1 079
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1730 days
Posts Archive
1 079
ዛሬ በይፋ መርቀን ስራ ያስጀመርነው የዘዉዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የላቀ የሕክምና ማዕከል ዓለም አቀፍ ጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ ተገንብቶ ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሟላ ነው።
በውጪ ሀገራት ንፁህ እና ዘመናዊ የህክምና መሳሪያ የተሟላላቸዉ የህክምና ማእከላትን ስናይ “ መቼ ይሆን በሃገሬ ይህንን የመሰለ ለባለሙያው፣ ለታካሚው እንዲሁም ለአስታማሚው ጭምር የተመቸ ዘመናዊ የጤና ማዕከል የሚኖረው?” ለሚለው ቀና ቁጭት ምላሽ የሰጠ ነው።
ይህ የላቀ የሕክምና ማዕከል የተለያዩ አገልግሎቶች የተካተቱበት ሲሆን ፦
• የተኝቶ ህክምና ህሙማን ክፍሎች (IPD)
• የጨረር ህክምና አገልግሎቶች
• ኤም አር አይ፣ ሲቲ-ስካንእና ኤክስሬይ
• የህፃናት እና የአዋቂዎች ፅኑ ህሙማን ክፍሎች (ICU)
• የኦክስጅን ማምረቻ ፕላንት
• የቪአይ ፒ አልጋዎች
• የኦፒዲ ክፍሎች
• የኦፕራሲዮን ክፍሎች(OR) እና የማገገሚያ ክፍሎች እንዲሁም
• የድንገተኛ ክፍል አልጋዎች
• በየህክምናው አይነትና በየወለሉ ፋርማሲ እና የመድሃኒት ስቶር
• ላቦራቶሪ
• የአስተዳደር ቢሮዎች
• የማብሰያ ክፍሎች፣ ዋና ካፊቴሪያ፣ በየወለሉ ለሚገለግሉ ባለሙያዎች የሚሆኑ ካፊቴሪያዎች
• የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ አገልግሎት የሚሰጡ ክፍሎችን ከውብ ምድረ ግቢ ጋር አካቷል፡፡
ይህን ለማሕበረሰባችን ፋይዳው እጅግ የላቀ የጤና ማዕከል ለአገልግሎት እንዲበቃ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ ያበረከታችሁ ተቋማት ፣ አመራሮች እና ባለሙያዎችን በተገልጋዩ ሕብረተሰብ እንዲሁም በራሴ እና በከተማ አስተዳደሩ ስም ከልብ አመሰግናለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1 079
መልክ-አዲስ፥ ተምሳሌተ አዲስ ትውልድ፣ የብልፅግና መንገድ፤
ከለዉጡ ማግስት ጀምሮ፥ የስኽበት ማዕከል በሆነችዉ አዲስ አበባ፣ በፍጥነትና በጥራት ከተጠናቀቁ መሰረተ - ልማቶች መካከል፥ ወጣቱን በአዕምሮ፤ በአካል እና በስነ-ልቦና የሚገነቡ፤ የከተማዋን ገፅታ የሚቀይሩ፤ በዓለም ተወዳዳሪነትን የሚያጎናፅፉ እና የትዉልዱን መፃኢ ዕድል የሚያመላክቱ፣ ዘመን ተሻጋሪ ዘመናዊ የስፖርት ማዘዉተሪያዎችና መዝናኛዎች በጥራት ገንብታ እንኾ ብላለች። እንዲሁም፤ ለኪነጥበቡ ዕድገት፣ ለተተኪ ከያኒ ምቾት፣ አንፊዎች እና በዓይነታቸው ልዩ የሆኑ ሲኒማ ቤቶች፣ ቴአትር ቤቶች እነኆ ብላለች። ቃል ወደ ተግባር የመቀየር ባህል በውል የታየባቸው የመንግስት እና የህዝብ ድምር ዉጤቶች ናቸዉ፡፡
ኑ! ተጠቀሙባቸው።
1 079
ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮልሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
1 079
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ያየሁት ነገር፤ ሰው የጠራ ራዕይ ካለው ፣ በከፍተኛ ዲሲፕሊን የሚሠራ ከሆነ አንድን ነገር ባየው ልክ ማሳካት እንደሚችል ፤ ኢትዮጵያ ብቃት ያላት ሀገር እንደሆነች ነው።
1 079
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+9
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና ጽሕፈት ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት በመለወጥ መሃል ከተማ ወደ ቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሕንፃ አዛውሯል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር ችሏል። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሕይወታችንን በፍጥነት በመቅረጽ ውስጥ ያለውን ስፍራ በሚያንፀባርቅ እና ሀገራችንም በዚህ አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር በንቁነት መሳተፏን በሚያረጋግጥ መንገድ ከፍታ ላይ ደርሷል። ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል።
በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ መዐከል ደግሞ ይኽንን ከባቢ የበለጠ ያጠናክረዋል። ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል። እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቅመዋል።
1 079
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሚዛን አማን ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩ 27 ደቡብ ሱዳናውያን ወጣቶች ተፈትተው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገለጸ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሚዛን አማን ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩ 27 ደቡብ ሱዳናውያን ወጣቶች ተፈትተው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገለጸ።
አርብቶ አደሮቹ ወጣቶች በኢትዮጵያ መቼ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ባይገለጽም፤ የደቡብ ሱዳን መገናኛ ብዙኃን አንድ ዓመት ገደማ በእስር ሳይቆዩ እንዳልቀረ ዘግበዋል።
ወጣቶቹን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሂደት በስኬት መጠናቀቁ የተገለጸው፤ የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር መንደይ ሰማያ ከኢትዮጵያ አቻቸው ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ጋር በጉዳዩ ላይ ያደረጉትን የስልክ ውይይት በማስመልከት በዛሬው ዕለት በተሰራጨ መግለጫ ነው።
የደቡብ ሱዳን መንግስት 27 የታጠቁ አርብቶ አደሮች፤ በኢትዮጵያ በእስር ላይ እንደሚገኙ ያረጋገጠው ባለፈው መስከረም ወር አጋማሽ ነበር።
የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ አፑክ አዩኤል ማየን በወቅቱ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ከምስራቅ ኢኳቶሪያ ግዛት 27 ወጣቶች “በድንገት” ሁለቱ ሀገራት የሚዋሰኑትን ዓለም አቀፍ ድንበር እንዳቋረጡ ተናግረው ነበር።
ከ1,100 ኪሎ ሜትር በላይ የሚረዝመውን የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን ድንበር እየተሻገሩ የሚፈጸሙ ጥቃቶች፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባዎች ጭምር በየጊዜው ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል።
ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በተጨማሪ በጋምቤላ በኩል ድንበር የሚሻገሩ የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች፤ ግድያ፣ የህጻናት አፈና እና የቀንድ ከብቶች ዝርፊያ እንደሚፈጽሙ ክልሉ በተደጋጋሚ ባወጣቸው መግለጫዎች ማስታወቁ አይዘነጋም።
ምንጭ ኢትዮጵያን ኢንሳይደር
1 079
የአማራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለፖሊስ አባላት እና መሪዎች እውቅና ሰጠ።
የአማራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የላቀ አፈጻጻም ላከናወኑ የፖሊስ አባላት እና አመራሮች የእውቅና እና የማበረታቻ መርሐ ግብር አካሄዷል።
ምክትል ኮሚሽነር አበበ ደለለ የአማራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ላለፉት 33 ዓመታት ከ130 ሺህ በላይ የፖሊስ አባላትን በተለያየ ሙያ አሰልጥኖ ወደ ስራ በማሰማራት ለህግ የበላይነት መከበር የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ያለ አንጋፋ የስልጠና እና የምርምር ተቋም ነው ብለዋል።
ላሳዩት የላቀ አፈፃፀም እንዲበረታቱ የተፈቀደላቸው የፖሊስ አባላት እና አመራሮች በቀጣይ የበለጠ የተጣለባቸውን ኀላፊነት እንዲወጡ አደራ ጭምር ነው ብለዋል።
የክልሉ መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከሐምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከኮሌጅ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ደረጃ እንዲያድግ መደረጉ ለተቋሙ ከፍተኛ መነሳሳት ፈጥሯል ብለዋል።
በተቋሙ አዳዲስ የስልጠና መርሐ ግብሮችን በመቅረጽ ዋና የጥናት እና ምርምር ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ፕሬዝዳንት አስገንዝበዋል።
የአማራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ደኅንነት በማረጋገጥ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለ የሚገኝ ተቋም ነው ያሉት የደብረ ማርቆስ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ ናቸው።
ተቋሙ ዓለም አቀፋዊ ይዘትን ተላብሶ የማኅበረሰብ አገልግሎት በመስጠት ልምድ የሚወሰድበት እንዲሆን በጋራ መስራት አለብን ሲሉ አክለው ተናግረዋል።
የምሥራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኑርልኝ ብርሀኑ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ በስነ-ምግባር የተገነቡ እና ተልዕኳቸውን በአግባቡ መወጣት የሚችሉ የፖሊስ አባላትን ለማፍራት የጀመረውን የሪፎርም ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
ዘመኑን የሚመጥን አሰራር በመዘርጋት ኅብረተሰቡ የሚፈልገውን የሕግ የበላይነት በማረጋገጥ ሕዝቡ ከገጠመው የጸጥታ ችግር ማሻገር የሚችል ፖሊሳዊ ተቋም እንዲሆን በጋራ መስራት አለብን ብለዋል።
የአማራ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በእውቀትእና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ብቁ የጸጥታ ኀይል በመገንባት እየተጋ ያለ ተቋም ነው ያሉት ደግሞ በዕውቅና ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት በሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ናቸው።
የፖሊስ አባላቱ ያገኙትን ማዕረግ ወደ ላቀ ተግባር በመቀየር እና ተልዕኮን በላቀ ቁርጠኝነት በመወጣት በክልሉ ያጋጠመው የጸጥታ መደፍረስ መቋጫ እንዲያገኝ የጋራ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በአሳዩት አፈፃፀም እውቅና እና ማበረታቻ የተሰጣቸው የፖሊስ አባላት እና አመራሮች ያገኙት ማዕረግ እድገት እና እውቅና የተሰጣቸውን ኀላፊነት አጉልተው በመወጣት ማኅበረሰቡ እያጋጠሙት ካሉ ችግሮች እፎይታ እንዲያገኝ በላቀ ደረጃ እንድንሰራ የሚያነሳሳ ነው ብለዋል።
በመድረኩ ተቋሙ በ1985 ዓ.ም ከማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተነስቶ አሁን ለደረሰበት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ደረጃ እንዲደርስ ጉልህ ድርሻ ላበረከቱ ተቋማት እና የስራ ኀላፊዎች ምስጋና ቀርቧል።
