1 079
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1730 days
Posts Archive
1 079
"እሰሯቸው‼"
ትናንት አዲግራት መንገድ ዘግተው ተቃውሞ ሲያሰሙ የነበሩትን የህውሃት አርሚ 15 አባላት እንዲታሰሩ ትግዛዝ መሰጠቱን የሚያመለክት የስልክ ቅጅ ወጥቷል።በትዕዛዙ ‟...ሰልፍ የወጡትን ታጋዮች ለቃቅማችሁ እሰሯቸው...” ይላል።
ሙሉው ከላይ ተያይዟል 👆
1 079
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የሞባይል ስልክ ስርቆት ፈፅመው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው በተለምዶ "ሿሿ” የተባለውን ወንጀል በመፈፀም ሞባይል ስልክ ሰርቀው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ናትናኤል አለሙ ፣ አቤል ኮርሳ ፣ ዕድላዊት መላከ፣ መቅደስ አቡሽ፣ ኢዛና ባህሩ፣ ፀጋ ታደሰ እና መቅደስ አምዴሳ የተባሉ ሲሆኑ ሽፈራው ገበየሁ በተባለ ግለሰብ ላይ ወንጀሉን የፈፀሙት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ኮዬ ቂሊንጦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ተጠርጣሪዎቹ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 89261 ኦ.ሮ በሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የግል ተበዳይን ጭነው እየተጓዙ ሞባይል ስልኩን ከኪሱ ከሰረቁ በኋላ "ትራፊክ ይቀጣናል ጋቢና ግባ ብለው" እንዳስወረዱት እና ከወረደ በኋላ ጥለውት እንዳመለጡ ተገልጿል፡፡
በግል ተበዳይ ላይ ወንጀል እንደተፈፀመ የተመለከቱ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ፖሊስ በጋራ ባደረጉት ክትትል ወንጀሉን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 5 ሴቶች እና 2 ወንዶች ሳሪስ አቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ ከተሽከርካሪው ወርደው ሊሰወሩ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
በወቅቱ በተሽከርካሪው ላይ በተደረገ ፍተሻ ከተለያዩ ግለሰቦች ላይ በተመሳሳይ መልኩ የተሰረቁ ዘጠኝ ሞባይል ስልኮች የተያዙ ሲሆን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ በተጠርጣሪዎቹ ላይ የጀመረውን የምርመራ ስራ አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ በተጠቀሰው ተሽከርካሪ እና በተያዙት ተጠርጣሪዎች ተመሳሳይ ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚል ግለሰብ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመቅረብ ከተያዙት ስልኮች መካከል የእሱ ንብረት ስለመኖሩ በማረጋገጥ እንዲወስድ እና ለፖሊስ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል፡፡
መሰል የወንጀል አፈፃፀሞችን ለመከላከል በየጊዜው የሚገለፁ የጥንቃቄ መልዕክቶችን ተግባራዊ በማድረግ በከተማችን ሊፈፀሙ የሚችሉ ወንጀሎችን አስቀድሞ መከላከል እና መቆጣጠር እንደሚቻል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውሶ አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥም ህብረተሰቡ ለፖሊስ መረጃ በመስጠት ተባባሪነቱን ማጠናከር እንደሚጠበቅበት ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
1 079
ሸኔ ሲያሠለጥናቸው የነበሩ 68 ሠልጣኞች በመከላከያ ሠራዊት ተይዘዋል።
የማዕከላዊ ዕዝ ጋሻ ኮር በምዕራብ ሸዋ ዞን ጅባት ወረዳ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና በአሸባሪው የሸኔ ቡድን እየሰለጠነ የሚገኘውን በርካታ የቡድኑን አባላት በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።
የኮሩ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ጥላሁን ዱጋሳ የኮሩ የሠራዊት አባላት የአካባቢውን ሠላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ቀን ከሌሊት የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነት ህዝባዊ ባህሪን በተላበሰ መልኩ እየፈፀመ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ሸኔ በተሳሳተ ፕሮፖጋንዳ ወጣቶችን የዕኩይ ተግባሩ መጠቀሚያ ለማድረግ በተለያዩ አካባቢዎች 18 ዓመት ያልሞላቸውን ህፃናት አስገድዶ በመውሰድ የህዝብ ጠላት ሲያደርግ መቆየቱን ጄኔራል መኮንኑ በቁጥጥር ስር ለዋሉ የሸኔ ሠልጣኞች አሥረድተዋል።
በሽቡር ቡድኑ ላይ በተወሰደው የተጠናከረ ዘመቻ በርካታ የቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ 68 እያሰለጠናቸው የነበሩ አባላቱ ከመሳሪያና ተተኳሽ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል።
1 079
አስደንጋጭ መረጃ‼️ 😭😡😭
የስፖርት ጋዜጠኞቹ ግርማቸው እንየው እና ሶፎንያስ እንየው የሴቶች የብሔራዊ ቡድን አባላት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት አስከፊ እየሆነ ነዉ ብለዋል።
ድርጊቱ በሴቶች ብሔራዊ ቡድን ውጤት እና የተጫዋቾቹ ብቃት ከእለት እለት አሽቆልቁሏል ብለዋል።
የቪዲዬም ሆነ የድምፅ መረጃዎች እጃችን ላይ ይገኛል ያሉት ጋዜጠኞቹ ችግሩ ይታረማል ብለን ብንጠብቅም በከፍተኛ ሁኔታ መሰራጨቱ ይፋ ለማድረግ ተገደናል ብለዋል።
1 079
Godina Harargee Lixaatti Hojii Kunuunsa Qabeenya Uumamaa Naannawaa Magaalaa Ciroo!
1 079
“የማዕድን ሀብቶቻችንን ለኢትዮጵያ ብልፅግና የማዋል ብርቱ ጉዞ ላይ ነን።
ዛሬ 4ኛውን የማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖን( MINTEX ETHIOPIA 2025) በይፋ ከፍተናል።” - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
1 079
ኬላዎችን የማንሳት ሥራ‼
ለምርት ነፃ ዝውውር እንቅፋት የሆኑ የክልል ሕገ-ወጥ ኬላዎችን የማንሳት ሥራ ተጀመረ
ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር፤ መንግሥት የማያውቃቸውና ለምርቶች ነፃ ዝውውር ተግዳሮት የፈጠሩ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ሕገ-ወጥ ኬላዎችን ማንሳት መጀመሩን አስታውቋል።
ቁጥራቸው ምን ያህል እንደሆነ እና በየትኛዎቹ ክልሎች እንደሚገኙ ያልተገለጸውን "ሕገ-ወጥ" የተባሉ ኬላዎች ከአገልግሎት ውጭ ለማድረግ፤ ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከጉምሩክ ኮሚሽን፣ ከትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ እንዲሁም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው ተብሏል።
"የሕገ-ወጥ ኬላዎች መብዛት ምቹ የንግድ እንቅስቃሴን አውኳል" ያሉት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ፤ የኬላዎቹ መፍረስ የምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ መቅረብና ያለ ገደብ መሰራጨት ያረጋግጣል፣ ሆነ ተብሎ የሚፈጠርን የምርት እጥረት ይከላከላል፣ ለውጭ ገበያ የሚበርቡበትን እድል ያሰፋል" ብለዋል።
የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ከአጠቃላይ የወጪ ንግድ 8 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ይህም ከ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ እንደነበር ተናግረዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት 9 ነጥብ 4 ቢልዮን ዶላር ለማግኘት መታቀዱን የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ ከዚህ ውስጥ ባለፉት ሦስት ወራት 2 ነጥብ 48 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ጠቁመዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ከ297 በላይ ሕገ-ወጥ ኬላዎች መኖራቸውን በመግለጽ፤ ኬላዎቹ ለማፍረስ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ቢሆንም፤ በዚህ ሕገ-ወጥ ተግባር ላይ የፀጥታ አካላትም በስፋት የሚሳተፍበት በመሆኑ ችግሩ አሁንም ድረስ መዝለቁን ስለማስታወቁ አሐዱ ከዚህ ቀደም መዘገቡ ይታወሳል
