Grace & Truth Ministry
Open in Telegram
እንኳን ወደዚህ ቻናል በሰላም መጡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ በእውነት ቃልና በፀጋው መንፈስ ይታነፁ
Show more1 029
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2030 days
Posts Archive
በዚህ ምድር ሰዎች ሁሉ የተሟላ ደስታን ይፈልጋሉ ፡ ምናልባትም ደስታውን የሚፈልጉበት መንገድ ይለያያል እንጂ ደስታን በየትኛውም አቅጣጫ የማይፈልግ የለም። ዳዊት በዚህ ጉዳይ ላይ "እግዚአብሔርን አሰብከት ደስም አለኝ " ሲል "ሲያስቡት እንኳ ደስ የሚያሰኝ እግዚአብሔር መሆኑን ይናዘዝልናል!
ሐዋሪያው፦ ኢየሱስ በስጋ ወራቱ ስለነበረው ምልልስ ሲገልፅልን: ፅድቅን በመወደዱ አመፀንም በመጥላቱ ከደቀመዛሙርቶቹ በበለጠ ሁኔታ በደስታ ዘይት ይመላለስ እንደነበር ይነግረናል። እኛ ከዚህ ምን እንማር?
ፅድቅን መውደድ ፦ ፅድቅ በእግዚአብሔር ፊት ያለምንም ሀፍረትና የበደልተኝነት ስሜት አሊያም ያለ ኃጢአት ትክክል ሆኖ መቆም ማለት ነው! ይሄን ከስጋ ለባሽ ማንም መፈፀም የሚችለው አልነበረም : ጌታ ኢየሱስ ግን ስለ እኛ በመስቀል ኃጢአት ሆነና(2ኛቆሮ5:21) በእግዚአብሔር ፊት ለዘለዓለም ፃድቅ አደረገን!! ይኼ ለሰዎች የቀረበ ታላቁ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። ስለዚህም ሁሌ ስንተኛ፣ ስንነሳ፣ ስንበላ ፣ ስንጠጣ ፣ ስንሰራ፣ ስንወጣ፣ ስንገባ. በእግዚአብሔር ፊት ያለ እኛ ብቃት የመቆም ብቃታችንን እያሰብን : በእግዚአብሔር እንደሰት! መፅሐፍ ሲናገር "የእግዚአብሔር ደስታ ኃይላችሁ ነው " ይለናል (ነህ8:10)
ያንን ስናደርግ ዓመፅን እንቃወማለን : አመፅ ማለት በእግዚአብሔር እውነት ላይ ባላንጣ የሆነው አቋም ማለት ነው። ሰላማችንን ደስታችንን እረፍታችንን እምነታችንን ሁሉ እግዚአብሔር በቃሉና በመንፈሱ በሚነግረን እውነት ላይ ስናደርግ ዓመፅን እንቃወማለን ማለትም የዚህን አለም አስተሳሰብ እንቃወማለን። ያንን የማድረግ አንዱና ዋናው በረከት በደስታ ዘይት መሞላት ነው።
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351
በዚህ አለም ላይ ያለው የአኗኗር ስርዓት በራሱ አይናችንን በሁኔታው ላይ እንድናደርግ ይጫነናል ወይም ይስቡታል፣ ትኩረታችንን ይፈልጋል። አለበለዚያ ጫናው ራሱ አሁን በሚታየው ነገር ላይ እንድንሆን ያስገድደናል። በዚሁ ሁሉ ግን አይናችንን ወደ መንግስቱ ወደ ጠራን፣ ሕይወቱን ወዳካፈለን ወደ እግዚአብሔር እንዲሆን መፅሀፍ ቅዱስ ያነቃቃናል።
በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ እያለፋችሁ ብትሆኑ.. ተስፋችሁ እግዚአበሔር አይደለምን? አይናችሁ በሁኔታው ላይ ተተክሎ ስለምን እንባን እንዲታዘሉ ትፈቅዳላችሁ? ለምንስ ብቻችሁን እንደሆናችሁ በማሰብ ትቆዝማላችሁ? እግዚአብሔር አባት አይደለምን? አባባ የምትሉበት መንፈስ በወስጣችሁ ያለ አይደለምን? ተነሱና ልመናችሁን ከምስጋና ጋር አስታውቁ እንጂ በምሬት አተለቃቅሱ! ወደ እርሱ በልበ ሙሉነት ቅረቡ.. በአንዳች አትጨነቁ ፣ የስሜታችሁን ቀጠና አልፋችሁ.. በእግዚአብሐር ታማኝነት ፣ በእግዚአብሐር ቃሉን ጠባቂነት ፣ በእግዚአብሐር አጋዥነት.. በመሳሰሉት ባሕሪያት ተገረሙ! የእርሱ ብርሃን መላ ሁለንተናችሁን ሲቆጣጠር ታዪታላችሁ።
#ፀሎት
አባቴ ሆይ ወደ አንተ ስቀርብ ጠንካራና ደስተኛ ስለምሆን አመሠግናለው ፣ ደግሞ የማልፍበት መንገድ ሁሉ የአንተን አብሮነት ሊሰውርብኝ ስለማይችል አንተ ራስህ ቀድመህ "አለቅህምም አልተውህም" ስላልከኝ ስለ ቃልህ አብረኸኝ ስለምትሆን አመሠግናለው.. በሚሰማኝ በሚታየኝ በምዳስሰው ፣ አልወሰድም በኢየሱስ ስም በእምነት እኖራለው አሚን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351
በዚህ አለም ላይ ያለው የአኗኗር ስርዓት በራሱ አይናችንን በሁኔታው ላይ እንድናደርግ ይጫነናል ወይም ይስቡታል፣ ትኩረታችንን ይፈልጋል። አለበለዚያ ጫናው ራሱ አሁን በሚታየው ነገር ላይ እንድንሆን ያስገድደናል። በዚሁ ሁሉ ግን አይናችንን ወደ መንግስቱ ወደ ጠራን፣ ሕይወቱን ወዳካፈለን ወደ እግዚአብሔር እንዲሆን መፅሀፍ ቅዱስ ያነቃቃናል።
በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ እያለፋችሁ ብትሆኑ.. ተስፋችሁ እግዚአበሔር አይደለምን? አይናችሁ በሁኔታው ላይ ተተክሎ ስለምን እንባን እንዲታዘሉ ትፈቅዳላችሁ? ለምንስ ብቻችሁን እንደሆናችሁ በማሰብ ትቆዝማላችሁ? እግዚአብሔር አባት አይደለምን? አባባ የምትሉበት መንፈስ በወስጣችሁ ያለ አይደለምን? ተነሱና ልመናችሁን ከምስጋና ጋር አስታውቁ እንጂ በምሬት አተለቃቅሱ! ወደ እርሱ በልበ ሙሉነት ቅረቡ.. በአንዳች አትጨነቁ ፣ የስሜታችሁን ቀጠና አልፋችሁ.. በእግዚአብሐር ታማኝነት ፣ በእግዚአብሐር ቃሉን ጠባቂነት ፣ በእግዚአብሐር አጋዥነት.. በመሳሰሉት ባሕሪያት ተገረሙ! የእርሱ ብርሃን መላ ሁለንተናችሁን ሲቆጣጠር ታዪታላችሁ።
#ፀሎት
አባቴ ሆይ ወደ አንተ ስቀርብ ጠንካራና ደስተኛ ስለምሆን አመሠግናለው ፣ ደግሞ የማልፍበት መንገድ ሁሉ የአንተን አብሮነት ሊሰውርብኝ ስለማይችል አንተ ራስህ ቀድመህ "አለቅህምም አልተውህም" ስላልከኝ ስለ ቃልህ አብረኸኝ ስለምትሆን አመሠግናለው.. በሚሰማኝ በሚታየኝ በምዳስሰው ፣ አልወሰድም በኢየሱስ ስም በእምነት እኖራለው አሚን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351
**የእግዚአብሔር ምሕረት ደካሞችን ብርቱ
ኋለኞችን ፊት ያደርጋል!!**: **የበዛልንን ምሕረት ስናስብ የእግዚአብሔር ፀጋ በመደነቅ ውስጥ ይጥለናል!!** **እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለጠጋ ነው**። **ሲሰጥ አይሰስትም አያንስበትም ከማንም ዕዳም የለበትም አሁንም ይምራል ይራራል** 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
@biruk351 Join & Share
ትላንት ወዲያ ጊታር የመግዛት እንቅስቃሴ እንደምጀመር ተናግሬ ነበር። በውስጥም ይጀምር የሚል ሀሳብ ያስቀመጣችሁልኝ ነበራችሁ ፣ ሁላችሁንም ስለ ቅንነታችሁ አመሠግናለው.. እኔ ያልኩት አንድ ሰው 200 ብር ቢሰጥና 130 ሰው ቢሆን በአጭሩ ይገዛል የሚል ሲሆን : መጠኑን አትገድበው የበለጠ በሺህ ቤትም የመስጠት ፍላጎት ያላቸው ይሳተፉ የሚል ምክር ተሰቶኛል። እኔም ይኼው በሞባዬል ባንኪንግ.. ይጀመር ስል አስቀምጬአለው።
ቤተክርስቲያኒቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ለመውሰድ ያደረገች ያላቹ ጥረት በአንዳንድ ነገሮች ምክንያት የተስተጓጎለ ሲሆን : በስር ያለው የተጠቀሰው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ : የቤተክርስቲያኒቱ ገንዘብ ያዥ አካውንት ሲሆን : የብርሃንና የዳሽኑ ግን በቤተክርስቲያኒቱ ስም የተከፈተ አካውንት ነው።
1000 50503 9355 ንግድ ባንክ
👉 አፈወርቅ አባተ
2500 20012 8997 ብርሃን ባንክ
👉ፀጋና እውነት አ/አ ቤተክርስቲያን
5021 54969 5011 ዳሽን ባንክ
👉ፀጋና እውነት ዓ/ዓ ቤተክርስቲያን
ስለዚም በፈለጉት መርጠው ማስገባት ይችላሉ ለአሰራር እንፈጥን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቢሆን ተመራጭ ነው።
ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች ምዕራፍ 2)
----------
14-15፤ በመጥፎና በጠማማ ትውልድ መካከል ያለ ነቀፋ የዋሆችም ነውርም የሌለባቸው የእግዚአብሔር ልጆች እንድትሆኑ ሳታንጐራጉሩ ክፉም ሳታስቡ ሁሉን አድርጉ፤
16፤ በእነርሱም መካከል የሕይወትን ቃል እያቀረባችሁ በዓለም እንደ ብርሃን ትታያላችሁ፥ ስለዚህም በከንቱ እንዳልሮጥሁ በከንቱም እንዳልደከምሁ በክርስቶስ ቀን የምመካበት ይሆንልኛል።
(የጊተሩ ግዢ አካውንት በኋላ ይለቀቃል)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ 👉@biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🔥🙏
ሰላም በፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን ላይ በሚለቀቁ ፁህፎችና ኦዲዮች የምትታነፁ ቅዱሳን.. አንድ ምርጥ ቤዝ ጊታር ለአገልግሎት ቦታችን እንዲገዛ አስቤአለው:
አንድ ሰው 200 ቢሰጥ
120 ሰው ቢሰጥ
ጊታራችን እንገዛለን: ይኼን ስንስማማና የድምፅ ብልጫ ሲገኝ የአካውንት ቁጥር እናስቀምጣለን.. በተረፈ የገንዘብ መጠን እንደፍላጎታችሁና እንደ አቅማችሁ መስጠትም ትችላላችሁ.. እናስማማ? 🙄
ይኼን ለማድረግ የሚፈልግ ወይም ይጀመር : የሚል በዚህ ሊንክ አዎንታውን ያስቀምጥልኝ
👉@lejbiruk
#እኔም_እመልሳለሁ
ይኼን በማድረግ እንድታበረታቱኝ በእግዚአብሔር ፍቅር እጠይቃለው
#አመሠግናለሁ ❤🙏
#ከመጀመሪያው_የቀጠለ
በሕይወቴ እግዚአብሔር የጀመረው መልካም ነገር እንዲፈፀም ምን ላድርግ? የተስፋን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና በምን መንገድ በሀሳቡ ልጓዝ? 🙄
" በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤"
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 1:6)
የጀመረ ሁሉ ላይጨርሥ ይችላል፣ ያሰበ ሁሉ አይፈፅም ይሆናል፣ የተመኘ ሁሉ አያገኝም፡፡ የተንቀሳቀሰ ሁሉ አይደርስም፡፡ የሳቀ ሁሉ አይደሰትም፡፡ የተፋቀረ ሁሉ አይጋባም፡፡ የተጋባ ሁሉ አብሮ እስከሞት አይዘልቅም፡፡ ኮሌጅ የገባ ሁሉ አይመረቅም፡፡ የተማረ ሁሉ አዋቂ አይሆንም፡፡.....ይኼ ሁሉ የእግዚአብሔር ፈቃድ ስለሆነ ነውን? አይደለም! በመጀመርና በመጨረስ መካከል ትልቅ ገደል አለ፤ የተጀመረ ነገር ከግብ እንዳይደርስ ወደ ግቡ እንዳይቾክል ውጊያ አለ። ያሰብከውን የምትሆነው፤ የተመኘኸውን የምታገኘው መካከሉ ላይ ባለህ አሰላለፍ፣ አስተሳሰብ፣ ምግባርና ተግባር ነው፡፡ የልብ ዝንባሌ የተበላሸ ከሆነ፣ ጥሩ ምልከታ ከሌለህ፣ አስተሳሰብህ እንደ ሰሚያዊ ክብር የበራ ካልሆነ ሜዳውን ገደል፤ ድልድዩን ጋሬጣ ሊያደርግብህ ይችላል፡፡
ጅማሬያቸው የሚያምር ፍጻሜአቸው ግን የሚያሳዝን ብዙ ታሪኮች አሉ፡፡ ተዋድደው ያልቀጠሉ፤ እንደተፋቀሩ ዘመናቸውን ያልጨረሱ መዓት ናቸው፣ ሰርጋቸው ያማረ ፍቺአቸው የፈጠነ ብዙ ትዳሮች አሉ፡፡ ጀማሪዎች ብዙ፤ ጨራሾች ግን ጥቂት ናቸው፡፡ በመጀመርና በመጨረስ መካከል ትግል፣ ፈተና፣ ውጣውረድ፣ ከፍታ ዝቅታ አለ፡፡ በዚሁ ሁሉ መሃል እግዚአብሔር ተጠያቂ ነውን? እግዚአብሔርስ ስላልረዳ ነውን?፣ ጥሩ ጀምረው ጥሩ ያልጨረሱ ሰዎች እግዚአብሔር በመሃል ትቶአቸው ነውን?፣ ከእግዚአብሔር ጋር ጀምረው ከአለም ጋር የጨረሱ የበዙ አይደለምን?፣ ተጠያቂው ማነው?
ይሄ ጉዳይ ማሰብ፣ ማገናዘብ፣ መረዳት ይጠይቃል፡፡ ይሄን ሁሉ ማለፍ የቻለ ነው ፍፃሜው እንደ ጅማሬው ያማረለት የሚሆነው፡፡
ጆይሲ ሜየር (JOYCE MEYER) የተባለች አሜሪካዊ ፀሐፊ “The mind connection” በተባለ መፅሐፏ፡- ‹‹የጀመርንበት ሁኔታ እንደምንጨርስበት መንገድ ያን ያህል አስፈላጊ አይደለም፡፡ ጅማሬአችን አንዴ ከቁጥጥራችን ውጪ ሆኗል፡፡ አጨራረሳችንን ግን እንዳሻን ልናደርገው ሃይልና ስልጣኑ አለን ትለናለች፡፡ ምንም እንኳ ከእግዚአብሔር ጋር ሆነን ጅማሬያችን ታናሽ ቢመስልም እንኳ ከእርሱ ጋር ከጨረስን ፍፃሜያችን ታላቅና የከበረ እንደሆነ መፅሐፍ ይመሰክራል (መፅ ኢዮ 8:7)
ወደፊት የሚያስወነጭፈን አልያም ወደኋላ የሚጎትተን በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ የለን አስተሳሰብ አለመታጠቃችን ነው፡፡ ብዙዎች ጀምረው ያልጨረሱት ዕድለቢስ ስለሆኑ አይደለም፤ አስተሳሰባቸው በዚህ እውነት ጠንካራ ስላልነበረ እንጂ፡፡
ሽንፈታችንም ሆነ የአሸናፊነታችን ጉዳይ ያለው ምን ያህል የሰማዩ ምስጢርና ክብር ገብቶናል የሚለው ላይ ነው፡፡ ድል ከሰማይ አይወርድም፤ ሽንፈትም ከመሬት አይበቅልም፡፡ የሁለቱም ምንጭ ፈቃዳችንን ምን ያህል ለመንፈስ ቅዱስ እናስገዛለን በሚለው ላይ ነው፡፡
ብዙዎች ጀምረው የማይጨርሱት ጠንካራ መረዳትና መስጠት ስላላዳበሩ ነው፡፡ አንዳንዶች ውጣውረዱ አሰልችቷቸው በቶሎ ተስፋ ይቆርጣሉ፡፣ ነገን አሻግረው መመልከት የማይችሉ በዛሬ ውጣውረድ እጅ ይሰጣሉ፣ አንዳንዶች የአለም ነገር ቶሎ ያታልላቸዋል፣ አንዳንዶች በውድቀቶቻቸው ቶሎ ተስፋ ይቆርጣሉ ፣ አንዳንዶች በአንዴ ትልቅ ቦታ ካልደረሱ ራሳቸውን እንደ ተራ ሰው ይመለከታሉ ፣ ስኬት በአንድ ሌሊት እውን እንደማይሆን ያልተረዱ በአጭር ይቀጫሉ፡፡ ብዙ ትላልቅ ውጤት ያመጣሉ ተብለው ታስበው የነበሩ ጅማሬዎች ተስፋ በቆረጡ ጀማሪዎች ምክንያት ውሃ በልቷቸዋል፡፡ ታላቁ ሳይንቲስት ቶማስ ኤዲሰን፡- ‹‹ ትልቁ ድክመታችን ያለው ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ነው፡፡ ትክክለኛው የስኬት መንገድ ደግሞ ተስፋ ሳይቆርጡ ሁልጊዜ መሞከር ነው የሚለን ለዚህ ነው፡፡ ቶማስ ፉለርም ‹‹ምንም ነገር ከመቅለሉ በፊት ከባድ ነው›› ይለናል። ሰው ደጋግሞ በሞከረ ቁጥር ከባዱን የመላመድና የማቅለል አቅም ያለው መሆኑን ለማመላከት ነው፡፡
መፅሀፍ ቅዱሳችን ‹‹ሰው በልቡ ያሰበውን ነው›› እንዲል አዕምሮህ በዋለበት ሁሉ ህይወትህም እንደዛው ነው፡፡ አዕምሮህን ላልተፈለገ ተልካሻ ነገር ካዋልከው፤ የሚሰጥህ ህይወትም እንደዚያው ነው።
ወዳጄ ሆይ.... ጅምርህን ሊያስጨርስህ የሚችል አስተሳሰብ ገንባ፡፡ የጅማሬህን መሰረት ዕይታህን በመንፈሳዊነት በመቅረፅ ላይ አበልፅግ፣ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእምነት በመፅናታቸው እግዚአብሔር ያከበራቸውና የሸለማቸው አባቶች ፈለግ ተመልከት፣ ከእግዚአብሔር ጋር እስከ መጨረሻ የመጓዛቸውን ምስጢር አጥና አሰላስል፣ እኔ ከዚህ ምን ልማር በል? የጎደለኝ መጨመር ያለብኝ ምንድነው በል? ሁሌም ትኩረትህ እግዚአብሔር በአንተ ሁኔታ ራሱን ሊገልጥ በሚወድበት መስመር ላይ ይሁን፣ መከራን ታገስ እርሱ በመስቀል ታግሶ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጧልና በነፍስህ እንዳትደክም ከኃጢአተኛው አለም የደረሰበትን ብርቱ ግፊያ በማሰብ በነገር ሁሉ ከኃጢአት በቀር እንደ አንተ የተፈተነ ነውና በፀሎት ዘወትር ወደ እርሱ ቅረብ ሊረዳህና ሊያበረታህ ስራውን በአንተ ሊፈፅም የታመነ ጌታ ነውና 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351 #እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🙏🔥
#የጀመረውን_ይፈጽማል!
“በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤”
— ፊልጵስዩስ 1፥6
✔እግዚአብሔር የመልካም ነገሮች ምንጭ ነው። እርሱ መልካም ሥራን በሰዎች ሕይወት ውስጥ ለመጀመር የልቡን አሳብ ያካፍላል፣ ተነሳሽነትን፣ አደራረግን፣ ጥበብና ብልሃትን፣ ጽናትንም ይሰጣል። እግዚአብሔር ጀምሮት ወደ ፍጻሜ ሳይደርስ የቀረ አንዳችም ነገር በታሪክ ውስጥ የለም፣ ወደፊትም አይኖርም። እርሱ ያስጀምራል ደግሞ እርሱ ያስፈጽማል። ሐዋርያው ጳውሎስ እዚህ መረዳት ላይ ቆሞ ነበር ለፊልጵስዩስ አማኞች በእነርሱ መካከል እግዚአብሔር የጀመረውን መልካም ሥራ እንደሚፈጽም መረዳቱን የጻፈላቸው።
✔እግዚአብሔር በእኛም መካከል የጀመረውን መልካም ሥራ ወደ ፍጻሜ ያመጣል። ምክንያቱም እርሱ ታማኝ ነውና። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የጀመረው ስራ ወደ ፍጻሜ እንዲመጣ ከእኛ ደግሞ የሚጠበቁ አንዳንድ ነገሮች በዛሬው መልእክታችን እንመልከት።
እግዚአብሔር በእኛ መካከል የጀመረው መልካም ሥራ እንዲቀጥል፦
✅የማያቋርጥ ትጋት ፣ መሠጠትና ተጋድሎ ማድረግ ይገባናል። እግዚአብሔርን ሥራ በቸልተኝነት ወደ ግብ ማምጣት አይቻልምና!
✅የእግዚአብሔር ሥራ በግለሰብ ደረጃ ሊጀመር ይችላል። ሆኖም በግለሰብ ደረጃ ብቻ ወደ ፍጻሜ መምጣት አይችልም። የሌሎች ሰዎችንም አስተዋጽኦና ርብርቦሽ ይጠይቃል። ስለዚህ ከሰዎች ጋር አብሮ የመስራት ባህልን ማዳበር ይገባናል።
✅የእግዚአብሔር ሥራ በብዙ ተግዳሮት ውስጥ ያልፋል። ስለዚህ ለተግዳሮቶች እጅ የማይሰጥ የአላማ ጽናት መሰነቅ የግድ ይላል።
✅የተጀመረው ሥራ ዋጋ የሚያስከፍልበት ጊዜ እንዳለ ሁሉ ፍሬው የሚታይበትም ጊዜ አለ። ያ ጊዜ እስኪመጣ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ያስፈልጋል።
✝እንግዲህ፥ አማኞች የእግዚአብሔርን ታማኝነት ከምናውቅበት መንገድ አንዱ እርሱ በእኛ የጀመረውን መልካም ሥራ በክብር እንደሚፈጽመው ተረድተን ከእርሱ ጋር አብረን ለመስራት፣ የተጀመረውን ነገር ወደ ፍጻሜ ለማምጣት በቁርጠኝነት እንነሳ።
እግዚአብሔር በሕይወቴ በመነቃቃቱ ያስጀመረው አሁን ግን ውጤት እያየሁበት ያልሆነውን እንዴት ላድርግ?:የጀመረው እንዲፈፀም የእኔ አስተዋጽኦ ምንድነው?
ይሄን መልስ በቀጣዩ ክፍል አድምቼ የምመልሰው ይሆናል።
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🙏❤
✝#የጀመረውን_ይፈጽማል!
“**በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና*፤”
— ፊልጵስዩስ 1፥6
✔እግዚአብሔር የመልካም ነገሮች ምንጭ ነው። እርሱ መልካም ሥራን በሰዎች ሕይወት ውስጥ ለመጀመር የልቡን አሳብ ያካፍላል፣ ተነሳሽነትን፣ አደራረግን፣ ጥበብና ብልሃትን፣ ጽናትንም ይሰጣል። እግዚአብሔር ጀምሮት ወደ ፍጻሜ ሳይደርስ የቀረ አንዳችም ነገር በታሪክ ውስጥ የለም፣ ወደፊትም አይኖርም። እርሱ ያስጀምራል ደግሞ እርሱ ያስፈጽማል። ሐዋርያው ጳውሎስ እዚህ መረዳት ላይ ቆሞ ነበር ለፊልጵስዩስ አማኞች በእነርሱ መካከል እግዚአብሔር የጀመረውን መልካም ሥራ እንደሚፈጽም መረዳቱን የጻፈላቸው።
✔እግዚአብሔር በእኛም መካከል የጀመረውን መልካም ሥራ ወደ ፍጻሜ ያመጣል። ምክንያቱም እርሱ ታማኝ ነውና። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የጀመረው ስራ ወደ ፍጻሜ እንዲመጣ ከእኛ ደግሞ የሚጠበቁ አንዳንድ ነገሮች በዛሬው መልእክታችን እንመልከት።
እግዚአብሔር በእኛ መካከል የጀመረው መልካም ሥራ እንዲቀጥል፦
✅የማያቋርጥ ትጋት ፣ መሠጠትና ተጋድሎ ማድረግ ይገባናል። እግዚአብሔርን ሥራ በቸልተኝነት ወደ ግብ ማምጣት አይቻልምና!
✅የእግዚአብሔር ሥራ በግለሰብ ደረጃ ሊጀመር ይችላል። ሆኖም በግለሰብ ደረጃ ብቻ ወደ ፍጻሜ መምጣት አይችልም። የሌሎች ሰዎችንም አስተዋጽኦና ርብርቦሽ ይጠይቃል። ስለዚህ ከሰዎች ጋር አብሮ የመስራት ባህልን ማዳበር ይገባናል።
✅የእግዚአብሔር ሥራ በብዙ ተግዳሮት ውስጥ ያልፋል። ስለዚህ ለተግዳሮቶች እጅ የማይሰጥ የአላማ ጽናት መሰነቅ የግድ ይላል።
✅የተጀመረው ሥራ ዋጋ የሚያስከፍልበት ጊዜ እንዳለ ሁሉ ፍሬው የሚታይበትም ጊዜ አለ። ያ ጊዜ እስኪመጣ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ያስፈልጋል።
✝እንግዲህ፥ አማኞች የእግዚአብሔርን ታማኝነት ከምናውቅበት መንገድ አንዱ እርሱ በእኛ የጀመረውን መልካም ሥራ በክብር እንደሚፈጽመው ተረድተን ከእርሱ ጋር አብረን ለመስራት፣ የተጀመረውን ነገር ወደ ፍጻሜ ለማምጣት በቁርጠኝነት እንነሳ።
እግዚአብሔር በሕይወቴ በመነቃቃቱ ያስጀመረው አሁን ግን ውጤት እያየሁበት ያልሆነውን እንዴት ላድርግ?:የጀመረው እንዲፈፀም የእኔ አስተዋጽኦ ምንድነው?
ይሄን መልስ በቀጣዩ ክፍል አድምቼ የምመልሰው ይሆናል።
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🙏❤
🔥“ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፥ ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ፤” ምሳሌ 3፥13
"ጥበብ ጮኻ አትጣራምን? ማስተዋልስ ድምፅዋን ከፍ አድርጋ አታሰማምን? በመንገድ አጠገብ ባሉ ኰረብቶች፣ መንገዶቹ በሚገናኙበትም ላይ ትቆማለች፤ ወደ ከተማዪቱ በሚያስገቡት በሮች አጠገብ፣ በመግቢያዎቹ ላይ፣ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ ስትል ትጮኻለች፤ “ሰዎች ሆይ፤ የምጠራውኮ እናንተን ነው፤ ለሰው ልጆች ሁሉ ድምፄን ከፍ አደርጋለሁ። እናንተ ብስለት የጐደላችሁ፤ ጠንቃቃነትን ገንዘብ አድርጉ፤ እናንተ ተላሎች፤ ማስተዋልን አትርፉ። የምናገረው ጠቃሚ ነገር ስላለኝ አድምጡኝ፤ ቀና ነገር ለመናገር ከንፈሮቼን እከፍታለሁ። አንደበቴ እውነትን ይናገራል፤ ከንፈሮቼ ክፋትን ይጸየፋሉና። ከአንደበቴ የሚወጡት ቃሎች ሁሉ ጽድቅ ናቸው፤ አንዳቸውም ጠማማና ግራ የሚያጋቡ አይደሉም። በጥልቅ ለሚያስተውሉ ሁሉም ቀና ናቸው፤ ዕውቀት ላላቸውም ስሕተት የለባቸውም። ከብር ይልቅ ምክሬን፣ ከንጹሕ ወርቅ ይልቅ ዕውቀትን ምረጡ፤ ጥበብ ከቀይ ዕንቍ ይበልጥ ውድ ናትና፤ ከምትመኙት ነገር ሁሉ አንዳች የሚስተካከላት የለም። “እኔ ጥበብ ከማስተዋል ጋር አብሬ እኖራለሁ፤ ዕውቀትና ልባምነት ገንዘቦቼ ናቸው። እግዚአብሔርን መፍራት ክፋትን መጥላት ነው፤ እኔም ትዕቢትንና እብሪትን፣ ክፉ ጠባይንና ጠማማ ንግግርን እጠላለሁ። ምክርና ትክክለኛ ፍርድ የእኔ ናቸው፤ ማስተዋል አለኝ፤ ብርታት አለኝ። ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፤ ገዦችም ትክክል የሆነውን ሕግ ይደነግጋሉ፤ መሳፍንት በእኔ ይገዛሉ፤ በምድር ላይ የሚገዙ መኳንንትም ሁሉ በእኔ ያስተዳድራሉ። የሚወዱኝን እወዳቸዋለሁ፤ ተግተው የሚሹኝም ያገኙኛል።
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ #ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ❤🙏
💚የምወዳችሁ ሆይ :-
✍️ወንጌላዊው ዮሐንስ በመልእክቱ :- "....ልጆቼ በእውነት እንዲሄዱ ከመስማት ይልቅ ደስታ የለኝም ...።" (3ኛ ዮሐ.ቁ-4) እንዳለ። በእውነት መንገድ መሄድ የእግዚአብሔርንና የቅዱሳኑን ልብ ያስደስታል። እውነት ዋጋ ቢያስከፍልም ፍፃሜው ግን የክብር ትንሣኤ ያለው ዘላለማዊ ደስታ ነው። ውሸት ግን የሰይጣን ገንዘብ ነውና ለጊዜው መሸሽና ማምለጥ ቢቻልም ኑሮው ግን የስጋትና ፍፃሜውም ዘላለማዊ ጸጸት ነው።
✍️ስለዚህም በሀሰት ከሚገኝ ክብር በእውነት የሆነ ውርደት ይበልጣልና አርነት የወጣህበትንና የዳንክበትን እውነት በምንም እና ስለ ማንም ሳትለውጥ እስከ መጨረሻው በያዝከው እውነት ጸንተህ ኑር።
☝የምንኖረው ለእግዚአብሔር ክብር እንጂ ሰዎችን ለማስደሰት አይደለም፡፡ እግዚአብሔርን ለማስደሰት ስንኖር የእግዚአብሔር የሆነው ሁሉ ይደሰትብናል፡፡ የመኖሪያ ፈቃዳችን የሚታደሰው በሰዎች አይደለም፡፡ የሚያኖረን እግዚአብሔር ነው፡፡ የዚህች ዓለም ባለቤትም ክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ ሰጥቶን የሚከለክለን እርሱ ከልክሎንም የሚሰጠን ማንም የለም፡፡ ይህ ብርሃን የሚበራልን ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወታችን ገዢ ሲሆን ብቻ ነው፡፡
በእውነት መንገድ በመኖር የቅዱሳንና ልብና እግዚአብሔርን የምታስደስቱ ሁኑ
🙏እግዚአብሔር ለክብሩ ያኑረን!
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🙏❤
ጅማ ለምትኖሩ ማሳሰቢያ
ነገ ማለዳ ከ3:00 እስከ 6:30
የትምህርትና የአምልኮና የምስክርነት ቀን
ከሰዓት ከ10:00 -12:30
የስብከት የፀሎት የፈውስ የነፃ መውጣት ሰዓት
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ኪቶ ስታዲየሙ አጠገብ
እናመሰግናለን.. ለበለጠ በውስጡ መልዕክት ያስቀምጡ 👉 @lejbiruk 🙏
#ስለ_ፀሎት_አንዳንድ_እውነታዎች
እግዚአብሔር ድንቅና ታምራት ማድረግ እንደሚችል ካመንን አለመፀለይ አንችልም:: በተውጣጣ ዶክትሪን የተገነባ theoretical God ከሆነ ያለን እንፈላሰፍበታለን: ነገር ግን ፈጣሪና በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ ጣልቃ የሚገባ እንዲሁም አሁን ሕያው የሆነ እግዚአብሔር ካለን እንፀልያለን:: ወደ እግዚአብሔር ስንፀልይም በክርስቶስ የሰራውን መሠረት በማድረግ ትልቁን ተአምራትና ምልክት እውቅና በመስጠት ነው።
ቀጥሎ ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ድንቅ ምልክት በብዙ መረዳት ለሰዎች እንዲደርስ መፀለይ ጅልነት አይደለም።
በምድር ላይ እንደ መፀለይ ከባድ ነገር የለም ምክንያቱም ሕያው በሆነና ፀሎትን በሚሰማ እግዚአብሔር ማመንን ይጠይቃል:
ፀሎት የፈሪዎች ወይም የፋራዎች ሳይሆን የደፋሮች ነው: ምክንያቱም ከፍተኛ እምነትን ይጠይቃል::
ፀሎት ብልጣብልጥነት ከሚጠይቅ የአቋራጭ መንገድ ይልቅ: በፍጹም ልባቸው በእግዚአብሔር የሚደገፉ ሰዎች የሚሄዱበት እግዚአብሔራዊ መንገድ ነው
#ስለዚህ_እላችኋለሁ_የፀለያችሁትንና የለመናችሁትን ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ ይሆንላችሁማል (ማር 11:24)👌
የምንፀልየው ራስ-በቆች ስላልሆንን ነው: በእውነተኛ ፀሎት ውስጥ ሁለት ነገሮች ይገለጣሉ፤ #1ኛ_በእግዚአብሔር_ ተደጋፊነትና #የእግዚአብሔር_መቻል_ናቸው:
እግዚአብሔር ይችላል!
በተለያዩ በሕይወት ተግዳሮት ውስጥ ሆናችሁ በፀሎት ላይ ያላችሁ 👉 አንዳንዴ እግዚአብሔር ፀሎታችንን የሚመልስልን ከገባንበት ነገር በማውጣት ሳይሆን በገባንበት ነገር ውስጥ ፀጋን በማብዛት ነው: ነጥቆ በማውጣቱም ይሁን ፀጋ በማብዛቱ እርሱ ሉአላዊ ነው:
"#ፀጋን_ሁሉ_ሊያበዛላችሁ_ይችላል"
ደግሞ በሕይወት ባላችሁ ነገር ተግዳሮታችሁ የቀነሰና የተረጋጋችሁ እናንተም ፀልዩ 👉የምንፀልየው ፀሎት ከእግዚአብሔር እጅ አንድ ነገር የመቀበያ መንገድ ብቻ ሳይሆን የአባትና የልጆች ሕብረት መገለጫና የአምልኮ አንዱ ክፍል ስለሆነም ነው::
#የፀሎት_ርእስ_ባይኖርም_ፀሎት_ግን_አለ::
፣የምንፀልየው በዚህ በክፉ በተያዘ አለም ውስጥ ከእግዚአብሔር ጋር መወገን ስለምንፈልግ እንጂ የምንፈልገውን ሁሉ ለማግኘት አይደለም: ከእግዚአብሔር ጋር የሚወግን ይፀልያል: ለማን ነው የምንወግነው?፣ የምንፀልየው እግዚአብሔር ነገሮችን መለወጥ እንደሚችል ስለምናምን ነው:#እግዚአብሔር_ጣልቃ ይገባል፣ የምንፀልየው እግዚአብሔር ስራ አስፈፃሚያችን ስለሆነ ሳይሆን ፡ እኛ የእርሱ ስራ ፈፃሚዎች ስራተኞቹ ስለሆንንም ነው። ፈቃድህ በላይ እንደሆነች በዚህም በእኛም ትሁን እንላለን እንጂ ፈቃዳችንን በላይ እንዳለ በምድር በዚህ ትሁን አንልም...ፀሎት በዋነኛነት የእግዚአብሔር Businesses እንጂ የእኛ Business አይደለም: የእኛ empire ሳይሆን የእግዚአብሔር መንግስት ነው የሚገነባበት: ፀሎትን ከእግዚአብሔር አቅጣጫ ማየት ትርጉሙን ይቀይርብናል::
አሁን ይሄን ሁሉ ስለ ፀሎት ከተነጋገርን በኋላ ይሄ ስሜታዊ ጭንቅላታችን እኮ እፍረተ-ቢስና ፈጣጣ ነው.. እንደዚህም ሳት ሲል ያስባል።
"በእውነት እግዚአብሔር ፀሎትን ይሰማልን?" ፣ የእኔ ፀሎት ለምንድነው የማይመለሰው?: ባክህ ዝም ብለህ አርፈህ ኑር ስለ ፀሎት ምንም የምታውቀው ስለሌለ ባትፀልይ ይሻላል.... ፣እያለ የሚሞግተን ጨቅጫቃ ጭንቅላታችን አንደኛው ነው: እንዲህ ጮክ ብላችሁ ከውስጣችሁ ጩኹበት**
#እግዚአብሔር_ፀሎትን_ይሰማል_ ይመልሳልም::
#ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ: ስለ ፀሎት በመንፈስ ቅዱስ በኩል አሁንም፣ አሁንም ጥቅሙንና ኃይሉን ክብሩን አስተምረንና በመንፈስህ ዘወትር ለፀሎት የተቀጣጠልን አድርገን በኢየሱስ ስም አሜን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ 👉@biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ ❤🙏
🔥#የቃሉ_ብርሃን_ያግኛችሁ_🔥!
በአእምሮ ክፍላችሁ ውስጥ ደባል ሆኖ የበቀለ እግዚአብሔር የማይከብርበት ነገር ካለ በስሙ ኃይል ይቆረጥ!! እግዚአብሔር በመረዳት ባለጠግነት ይባርካችሁ! የመንፈስ ቅዱስ አብርሆት ይብዛላችሁ!
✍️ክርስትና
.
.
ማስመሰል
.
.
ሳይሆን
.
.
መምሰል ነው‼️
የትወና ሕይወት ከሕይወታችን ይቆረጥ!✂️
**የተወደዳችሁ ሆይ መንፈሳዊ ጤንነታችሁን በመንፈሱ በፀጋው ቃል በኩል ጠብቁ**
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ 👉 @biruk351
#እናመሰግናለን🙏 ❤
