en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 479 subscribers, ranking 6 043 in the Religion & Spirituality category and 2 334 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 479 subscribers.

According to the latest data from 30 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 530 over the last 30 days and by 23 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 39.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.20% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 666 views. Within the first day, a publication typically gains 1 477 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 33.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 479
Subscribers
+2324 hours
+1447 days
+53030 days
Posts Archive
ቅዱስ ሲኖዶስ ለትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ እና መልሶ ግንባታ የ20 ሚልየን ብር ድጋፍ አደረገ !!! ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጦር
+4
ቅዱስ ሲኖዶስ ለትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ እና መልሶ ግንባታ የ20 ሚልየን ብር ድጋፍ አደረገ !!! ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጦርነቱ ወቅት ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰበት የትግራይ ክልል ለሰብዓዊ ድጋፍ እና ለመልሶ ግንባታ የሚውል የሃያ ሚልየን ብር ድጋፍ አድርጓል። የቅዱስ ሲኖዶሱን የገንዘብ ድጋፍ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዛሬው ዕለት ለክልሉ ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ አስረክበዋል። በዛሬው ዕለት ቅዱስነታቸውን ጨምሮ የቅዱስ ሲኖዶሱ የሰላም ልዑክ ይህንን ድጋፍ ለማስረከብ እና በትግራይ ክልል ከሚገኙ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ለመወያየት ወደ መቐለ ማቅናቱ ይታወቃል። በዚሁ የሰላም ልዑክ ላይ ከሰንበት ት/ቤት አንድነት የተወከሉ የአንድነቱ አመራሮች ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ።

“ንጹሐንን ከርኩሳን ጋር አታጥፋቸው” ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ በግዞት ካለበት ወደ እስክንድርያ እንደማይመለስ ያረጋገጠው አርዮስ የእስክንድርያ ክርስቲያኖች ሊቀበሉት እንደሚችሉ ተስፋ በማድረግ ወደ
“ንጹሐንን ከርኩሳን ጋር አታጥፋቸው” ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ በግዞት ካለበት ወደ እስክንድርያ እንደማይመለስ ያረጋገጠው አርዮስ የእስክንድርያ ክርስቲያኖች ሊቀበሉት እንደሚችሉ ተስፋ በማድረግ ወደዚያ ሔዶ ነበር። የአርዮስ ወደ እስክንድርያ መመለስ በቀላሉ ሊበርድ የማይችል ሁከት አስነሣ። የሁከቱ ምክንያትም የእስክንድርያ ክርስቲያኖች መንፈሳዊ አባታቸውን ቅዱስ አትናቴዎስን በስደት ማጣታቸው አንሶ በአርዮስ መመለስ እጅግ መበሳጨታቸው ነበር (አዶንያስ ብርሃነ፣ ገጽ ፪፻፴፭)። .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ንጹሐንን-ከርኩሳን-ጋር-አታጥፋቸው/ “ንጹሐንን ከርኩሳን ጋር አታጥፋቸው” ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

በትሕትና የሚሸሹት በፍቅር የሚሸከሙት የክርስትናን ቀደምት ዘመናት ታሪክ ስናገላብጥ የአበው እና እማት የኑራቸው ፍሬዎች፣ የተጋድሏቸው ምስክሮች የሆኑ ድንቅ ድንቅ ታሪኮች ተመዝግበው እናገኛለን፡፡ ቅ
በትሕትና የሚሸሹት በፍቅር የሚሸከሙት የክርስትናን ቀደምት ዘመናት ታሪክ ስናገላብጥ የአበው እና እማት የኑራቸው ፍሬዎች፣ የተጋድሏቸው ምስክሮች የሆኑ ድንቅ ድንቅ ታሪኮች ተመዝግበው እናገኛለን፡፡ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ብሎ ያዘዛቸውን አምላክ ቃል ሲተገብሩት እናያለን፡፡ ማስተዋል ለቻለ ትእዛዙን ጠብቀው፣ በፍጹም ልባቸው ፈጣሪያቸውን በማመን፣ በትሕትና፣ በመታዘዝ፣ ወንድማቸውን እንደ ራስ በመውደድ ቅድስናን ገንዘብ ሊያድርጓት ያለ መታከት የተጋደሉበት ፍኖት ትልቅ የወንጌል መዓድ ነው፡፡ ቢያነቧቸው ትምህርት የሚሆኑ፣ ቢተገብሯቸው በረከት የሚያሰጡ አስደማሚ የቅዱሳን ገድል ተከትበውባቸዋልና፡፡ ዛሬ አንዱን ቅዱስከድርሳንቀድተን እንዘክራለን፡፡ .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/በትሕትና-የሚሸሹት-በፍቅር-የሚሸከሙት/ በትሕትና የሚሸሹት በፍቅር የሚሸከሙት ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፤ ዛሬ ረቡዕ፣ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በአካሄደው ልዩ ስብሰባ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መርጧል። የተመረጡት ኢጲስ ቆጶሳት
+1
ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፤ ዛሬ ረቡዕ፣ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በአካሄደው ልዩ ስብሰባ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መርጧል። የተመረጡት ኢጲስ ቆጶሳት በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልሎች፤ ተደርበው በቆዩ፣ ክፍት በሆኑ እና አንገብጋቢ ተብለው በግንቦት 2015 ዓ.ም. በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤ ስብሰባ ላይ በተለዩትና ሰባት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ያሉበት አስመራጭ ኮሚቴ በተሰየመላቸው መሠረት ነው። ኢጲስ ቆጶሳቱ የተመረጡላቸው ሀግረ ስብከቶች ሰባቱ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ሲሆን ሁለቱ በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ ናቸው። ከይፋዊው የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ላይ ባገኘነው መረጃ መሠረት ዝርዝራቸ፦ ለኦሮሚያ ክልል ሰባት አህጉረ ስብከት፤ 1. አባ ሣህለ ማርያም ቶላ - ምዕራብ አርሲ - ሻሸመኔ ሀገረ ስብከት 2. አባ ወልደ ገብርኤል አበበ - ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት 3. አባ ጥላሁን ወርቁ - ምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት 4. አባ ዓምደ ሚካኤል ኀይሌ - ሆሮ ጉድሩ ወለጋ - ሻምቡ ሀገረ ስብከት 5. አባ ኀይለ ማርያም ጌታቸው - ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት 6. አባ ተክለ ሃይማኖት ገብሬ - ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት 7. አባ እስጢፋኖስ ገብሬ - ቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ለደቡብ ኢትዮጵያ ሁለት አህጉረ ስብከት፤ 8. አባ ክፍለ ገብርኤል ተክለ ሐዋርያት - ጌድኦ አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት 9. አባ ስብሐት ለአብ ወልደ ማርያም - ዳውሮ እና ኮንታ ሀገረ ስብከት ናቸው። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

ለክፉዎች መድኃኒት የሚሆን የጵጵስና አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በክፋቱ በሚታወቀው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት ብፁዕ አባ ጢሞቴዎስ የሚባሉ በሀገረ ግብፅ የእንስና ወይም እንዴናው ሀገረ ስብ
ለክፉዎች መድኃኒት የሚሆን የጵጵስና አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በክፋቱ በሚታወቀው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት ብፁዕ አባ ጢሞቴዎስ የሚባሉ በሀገረ ግብፅ የእንስና ወይም እንዴናው ሀገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ ነበሩ። የወንጌል ገበሬ ስለነበሩ በሀገረ ስብከታቸው እየዞሩ ወንጌለ መንግሥትን ለሰው ልጅ ሁሉ ያስተምሩ የነበረው ሳይታክቱ ነበር። የኤጲስ ቆጶሱ ዞረው ወንጌልን ማስተማራቸው የጠቅላይ ግዛቱን ገዥ ዕለት ዕለት ያበሳጨው ነበር። ሀገረ ገዥውም ስለተበሳጨ አስጠርቶ “በክርስቶስ ማመንህንና ወንጌልን ዞረህ ማስተማርህን ተው” በማለት አስጠነቀቃቸው (መጽሐፈ ስንክሳር ኅዳር ፲፫ የሚነበበው)። አባ ጢሞቴዎስ ግን ድሆችን ከመደገፍ፣ ከማስተማር እና ከማጽናናት እንዲሁም አሕዛብን ከማስተማር የሚያቆሙት ሲሞቱ ብቻ መሆኑን እቅጩን ነገሩት። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ለክፉዎች-መድኃኒት-የሚሆን-የጵጵስና-አገ/ ለክፉዎች መድኃኒት የሚሆን የጵጵስና አገልግሎት ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የመንግሥት ጣልቃገብነት ከሕገ ወጡ ቡድን ድጋፍ እስከ ጳጳሳት ምርጫ የሃይማኖትና የመንግሥት ግንኙነትን በተመለከተ አገራት የየራሳቸውን ሥርዓት ይከተላሉ። መንግሥት ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮም በተለያዩ
የመንግሥት ጣልቃገብነት ከሕገ ወጡ ቡድን ድጋፍ እስከ ጳጳሳት ምርጫ የሃይማኖትና የመንግሥት ግንኙነትን በተመለከተ አገራት የየራሳቸውን ሥርዓት ይከተላሉ። መንግሥት ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮም በተለያዩ ዘመናት ሃይማኖትና መንግሥት የተለያዩ የግንኙነት መርሖችን አልፈዋል። ሃይማኖት ከመንግሥት በላይ የሆነበት ጊዜ የነበረውን ያህል መንግሥትም ከሃይማኖት በላይ ተደርጎ የተወሰደበት ዘመን እንደነበር የዘርፉ ምሁራን ይገልጻሉ። ባለንበት ዘመን አብዛኛዎቹ አገራት የሚመሩት መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው በሚለው መርሕ ነው። ይህም ሆኖ ዓለማዊ መንግሥት ኖሯቸው፣ አንድን ሃይማኖት ብሔራዊ ሃይማኖት አድርገው ያወጁ አገራት አሉ። እንግሊዝ እና ግብጽ ለዚህ ተጠቃሽ ምሳሌዎች ናቸው። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የመንግሥት-ጣልቃገብነት-ከሕገ-ወጡ-ቡድን/ የመንግሥት ጣልቃገብነት ከሕገ ወጡ ቡድን ድጋፍ እስከ ጳጳሳት ምርጫ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ ያከናወናቸው ተግባራትና ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገባቸው ጉዳዮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም በነበረው የርክበ ካ
የኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ ያከናወናቸው ተግባራትና ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገባቸው ጉዳዮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤው ዘጠኝ አዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም ሰባት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ያሉበት አስመራጭ ኮሚቴ መሠየሙ ይታወቃል። አዲስ ኤጲስ ቆጶሳት የሚመደብባቸው ዘጠኙ አህጉረ ስብከትም ምዕራብ ወለጋ፣ ምሥራቅ ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ምዕራብ አርሲ (ሻሸመኔ)፣ ድሬ ዳዋ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ፣ ቡኖ በደሌ፣ ጌዴኦ፣ ቡርጂና አማሮ እንዲሁም ዳውሮ ኮንታ አህጉረ ስብከት ናቸው። የአስመራጭ ኮሚቴው አባላት ደግሞ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስና ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሲሆኑ አስመራጭ ኮሚቴው ግንቦት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ሥራውን በይፋ የጀመረ መሆኑን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት አሳውቋል። .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የኤጲስ-ቆጶሳት-አስመራጭ-ኮሚቴ-ያከናወና/ የኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ ያከናወናቸው ተግባራትና ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገባቸው ጉዳዮች ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ተሿሚዎችን ለምእመናን አለማሳወቅ የሚያስከትለው መዘዝ በዘመናችን ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የሚፈጸሙ ጉዳዮች በርክተዋል። አባቶች የሠሩትን ቀኖና እያፈረሱ የቤተ ክርስቲያንን ሐዋርያዊ ቅብብሎሽ አስ
ተሿሚዎችን ለምእመናን አለማሳወቅ የሚያስከትለው መዘዝ በዘመናችን ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የሚፈጸሙ ጉዳዮች በርክተዋል። አባቶች የሠሩትን ቀኖና እያፈረሱ የቤተ ክርስቲያንን ሐዋርያዊ ቅብብሎሽ አስጠብቃለሁ ብሎ መናገር አይቻልም። ከእግዚአብሔር ይልቅ ቄሳርን ለማስደሰት የሚደረገው ሙከራ በእግዚአብሔር የሚያስጠይቅ በታሪክም የሚያስወቅስ ነው። ቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ከለባት ብላ በምትጠራው የኬልቄዶን ጉባኤ እነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ንጉሥ ለማስደሰት ብለው እንደ ሌሎቹ መለካውያን ቢሆኑ ኖሮ ርትዕት የሆነችው ሃይማኖት ከዘመናችን ባልደረሰች ነበር። .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ተሿሚዎችን-ለምእመናን-አለማሳወቅ-የሚያ/ ተሿሚዎችን ለምእመናን አለማሳወቅ የሚያስከትለው መዘዝ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ከጠቅላይ ቤተ ክሕነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋር መክሯል ----- የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት በትግራይ ክልል ከተፈጠረው  ወቅታዊ ችግር ጋር በተያያዘ በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰኑ ውሳኔዎች አፈፃፀምን በተመለከተ  ከጠቅላይ ቤተ ክሕነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ከብጹእ አቡነ አብርሃም ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ ከተነሱ ጭብጦች መካከል ቅዱስ ሲኖዶስ  በጀት ወስኖ አቅጣጫ ያስቀመጠበት ለትግራይ ክልል ይላካል የተባለው እርዳታ ተፈጻሚ ያልሆነበት ምክንያትና  በፍጥነት ሊፈጸም ስለሚችልበት ሁኔታ፤ እንዲሁም በትግራይ የሚገኙ አገልጋዮች ደሞዝና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ ከብጹእነታቸው ጋር መክሯል። ብጹእነታቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተፈጻሚ ያልሆነበትን ምክንያቶች አስረድተው፣ “የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢያዘገዩንም በአጭር ጊዜ ውስጥ እርዳታውን ለማድረስ ጥረት እያደረግን ነው” ብለዋል። አክለውም፤ የካሕናቱ ደሞዝና ተያያዥ ጉዳዮች እየታዩ መሆኑንን ገልጸዋል። በትግራይ ክልል ከተፈጠረው አስከፊ ሁኔታ በተጨማሪ የምእመኗ እና የካሕናቷ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳዋ መሆን የሚገባት ቤተ ክርስትያን የትኛውንም መሰናክል አልፋ ቅዱስ ሲኖዶስ በወሰነው ውሳኔ መሠረት ተገቢውን እርዳታ ወደ ክልሉ በአፋጣኝ መላክ እንዳለበት እና በትግራይ የሚገኙ ካሕናት ደሞዝና ተያያዥ ጥያቄዎች በአፋጣኝ እንዲመለሱ የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት አሳስቧል። ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ በቅድስት ቤተ ክርስትያናችን በትግራይ በሚገኙ ቅዱሳን አባቶችና በመዓከል ከሚገኙ አባቶች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ለመፍታት ከተቋቋመው ኮሚቴ አባል ከሆኑት ከብጽእ አቡነ ፊሊጶስ ጋር የእርቅና የሰላም ሂደቱ ምን ላይ እንደደረሰ አንድነቱ ተወያይቷል። በዚህ ውይይት፤ የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት አሐቲ ቤተ ክርስትያንን ከመጠበቅና ከማስቀጠል አንጻር የተቋቋመው ኮሚቴ በአባቶች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት በፍጥነት በእርቅ እና በሰላም እንዲፈታ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንዲገፋበት በማሳሰብ፤ ከሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት የሚጠበቁ ግዴታዎችን ሁሉ ለመወጣት ቃል ገብቷል። [የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት ከብፁእነታቸው ጋር ያደረገው ምክክር የተከወነው ከትናንት በስትያ ነው።] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ከጠቅላይ ቤተ ክሕነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋር መክሯል ----- የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት በትግራይ ክልል ከተፈጠረው  ወቅታዊ ችግር ጋር በተያያዘ በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰኑ ውሳኔዎች አፈፃፀምን በተመለከተ  ከጠቅላይ ቤተ ክሕነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ከብጹእ አቡነ አብርሃም ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ ከተነሱ ጭብጦች መካከል ቅዱስ ሲኖዶስ  በጀት ወስኖ አቅጣጫ ያስቀመጠበት ለትግራይ ክልል ይላካል የተባለው እርዳታ ተፈጻሚ ያልሆነበት ምክንያትና  በፍጥነት ሊፈጸም ስለሚችልበት ሁኔታ፤ እንዲሁም በትግራይ የሚገኙ አገልጋዮች ደሞዝና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ ከብጹእነታቸው ጋር መክሯል። ብጹእነታቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተፈጻሚ ያልሆነበትን ምክንያቶች አስረድተው፣ “የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢያዘገዩንም በአጭር ጊዜ ውስጥ እርዳታውን ለማድረስ ጥረት እያደረግን ነው” ብለዋል። አክለውም፤ የካሕናቱ ደሞዝና ተያያዥ ጉዳዮች እየታዩ መሆኑንን ገልጸዋል። በትግራይ ክልል ከተፈጠረው አስከፊ ሁኔታ በተጨማሪ የምእመኗ እና የካሕናቷ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳዋ መሆን የሚገባት ቤተ ክርስትያን የትኛውንም መሰናክል አልፋ ቅዱስ ሲኖዶስ በወሰነው ውሳኔ መሠረት ተገቢውን እርዳታ ወደ ክልሉ በአፋጣኝ መላክ እንዳለበት እና በትግራይ የሚገኙ ካሕናት ደሞዝና ተያያዥ ጥያቄዎች በአፋጣኝ እንዲመለሱ የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት አሳስቧል። ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ በቅድስት ቤተ ክርስትያናችን በትግራይ በሚገኙ ቅዱሳን አባቶችና በመዓከል ከሚገኙ አባቶች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ለመፍታት ከተቋቋመው ኮሚቴ አባል ከሆኑት ከብጽእ አቡነ ፊሊጶስ ጋር የእርቅና የሰላም ሂደቱ ምን ላይ እንደደረሰ አንድነቱ ተወያይቷል። በዚህ ውይይት፤ የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት አሐቲ ቤተ ክርስትያንን ከመጠበቅና ከማስቀጠል አንጻር የተቋቋመው ኮሚቴ በአባቶች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት በፍጥነት በእርቅ እና በሰላም እንዲፈታ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንዲገፋበት በማሳሰብ፤ ከሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት የሚጠበቁ ግዴታዎችን ሁሉ ለመወጣት ቃል ገብቷል። [የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት ከብፁእነታቸው ጋር ያደረገው ምክክር የተከወነው ከትናንት በስትያ ነው።] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ፍኖተ-ጎርጎርዮስ የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን አባቶች የኤጲስ ቆጶስነት መንበሩ የሚጠይቀው መንፈሳዊ ሕይወትና የትምህርት ዝግጅት እያላቸው፣ ትእምርታዊ ገድል እየተጋደሉ፣ የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ ተልእ
ፍኖተ-ጎርጎርዮስ የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን አባቶች የኤጲስ ቆጶስነት መንበሩ የሚጠይቀው መንፈሳዊ ሕይወትና የትምህርት ዝግጅት እያላቸው፣ ትእምርታዊ ገድል እየተጋደሉ፣ የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ ተልእኮ በፍጹም ፍቅር እየፈጸሙ እና በተግባር እየኖሩት ሹመቱን ግን እንደ ጦር ሲፈሩት ኖረዋል፡፡ ሽሽታቸው አፍአዊ እንዳልነበረ ለዚህ ዘመን የሚተርፍ ጥብዓታቸውን በዚህ ጽሑፋችን ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ወሳኝ የታሪክ አንጓዎች ላይ እየተከሠቱ በቃልና በኑሯቸው በተራራ ላይ እንዳለች መብራት ሲያበሩ የኖሩት አበው ከሢመት የመሸሻቸው ምክንያቱ ከልብ የመነጨ ትሕትና ነበር፡፡ በልብ ‹‹ምን አማራጭ አላቸው ዙረው ዙረው እኔው እግር ላይ ተደፍተው መለመናቸው አይቀርም፤›› ከሚል ራስን የትምክህት ማማ ላይ ሰቅሎ በአፍኣዊ ግን ትሑት መምሰልን ከመሻት የሚቀዳ ሽሽት አልነበረም፡፡ የራስን ዐቅም በትሑት ሰብእና መዝኖ፣ በማንኛውም ሥጋ ለባሽ ልብ ውስጥ ቦታ ያለውን ከፍ ያለ ሥልጣን የማግኘት መሻትን ተዋግቶ በመግራት የሚደረስበት ውሳኔ ነው፡፡ .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ፍኖተ-ጎርጎርዮስ/ ፍኖተ-ጎርጎርዮስ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ሄሮድያዳ ዛሬም የዮሐንስን አንገት ለማስቀላት እየተዋጋች ነው። ቍስጥንጥንያ አዲሲቷ ሮም በሚል ስያሜ የምሥራቅ ሮማ ግዛት ዋና ማዕከል ነበረች፡፡ ከአራተኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ያለፈቃዱ ቢሆንም
ሄሮድያዳ ዛሬም የዮሐንስን አንገት ለማስቀላት እየተዋጋች ነው። ቍስጥንጥንያ አዲሲቷ ሮም በሚል ስያሜ የምሥራቅ ሮማ ግዛት ዋና ማዕከል ነበረች፡፡ ከአራተኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ያለፈቃዱ ቢሆንም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾሞላታል፡፡ የቅዱሱን ሹመት ተከትሎ የቁስጥንጥንያ መንበረ ፓትርያርክ እና ካህናቱ ከቅምጥል የአኗኗር ዘይቤ ጋር ተለያይተዋል፡፡ መንበረ መንግሥቱ ደግሞ በንጉሠ ነገሥት አርቃድዮስ (አርቃዲዎስ) እጅ ሲሆን ንግሥቲቷ አውዶክስያ ነበረች፡፡ ------- ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ሄሮድያዳ-ዛሬም-የዮሐንስን-አንገት-ለማስ/ ሄሮድያዳ ዛሬም የዮሐንስን አንገት ለማስቀላት እየተዋጋች ነው። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

“ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁ” ገላ. ፪፡፲፬ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የተጠመቅን ሁላችን ክርስቶስን እንደለበስን፣ በክርስቶስ አንድ እንደሆንን፣ ከዚህ አንድነት መውጣት ከክርቶስ አካል
“ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁ” ገላ. ፪፡፲፬ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የተጠመቅን ሁላችን ክርስቶስን እንደለበስን፣ በክርስቶስ አንድ እንደሆንን፣ ከዚህ አንድነት መውጣት ከክርቶስ አካልነት ከቤተ ክርስቲያን ኅብረት መለየት መሆኑን ደጋግሞ ነግሮናል። ለዚህም ነው ለገላትያ ክርስቲያኖች “አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፤ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፤ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና” በማለት የነገራቸው። የክርስቶስ አካልነት በዘር፣ በጎሣ፣ በቋንቋ ወይም በፆታ የሚገኝ ሳይሆን መንፈሳዊ ሰው ለመሆን በመሠራት ገንዘብ የሚደረግ ነው። ቤተ ክርስቲያንም አካለ ክርስቶስ እንደመሆኗ በቋንቋና በዘውግ የምትወሰን አይደለችም። እንዲያውም ቤተ ክርስቲያንን በእነዚህ ምድራዊ አሳቦች መወሰን በመንፈስ ቅዱስ ላይ ትልቅ ጽርፈት ነው። አምላካዊውንም ሕግ በሰብአዊ ሕግ ለመተካት መሞከር ነው። ቅዱስ ዮስጢኖስ ፖፖቪች የተባለ አባት ስለዚህ ጉዳይ ሲናገር እንዲህ ብሏል። ------- ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ሁላችሁ-በክርስቶስ-ኢየሱስ-አንድ-ሰው-ና/ “ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁ” ገላ. ፪፡፲፬ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ ለአስመራጭ ኮሚቴው በደብዳቤ አሳውቋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት፤ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን አግባብ የኢጲስ ቆጶሳት ምልመላ፣ መስፈርት እና ሂደት ለሕዝብ ይፋ ሆኖ በግልፅ መከናወን እንደሚኖርበት በደብዳቤው አጽእኖት ሰጥቷል። በተጨማሪም፤ እስካሁን በተኼደበት መንገድ ከተቀጠለ፤ የሕግና የቀኖና ጥሰት፣ እንዲሁም ይሁንታ የማጣት ጉዳይ ሊከሰት እንደሚችል አሳስቧል። ደብዳቤውን የተረከቡት የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ደብዳቤውን ለኮሚቴው አቅርበው እንደሚመክሩበት አሳውቀዋል። በሌላ በኩል፤ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በግቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የወሰነውን የአዳዲስ ኢጲስ ቆጶሳት ሢመት በተመለከተ በምልዓተ ጉባኤው የተሰየሙት የአስመራጭ ኮሜቴ አባላት ሥራቸውን ያጠናቀቁ መሆኑን በመግለጽ ኮሚቴው አዘጋጅቶ በሚያቀረበው እጩ ኢጲስ ቆጶሳት ምርጫ ዙርያ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ለማስተላለፍ ይቻል ዘንድ በሚል ለሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ምልዓተ ጉባኤ ጠርቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለአስመራጭ ኮሚቴው በደብዳቤ ያሳወቃቸው ጥያቄዎች ከተጠራው ምልዓተ ጉባኤ መስየም እና የመጨረሻ ውሳኔ በፊት ታይተው የተዛቡ አካሄዶች ይስተካከላሉ የሚል እምነት አሳድሯል። https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ትምህርት-ቤቶች-አንድነት-በኤጲ/ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ ------- ዝርዝሩን ይመልከቱ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org
የሰንበት ትምሕርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ ------- ዝርዝሩን ይመልከቱ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ትምህርት-ቤቶች-አንድነት-በኤጲ/ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሃያ አንድ በዚች ዕለት የአዳምና የዘሩ ድኅነት የተደርገባት አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የታላቁ በዓል መታሰቢ
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሃያ አንድ በዚች ዕለት የአዳምና የዘሩ ድኅነት የተደርገባት አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የታላቁ በዓል መታሰቢያና በዓለም ሁሉ የቤተ ክርስቲያን መታነጽ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሳችሁ! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU - Statistics & analytics of Telegram channel @eotcgssu21