1 079
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1730 days
Posts Archive
1 079
የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ የሆነው እና በማኅበራዊ ሚዲያ ስለ አፍሪካ መልካም ገጽታ የሚሰራው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አኮን ወይም በማኅበራዊ ሚዲያ ሥራዎቹ ዎዴ ማያ በመባል የሚታወቀው ጋናዊው ወጣት በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን እንደሚከተለው አጋርቷል።
በኢትዮጵያ የነበረውን ቆይታ የሚያሳይ ሙሉ ዘጋቢ ፊልሙ የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ይመልከቱ ...
https://youtu.be/N-9ziUnJVeE?si=mPqhFI9q2J7yvwAG
1 079
ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት የአፍሪካ ግብርና
ባለራዕይ ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸናፊ ሆኑ
የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተሸላሚ ናቸው ተብሏል
ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት ፕ/ር ጥላሁን አመዴ፤ የ2025 የአፍሪካ ግብርና ባለራዕይ ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸናፊ ሆኑ፡፡
ፕሮፌሰር ጥላሁን በግብርናው ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋፅኦ ሽልማቱ እንደተበረከተላቸው ተዘግቧል፡፡
ሳይንቲስቱ በአፈር ጤና፣ የአየር ጸባይን ታሳቢ ያደረገ ግብርናን ለማከናወንና ቀጣይነት ያለው የምግብ ሥርዓትን በአፍሪካ እውን ለማድረግ ባከናወኗቸው ተግባራት እውቅና አግኝተዋል፡፡
ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት ከአሜሪካ የአፈር ሳይንስ ሶሳይቲ ያገኙት ሽልማት፣ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ እንደሚያደርጋቸው ተዘግቧል፡፡
1 079
" ያለ ስራ ስነምግባር በስራ ቦታ ባልተገባ መንገድ ሰራተኛን የደበደበ ቻይናዊን ጨምሮ በአራት ሰዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል " - የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ
➡️ " ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል "
በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የሚሰሩ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረሱት ቅሬታ በፓርኩ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በውጭ ሀገራት ዜጎች አካላዊና ስነልቦናዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸው ገልጸዋል።
ባሳለፍነው እሁድም በፓርኩ ውስጥ በሚገኝ 'ቶዮ ሶላር' በተባለ ኩባንያ አንድ ቻይናዊ አንድን ኢትዮጵያዊ ሲደበደበዉና ልጁም መሬት ላይ ወድቆ የሚያሳይ ቪዲዮም ልከዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቪዲዮዉን ከተመለከተ በኋላ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞችንና አመራሮች እንዲሁም የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥራ አስኪያጅ ለማነጋገር ሞክሯል።
ሰራተኞች ምን አሉ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞች አግኝቶ ለማነጋገር ቢሞክርም ለደህንነታቸው ሲሉ ለጊዜዉ ያለውን ችግር ለማውራት እንዳልተመቻቸው ገልፀው በሌላ ጊዜ መረጃ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
በሌላ መልኩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ አመራሮችን ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ስልክ ባለማንሳታቸው ለጊዜው አልተሳካም።
ነገር ግን በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚሰሩ ሌሎች ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " መብታችን ተረግጦ ነው እየሰራን ያለነው። የዚህ ልጅ ድብደባ በቪድዮ ወጣ እንጂ ሌሎችም ብዙ መሰል ነገር ያጋጥማቸዋል። ለሰው ኃይል ክፍል ሲከሱ ብር ይቀጧቸውና ወደ ስራ ነው የሚመልሷቸው " ብለዋል።
" አቤት የምንልበት አጥተናል ሰው እንዴት በሀገሩ እንዲህ ይደረጋል ? የምንሰራው አስራ ሁለት ሰዓት ነው። በዛ ላይ ክፍያው ልፋታችንን የሚመጥን አይደለም ለመኖር ነው የምንሰራው። እንደዛም ሆኖ ግን ክብር በሌለበት ነው የምንሰራው። ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ድብደባ፣ ስድብ ፣ ማንቋሸሽ ይደርስባቸዋል፤ የጉልበት ስራ እንደ አህያ እያሸከሙ ነው የሚያሰሩት " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይሄን ነገር መንግሥት ያውቀዋል ? ከባድ ነገር ነው እየገጠመን ያለው፤ ድምጻችንን ስሙልን " ብለዋል።
ፓርኩ ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊን አግኝቶ አነጋግሯል።
አቶ ማቴዎስ ፤ " በፓርኩ በሚገኘዉ ቶዮ ሶላር ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚሰራ ኢትዮጵያዊ ሞያተኛ እና የውጪ ሀገር (ቻይናዊ) ዜግነት ባለው ሱፐር ቫይዘር መካከል በስራ ቦታቸዉ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት የተስተዋለው ጠብና ድብድብ ፍፁም ከስራ መርህ ውጭ የሆነና የፓርኩን መተዳደሪያ ደንብ የሚፃረር ነው ፤ የሚወገዝም ተግባር ነው " ብለዋል።
ፓርኩ ከኢትዮጵያ ኢንዱትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን አስፈላጊውን ማጣራት አድርጎ በሂደቱ ውሰጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ የነበራቸውን ሁለት የውጪ ዜጎች ከስራ እንዲባረሩና #ከሀገር_እንዲወጡ እንዲሁም በካምፓኒዉ ውስጥ ያሉ በጉዳዩ ቀጥተኛ ተሳታፊ ያልሆኑ ሶስት አመራሮች ደግሞ ከባድ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው መደረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
ከዚህ ባለፈ ፥ ካምፓኒው ጉዳዩ በቪዲዮ ከተላለፈው በዘለለ በሰራተኛውና በቅርብ አለቃው መካከል ለተስተዋለው ግጭት መነሻ የነበሩ ምክንያቶችን በመዘርዘር ሁለቱም የተጋጩበትን መንገድ ፤ ኢትዮጵያዊውም የነበረውን ጥፋቶች በመዘርዘር ከስራ እንዲባረር ወስኖ የነበረ ሲሆን ፓርኩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ስራ እንዲመለስ መወሰኑን ተናግረዋል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚዘዋወሩ መረጃዎች መበራከታቸውን በመግለፅ " ልጁ ሞቷል፣ አጥንቱ ተሰብሯል " የሚሉና መሰል መረጃዎች የተሳሳቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
" ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል " ሲሉ አክለዋል።
1 079
ለኤሌክትሪክ ባስ አገልግሎት ፈጣን መንገድ ሊገነባ ነው!
በአዲስ አበባ ከተማ ለኤሌክትሪክ ባስ አገልግሎት የሚውል ፈጣን መንገድ ሊገነባእንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ነው የገለጸው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ እያሱ ሰለሞን እንደገለጹት ፈጣን መንገዱ በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን እና በአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ በጋራ የሚገነባ ነው።መንጠዱ15 ነጥብ 64 ኪሎ ሜትር ርዝመት ይኖረዋል።
ፕሮጀክቱ 20 ዘመናዊ ጣቢያዎችና 12 ተጨማሪ አገልግሎቶች የያዘ ነው ብለዋል፡ፕሮጀክቱ በቀን 400 ሺህ የሚደርሱ መንገደኞችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ገልጸው፤ በየመዳሻዎቹ ከአንድ እስከ 15 ደቂቃ ባለው ጊዜ የሚደርስ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ርዝመት ከፒያሳ እስከ ጀሞ-3 ኮንዶሚኒየም ያሉትን መንገዶች የሚሸፍን ሲሆን ወጪውም የከተማው አስተዳደር እንዲሁም በአጋርድርጅቶች እንደሚሸፈን የዘገበው ኢፕድ ነው።
1 079
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 22ተኛ ኤርባስ ኤ350-900 አውሮፕላኑን በዛሬው ዕለት ተቀበለ። አየር መንገዱ ዛሬ የተረከበው ይህ ዘመናዊ አውሮፕላን 21ደኛ ኤ350-900 አውሮፕላኑን ከተቀበለ ሁለት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሲሆን ይህም በዓለም ዙሪያ ለሚያጓጉዛቸው መንገደኞቹ እጅግ ዘመናዊ፣ የላቀ እና ምቹ አገልግሎትን ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ 22ተኛ ኤርባስ ኤ350-900 አውሮፕላኑን በዛሬው ዕለት ተቀበለ። አየር መንገዱ ዛሬ የተረከበው ይህ ዘመናዊ አውሮፕላን 21ደኛ ኤ350-900 አውሮፕላኑን ከተቀበለ ሁለት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሲሆን ይህም በዓለም ዙሪያ ለሚያጓጉዛቸው መንገደኞቹ እጅግ ዘመናዊ፣ የላቀ እና ምቹ አገልግሎትን ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
1 079
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ራዕይ ብልጽግናን ማረጋገጥ ነው!!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ራዕይ ብልጽግናን ማረጋገጥ ነው። ከትናንት ወረት ቆጥረን ዛሬን በትጋትና ጥበብ ሠርተን ለትውልድ የበለጸገ ሀገር ማሻገር ራዕይን ሰንቀናል፡፡ ራእያችንን ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲጋሩን እንፈልጋለን፡፡ በዚህ ራዕይ ውስጥ የኢትዮጵያዊ ማኅፀን ያፈራው ሁሉ ራሱን ሊመለከትበት ይገባል፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን በከፋ ጭቆና፣ በተደጋገመ ጦርነት፣ በአሰቃቂ ረሃብ፣ አንገት በሚያስደፋ ስደትና ጉስቁልና ውስጥ አልፈናል፡፡ መከራና ችግር እንደዶፍ ቢወርድብንም፣ የድህነት ሐሩር እንደሰም አቅልጦ እንደጧፍ ቢያነደንም፣ ሳንረታና ሳንበተን በብርታት ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ በፈተና ውስጥ ያበረታን ወረታችን ነው፡፡ ዐርበኝነትና መንፈሳዊነት ታላላቅ ወረቶቻችን ናቸው፡፡ ዛሬ እነዚህን አንጡራ ወረቶቻችንን ይዘን፣ ጉልበታችንን ያዛለውን ድህነትን አራግፈን፣ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ ራዕይ ሰንቀናል፡፡
የመደመር መንግሥት ገጽ 295፣ 2018 ዓ.ም
1 079
ተጠርጣሪው ተይዟል‼
በተማሪ ሊዛ ደሳለኝ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል።
የደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከአንድ ወር በላይ በፈጀ ምርመራና ክትትል በተማሪ ሊዛ ደሳለኝ ግድያ የተጠረጠረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎታል።
የግድያው ተጠርጣሪ ደሳለ ሲሳይ የሚባል ሲሆን እዛው ደሴ ከተማ የታክሲ ረዳት ሆኖ ሲሰራ ማክሰኞ ህዳር 2/2018ዓም በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል።
ተማሪ ሊዛ ከራያ አካባቢ ወደ ደሴ ከተማ በመሄድ የኮሌጅ ትምህርቷን ስትከታተል ነበር።
መስከረም 28/2018ዓም ስልክ ለማሰራት በወጣችበት ግድያ እንደተፈፀመባት ከዚህ በፊት መዘገቡ ይታወሳል።
በጉዳዩ ላይ ፖሊስ መምሪያው ዛሬ ህዳር 4/2018 ዝርዝር መግለጫ እንደሚሰጥ ታውቋል።
የደሴ ከተማ ፖሊስ ወንጀልን መከላከልና ወንጀል ፈፃሚን ለህግ ማቅረብ ስራችሁ ቢሆንም ይህንን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ለማድረግ የሄደበት ርቀት የሚደነቅና የሚያስመሰግን ነው።
1 079
Wiirtuu Kenna tajaajila Iddoo tokkoo magaalaa #Adaamaa!
Wiirtuun kenna tajaajila iddoo tokkoo (MESOB) tajaajilli kennamu fedhii lammiilee giddu-galeessa kan godhate taasisuu, mootummaafi lammiilee gidduutti walitti - dhufeenya gaarii uumuu, alseerummaafi alnaamusummaa hojimaata duubatti hafaa hambisuu, sirna iftoominaa kenna tajaajilaa keenya dijjitalessuu, saffisiisuufi itti gaafatamummaa mirkaneessuu keessatti qooda guddaa qaba!
