጓል። በዚህ አዲሱ ዓለም አቀፍ ደረጃ መሠረት መዲናችን አዲስ አበባ ከዓለም አቀፍ ከተሞች ሁሉ በ2ኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥ አስደናቂ ስኬት አስመዝግባለች። ጥናቱ የከተሞችን ዝግጁነት የለካው ከተፈጥሮ አደጋዎች ተጋላጭነት ነጻ በመሆናቸው ብቻ ሳይሆን አደጋዎችን የመከላከል፣ የማላመድ እና የመቋቋም አቅማቸውን መሠረት በማድረግ ነው። በዚህ መሠረት የአሜሪካዋ ቺካጎ ከተማ በ1ኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ፣ አዲስ አበባ ደግሞ እንደ ሜልቦርን፣ ባርሴሎና እና ፓሪስ ያሉ ታላላቅ የዓለም ከተሞችን በልጣ በዓለም 2ኛ ተስፋ ሰጪ እና ጽኑዕ ከተማ በመሆን ተመዝግባለች። ይህ ታሪካዊ ውጤት በአዲስ አበባ ከተማ በመከናወን ላይ ያሉ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር፣ የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች ለከተማዋ አደጋዎችን የመቋቋም አቅም ያበረከቱትን ታላቅ አስተዋጽኦ በተግባር ያረጋገጠ ነው። ጥናቱ እንደሚያመላክተው፣ ብዙኃኑ የደቡብ እስያ ከተሞች ለአየር ንብረት አደጋ ከፍተኛ ተጋላጭ ሆነው ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ወድቀዋል።

የስራ ክፍሉ ባለሙያዎች ስልጠናው መደበኛ ስራቸውን በማከናወን ሂደት ሊከተሏቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በማንሳት ተጨማሪ እውቀት እንዳገኙበት ገልጸው ስልጠናው ወቅቱን የጠበቀና ሚዲያን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችል ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ ስልጠናው በዋናነት የዲጂታል ሚዲያና የሶሻል ሚዲያ ምንነት እና ባህሪያት ፤የዲጂታል ሚዲያ ጠቀሜታና ሊያስከትላቸው የሚችሉ ጉዳቶች እንዲሁም የሶሻል ሚዲያ ይዘት መረጣ በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ፤የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ትምህርት ክፍል የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን መምህርና የእቅድና ጥናት ክፍል ኃላፊ በሆኑት ፈይሳ ግርማ አማካኝነት ተሰጥቷል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

በሶሻል ሚዲያ እና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀምና ይዘት መረጣ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የሚዲያ ይዘት ማበልፀግና ስርጭት ዳይሬክቶሬት በስራክፍሉ ለሚገኙ ባ
+5
በሶሻል ሚዲያ እና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀምና ይዘት መረጣ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የሚዲያ ይዘት ማበልፀግና ስርጭት ዳይሬክቶሬት በስራክፍሉ ለሚገኙ ባለሙያዎች በሶሻል ሚዲያ እና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀምና ይዘት መረጣ ላይ ትኩረት ያደረገ አቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ፡፡ የሚዲያ ይዘት ማበልፀግና ስርጭት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ የውብዳር አያሌው በሶሻል ሚዲያ እና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀምና ይዘት መረጣ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ትክክለኛ መረጃ ለማሰራጭት ያለው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸው ፤ የሚዲያ ይዘት ዳይሬክቶሬት የቢሮውን የስራ ተልእኮ ከግብ ለማድረስና በቴክኖሎጂ የታገዘና ጥራት ያለው ትምህርት ለማህበረሰቡ ማስተላለፍ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንና ስልጠናው መዘጋጀቱ የስራ ክፍሉ ባለሙያዎች በሶሻልና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያላቸውን አቅም እንደሚያሳድግ ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሯ አያይዘውም ሰልጣኞች ጥራቱን የጠበቀና ተአማኒነት ያለው፤ የሚዲያ ስነምግባርን የጠበቀ መረጃ በማስተላለፍ ሂደት ሊተገብራቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦችን ከስልጠናው በመውሰድ በዘወትር ስራቸው ሊተገብሩት እንደሚገባ ተናግረው፤ ዳይሬክቶሬቱ የባለሙያዎችን ክህሎት ለማሳደግ በየጊዜው ወቅቱን የጠበቀ ሙያዊ ስልጠና ለመስጠት እቅድ መያዙን አብራርተዋል፡፡

የስራ ክፍሉ ባለሙያዎች ስልጠናው መደበኛ ስራቸውን በማከናወን ሂደት ሊከተሏቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በማንሳት ተጨማሪ እውቀት እንዳገኙበት ገልጸው ስልጠናው ወቅቱን የጠበቀና ሚዲያን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችል ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ ስልጠናው በዋናነት የዲጂታል ሚዲያና የሶሻል ሚዲያ ምንነት እና ባህሪያት ፤የዲጂታል ሚዲያ ጠቀሜታና ሊያስከትላቸው የሚችሉ ጉዳቶች እንዲሁም የሶሻል ሚዲያ ይዘት መረጣ በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ፤የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ትምህርት ክፍል የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን መምህርና የእቅድና ጥናት ክፍል ኃላፊ በሆኑት ፈይሳ ግርማ አማካኝነት ተሰጥቷል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘመን ተስፋዬ በበኩላቸው ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በባህልና በጋራ ማንነት ላይ በመስራቱ የተመዘገበው ለውጥ ትልቅ መሆኑን ገልጸዋል። ቀጣይነት ያለው ልማትና የዘላቂ ልማት ግቦችን ከማረጋገጥ አኳያ ትምህርት ትልቅ አቅም መሆኑን ጠቁመው፣ ላለፉት አምስት ዓመታት የክፍለ ከተማው ውጤት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ይህ ስኬት የመምህራን፣ የሱፐርቫይዘሮች፣ የወላጆች እና የተማሪዎች ለትምህርት ያላቸው ዝግጁነት ውጤት መሆኑን ገልጸው፣ የትምህርት ግቢዎችን ለማስተማር ምቹ ለማድረግና የትምህርት ትውልድ ንቅናቄዎችን በማህበረሰብ ተሳትፎ ለማጠናከር የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሰማኸኝ አስታጥቄ የበጀት ዓመቱ የተቋማዊ አፈጻጸም የታየበትና የውጤት ዓመት መሆኑን ገልጸዋል። ከተቋማት መካከል እኩል የመስራት፣ የመረጃ ወቅታዊነትን የማስተካከል እና ስነምግባርን የመቆጣጠር ስራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ መሰራቱን ጠቁመዋል። ከከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና ከክፍለ ከተማው ካቢኔ የተደረገላቸውን ልዩ ድጋፍ በማስታወስ ለአካላት ምስጋና አቅርበዋል። በጉባኤው ላይ የተገኙት ርእሰ መምህራን በበኩላቸው ፣ በትምህርት ቤቶች ውስጥ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማሳለጥና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከወላጆችና ከትምህርት ጽህፈት ቤቱ ጋር በመቀናጀት የተሰሩ ስራዎች ለተመዘገበው ውጤት መሰረት መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የትምህርት ግቢዎችን ደህንነትና ምቹነት በመጠበቅ፣ እንዲሁም የተማሪዎችን ስነምግባርና ውጤት ይበልጥ ከፍ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ አርአያነት ያለው ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በበኩላቸው ለተመዘገበው ስኬት የመምህራኖቻቸው እና የወላጆቻቸው ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበር ገልጸዋል። የተሸለሙት ተማሪዎች በቀጣይም በትምህርታቸው ተግተው በመማር ለሌሎች አርአያ እንደሚሆኑና ሀገርን በብቃትና በእውቀት የሚረከብ ትውልድ ለመሆን እንደሚተጉም ተናግረዋል ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

ወላጆች ለትምህርት ልማት ስራዉ ስኬት የሚናቸዉን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት ማጠቃለያ ጉባኤ የትምህ
+9
ወላጆች ለትምህርት ልማት ስራዉ ስኬት የሚናቸዉን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት ማጠቃለያ ጉባኤ የትምህርት ዘርፉ ማህበረሰብ፣ ርእሰ መምህራን፣ የትምህርት ሱፐርቫይዘሮች፣ የአስሩም ወረዳዎች ትምህርት ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች እና ተማሪዎች በተገኙበት አካሄዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አማካሪ አቶ ጥላሁን ፍቃዱ በጉባኤው ላይ የትምህርት ማህበረሰቡ አገርን ለማሻገርና ለማስቀጠል በመተጋት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። ተማሪዎች የሀገር ተስፋና ነገ ሀገርን የሚረከቡ መሆናቸውን በመጥቀስ፣ በተለይ ከስድስተኛ ወደ ሰባተኛ እና ከሰባተኛ ወደ ስምንተኛ ክፍል ያለፉ ተማሪዎች ይህንን አርአያነት ይዘው በመሄድ ሌሎችም ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ወላጆችም ከትምህርት ቤት ጎን በመቆም የክትትልና የድጋፍ ሚናቸውን ሊጫወቱ እንደሚገባ አሳስበዋል። አያይዘውም እንደ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ያሉ አካባቢዎች በብዙሃን ቋንቋ አተገባበር ላይ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባቸውና ተማሪዎች በሚፈልጉት ቋንቋ እንዲማሩ የማድረግ ሃላፊነት ላይ ጥረት እንዲደረግ ጠቁመዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሌሊስቱ ተስፋዬ በክፍለ ከተማው በ2018ዓ.ም የበጀት አመት የትምህርት ጥራትንና ፍትሀዊነትን ለማረጋገጥ በርካታ አዳዲስ ተቋማት ተገንብተው አገልግሎት እንዲሰጡ ከመደረጉ ባሻገር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሳደግ የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር ለማሻሻል በተሰሩ ውጤታማ ስራዎች ክፍለ ከተማው 5 ትምህርት ቤቶችን ወደ ደረጃ 4 ማስገባት መቻሉን አስታውቀዋል። በጉባኤው የጽህፈት ቤቱ የ2018 ዓ.ም የበጀት አመት እቅድ አፈጻጸም እና የተማሪ ውጤት ትንተና ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን የክፍለ ከተማው መምህራን ማህበር እና የተማሪ ወላጅ ማህበር ሰብሳቢዎች መልዕክት አስተላልፈዋል። በመርሀግብሩ ማጠቃለያ የጉባኤተኛው የተዘጋጀ ባለ 12 ነጥብ የአቋም መግለጫ ከመቅረቡ ባሻገር በበጀት አመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት እና ተማሪዎች እንዲሁም ደረጃ 4 ለገቡ ትምህርት ቤቶች ዕውቅና ተሰጥቷል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የትምህርት ባለድርሻ አካላት ርብርብ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትልቅ ሚና እንዳለው ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) ጽህፈት ቤቱ 33ኛውን ክፍለ ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ "ብሩህ ነገን በዛ
+9
የትምህርት ባለድርሻ አካላት ርብርብ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትልቅ ሚና እንዳለው ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) ጽህፈት ቤቱ 33ኛውን ክፍለ ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ "ብሩህ ነገን በዛሬ አዕምሮዎች" በሚል መሪ ቃል የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በድምቀት አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የመርሀግብሩ የክብር እንግዳ አቶ ሳምሶን መለሰ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽህፈት ቤት በ2018 የትምህርት አመት አዳዲስ የትምህርት ተቋማትን በመገንባት ተማሪዎች ምቹ ሳቢና ማራኪ በሆኑ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ተከታትለው ውጤታማ እንዲሆኑ ማስቻሉን አስታውሰው በበጀት አመቱ በትምህርት ልማት ስራው ለተመዘገበው ውጤት የክፍለ ከተማው አስተዳደር ሲያደርግ የነበረው ድጋፍ የነበረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ በክፍለ ከተማው በ2018 ዓ.ም በ6ኛ ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል የተመዘገበው አበረታች ውጤት በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም ባለድርሻ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባው አስገንዝበዋል። የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራ አድፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ልመነህ ምህረቱ በበኩላቸው ትምህርት በስነ ምግባር የታነጸ ፣ በዕውቀትና ክህሎት የበቃ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጋ ለመፍጠር የሚሰራበት ሴክተር መሆኑን ጠቁመው የክፍለ ከተማው አስተዳደር የጉባኤው ተሳታፊዎች የሚያስቀምጡትን ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሰረት በማድረግ በክፍለ ከተማው የመማር ማስተማር ስራው ውጤታማ እንዲሆን የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አመላክተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አማካሪ ወ/ሮ አበበች ነጋሽ በከተማችን በኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ዘርፍ እየተመዘገቡ ያሉ አመርቂ ውጤቶች ለማስቀጠል የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም በትምህርት መዋቅሩ ውስጥ ያሉ አካላት በትምህርት ስራ ላይ በርብርብ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው ፤ በ2018 ትምህርት ዘመን የመጡ ውጤቶችን በ2019 ትምህርት ዘመንም በተደማሪ ውጤት ለመድገም የትምህርት ጉባኤ መድረክ የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ወ/ሮ አበበች አያይዘውም የትምህርት ጉባኤው ላይ የሚደረጉ ውይይቶች ቢሮው በ2019 ትምህርት ዘመን ያስቀመጣቸው የትኩረት አቅጣጫዎች ሰፊ ርብርብ የሚጠይቁ በመሆኑ፤ የተጀመሩ አበረታች ውጤቶች ፍሬ እንዲያፈሩ የክፍለከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ፣ ወላጆች ፣ የትምህርት ማህበረሰቡና አመራሩ ለስኬት የምንመክርበት እንዲሁም ባስቀመጥነው የጋራ አላማ ላይ በቅንጅት ለመስራት ቃል የምንገባበት እንደሚሆን ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ  በ2018 የትምህርት ዘመን በትምህርት ዘርፍ የተሰሩ ስራዎችና የተማሪዎች ውጤት ትንተና ሪፖርት እንዲሁም የ2019 እቅድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል፤ በክፍለ ከተማው በ2018 ትምህርት ዘመን  ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችም እውቅና ተሰጥቷል ፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

ብቁ ትውልድ ለማፍራት በዛሬ አእምሮዎች ላይ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የጉለሌ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን 33ኛው የትምህርት ጉባኤው
+9
ብቁ ትውልድ ለማፍራት በዛሬ አእምሮዎች ላይ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የጉለሌ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን 33ኛው የትምህርት ጉባኤውን "ብሩህ ነገን በዛሬው አእምሮዎች!" በሚል መሪ ሃሳብ በዛሬው እለት አካሂዷል። የጉለሌ ከፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባርኬ ዲኬ በተማሪዎች ላይ መስራት ሀገራችንን ወደላቀ ደረጃ በማሻገር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልጸው፤ አመታዊው የትምህርት ጉባዔ በትምህርት ዘመኑ የነበሩንን ስኬቶች በመጪው ዘመን በተሻለ ለመድገምና ያጋጠሙ ችግሮች ላይ በመወያየት የመፍትሄ አቅጣጫ የምናስቀምጥበትና ስንቅ የምንይዝበት ይሆናል ብለዋል፡፡ አቶ ባርኬ 2018 የትምህርት ዘመን የተማሪ ውጤትና ስነምግባር ማሻሻል ላይ ትኩረት በመስጠት እንዲሁም የማላቅ ስትራቴጂን ተግባራዊ በማድረግ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ያሻሻልንበት ፤ በ6ኛና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናም ክፍለከተማው ባለፉት አመታት ከነበረው ውጤት የተሻለ ውጤት ያስመዘገበበት መሆኑን ገልጸው ለዚህ ውጤት መመዝገብ የተማሪዎች ወላጆች የትምህርት አመራሩና የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ እንደነበር አብራርተዋል፡፡ የክፍለከተማው ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰ መምህራንን በማብቃት በውጤት የበረታ ፤ በስነምግባር የታነጸ ፤ በስፖርታዊ እንቅስቃሴና በከተማ ግብርና ስራ ላይ ተሳትፎ የሚያደርግ ብቁ ትውልድ ለማፍራትና ከመቼውም ጊዜ በላይ ብሩህ ነገን ለመፍጠር በዛሬ አእምሮዎች ላይ ጸንተንና ተግተን በመስራት የትምህርትን ጥራት እናረጋግጣለን ብለዋል፡፡

የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አንድነት ኃላፊነትና ተሳትፎ ጭምር መሆኑ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት እና ዲዛይንና ግን
+5
የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አንድነት ኃላፊነትና ተሳትፎ ጭምር መሆኑ ተገለጸ፡፡ (ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት እና ዲዛይንና ግንባታ ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ጷግሜ 3 የፅናት ቀንን የብሄራዊ ሰንደቅ አላማ በጋራ በመስቀል አክብረዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አማካሪ አቶ ጥላሁን ፍቃዱ የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አንድነት ኃላፊነትና ተሳትፎ ጭምር መሆኑን በመግለጽ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ አክለዉም የአዲስ አመት መሸጋገሪያ የሆነችው የጳጉሜ ወር ቀናት በተለያዩ ሀገራዊ ድሎችን በሚዘክሩ ስያሜዎች እየተከበሩ እንደሚገኙ ጠቁመዉ ቀደምት አባቶቻችን በአንድነት ቆመው የፀናች ሀገርን እንዳስረከቡን ሁሉ የአሁኑ ትውልድም ሀገርን በሚያፀኑ የልማትና የለውጥ ስራዎች በአንድነት በመቆም የሀገርን ፅናት ማረጋገጥና ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር ኤልያስ ከበደ በበኩላቸው በመሰናሰልና በጋራ በመሆን ብሎም በቁርጠኝነት በመስራት ለላቀ አፈጻጸም ልንተጋ ይገባል ብለዋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc