en
Feedback
Estifanos Getahun

Estifanos Getahun

Open in Telegram
1 079
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1730 days
Posts Archive
photo content
+3

photo content

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ ነገ እሁድ ህዳር  7 ቀን 2018 ከሌሊቱ 6:00 እስከ ሌሊቱ 9፡45 ሰዓት ድረስ በሲቢኢ ብር ከሚሰጡ አገልግሎቶች በስተቀር ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አገልግሎቶች እንደሚቋረጡ አስታውቋል **** "ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ ነገ እሁድ ህዳር  7  ቀን 2018 ከሌሊቱ 6:00 እስከ ሌሊቱ 9፡45 ሰዓት ድረስ በሲቢኢ ብር ከሚሰጡ አገልግሎቶች በስተቀር ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አገልግሎቶች  ማለትም  በሞባይል ባንኪንግ፣ በኢንተርኔት ባንኪንግ፣  በኤቲኤም ማሽኖች እንዲሁም በፖስ ማሽኖች እና በኮር ባንኪንግ የሚሰጡ አገልግሎቶች (Core Banking Services) በጊዜያዊነት ይቋረጣሉ። በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህን አውቃችሁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እያሳወቅን፣ ለሚፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል ይቅርታ እንጠይቃለን። ብሏል"

photo content

"ደሴ ከለውጥ በኋላ የሠላም፣ የልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ተምሳሌት ከሆኑ ከተሞቻችን ውስጥ አንዷ እየሆነች ነው" - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Jaalalli Walloorraa maddu Itoophiyaa maraaf ga'aadha

በጉራጌ ዞን በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስም የተሰየመው ት/ቤት በዛሬው እለት ተመርቋል። በምስጋና የበጎ አድራጎት ድርጅት ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነባው የዶክተር አብይ አህመድ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ሀዋሪያት ከተማ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ ሀላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል። በዚህም የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱ የሚታወቅ ሲሆን የተገነባው ትምህርት ቤት የዞኑ የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር ከማሻሻል ባለፈ በሀገር ደረጃ ብቁ ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት አበርክቶው ከፍተኛ ነው ተብሏል። የትምህርት ቤቱ ግንባታም 8 የመማሪያ ክፍሎች፣ ዘመናዊ ቤተመጽሀፍት፣ የአስተዳደር ቢሮ፣ የመምህራን ስታፍና ሌሎችም ያካተተ ነው ተብሏል። በምረቃ ፕሮግራሙም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዋና ገዥ ዶክተር እዮብ ተካልኝ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል፣ የምስጋናው የበጎ አድራጎት መስራችና የበላይ ጠባቂ አምባሳደር ምስጋናው አርጋው እና የእምድብር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሉቃስ ፍቅሬ ተገኝተዋል።

photo content

ሠራዊታችን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን እያፀና ነው -   ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ ሠራዊቱ የኢትዮዽያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ ገለጹ፡፡ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ፤ በሰሜን ጎጃም እና በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች በግዳጅ ላይ የሚገኘውን ኮር የግዳጅ አፈጻጸም የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ከመስክ ምልከታቸውም በኋላ ከዞንና ከወረዳ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አመራሮች ጋር የተወያዩ ሲሆን በሰሜን አቸፈር ወረዳ ሊበን ከተማ በአንድ ክፍለ ጦር የስልጠና ማጠናቀቂያ ላይ በመገኘትም የስራ መመሪያና ስምሪት ሰጥተዋል። ሌተናል ጄኔራል መሃመድ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሰራዊቱ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት የተሰለፈውን ፅንፈኛ ቡድን ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና ይገኛል ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች በመሽሎክለክ ሕብረተሰቡን በማገትና በመዝረፍ ወንጀል የሚፈፅመውን ፅንፈኛ ቡድን ሰራዊቱ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር ተከታትሎ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አንስተው፤ ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመቀበል በክህደት በዜጎች ላይ ወንጀል ለመፈፀም የሚንቀሳቀሰውን ፅንፈኛ ቡድን በየደረጃው የሚገኘው አመራር፣ ሕዝቡና የፀጥታ ሃይሉ በትብብር ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ኢዜአ እንደዘገበው በኢትዮጵያ ሁሉም አካባቢዎች ሰላምን በማፅናትና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማሳካት የኢትዮጵያን እድገትና ብልፅግና ማረጋገጥ የሁላችንም አደራ እና ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የሰላምና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለኢትዮጵያ ክብርና ሉአላዊነት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ዝግጁነት የሚገኝ መሆኑን ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ አረጋግጠዋል።

photo content
+2

በ20 ብር ስልካቸውን ሱቅ የሚያስቀምጡት ተማሪዎች ተጨማሪ ይመልከቱ 👉 https://getutemesgen.et/32162/ #Ethiopia | የሞባይል ስልካቸውን 20 ብር በመክፈል ሱቅ አስቀምጠው ወደ ክፍል የሚገቡ  ተማሪዎች እየተበራከቱ መምጣታቸውን ባደረግነው ቅኝት መመልከት ችለናል። የትምህርት ሚኒስትር ባወጣው መመርያ መሰረት ማንኛውም ተማሪ የሞባይል ስልክ ይዞ ት/ቤት እንዳይገባ በመመርያው ሰፍሮ ይገኛል። ይህንንም ተከትሎ ወላጆች ልጆቻቸው ስልክ ይዘው ወደ ት/ቤት እንዳሄዱ እንዲያደርጉም ሲል ነበር ያዘዘው። ግን ቅኝት ባደረግንባቸው የመንግስትና የግል ት/ቤቶች በርካታ ተማሪዎች ስልካቸውን ከት/ቤታቸው አቅራቢያ በሚገኙ ሱቆች 20 ብር በመክፈል አስቀምጠው ወደ ክፍል እንደሚገቡ ተመልክተናል። ተማሪዎቹ ለምሳ በሚለቀቁበት ሰአት ስልካቸውን ተቀብለው ባላቸው ሰአት የማህበራዊ ሚዲያ እንደሚጠቀሙም ተመልክተናል። እንዲያውም ከምሳ በፊት የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ለቲክቶክ ሰርተው እንደሚለቁም ለመታዘብ ሞክረናል። ለሱቅ 20 መክፈል ያልቻሉ አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ በምሳ እቃቸው ስልኩን ደብቀው እንደሚገቡም ነው ከአንዳንድ እማኞች የሰማነው። ባስ ሲል ደግሞ ከአቅም በላይ የሆኑ ውስን ተማሪዎች ስልካቸውን በግልጽ በመያዝ የመምህራን እንቅስቃሴ በመቅረጽ በማህበራዊ ሚዲያ ሲለቁት ይስተዋላል። ተማሪዎቹ ስልካቸው ሱቅ ማስቀመጥና ይዘው መግባታቸው አይደለም ዋናው ችግር። ችግሩ ተማሪዎቹ ክፍል ውስጥ የሚያከናውኑት ክዋኔ ነው። # የውጭ ተከታታይ ፊልሞች መመልከት # የተለያዩ የእግር ኳስ ውርርድ ጫወታዎች መወራረድ እና ሌሎችም ተግባራቶች እንደሚያደርጉ ነው የሰማነው። # የወሲብ ፊልሞች መመልከት እስኪ እነዚህን ጥያቄዎች እንመልሳቸው ወላጆች ልጆቻችሁን ወደ ት/ቤት ስትልኩ ምን እንደያዙ ምን ያህል ታረጋግጣላችሁ? እንዲሁም የቀን የት/ቤት ቆይታቸው ምን መልክ እንደነበረውስ ለማወቅ የምትሄዱበት ርቀት አለ ወይ? ትምህርት ሚኒስትርስ ያወጣውን መመርያ መሬት ላይ መሩረዱን አረጋግጦ ይሆን? ይህ ችግርስ እንዳለ ት/ቤቶች ያውቁ ይሆን? ከተማሪዎቹ 20 ብር ተቀብለው ስልካቸውን የሚያስቀምጡ ባለ ሱቆችስ ይህ መመርያ እንደወጣ ያውቁ ይሆን? ለዚህ ጉዳይ ተጠያቂው ማን ነው ትላላችሁ?

photo content

ዕዙ ማንኛውንም ተልዕኮ መፈፀም በሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል።      ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ዕዙ ከየትኛውም አቅጣጫ ሊሰነዘር የሚችል ጥቃትን መመከት በሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ ። ዋና አዛዡ ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዕዙ የግዳጅ  ቀጣናዎች አሁናዊ የተልዕኮ አፈፃፀም ዙሪያ የመስክ ምልከታና  ቅኝት አድርገዋል። ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ከከፍተኛ አመራሮቹ ጋር በነበራቸው ቆይታ የሠራዊቱ ዝግጁነትና ተልዕኮ አፈፃፀም የባዳውን ዕኩይ ሴራዎች መከታተልና መቆጣጠር በሚያስችል ደረጃ የተጠናከረ መሆኑን አንሰተዋል። የባንዳዎቹ ተስፋ ከባዳዎቹ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ባንዳዎቹ ህይወታቸውን ለማቆየት ከባዳዎቹ የሚጠብቁት ፍርፋሪና ባዳዎቹ በህገወጥ መንገድ ማግበስበስ የሚፈልጉት የኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት በጠንከራ ቁጥጥርና ክትትል የበለጠ መጥበብ አለበት ሲሉም አሳስበዋል። የሠራዊቱ አሰፋፈር፣ ቁርጠኝነትና የስነ - ልቦና ዝግጁነት ከመቼውም ጊዜ የላቀ ነው ያሉት ዋና አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ባዳዎቹ ስለ ኢትዮጵያ ምንም ሊያስቡ ይችላሉ ነገር ግን ለመተንኮስ ሲያስቡ ከባድ ዋጋ እንደሚከፍሉም ጭምር ማሰብ ይገባቸዋልም ብለዋል። በፅንፈኛው ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጃ በላኪውም ሆነ በተላላኪው ላይ ድንጋጤ ፈጥሯል ያሉት አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ የሠላም አማራጭ በማይከተሉ፣ የኢትዮጵያን ልማት በሚያደናቅፉና የባዳዎቹን ተልዕኮ ለማስፈፀም በሚፍጨረጨሩ ኃይሎች ላይ የምንወስደው እርምጃ ጠንከር ያለ ነው ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ዘገባው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ነው።

photo content
+2

በማኅበራዊ ሚዲያ ስለ አፍሪካ መልካም ገጽታ የሚሰራው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አኮን ወይም በማኅበራዊ ሚዲያ ሥራዎቹ ዎዴ ማያ በመባል የሚታወቀው ጋናዊው ወጣት በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ በርካታ የተፈጥሮ ሀብቶች እና በሰው ዘር መገኛዋ አፋር ተገኝቶ ያደረገውን ጉብኝት እንደሚከተለው አጋርቷል። ሙሉ ዘጋቢ ፊልሙ የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/N-9ziUnJVeE?si=IA_NzGC1Jwq0YQCK

ዛሬ ጠዋት በአማራ ክልላዊ መንግሥት ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው ከሚሴ ተገኝቼ ለሕዝቡ መልዕክት አስተላልፌያለሁ። በአማራ ክልል ከጎበኘኋቸው ዞኖች እስከአሁን ያልጎበኘሁት ዞን በ
+9
ዛሬ ጠዋት በአማራ ክልላዊ መንግሥት ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው ከሚሴ ተገኝቼ ለሕዝቡ መልዕክት አስተላልፌያለሁ። በአማራ ክልል ከጎበኘኋቸው ዞኖች እስከአሁን ያልጎበኘሁት ዞን በመሆኑ ጉብኝቱን የተለየ ያደርገዋል። የከሚሴ የኮሪደር ልማት ሥራ በጅምር ደረጃ ያለ ቢሆንም የ1.3 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መንገድ እና የእግረኛ መንገድ ሥራዎች የሚመሰገኑ ናቸው። የኮሪደር ልማት ሥራ የሕዝባዊ ሥፍራዎችን ደረጃ ከፍ በማድረግ ዕሳቤ በሁሉም ደረጃ በመላው ኢትዮጵያ እየተተገበረ መሆኑን ያሳያሉ። በከተማዋ ለሌማት ትሩፋት ሥራችን አስተዋጽዖ እያበረከተ ያለውን የኤልፎራ አግሮ-ኢንዱስትሪ የተቀናጀ የግብርና ልማት ፋብሪካንም ጎብኝተናል።

photo content
+8

ሰሞኑን ጂንካ ላይ የታየው ወረርሽኝ የኢቦላ ዝርያ ግን ከኢቦላም የከፋ መሆኑ ተረጋገጠ‼️ ወረርሹኙ  ማርበርግ የተሰኘ ቫይረስ ( Marburg virus) የሚያስከትለው በሽታ መሆኑን የኢትዮጵያ ጤና ሚንስተር አረጋግጧል። የአሜሪካው የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ማዕከል (CDC) ቫይረሱን “እምብዛም የማይከሰት  ግን በጣም የከፋ በማለት ገልፆት ገዳይ ሊሆን ይችላል” ብሏል። በሽታው ከ ‘ ግብጿ የፍራፍሬ  ለሊት ወፍ’ ( Egyptian fruit bat)  የሚመጣ ሲሆን  በህመሙ ከሚያዙ ሰዎች ግማሽ ያህሉ ህይወታቸው እንደሚያልፍ ጥናቶች ያሳያሉ። በሽታዉ የሚተላለፈው በሰውነት ፈሳሽ ንክኪ ፤  ህክምናው ደግሞ እረፍትና ፈሳሽ አብዝቶ መውሰድ (የእገዛ ህክምና) መሆኑ ተዘግቧል። ህብረተሰቡ የቫይረሱን  መተላለፊያ  መንገድ በመረዳት አስፈላጊውን ጥንቃቄ  ማድረግ ይኖርብናል። የበሽታው መተላለፊያ መንገዶች እና ማዳረግ ስለሚገባን ጥንቃቄ ጤና ሚኒስቴር ያወጣውን መረጃ ከላይ ተያይዟል።