Grace & Truth Ministry
Open in Telegram
እንኳን ወደዚህ ቻናል በሰላም መጡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ በእውነት ቃልና በፀጋው መንፈስ ይታነፁ
Show more1 029
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2030 days
Posts Archive
መንፈሳዊ ውጊያ
በዓለም ላይ ልትሰጡት ከምትችሉት የጭካኔ ፍርድ'ና ክስ የላቀው እናንተው በራሳችሁ ላይ የምታመጡት ፍርድና ክስ ነው፡፡ የየእለት ድካማችሁን፣ ስህተታችሁን፣ ትግላችሁንና የመሳሰሉትን ነገሮቻችሁን ማንም ሰው ከሚያውቃችሁ በላይ ራሳችሁን ስለምታውቁት ራሳችሁን ለመኮነንና በራሳችሁ ላይ የተዛባ አመለካከትን ለመያዝ እጅግ ቅርብ ናችሁ፡፡ ስለዚህ በራሳችሁ ላይ የምታስቡት ሃሳብም ሆነ ለራሳችሁ የምትሰጡት ፍርድ በሚዛናዊነት ሊያዝ ይገባዋል፡፡ ሕሊናችሁን በቃለ-እግዚአብሔር ካልተቆጣጠራችሁት በሰይጣን ክስ ውስጥ ከወደቃችሁ መንፈሳዊ ውጊያ ላይ በራሳችሁ ላይ ሽንፈትን ትጨመራላችሁ።
ያላችሁን የራስ-በራስ ግምገማና ትችት በፍጹም ችላ ልትሉት አይገባም፡፡ ነገር ግን በሚዛናዊነት ተገቢውንና ሚዛናዊውን እየለያችሁ ራስን ለመለወጥ መጠቀም አስፈላጊ ነው፡፡
ራሳችሁን እስከመኮነን ድረስ በራሳችሁ ላይ አትጨክኑ፡፡ በራሳችሁ ላይ ያላችሁ አመለካከት እስከሚወርድ ድረስ በራሳችሁ ላይ አትፍረዱ፡፡ ሌላ ውሳኔ ለመወሰን ያላችሁ ድፍረት እስከምታጡ ድረስ ባለፈው ውሳኔያችሁ ስህተት ራሳችሁ አትደብድቡ፡፡ ስህተታችሁን እወቁ፣ አርሙ፣ ደግማችሁ ላለመስራት ወስኑ፡፡ ከዚያም ቀና ብላችሁ በአዲስ መንፈስ ወደፊት!
ይኼንን እወቁ ሰይጣን እናንተን እግዚአብሔር ፊት ሄዶ ሊከስ አይችልም። ድሮ በአሮጌው ኪዳን ወቅት ላይ እንደዚህ ያደርግ ነበር ካህኑ ኢያሱን ፣ ኢዮብን ጨምሮ ከሶታል።
አሁን ግን በእግዚአብሔር ፊት እኛ የምንከሰስበት የኃጢአት ዕዳ በክርስቶስ መስቀል ስለተደመሰሰ : ሰይጣን ስለ ኃጢአታችን እግዚአብሔር ፊት መሄዱ ቀረ። ስለዚህም አሁን በአየር ላይ የሚሸከረከር መንፈስ ሆነ : እግዚአብሔርጋ እንዳይሄድ ታላቅ ጠበቃ ስላለ የማይደፈር ሲሆንበት አሁን እኛጋ ከመንፈሳዊ አለም ወደ አካላዊ አለም ለመገለጥ የክስ ዶሲዎችን ወደ አእምሯችን ይወረውራል። እኛ የእሱን ክስ ተቀብለን: ከሕሊናችን ጋር ተስማምተን በራሳችን ላይ ከፈረድን መንፈሳዊ ውጊያ ላይ ቅድሚያ ተሸናፊዎች ሆነን እንገኛለን።
በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉ አሁን ኩኔኔ የለባቸውም የሚለው ቃል በልባችሁ አሰላስሉ(ሮሜ8:1)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_
#ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ 👉@biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🙏❤
(መንፈሳዊ_ውጊያ
=============================
"ዲያብሎስን ተቃወሙ!" ምን ማለት ነው?
-------------------------
✍ አሁን ላይ በየቤተክርስቲያኑ እንደምንሰማውና እንደምናየው ዲያብሎስን መቃወም ማለት ለረጅም ሰዓታት የአጋንንትን ስም እየጠሩ "የተቃውሞ ጸሎት" ማድረግ ወይም ሺህ ጊዜ በኢየሱስ ስም እያሉ "መገሰጽ" ነው ብለው ብዙዎች ያስባሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን እንደዛ አያስተምረንም!
📌መጽሐፍ ምን ይላል፦
----------------
✍" እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን #ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል" (ያዕ 4: 7)
እዚህ ጥቅስ ውስጥ "ተቃወሙ" የሚለውን ቃል አዲስ ኪዳን ግሪክ "ἀνθίστημι"( አንቲስቴሚ) ብሎታል፥ ትርጉሙም "በተቃርኖ መቆም" ማለት ነው፡፡ ይህም በዲያብሎስ ሃሳብና ሽንገላ ፈጽሞ አለመስማማትን ያመለክታል፡፡
✍ ያዕ. 4:7ን በሌላ አገላለፅ ብናስቀምጥ "ለእግዚአብሔር እሺ በሉ፤ ለዲያብሎስ ሽንገላ ግን እንቢ በሉ" እንደማለት ነው፤ በእግዚአብሔር ቃል መስማማትና በዲያብሎስ የማታለያ ሃሳብ ግን አለመስማማት ማለት ነው፡፡
📌 ለምሳሌ፦ ጠላት ለኃጢአት ሲቀሰቅስህ ፥ "እኔ ለኃጢአት ሞቻለሁ፥ በአዲስ ሕይወት እመላለስ ዘንድ ለጽድቅ ሕያው ነኝ" በማለት በተረዳኸው የወንጌል እውነት ጸንተህ በመቆም የጠላትን ማባበያ ትቃወማለህ ማለት ነው፡፡
ጠላት ሊኮንንህ ሲመጣ በክርስቶስ ኩነኔ የሌለብህ ጻድቅ መሆንህን ትናገረዋለህ ማለት ነው፡፡
✍" የዲያብሎስን ሽንገላ #ትቃወሙ_ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።" (ኤፌ 6: 11)
ይሄ ጥቅስ ደግሞ የዲያብሎስን ሽንገላ ለመቃወም #የእግዚአብሔርን_ሙሉ_የጦር_ትጥቅ መልበስ እንዳለብን ይናገራል፡፡ ትጥቅ #የእግዚአብሔር እንጂ እኛው ለእኛ በልካችን የምንሰፋው አይደለም፡፡
እግዚአብሔር በክርስቶስ ሥራ ለእኛ ያሰናዳውን ትጥቅ ነው የምንታጠቀው፡፡
📌 በኤፌ. 6:11 ላይ "ዕቃ ጦር ሁሉ" የሚለውን ሐረግ( phrase) ግሪኩ "ፓኖፕሊያ" በሚል አንድ ቃል ይገልጸዋል፡፡ ፓኖፕሊያ በአንዴ ሁሉን ያሟላ #ሙሉ_ትጥቅ ( complete armor) ነው፡፡
በዚህ ሙለ ትጥቅ ውስጥ የተካተቱ መሣሪያዎች ኤፌ 6:14-17 ተዘርዝረዋል
👉የእውነት መታጠቂያ [#ቀበቶ]-
የጠላትን ውሸት የምንመክተው በእግዚአብሔር ቃል እውነት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል እውነተኝነት ማመን ቃሉ እንደሚለን እንደዚያው እንደሆንን እውቅና መስጠት።
👉የጽድቅ ጥሩር-
የጽድቅ ጥሩራችን የተረዳነው የጽድቅ እውነት ነው፡፡ ጥሩር ደረት አካባቢ የሚረግ ትጥቅ ነው፡፡ ልብ እንዳይጎዳ ይከላከላል፡፡መንፈሳዊ ጥሩራችን በክርስቶስ መጽደቃችንና የተገለጠ የጽድቅ ኑሯችን ሲሆን የውስጥ ሕሊናችንን ከጠላት ክስ የምንከላከልበት የጽድቅ እውነት ነው፡፡
👉የሰላም ወንጌል_
ወንጌላችን የሰላም ወንጌል ነው፡ ወንጌሉን በመኖርና በመመስከር ያለመታወክ ተረጋግተንና ጸንተን መቆም የምንችለው በተረዳነው የሰላም ወንጌል ነው፡፡
👉የእምነት ጋሻ-
የትኛውንም የጠላት የክፋት ፍላጻ መከላከል የምንችለው ባመንነው እምነት ነው፡፡ እምነትን የሚሸረሽሩ እንደ እግዚአብሔር ቃል ያልሆነ ከሰይጣን የሚወረወሩ የሀሰት ፍላጻወችን የምንከላከለው በእምነት ጋሻ ነው።
👉የመዳን ራስ ቁር-
ስለመዳናችን የተረዳነው እውነት ላይ እርግጠኛ በመሆንና በማስጠበቅ ሁልጊዜም በዚህ እውነት መመላለሳችን ለእኛ ጭንቅላታችንን[ የአስተሳሰብ ክፍላችንን] ይከላከልልናል፡፡
👉 የመንፈስን ሰይፍ የእግዚአብሔርን ቃል ያዙ ይላል።
አስተውለን ከሆነ ከላይ የተዘረዘሩት የጦር እቃዎች መከላከያዎች ናቸው። የእግዚአብሔር ቃል ደግሞ የመንፈስ ሰይፋችን ነው። ጠላት ኢየሱስን ሊፈትነው በመጣ ጊዜ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል በማለት እንደመለሰው እኛም የጠላትን ሽንገላ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል ብለን እንዳይሳካለት ማድረግ እንችላለን። ለዚህም የእግዚአብሔር ቃል ሙላት ያስፈልገናል።
👉 በፀሎትና በልመና በመንፈስ ዘወትር በመንፈስ ፀልዩ : በዚሁ ሀሳብ ስለ ቅዱሳን እየለመናችሁ በመፅናት ሁሉ ትጉ
📞 ፀሎት ከአጠቃላይ የጦር መሪያችንና ጌታችን ጋር መገናኛ የስልክ መስመራችን ነው። ወታደሮች ብንሆንም ያለ ጦር መሪያችን ምሪት ብንሰማራ ተጠቂዎች ነን። ስለዚህ ጌታ በጳውሎስ በፀሎት ስሜት ዘወትር እንድንኖር ያነሳሳናል ፣ በመንፈስ እንድንፀልይ የሚያነሳሳን አጋዣችን መንፈስ ቅዱስ ነው። እርሱ እንዴት መፀለይ እንኳ እንደሚገባን የማናውቅ እኛን ድካማችንን በማገዝ ያበረተናል።
📌 እነኚህ ነገሮች ሁሉ በክርስቶስ የእኛ ናቸው፡፡ በየቀኑ እነኚህን ነገሮች መልበስ [ በነኚህ ነገሮች መሸፈን] ነው የሚጠበቅብን፡፡
ጠቅለል ስናደርግ ዲያብሎስን መቃወም ማለት መጮህ ሳይሆን በተረዱት እውነት ጸንተቶ መቆም ማለት ነው፥ ከእግዚአብሔር ጋር መስማማት ከጠላት ውሸት ጋር አለመስማማት ማለት ነው።
ከወንጌል እውነት ቤተክርስቲያን በመተባበር የተነደፈ መልዕክት ፀጋና እውነት ቤተክርስቲያን
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉 @biruk351
#እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🙏❤
በመንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ ሊኖረን የሚገባ አስተሳሰብ
" ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።"
(ወደ ዕብራውያን 4:15)
ኢየሱስ በሰይጣን ስንፈተን የሚራራልን ሊቀ ካህናት ነው፤ ለምን ?ለራሱም ስለተፈተነ። ለራሱ በምን ተፈትኗል? እንደ እኛ ?
ኢየሱስ; በሰይጣን ሲፈተን ባለመውደቁ ፣ሰይጣን በተለያየ መንገድ ፈትኖታል ። ሰይጣንም ለመጣል ያለውን ኃይሉንና ጥበቡን ሁሉ አሟጦ በኢየሱስ ላይ ተጠቅሞበታል ። መላእክት መጥተው እስከ ሚያገለግሉት ድረስ። ከዚህ የተነሳ ኢየሱስ የሰይጣንን አቅም በራሱ ላይ ከቀረበው ፈተና አንፃር በሚገባ ያውቃል ማለት ይቻላል ። ስለዚህም እኛን ፈትኖ ቢጥለን ፣ ከመፍረድ ይልቅ ያዝንልናል፤ ይራራል ። ምክንያቱም እኛን ስለኾነ #የሥጋ_ደካማነትንና የሰይጣን ጥበቡንና ሃይሉን በሚገባ ስለሚያውቅ ።በዚህም ምክንያት ሊቀ ካህናታችን ይራራልናል።ስንደክም አቅምን [ጸጋን] ለመጨመር እጁን ይዘረጋል ፤ድል እንድንነሳ።
ሰይጣን እንደሚጠላን፣ የእግዚአብሔር ልጆችን ፈቃዱ እንዳይከናወንባቸው እንደሚዋጋ በደንብ ኢየሱስ ያውቃል፣ እምነታችንን ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥር ሲነሳ ያውቃል ፣ ስለዚህ በውደቃታችን ሳንማረር ወደ ኋላ ሳንፈገፍግ በድል አስተሳሰብ ውስጥ እንድንሆን ኢየሱስ ይፈልጋል። በእርሱ ወዳለን ማንነትና እርሱ በውስጣችን ባፈሰሰው የትንሣኤ መንፈስ እንድንታመን ይፈልጋል።
ሀይልን በሚሰጠኝ በእርሱ ሁሉን እችላለሁ እንድንል ይፈልጋል
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉biruk351
በመንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ ትልቁ ስልት : የጠላትን ኃይል ማወቅ አይደለም : ይልቁንም ከእኛ ጋር ያለውን ማወቅና በእርሱ እኛ ማን እንደሆንን መረዳት ነው!!
✞የእግዚአብሔር ልዩ ፍቅር✞
👉ከእግዚአብሔር ጋር ያለህ ግንኙነት ከሌሎች ጋር ከሚኖርህ ግንኙነት የተለየ ነው፡፡ እግዚአብሔር ለአንተ ለየት ያለ ፍቅር አለው፡፡ ፍቅሩ በሁኔታዎች ላይ የተመሠረተ አይደለም (አንዳንድ ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት ላይ የተመሠረተ አይደለም)፡፡ እግዚአብሔር የሚወድህ ስለ ወደደህ ብቻ ነው፡፡
“በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር ለእኛ ተገለጠ፣ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንደ እግዚአብሔር አንደ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና፡፡ #ፍቅርም_እንደዚህ_ነው፤ እግዚአብሔር ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስታሰሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደወደድነው አይደለም” (1ኛ ዮሐንስ 4፡9-10)
👉ቅልጥፍናህንና ሥራህን አይቶ አልወደደህም፡፡ እግዚአብሔር አሁን ከሚወድህ በላይ እንዲወድህ ሊያደርገው የሚችል ምንም ነገር ሠርተህ እንዲወድህ ልታደርገው አትችልም፡፡ ፍቅሩንም እንዲቀንስ ሊያደርገው የሚችል ነገር የለም፡፡ አንተ ራስህን እንኳን ከምትወደደው የበለጠ እርሱ ይወድሃል፡፡
👉እስካሁን በሕይወትህ የተለማመድከው በሁኔታዎች ላይ የተመሠረተውን ፍቅር ይሆናል፡፡ በሁኔታ ላይ የተመሠረተ ፍቅር አንተ በምታከናውነው ተግባር ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በሥራ፣ በቡድን፣ ወይም በግንኙነትህ ጥሩ እንቅስቃሴ ካደረግህ “ትወደዳለህ”፡፡
👉ሕይወትህን ለክርስቶስ በመክፈትህ፣ ፍጹም ፍቅርንና ተቀባይነትን አግኝተሃል፡፡ ከዚህ ቀደም ከማንም ሰው ፍፁም ፍቅርንና ተቀባይነትን አግኘኝተህ የማታውቅ ከሆነ ነገሩን በውል መረዳት እጅግ ያስቸግርሃል፡፡ ግን ልንነግርህ የምንሻው እውነት ነው! የሚያሳዝነው ግን፣ እግዚአብሔር ይወደኛል የሚል ስሜት ዘወትር አይኖርህም፡፡ እንዲያውም ፍቅሩን ብቻ ሳይሆን፣ የመኖሩንም ጉዳይ ስትጠራጠር ራስህን ታገኘዋለህ፡፡ ምናልባት የተሸነፍህ ሊመስልህ ይችላል፡፡ አይሰማህ፡፡
👉እግዚአብሔር አዲስ ሕይወት ሲሰጥህ፣ የሚሰጥህ ሕይወት ውብና ማራኪ ሆና በሽቶ መዓዛም እንደተሸሞነሞነች አይነት አትመጣም፡፡ ኢየሱስ ምድራዊ ሕይወቱን የጀመረው፣ የማይጣፍጥ ጠረን በሞላባትና በከብቶች ሽንት በረጠበች ግርግም ውስጥ ነበር፡፡ እርሱ የእውነተኛውን ሕይወት ጣዕም አጣጥሞታል፣ ያም አንተ ከክርስቶስ ጋር የምታደርገው ጉዞ መዓዛም ያው ይሆናል፡፡ ምትሃታዊ ነገር ሳትጠብቅ፣ አብሮህ የሚኖረው እርሱ ሁልጊዜ አብሮህ እንደሚሆን የሰጠህ ተስፋ የታመነ ነው፡፡
📖እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፣ “… በዘላለም ፍቅር ወድጄሻለሁ፤ ስለዚህ በቸርነት ሳብሁሽ” (ኤርምያስ 31፡3)፡
👉እምነታችን የሚያርፈው እግዚአብሔር ለእኛ ስለ ራሱ በገለጠልን ላይ ነው፡፡ በተለይም ደግሞ እርሱ ለእኛ ባለው ፍቅር እንድናምንና እንድንደገፍ ይፈልጋል፡፡
👉“እንደ ልቤ የሆነ ሰው" ተብሎ የተመሠከረለት፣ ንጉሡ ዳዊት፣ በእግዚአብሔር ፍቅር በመታመን፤ “እኔ ግን ለኃይልህ እቀኛለሁ፤ በምሕረትህም ማልዶ ደስ ይለኛል፤ በመከራዬ ቀን መጠጊያዬና አምባዬ ሆነኸኛልና፡፡ ረዳቴ ሆይ፣ ለአንተ ለአምላኬ እዘምራለሁ፤ አንተ፣ አምላኬ፣ መጠጊያዬ ምሕረቴም ነህና፡፡” (መዝሙር 59፡16-17)
❤ኢየሱስ ለእኛ ያለውን የፍቅሩን ጥልቀት እንዲህ ሲል ገልፆታል፣ “አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ #በፍቅሬ_ኑሩ፡፡ እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፣ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ፡፡ ደስታዬም በእናንተ እንዲሆን ደስታችሁም እንዲፈፀም ይህን ነግሬአችኋለሁ” (ዮሐንስ 15፡9-11)፡፡ ምንም ይሁን ምን መታዘዝ ሲያቅተንም እንኳን ይወደናል፣ ስንታዘዘው ግን በፍቅሩ እንኖራለን፣ በፍቅሩም ደስ ይለናል፡፡
✞✞✞#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ይንኩ👉@biruk351
ያልተገባ ሃዘን
“ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች” ዮሐንስ 20፥11
ማርያም ለምን አለቀሰች? ምክንያቱም መቃብሩ ባዶ ነበር! ከእምነት ማጣት በኋላ ምን ዓይነት አላስፈላጊ ሃዘኖች ይከተላሉ? እነዚያ በእንባ የተዳከሙ ዓይኖች የጌታን ትንሣኤ ማስረጃ አላዩም፡፡ እናም መላእክት “ አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? አሉአት። እርስዋም፦ ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው።” ዮሐንስ 20፥13።
ምስኪን ሴት! ምርጫ ያደረገችው አስከሬኑን በመቃብሩ ማግኘት ነበር እንጂ መሻቷ ትንሳዔውን ማየት አልነበረም።
ሌሎች ሁለት ደግሞ ወደ ኤማውስ የሚጓዙ ነበሩ፣ ሁኔታቸውም ከማዘን የተናነሰ አልነበረም፡፡ እነዚህ ሰዎች ደግሞ ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ስለተከናወኑ ነገሮች ሁሉ አብረው እየተናጋገሩ ነው እና ሲነጋገሩ እና ሲያስቡ፣ ኢየሱስ ራሱ ቀርቦ ከእነርሱ ጋር መጓዝ ጀመረ፣ ግን እንዳያውቁት ዓይኖቻቸው ተይዘው ነበር፡፡ " ሲነጋገሩና ሲመራመሩም፥ ኢየሱስ ራሱ ቀርቦ ከእነርሱ ጋር ይሄድ ነበር፤ ነገር ግን እንዳያውቁት ዓይናቸው ተይዞ ነበር። እርሱም፦ እየጠወለጋችሁ ስትሄዱ፥ እርስ በርሳችሁ የምትነጋገሩአቸው እነዚህ ነገሮች ምንድር ናቸው? አላቸው። ሉቃ 24:15-17
እዚህ ክፍል ውስጥ “መራመድ” የሚለው ቃል ዝም ብሎ መራመድ ማለት ሳይሆን፣ መራመድ የሚለው ያለ ዓላማ መንከራተት ማለትን ያመለክታል፡፡ ወደ ኤማሁስ እየተጓዙ ነበር፣ ግን በጣም ልባቸው ስለ ተሰበረ ወደዚያ መድረሱ ወይም አለመድረሱ ላይ ምንም ግድ የላቸውም። ተስፋቸውን እንዲተው ያደረጋቸው ምንድን ነው? የራሳቸውን ማብራሪያ እናድምጥ “እኛ ግን እስራኤልን እንዲቤዥ ያለው እርሱ እንደ ሆነ ተስፋ አድርገን ነበር፤ ደግሞም ከዚህ ሁሉ ጋር ይህ ከሆነ ዛሬ ሦስተኛው ቀን ነው።” ሉቃስ 24፥21
ተስፋቸውን ጥለው ነበር ምክንያቱም ጌታ ከተሰቀለበት ጊዜ አንስቶ ይህ ሦስተኛው ቀን ነው ፣ ግን እሱ ራሱ ተደጋግሞ በተናገረው ቃል መሠረት ከሞት የሚነሣበት ይህ ቀን ነበር።
መቃብሩ ባዶ ስለሆነ ማርያም አለቀሰች! ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ልባቸው ተሰብሯል ምክንያቱም ከሞተ አሁን ይህ ሶስተኛ ቀን ነው! ባለማመናቸው ምፀት ፈገግ ልንል እንችላለንን! ግን ስለራሳችንስ ያለን አተያይ ምን ይመስላል? ከሙታን የተነሳው፣ የከበረው ክርስቶስ ዛሬም እጅግ የላቀ ኃይልን ይዟል፣ እናም የጥንት ተከታዮቹ ስለማንኛውም ነገር ከማያውቁት በላይ አሁን ለአማኞች እጅግ የላቀ በረከቶችን ይሰጣል።
ብዙውን ጊዜ ሰላም በማጣት እንባዝናለን! ለምንስ አላስፈላጊ ሥቃይ እንሸከማለን? ይህ ሁሉ የሚሆነው ደግሞ እግዚአብሔርን በቃሉ ውስጥ ማግኘትና እግዚአብሔርን መስማት ስለተሳነን ነው። ቃሉን ሰምተን፣ እግዚአብሔርን አድምጠን በሰላም መመላለስ ይሁንልን፣ ህይወታችን ከሃዘን እና ከስቃይ የራቀ ይሆን ዘንድ ለቃሉ ሥፍራን እንስጥ! ጌታ ይርዳን!
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ይንኩ👉 @biruk351
መንፈሳው ውጊያ
#የቀጠለ
እነዚህ የኤፌሶን አማኞች በሰማያዊ ስፍራ የተቀመጡ ናቸው፣ እንዲሁም በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የተባረኩ ናቸው፡ ነገር ግን መንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ ደግሞ ነበሩ፡ በመንፈሳዊ በረከት መባረካቸውና በሰማያዊ ስፍራ መቀመጣቸ ከመንፈሳዊ ውጊያ ነጻ አያደርጋቸውም፡ እንደውም ውጊያውን ያሳልጠዋል።
የኤፌሶን አማኞች ይህንን ውጊያ ድል ማድረግ የሚችሉት በሰውኛ ሳይሆን በእግዚአብሔርኛ ብቻ ነው፡ እነዚህ የተዘረዘሩት አለቆች፣ ባለስልጣናት፣ ገዦችና በሰማያዊ ስፍራ ያሉ ክፉ መንፈሳውያን ሰራዊ የሚገባቸው ቋንቋ እግዚአብሔርኛ ብቻ ነው፡ ስለዚህ ነው ጳውሎስ ኤፌሶኖች “በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ” የሚላቸው፡ የእግዚአብሔርን እቃ ጦር ሁሉ በማንሳት ብቻ ነው ይህን ጦርነት ማሸነፍ የሚቻለው፡ ይሄ ጦርነት የኤፌሶን አማኞች ጉልበት ሳይሆን የእግዚአብሔር ጉልበት የሚገለጥበት ጦርነት ነው፡ ልክ ጎልያድ፦ ዳዊት ቀይ ያማረና የቤት ልጅ መሆኑን አይቶ ሲንቀው ዳዊት ግን “አንተ በተገዳደርከው በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ” እንዳለው ማለት ነው፡ ጎልያድ ጉዳዩ የዳዊት መስሎታል፡ አላወቀም፡ ዳዊት ግን ጉዳዩ የእግዚአብሔር እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል፡ ይሄ ጦርነት ዳዊት ቢሠለፍበትም ውጊያው ግን የእግዚአብሔር ነበር።
ጳውሎስ በአጭሩ የኤፌሶንን አማኞች መንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ ናችሁ እያላቸው ነው፡ የማይናቅ ውጊያ፡ ይህ ውጊያ በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ክፉ መናፍስቶች ጋር ነው ፣ ከአለቆችና ከስልጣናት ጋር ነው...የውጊያው ቦታ ግን አሁን መንፈሳዊ አለም ላይ በሰማያዊ ስፍራ አይደለም! የውጊያው ጦር ሜዳ አሁን በአእምሯችን ውስጥ ነው: አሁን ከሀሳቦች ፣ ከምናቦች ፣ ከአንዳንድ ክፉ ሕልሞችና ከቃላቶች ጋር ነው.. እግዚአብሔር በክርስቶስ ተዋግቶ በማሸነፉ የድል ሰዎች አድርጎ ስልጣኑን ሰጠን.. ይኼንን እውነት እንዳናጣጥም መዳናችንን እንኳ እንድናጠራጠር የሚተጉ ወደ አእምሯችን ጥርጣሬን የሚረጩ መናፍስቶች አሉ። በእነዚህ መናፍስቶች ሀሳባቸውን ተቀበልን ከተቀመጥን የእግዚአብሔርን ሕይወት ከማጣጣም ያዘገዩናል። ከእግዚአብሔር ነገሮች ወደ ኋላ ይስቡናል.... የእግዚአብሔርን ቃል ያዙ ያንን አሰላስሉ ቀጥሎም ፀልዩ..
ምክንያቱም ጳወሎስ ይህንን ውጊያ እንዲያሸንፉ የጦርነት መሳሪያ አድርጎ ከሚያስታውሳቸው ነገሮች መካከል አንዱ ደግሞ ጸሎትን ነው፡ ለራሳችሁም፣ ለሌሎች ቅዱሳንም እንዲሁም ለእኔም ጭምር ጸልዩ ይላቸዋል፡ የሚገርመው ለእኔም ጸልዩ ሲላቸው የእግዚአብሔርን ቃል በግልጥነት መናገር የሚገባኝን ያህል እንድናገር ብሎ የጸሎት ርዕስ በመስጠት ነው፡ አይገርምም! ጳውሎስ ጸልዩልኝ ሲል፡ የመናገር ችሎታ ስላለው፣ ወይም ብዙ ስላነበበ፣ ወይም ትናንት ሌላ ቦታ ጥሩ ስላገለገለ፣ ወይም ብዙ ደጋፊዎችም ስላሉት ዛሬም እንደዛ ይሆንልኛል ብሎ አያስብም፡ ዛሬም ጸሎት እንደሚያስፈልገው ይነግራቸዋል፡፡
የንግግር ችሎታ የጌታ ቃል አገልጋይ አያደርገንም።
በአብዛኛው ጸሎት በእኔ እጅ ላይ ነው የተበላሸው፡ የእኔን አጀንዳ ማስፈጸሚያ መንገድ ብቻ አድርጌ ነው የማስበው፡ እኔ የምፈልገውን ሁሉ ለማግኘትና ልደረምሰው የምፈልገውን ሁሉ ለመደርመስ የምወስደው ርምጃ ነው የሚመስለኝ፡ አይደለም! በክፉ በተያዘ በዚህ አለም ውስጥም ለእግዚአብሔር መወገናችንንና ከማንም ፈቃድ ይልቅ ለእርሱ ፈቃድ ማድላታችንን የምንገልጥበት የታማኝነት መንገድ ነው።
አንድ ጊዜ Steve Brian የሚባሉ የአዲስ ኪዳን ምሁር ጸሎትን አስመልክቶ እንዲህ ብለው ተናገሩ፡
“ጸሎት እዚህ አለም ውስጥ ባለ እሴተ-ስርአት ላይ ማመጽና በተቃራኒው መቆም ነው”
እኚህ ሰው እውነታቸውን ነው፡ የሚጸልይ ሰው አንድ ነገር እየተናገረ ነው፡ እንዲህ እያለ ነው፤
ለእግዚአብሔር ሐሳብ ተቃራኒ ለሆነ ነገር በሙሉ እኔ ደግሞ በተቃራኒው እቆምበታለሁ፡ ከእግዚአብሔር ሐሳብ ጋር እወግናለሁ እያለ ነው።
ስንጸልይ የእግዚአብሔር ፕሮግራም ውስጥ ነን፡ ስንጸልይ በክፉው ሐሳብ ተቃሪኒ እየቆምን ነው፡
ጸሎት እንጀራ መለመኛ ብቻ ሳይሆን በዚህ ክፉ አለም ላይ በማመጽ የእግዚአብሔር ወዳጅ መሆናችንን የምናሳይበትም መንፈሳዊ እሴት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን ካመንህ አሁንና እዚህ መንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ ነህ:!
#ይቀጥላል
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ይንኩ 👉@biruk351
ከወደዱት ሼር ❤
እናመሰግናለን🙏
ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን ደብዳቤው የኤፌሶንን አማኞች ውጊያቸው ምን አይነትና ባላንጣዎቻቸው ደግሞ እንዴት ያሉ እንደሆኑ ይነግራቸዋል፡፡
..... #ይቀጥላል
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ሁለት ጊዜ ይኼንን ሊንክ ይንኩ👉@biruk351
#መንፈሳዊ_ውጊያ
ጠላትህንና ራስህን ካወቅህ ስለመቶ ጦርነቶች ውጤት መጨነቅ የለብህም፣ ራስህን አውቀህ ጠላትህን ካላወቅህ ደግሞ ለምታጣጥማት እያንዳንዷ ድል ሽንፈትንም ትጎነጫለህ፡ ጠላትህንም ሆነ ራስህን ካላወቅህ ግን በጦርነቶች ሁሉ እጅህን ትሰጣለህ፡
አንዳንዴ መጽሐፍ ቅዱሳችን የሚነግረን ታሪክ rationalize አደርጋለሁ ለሚል ሰው ብዥታን መፍጠሩ አይቀርም፡ ለምሳሌ ያህል በመንፈሳዊ አለም ውስጥ በመንፈሳዊ አካላት የሚደረግ መንፈሳዊ ውጊያ ላይዋጥለት ይችላል፡ ያም ሆነ ይህ መጽሐፍ ቅዱሳችን ስለ እንደዚህ አይነት በመንፈሳዊ አለም ውስጥ በመንፈሳዊ አካላት ስለሚደረግ መንፈሳዊ ውጊያ መናገር ብቻ ሳይሆን “በስጋ ያለንና በሚታየው አለም የምንቀሳቀስ እኛን” ወደዚህ መንፈሳዊ ውጊያ ይጋብዘናል።
ይኼን ሀሳብ በስብከት መልክ ያቀረብኩ ሲሆን: በኦዲዮ በዚሁ ቻናል አቀርብላችኋለው።
ዳንኤል በምርኮ በፋርስ መንግስት ውስጥ ለሕዝበ-እስራኤል ይጸልይ በነበረበት ጊዜ ነገር ይገለጥለታል፤ ነገሩም “ታላቅ ጦርነት” ነበር፡ አንድ መልአክ የእግዚአብሔርን ፕሮግራም ለዳንኤል ለመንገር ተልኮ ቢሆንም ሃያ አንድ ቀን ግን “መንገድ” ላይ በሚቋቋመው ሌላ መንፈሳዊ ኃይል ዘግይቶ እንደነበር ለዳንኤል ይነግረዋል።
መልአኩ ለዳንኤል መዘግየቱን ብቻ ሳይሆን ለምን ወይም ምን እንዳዘገየው እንዲህ ብሎ ይነግረዋል፤
“ዳንኤል ሆይ፥ አትፍራ፤ ልብህ ያስተውል ዘንድ፥ ሰውነትህም በአምላክህ ፊት ይዋረድ ዘንድ ካደረግህበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ቃልህ ተሰምቶአል፤ እኔም ስለ ቃልህ መጥቻለሁ። የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት”
መልአኩ ለዳንኤል የሚነግረው ነገር በጣም “እንግዳ” የሆነ ነገር ነው፡ በየትኛውም የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት እንዲህ አይነት ነገር አልተከተበልንም፡ ይህ ጉዳይ በብሉይ ኪዳን ውስጥ በአይነቱ አዲስና የተለየ ነው።
የእግዚአብሔርን ፕሮግራም ለዳንኤል ይዞ የነበረው መልአክ ለ21 ቀን በአየር ላይ አታልፍም ተብሎ “ታግቶ” ነበር፡ በመሠረቱ አንዳንድ ትርጉሞች “detain” ተደርጎ ነበር ነው የሚሉት፡ ይህንን የእግዚአብሔርን ፕሮግራም ይዞ ወደ ዳንኤል የሚመጣውን መልአክ መንገድ ላይ ያዘገየው የፋርስ ንጉስ ቂሮስ ሳይሆን የፋርስ “መንግስት አለቃ” ነው፡ ይሄ የፋርስ መንግስት አለቃ ከንጉሱ ቂሮስ የገዘፈና መንፈሳዊ አካል ሲሆን የእግዚአብሔርን መልአክ በአየር ላይ ተቋቁሞ ለማዘግየት አቅም ያለው ማንነት ነበር።
የሚገርም ነው! የእግዚአብሔርን ፕሮግራም የያዘ የእግዚአብሔር መልአክ በዚህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ተቃራኒ በሆነ አለቃ detain ተደረገ።
አንዳንዴ ነገሮች እኛ እንደምናስባቸው አይደሉም፡ እግዚአብሔር መጋረጃውን ገልጦ ጀርባውን ወይም ውስጡን ሲያሳየን ብቻ ነው የምናውቀውና “እንዴ! እንዲህ ነበር እንዴ?!” የምንለው።
ዳንኤል መልአኩ ባይነግረው ኖሮ ለምን 21 ቀን እንደዘገየ አያውቅም ነበር: የኛ መላ ምትና እውነታው ለየቅል ናቸው::
በምዕራፍ ዘጠኝ ላይ ዳንኤል የነብዩ የኤርምያስን መፅሐፍ አንብቦ 70 አመት በምርኮ በዚያ የመኖራቸው ጊዜ እንደተገባደደ በማወቅ : የሕዝቡንና የራሱን ኃጢአት በመናዘዝ እግዚአብሔር ፊት ምልጃውን ማሰማት ጀመረ... በጣም የሚገርመው ወዲያው በአምስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መልስ መጣለት.. (ትን ዳን 9:20-21). (አምስት ዲቂቃ ያልኩት እግዚአብሔር በሙላት ካለበት ገብርኤልም በዚያ ከሚገኝበት መንፈሳዊ አለም: ወደ አካላዊ አለም ለመገለጥ ምናልባት በብርሃን ፍጥነት አምስት ዲቂቃ ፈጅቶበት ይሆናል: ምክንያቱም መላእክት ፍጡር ስለሆነ በአንዴ እዚህና እዚያ አይገኝም ፡ ስለዚህ ምናልባት ከ3 እስከ 5 ደቂቃ ሊፈጅበት ይችላል በሚለው ነው) ይሁን እንጂ በምዕራፍ 10 ፀሎት መልሱን ለማግኘት 21 ቀን ዳንኤል ፈጀበት። አንዳንዴ በእኛም ሕይወት እንደዚህ ነው : አንዳንድ ፀሎቶች ቶሎ ምልሽ ስናገኝ የሆኑ ፀሎቶች ግን መልሱ ቶሎ አይገለጥም : እናም ከዚህ አንዳንድ ነገሮችን ተረድተን : የእምነት አቋማችንን ማረም ይኖርብናል። የሆነ ነገር ፀልየህ መልሱ ቶሎ አልገለጥ ሲልህ ማጉረምረም ፣ ደግሞ ደጋግሞ ያንኑ ፀሎት መፀለይና .. ጌታ ሆይ መች ነው ፀሎቴን የምትሰማው? ለምን ቸል ትለኛለህ? ለምን ራክብኝ አይነት ስሜት ውስጥ በመውደቅ ከእምነት አለም ስርዓት ከምንተላለፍ ፀሎትህ እንደተሰማህ አውቀህ፡ ነገሩ እንዲገለጥ የአንተን ሀላፊነት መወጣትና(ለእግዚአብሔር መገዛትና ዲያብሎስን መቃወም) መንፈስ ቅዱስ ስለ ነገሩ የሆነ መገለጥ እንዲሰጥህ መጠየቅ ይኖርብሃል።
ዳንኤል ባለፎ ስፀለይ አምስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መልሴ መጣ አሁን ግን ፀሎቴን ከጀመርኩ 21ቀኔ ነው በማለት ፀሎቱን አላቋረጠም ። እሱ እዛው በመሰውያው በእምነቱ ቆሞ ነበር። እናም ገብርኤል መቶ ነገሩን ገለጠለት።
ይሄ የእግዚአብሔርን ፕሮግራም ለዳንኤል ለመንገር የተላካው መልአክ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ ባይመጣ ኖሮ ማለፍ አልችልም ነበር ብሎም ይነግረዋል፡ ለእግዚአብሔር መልአክ ሚካኤል ባይደርስለት ኖሮ የፋርስ መንግስት አለቃ ምን ያህል ቀን ያቆየው ይሆን? ጭራሽ ዳንኤልስ ጋር ይመጣ ነበር? ነገር ግን ሚካኤል ውጊያውን ሲሸፍንለት እርሱ በዛ አጋጣሚ ዳንኤል ጋር መጣ።
አንዳንዴ ነገሮች እኛ እንደምናስባቸው አይደሉም፡ የእግዚአብሔርን ፕሮግራም የያዘ የእግዚአብሔር መልአክ እንኳን በሌላ ክፉ አለቃ በአየር ላይ ሊዘገይ ይችላል፡ ብዙ የማናውቀው ነገር አለ፡ እኛ በዚህ ቁስ አለም ውስጥ የሚሆነውን ነው የምናውቀው እንጂ ከመጋረጃው በስተጀርባ ማን ምን እያደረገ እንደሆነ የማወቅ አቅም የለንም፡ ክህሎቱን እግዚአብሔር ካልሰጠን በስተቀር።
እንዴ መላእክት ይዋጋሉ እንዴ? መጽሐፍ ቅዱስ አዎ ይዋጋሉ ይለናል፡ ውጊያው ምንም ይምሰል ምን ነገር ግን ውጊያ አለ፡ እኛ ከመጋረጃው ወዲህ ያለውን ነገር ብቻ ነው የምናውቀው፡ ከመጋረጃው ማዶ ያለውን ለማየት መጋረጃው መገለጥ አለበት።
ይሄ በላይ ወይም በመንፈሳዊው አለም ውስጥ ያለው መንፈሳዊ ውጊያ የምድር ታሪክ ላይ ጥላውን ያጠላል ማለት ነው? አሁንም በጸና መልኩ “አዎ!” ብለን መናገር ቢያስቸግርም ቢያንስ ግን የፋርስ መንግስት አለቃ የእግዚአብሔርን ፕሮግራም የያዘውን መልአክ ለሃያ አንድ ቀን እንዳዘገየው ማየት አይቸግርም፡ ሚካኤል ባይመጣና ባይረዳው ደግሞ ከዛም በላይ ሊሆን ይችል ነበር።
ጳውሎስ የተስሎንቄ አማኞችን በአይነ-ስጋ የማየት ታላቅ ፍላጎትና ፀሎት ነበረው ; ይሁን እንጂ ፡ ወደ እናንተ ልመጣ ከአንድም ሁለት ጊዜ.. ሰይጣን ግን አዘገየኝ ይላል(1ኛ ተስ 2:18) አያችሁ አንዳንድ መዝግየቶች ከመንፈሳዊ አለም ጋር ይገናኛል ፣ አንዳንድ ገንዘቦች ፣ አንዳንድ ሰዎች ፣ አንዳንድ የትዳር በረከቶች መምጣት ባለባቸው ሰዓት እንዳይመጡ የሚታገሉ ኃይላት አሉ። ማስቀረት አይችሉም ግን ያዘገያሉ በምትፈጉት ሰዓት እንዳይገለጥ ያደርጋሉ። በእንዲህ ያሉ ወቅቶች ውስጥ በመንፈሳዊ አለም ስላለው የውጊያ ስርዓት መረዳት ይኖርብናል።
#የዕለቱ_ቃል
አሰላስሉት ፀልዩ
"ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪ የውስጥ ሰውነቴም ሁሉ ቅዱስ ስሙን ባርኪ። ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪ፤ ውለታውንም ሁሉ አትርሺ፤ ኀጢአትሽን ሁሉ ይቅር የሚል፣ ደዌሽንም ሁሉ የሚፈውስ፣ ሕይወትሽን ከጥፋት ጒድጓድ የሚያድን፣ ምሕረትንና ርኅራኄን የሚያቀዳጅሽ፣ ጐልማሳነትሽም እንደ ንስር ይታደስ ዘንድ፣ ምኞትሽን በበጎ ነገር የሚያረካ እርሱ ነው። እግዚአብሔር ለተጨቈኑ ሁሉ፣ ቅን ፍርድንና ፍትሕን ይሰጣቸዋል። እግዚአብሔር መሓሪና ይቅር ባይ፣ ለቍጣ የዘገየ፣ ፍቅሩም የበዛ ነው። እርሱ ሁል ጊዜ በደልን አይከታተልም፤ ለዘላለምም አይቈጣም። እንደ ኀጢአታችን አልመለሰልንም፤ እንደ በደላችንም አልከፈለንም። ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፣ እንዲሁ ለሚፈሩት ምሕረቱ ታላቅ ናት። ምሥራቅ ከምዕራብ እንደሚርቅ፣ መተላለፋችንን በዚያው መጠን ከእኛ አስወገደ። አባት ለልጆቹ እንደሚራራ፣ እግዚአብሔር ለሚፈሩት እንዲሁ ይራራል። እርሱ አፈጣጠራችንን ያውቃልና፤ ትቢያ መሆናችንንም ያስባል። ሰው እኮ ዘመኑ እንደ ሣር ነው፤ እንደ ዱር አበባ ያቈጠቍጣል፤ ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ግን ድራሹ ይጠፋል፤ ምልክቱም በቦታው አይገኝም። የእግዚአብሔር ምሕረት ግን፣ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚፈሩት ላይ ነው፤ ጽድቁም እስከ ልጅ ልጅ ድረስ በላያቸው ይሆናል፤ ኪዳኑን በሚጠብቁት ላይ፣ ትእዛዙንም ለመፈጸም በሚተጉት ላይ ይሆናል። እግዚአብሔር ዙፋኑን በሰማይ አጽንቶአል፤ መንግሥቱም ሁሉን ትገዛለች። እናንተ ፈቃዱን የምትፈጽሙ አገልጋዮቹ፤ ሰራዊቱ ሁሉ፣ እግዚአብሔርን ባርኩ። እናንተ በግዛቱ ሁሉ የምትኖሩ፣ ፍጥረቱ ሁሉ፣ እግዚአብሔርን ባርኩ፤ ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪ። (መዝሙር 103:1--22)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ_
ወደ ቻናላችን ሌሎችን ይጋብዙ
👉 @biruk351
👉 @biruk351
#እናመሰግናለን_ተባርካችኋል
ለምንድነው የተፈጠርኩት?
ከየት ነው የመጣሁት ምንጬ የቱ ጋር ነው?
ለምንድነው እዚህ ምድር ላይስ የምኖረው?
ከስጋ ስለይስ ወዴት ነው የምሄደው?
በስጋ ወራቴ ልፈፅመው የሚገባ ትክክለኛ የመኖር ትርጉም ምንድነው?
መልሱን አውቆ መኖር እረፍት ይመስለኛል!...ይኼንን ጥያቄ ለመመለስ አለም ልክ በአረም እንደተወረረ እርሻ መስላለች። ፈላስፋው ይነሳል የራሱን መላምንት ያስቀምጣል፣ የአለም ጠቢባን ይነሳሉ እነርሱም በሳይኮሎጂ እውቀታቸው መልሱን ለመስጠት ደፋ ቀና ይላሉ፣ ሀይማኖት በራሱ ዘዴ በመዘየድ ውስጥ ነው.... እናም አለም ለዚህ መልስ መስጠት አትችልም፣ እናንተ በዚህ ነገር ዙሪያ ከአለም መፅሐፎች የተለያዩ እውቀቶችን ቀስማችሁ ይሆናል፣ ይሁን እንጂ ሩብ እውቀት እንጂ ሙሉ እውቀት በፍጹም ማግኘት አትችሉም! ሰይጣንም ቢሆን ሙሉ ውሸት ይዞ አይመጣም! የሆነ እውነት ይጠቀማል ምናልባትም ጥቅስ ያጣቅሳል እናም ብዙ ሰዎችን ያስታል።
ለእነዚህ ነገሮች ሙሉ መልስ የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው! እርሱን አግኝተህ ከእነዚህ ጥያቄዎች ነፍስህ ነፃ አልወጣች እንደሆነ ማግኘትህን እጠራጠራለሁ!.. ወይንም አንተ እርሱን ለማወቅ አትተጋም ማለት ነው: ምክንያቱም ሙሉ መልስ እንደሆነ እያመንክ አይደለም ማለት ነው!
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ጥያቄ ሁሉ መልስ ያደረገው ኢየሱስን ነው!
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ይኼ እውነት ሙሉ በሙሉ እንዲበራልን አድርገን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ይኼንን ቻናል መቀላቀል ከፈለጉ ሁለት ጊዜ ይኼንን ሊንክ ይንኩ👉@biruk351
እግዚአብሔር ከጠራን በራሱ term እንጂ በኛ term አያስኬደንም
እምነት እግዚአብሔር የሚለውን መስማት እንጂ አእምሮአችን የሚለንን መስማት አይደለም: ይሄ ከባድ አባባል እንደሆነ አውቃለሁ ነገር ግን አናሻሽለውም።
እንደዚህ ሲሆን ደግሞ የመጀመሪያው “ጠላት” ሆኖ የሚነሳብን የራሳችን አዕምሮ ነው፡ ለምን በዚህ መንገድ ይመራናል? ለምን ይህን ያህል ጊዜ እንጠብቃለን? ለምን ትናንት ሳይደርስ ዛሬ ደረሰ? ለምን ይህን አደረገ? ለምን? ለምን? ለምን?
አእምሮውን “የጣለ” ወይም ለእግዚአብሔር ያስገዛ ከጠሪው ሐሳብ ጋር ተስማምቶ ይሄዳል፡ እንዲህ አይነት ሰው አእምሮው ከሚነግረው ነገር በላይ እግዚአብሔር የነገረውን ያምናል፡ እንደዚህ አይነት ሰው ሁኔታዋች ከሚነግሩት በላይ የጠራው እግዚአብሔር የሚነግረውን ይቀበላል፡፡
ይሄ ታዲያ realityን ወይም ያለንበትን ሁኔታ መካድ ሳይሆን ከሁንኔታችን በላይ የሆነውን እርሱን በሁኔታችን ውስጥ መስማት ማለት ነው።
ብዙ ጊዜ አእምሮአችን ከሁኔታዎች ጋር ወይም ከሚታየውና ከሚሰማው ጋር መጋባት ብቻ ነው የሚፈልገው፡ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ደግሞ እግዚአብሔር የሚለውን መስማትና በሚናገረው ላይ የእምነት ርምጃ መውሰድ በጣም ፈታኝ ነው፡ እነዛ የተደበቁት “ለምን?” “መቼ?” “እንዴት?” የሚሉት ጥያቄዎች ተግተልትለው ይወጣሉ።
እምነት እግዚአብሔር የሚለውን መስማት እንጂ አእምሮአችን የሚለንን መስማት አይደለም: ይሄ የሚከብድ አባባል እንደሆነ አውቃለሁ ነገር ግን አናሻሽለውም።
በሰማርያ ርሃብ በነበረበት ጊዜ እግዚአብሔር “ነገ እንዲህ ይሆናል” ብሎ ለንጉሱ መልካም ነገር ተናገረ፡ ሆኖም ግን ንጉሱ ይደገፈው የነበረው ሰው፦
“በውኑ እግዚአብሔር የሰማይ መስኮቶችን እንኳን ቢከፍት ይህ ይሆናል?”
የሚል አይነት ጥያቄ ጠየቀ፡
ከእርሱ አቅጣጫ እውነቱን ነው፡ ችግሩ የከፋ ስለነበረ አእምሮው የለመደው ያንን ነው፡ ከዛ ውጭ ማሰብ አይችልም፡ ነገር ግን በእንደዛ ሰማርያን ባናወጠ ችግር ውስጥ እግዚአብሔር የተናገረውን መስማት ብቸኛው መድሃኒት ነበር፡፡
ከሁኔታውና አእምሮአችን ከሚነግረን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር የሚናገረው አንድ ነገር ይበልጣል።
ከፊታችን ካሉት የኤርትራ ባሕር፣ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ የኢያሪኮ ቅጥር፣ ጎየልያድና የሰናክሬም ዛቻ ይልቅ እግዚአብሔር የሚለን አንድ ነገር ያረጋጋናል።
ደግሞ በልጁ አንድ ጊዜ ተናግሮናል በዚህ ንግግር ላይ ጸንተን እንቆማለን፡ የጠራቸውን ያከብራቸዋልና በመንገድ በቃሉ እንበረታለን።
ሰማርያ በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ልትሆን ትችላለች ነገር ግን እግዚአብሔር ከተናገረ ማመን ያለብን ያንን ብቻ ነው።
ትንሽ ያወቅን ሲመስለን ግን ይሄ መንገድ ከባድ ነው። የሚያድነን እግዚአብሔር የሚለን እንጂ እኛ የምናስበው አይደለም፡ ስለዚህ የሚያድነን መታመኑ እንጂ መፈላሰፉ አይደለም። ብዙ ጊዜ ስሜታዊው አእምሯችን ይፈትነናል። እንኳ እግዚአብሔር የሚለንን ለመስማት ወደ እግዚአብሔር ለመፀለይ እንኳ ይፈትነናል።
ላለመፀለይ እንቅፋት ከሚሆኑ ነገሮች መካከል "እውነት እግዚአብሔር ፀሎትን ይሰማል?" እያለ የሚሞግተን ጭንቅላታችን አንደኛው ነው:
በእግዚአብሔር ታመኚ ነፍሴ፣ በእግዚአብሔር ታመኚ ተይ አታውኪኝ፣ ተይ አትጨቅጭቂኝ፣ ተይ ጌታሽን አጠርጥሪው።
እግዚአብሔር ፀሎትን ይሰማል ይመልሳልም::
#በቃሉ_ላይ_መቆም_ይብዛልን።
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ሁለት ጊዜ ይኼንን ሊንክ ይንኩ 👉 @biruk351
እናመሰግናለን🙏
የእግዚአብሔር ሰው በብዙዎቹ ሕይወት ውስጥ መለኮታዊ መነቃቃት እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆን ነው! በሰዎች ልብ ውስጥ የኢየሱስን የፍቅር ትኩሳት የሚለቅቅ ፣ ከአለማዊነት የሚያላቅቅ ፣ ከባዶነት ከብቸኝነት የሚያወጣ እልፍ ሰራዊት አርጎ የሚያሰልፍ: አንድ ሰው አሁንም በየዘመናቱ መንፈሳዊ አለም ላይ አሁንም ይፈልጋል!! አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ሲቆም ከእውነት ጋር ሲሰለፍ እልፍ ትውልድ ይዞ ይወጣል።
ይኼ ሰው የፀሎት ሰው ነው ፣ ይኼ ሰው የንባብ ሰው ነው ፣ ይኼ ሰው የአላማ ሰው ነው ፣ ይኼ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ባለው ግንኙነት ልባዊ ሰው ነው.. ይኼ ሰው እግዚአብሔር ሊገልጥ ስላለው የዘመኑን ሀሳብ ለማወቅ በጥልቀት እየተዘጋጀ ያለ ሰው ነው!
ይኼ ሰው በላው ጠጣው፣ ተማርኩ ተመረኩ፣ አገባው ወለድሁ ፣ቤት ሰራው ኖርኩ መባልን እጅግ ይፈራል!!! ይኼ መኖር መስሎ አይታየውም እንደውም እንደዚሁ እቀጥል ይሁን እያለ ይፈራል...እንደውም እንደዚህ ከመኖር ብሞት ይሻለኛል ይላል!፣ በእኔ ውስጥ ያለው የእግዚአብሔር ሕይወት በሆኑ ሰዎች ላይ ተፅዕኖ አሳድሮ ተማርከው ካለየው ብሞት ይሻለኛል ይላል! የደመ-ነብስ ኑሮ የእንስሳት ኑሮ መኖር አልፈልግም.. መኖሬ መኖር የሚያሰኘው የአንተ ሕይወት ሲገለጥ ሳይ ነው የሚል የነፍስ ሲቃ አለበት..... ይኼ ሰው ብፁዕ ሰው ነው፣ ይኼ ሰው ጌታው በቤቱ ላይ ታማኝ አርጎ የሚሾመው የተባረከ ሰው ነው፤ ይኼ ሰው በመንፈሳዊና ሰማያዊው አለም የተማረከ ነው🙏
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ይንኩ 👉 @biruk351
እናመሰግናለን 🙏
'' #ኢየሱስን_ምን_ፈልገን_ተከተልነው_ ! ?
የጌታን መንገድ ለመጥረግ የተላከው መጥምቁ ዮሐንስ ጌታችን ኢየሱስ ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እነሆ የእግዚአብሄር በግ በማለት ለደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስን አስተዋወቃቸው ። ሁለቱም ደቀ መዛሙርት የዮሐንስን ምስክርነት ሰምተው ኢየሱስን ተከተሉት ፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ ፦
በነገው ደግሞ ዮሐንስ ከደቀ መዛሙርቱም ሁለት ቆመው ነበር፥ ኢየሱስም ሲሄድ ተመልክቶ፦ እነሆ የእግዚአብሔር በግ አለ።
ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ሲናገር ሰምተው ኢየሱስን ተከተሉት። (ዮሐንስ 1፥35-37)።
ነገር ግን ጌታችን ኢየሱስ በዮሐንስ ምስክርነት እርሱን የተከተሉትን ሰዎች ምን ትፈልጋላችሁ? አላቸው( ዮሐ 1:38) ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ይህን ያለበት ምክንያት እርሱን ለምን እንደሚከተሉት እንዲያውቁና ለመከተላቸው ትክክክለኛ ግብ እንዲኖራቸው ፈልጎ ነው ። ዛሬም ጌታ ኢየሱስ እርሱን የምንከተል እያንዳንዳችን ይህን ጥያቄ በየግላችን ይጠይቀናል ፡፡ እንዲህ ሲል ምን ትፈልጋላችሁ? (ዮሐ 1:38)።
ውድ አንባቢ ሆይ እኛስ ጌታ ኢየሱስን የተከተልነው የምንከተልበትስ ዓለማ ምንድን ነው ? በ4ቱም ወንጌላት ውስጥ ስንመለከት የተለያዩ #ሰዎች_ኢየሱስን_የተከተሉበት #ብዙ_ምክንያትና_ዓላማ እንደነበራቸው እናነባለን ፡፡ ለምሳሌ ፡ -
1ኛ/ ጌታ ታአምር እና ድንቅን ስለሚያደርግ የሚያደርገውን ተአምር ለማየትና ለማድነቅ (ማቴ 9፡33 )
2ኛ/ ጌታ ኢየሱስ ብዙዎችን ይመግብ ስለነበር የሚጠፋ እንጀራ ፍለጋ ዮሐ6፡25-29
3ኛ/ ጌታ ኢየሱስ ፈዋሺ ስለነበር የስጋ ፈውስ በመፈለግ (ማር 6፡53-6) … ወ.ዘ.ተ በመሰሉት ብዙ ምክንያቶች ሰወች ጌታን ተከትውት ነበር ። ሌሎች ደግሞ ኢየሱስ የዘላለም ህይወት እንደሆነ ገብቷቸው (ዮሐ 6:68-69)ተከትለውት ነበር ።
ዛሬም ብዙ ሰዎች ኢየሱስን እንከተላለን የሚሉበት ብዙ ምክንያቶችና አላማዎች ይኖራቸዋል ። ብዙዎች ለስጋ ፍላጎት ኢየሱስን ሲከተሉ የነበሩት ከእርሱ ጋር አልዘለቁም ዛሬም እንዲሁ ነው ። ከውስጥ ኢየሱስን የሚከተሉበት ምክንያት ሌላ ሆኖ የክርስትናን ጉዞ ጀምረው የውስጥ ማንነታቸው ሲገለጥና ጭንብላቸው ሲገፈፍ ፥ያሰቡት የስጋ ፍላጎት ሳይሳካ ሲቀር ወደ ትፋታቸው ይመለሳሉ ።
ነገር ግን የሚከተሉትን ማንነትና የሚከተሉበትን አላማ አጥርተው ያወቁ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የህያው እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ያመኑት ጥቂት ቅሬታዎች ግን እስከ መጨረሻው ከእርሱ ጋር ጸንተዋል ፡፡
ለተከተሉት ሰዎች ምን ትፈልጋላችሁ ያለው የጌታ ቃል ዛሬም እያንዳንዱ ጌታን የሚከተል አማኝ ምላሺ ሊሰጥበት ይገባል ፡፡ ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሲከተሉትም አይቶ። ምን ትፈልጋላችሁ? አላቸው (ዮሐ.1:38 )።
በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተለኝማል፤ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም (ዮሐ.10:27-8) ።
ወዳጀ አንተስ ጌታ ኢየሱስን የተከተልክበት ምክንያትና ዓላማህ ምንድን ነው ? የእርሱን የእግዚአብሔር ልጅነትና ብቸኛ አዳኝነት አምነህ በእርሱ ብቻ የዘላለም ህይወት እንደሚገኝ ( ዮሐ 3:14-15 ;3:36 : 20:31 ) ተረድተህ ነውን ? ወይስ ለፈውስ ፣ ለተአምር ለሚጠፋ መብል ወይስ ለምድር ቅራቅንቦ ነው የምትከተለው ?
ይኼን ስል ኢየሱስ ለምድራዊ ነገራችን፣ ለጤናችን፣ ለሁኔታዎቻችን ግድ አይለውም እያልሁ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ! ከእርሱ ጋር እውነተኛ ሕብረት ስትጀምር ለእንዲህ ያሉ ነገሮች ብቻ ሳይሆን ግድ ይለዋል ብለህ ስለማታስባቸው ጥቃቅን ነገሮች እንኳ ጌታ ግድ ሲለውና ጣልቃ ሲገባልህ ታየዋለህ! ነገር ግን በእርሱ ከምን እንደዳንክ በነፍስ ወክፍ ላይ በእርግጥ ገብቶሃል? ደሞስ ምንስ ባይሰጥህ እወድሃለሁ አሁን በእጄ ከሌለው ይልቅ የሰጠኸኝ ሕይወት ይበልጣል! ልስግድልህ እፈልጋለሁ ልትለው ትችላለህ?
(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6)
----------
67፤ ኢየሱስም ለአሥራ ሁለቱ። እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን? አለ።
68፤ ስምዖን ጴጥሮስ። ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ_
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ጽድቅህን_ተናገር
#ማለትም_በክርስቶስ_ከእግዚአብሐር እንዲያው ያገኘኽውን ለራስህ ተናገር እራስህንም በቃሉ እውነት_አበረታታ
➖➖➖➖➖➖➖
✍️ ወደ ሥራ ቦታ ስትሄድ፣ መኪና እየነዳህም ይሁን፣ የምግብ ሸቀጦችን እየገዛህ፣ ወይም ምግብ እያዘጋጀህ ቀኑን ሙሉ በዝምታ በትንፋሽህ ሥር “እኔ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ጽድቅ ነኝ፣ ለጻድቅ የሆኑት ቃል ኪዳኖች፣ በረከቶች እና ጥበቃዎች ሁሉ የእኔ ናቸው።” በል።
✍️ ይህንን በተደጋጋሚ በማወጅ በክርስቶስ ያለህን የጽድቅ ማንነት እንድታሳድግ ፍላጎትህን ለመቀስቀስ እፈልጋለሁ።
✍️ ብዙ አማኞች በህይወታቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ ጥሶ መውጣት አይተዋል፣ ያ ጥሶ መውጣት ግን ዘላቂ አይደለም። ለምን? ምክንያቱም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በመጀመሪያ ደረጃ ጥሶ መውጣትን አስችሏቸው የነበረውን የተቀበሉትን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አዋጅ ወይም መርሕ ረስተውታል።
ነገር ግን ብዙ አማኞች ይህ አዋጅ ሊሰረቅ እና ሊረሳ እንደሚችል አይገነዘቡም። በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስርዓት-አልባኝነት ለማስተካከል: ጳውሎስ በክርስቶስ ያላቸውን የጽድቅ ማንነት ወደ ማስታወስ ነበር የሄደው።
✍️ አንደዚህ አይነቱን ዘላቂ ጥሶ መውጣት ለማግኘት ጠንካራ እና ጠቃሚ የሆነው አንዱ መንገድ ከአሁን ጀምሮ በክርስቶስ ያለህን ጽድቅ መናገርህን መቀጠል ነው።
አንተ ስሕተትህንና ድክመትህን ስታይ፣ በውድቀትህም እጅግ ስትረበሽ: እግዚአብሔር ግን በአንተ ውስጥ ያለውን ልጁን ያያል : ማለትም በክርስቶስ የተነሳ በእግዚአብሔር የራሱ ፅድቅ ነህ።2ኛ ቆሮ5:21) ይህ አንተ ራስህን ከምታይበት የተለየ ነገር ነው።
ወዳጄ በድካምህ ምክንያት ራስህን ወደ መጥላትና በኩነኔ ከመታሰርህ በፊት ጠበቃ፣አማላጅ አሁን በሰማያት ስለ አንተ የሚታይ ሊቀካህናት እንዳለህ አስብና ትንፋሽህን ሰብሰብ አርገህ " እኔ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ፅድቅ ነኝ በል"፣ አሁን በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ነኝ በል። ድካምህን እያበረታታው ሳይሆን ድካምህን ማስወገድ የምችልበትን መንገድ እያሳየሁ ነው
✍️ውድ ወዳጄ፣ ስትጨነቅና ብዙ ነገሮች ትኩረትህን ለማግኘት ሲጮሁ በእስትንፋስህ ሥር በዝምታ “እኔ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ጽድቅ ነኝ” በል።
✍️ በጠዋት በቲቪ ደጆች ላይ አሰቃቂ ዜናዎችን ስትሰማ እና ለምትወዳቸው ሰዎች በማሰብ ልብህ በፍርሃት ስትያዝ, በእስትንፋስህ ውስጥ በዝምታ “በክርስቶስ እኔ የእግዚአብሔር ጽድቅ ነኝ” በል።
✍️ማንም በማያውቀው ሚስጥራዊ ሱስ በመገዛት ከባድ ፈተና ላይ እንዳለህ የሚሰማህ ከሆነም በትንፋሽህ ሥር በዝምታ “እኔ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ጽድቅ ነኝ።” በል።
✍️ ያንተ ድል ህሊናህ በክርስቶስ ያለህን የጽድቅ ማንነት ምን ያህል ያስባል ከሚለው ጋር በቀጥታ ይገናኛል። በሕይወትህ የበለጠ ጥሶ መውጣቶችን ማየትና ከሽንፈት በላይ የመኖር ኃይል ማግኘት የምትፈልግ ከሆነ፣ አንተ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ጽድቅ መሆንህን ተናገር! ጮክ ብለህ ያለ ምንም መጠራጠር ተናገር።
✍️ ከዚህ በፊት ከነበረው በላይ ከጭንቀትና ከፍርሃት ነጻ የሆነ፣ በድፍረትና በድል የተሞላ ሕይወት መኖር ትጀምራለህ!
ተሻግሮ ያሻገረ በግ፤
ሸልሞ ሚያከብር በማዕረግ፤
ክህነቱ ዘላለማዊ፤
ኢየሱስ ደጉ ሳምራዊ፤
አካሉ በደም እረጥቦ፤
ሰማይ ያስገባን አንግቦ፤
እልፈት በሌለው ክህነቱ፤
አወዳጅቶናል ከአባቱ።
ሊቀ ካህናት -(ዘማሪ አሸናፊ ገመዳ)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ_
#ወደ_ቴሌግራም_ቻናላችን_ይቀላቀሉ_ይታነፁ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ይንኩ👉 @biruk351 #ከወደዱት_ለወዳጆ_ሼር_ያድርጉ ❤
#እናመሰግናለን 🙏
የመገናኛው ድንኳን ክፍል 4
https://youtube.com/watch?v=6q0EALfeWSw&si=XVWMwViOk5JTHUHe
ነገ እሁድ ከ3:00- እስከ 6:30
የአምልኮና የትምህርት ጊዜ 👉 የማደሪያው ድንኳን
ከሰዓት ከ10:00-12:30 የስብከትና የፀሎት ጊዜ 👉 "ኢየሱስም በምኩራባቸው እያስተማረ.......በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕመም ሁሉ እየፈወሰ.. ይዞር ነበር" (ማቴ 9:35)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 👉ኪቶ ስታዲየሙ አጠገብ 👉 ለበለጠ መረጃ 0984970314
በወጣትነቴ በስጋ እዚሁ አለም በመምጣት ያገለገለኝን እግዚአብሔርን በማገልገሌ ደስተኛ ነኝ ❤
**የሚለቀቁ ትምሕርቶቾ ስብከቶቾ በኦዲዮና በፁህፍ እንዲደርሶት ይኼን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ** 👉👉👉👉👉@biruk351
አሁን የብዙ ጊዜ የስብከትና የፀሎት ልምምዳችን ጋር ሳላውቅ ልጋጭ ይሁን? እሺ እኔ በአንዳንዶች አማረኛ የተቀቡ ሰዎችን የአሰባበክ ስልት ላይ አፌን የከፈትኩ ይሁን? የኪዳናችን መሠረት ስነካካ የሚንገጫገጩ ካሉ: በቃ ከእኔ አይደለምና ታገሱኝ : ይኼን እውነት ከቃሉ ስናገር ወይ ትናደድብኛለህ ወይ ትወደኛለህ.. ከተናደድክም በእኔ ሳይሆን በቃሉ ተናደድ፡ እኔ በቃሉ ያለውን እውነት ነው የምናገረው..
አዲስ ቅባት መቀበል፣ አዲስ ኃይል መሞላት ፣ ተጨማሪ እምነት ማግኘት ፣ ሞገስ ማግኘት፣ ፀጋ ማግኘት፣ እጥፍ መንፈስ መቀበል.. እነዚህ በቀደመው ኪዳን የሰሩና ያበቃላቸው ርዕሶችና ልምምዶች ናቸው። ... እጥፍ መንፈስ ከኤልያስ ስለ መቀበል የጠየቀው ኤልሳዕ ነው. ሲጀመርም ኤልያስ ራሱ ሙሉ መንፈስ አልነበረውም : እንደ አዲስ ኪዳን አማኝ ሙሉ መንፈስ አለኝ. ከኤልያስ በአገልግሎትም በክብርም እበልጣለሁ .. አባባ ብዬ እፀልያለሁ፣ አባቴ ቅዱሱ ልጄ እሰምሃለው ይለኛል.. አእምሮ ውስጥ እንደ ኤልያስ መች የሞተ አስነሳህ እያልክ ይሆናል.. ሲጀምር ያን ያደረገው የእግዚአብሔር መንፈስ አሰራር እንጂ ኤልያስ አይደለም. ያ ከሆነ በእኔም የሞተ ሰው ሲነሳ አይቼአለሁ.. ወንጌል ስናገር ሰዎች ዳግመኛ ተወልደው ከሙት መንፈስነት ተላቀው ሕያው የእግዚአብሔር ልጆች ሲሆኑ: የመንፈስ ቅዱስን አሰራር አይቼአለሁ(ይኼ ከኤልያስ በእውነት ይበልጣል ወንጌል መናገር መላእክት እንኳ ያልተሰጣቸው የከበረ ሀላፊነት ነው: ለአንተ እንደ ቀላል ከሆነ ኢየሱስን የምትረዳበት መንገድ ነውና አልገረምብህም) .. ስለዚህ የሚበልጥ የክብር አገልግሎት ውስጥ ያለሁት እኔ መሆኔን በተጨባጭ ላስረዳህ እችላለሁ።
ይሁን እንጂ በእነዚህ ቀበፂ የተፈፀሙ ተስፋዎች ልብ አነውላኝ ርዕሶችን በመፍጠር "ዶሮን ሲያታልሏት አይነት" ጫወታን መስቀሉ አከባቢ የሚጫወቱ መዓት ቁማርተኞች አሉ።
አንተ ተሰማህም አልተሰማህም እነዚህ ነገሮች ተፈፅሟል: አንተ ረካህም አልረካህም እግዚአብሔር አብ ረክቷል!.. ግን ብዙ አማኞች በስጋዊነት ተይዘው አይ ቃሉን ባርመው ጥሩ ነው #ታግተው የጠፉ ምርኮኞች መስለዋል፣ ስለዚህ ለእነዚህ ርዕሶችና ፀሎቶች ታልፈው ተሰተዋል። እናም የእንቁልጭልጭ ወይም የሞኞት ኑሮ ነው የሚኖሩት. አንድ ቀን ጌታ ሲፈውሰኝ ፣ አንድ ቀን ጌታ ሲባርከኝ ፣ አንድ ቀን ጌታ ኃይል ሲሰጠኝ ፣ አንድ ቀን ቅባቱን ሲሰጠኝ... አንድ ቀን ፣ አንድ ቀን...ኤጭ! ይኼ ዱቤ ከፈለክ ነገ ና አይነት ተስፋ አስቆራጭ አስተሳሰብ ነው። ሁሉም ነገር አሁን ያለና የዛሬ 2000አመት ተፈፅሞ ለአንተ እንዲሁ በፀጋ የተገባ ሆኖ የቀረበ ነገር ነው። አንተ አሁን በብዛት ከውጭ የምትፈልገው ነገር እግዚአብሔር ኢየሱስ በሚባል አካውንት ውስጥ ለቆቷል ፣ ስታምን ለአንተ ሆኖ ተቆጥሯል.. አሁን አንተ የሚጠበቅብህ ጥቂት የእምነት ሕጎች(ሰነዶችን) ማወቅ ነው። ለአንተ አይገባህም ነበ፡ እግዚአብሔር ግን ከፀጋው ባለጠግነት የተነሳ የተገባ አረገው፣ እናም ለመጠቀም ቃሉ የሚልህን እውነቶች እውቅና መስጠት ይኖርብሃል።
ሁሉም እየተራበ ነው ያለው: ጌታ ሆይ ንከን፣ ጌታ ሆይ መንፈስህን አብዛ፣ ጌታ ሆይ ቀባን፣ ጌታ ሆይ ተነሳ ጠላቶችህን በትናቸው ኃይልህን ልቀቅ.. ይኼ የቡሊይ ሰዎች የፀሎት አቀራረብ ነው። በፍጹም የአንተ ልታደርገው አትችልም! እግዚአብሔር በዚያ መንገድ ይሰራ ነበርና በዚያ መንገድ መፀለይ ነበረባቸው። አሁን እግዚአብሔር የምትቀሰቅሰውና በፀሎትህ ጫና የምታደርግበት አይደለም! ያለ ምንም ያለ አንተ አስተዋጽኦ በኢየሱስ ተንቀሳቅሷል።
ይኼን ስል እኔ አሁን የመነቃቃትና የመንፈስ ቅዱስ እንስቅስቃሴ ተቃራኒ ነኝን? ይኼን እግዚአብሔር ከእኔ ያርቀው! እንደዛ አይደለም። ፈዘናል፣ ኃይል የሌለው መስለናል፣ መነቃቃት ያስፈልገናል. ግን እግዚአብሔርን ተነሳ ፣ ተንቀሳቅሳ ፣ ቀባና ና ስራ በማለት አይደለም። አሁን ፀሎትህ አዲስ ነገር እንዲሰራ አይደለም ፣ እንደ አማኝ ከእግዚአብሔር የሆነ ነገር ለማግኘት መታገልህን መጀመሪያ አቁም! በእውነት ኢየሱስ በሚባለው ማንነት ውስጥ እግዚአብሔር ሁሉን የተስፋ ቃል ፍፃሜ እንደሰጠ ታምናለህ ወይ? ከቃሉና ከመንፈሱ ጋር በግልህ የማትቆይ ከሆነ ተባራሪ ስብከትና ልምምድ በነፍስህ ክፍልህ ሕያው ይሆንና ለቃሉ እንኳ ጆሮህን ትዘጋለህ። የምትፈልገው የትኛውም ነገር አሁን እግዚአብሔርጋ የለም ስለ ኃጢአታችን ሳይራራ በሰጠው ጊዜ የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ ከእርሱ ጋር እንዲያው ሰጠ! እግዚአብሔር እንደ ሰው የሚታይ የሚዳበስ የሚፈተሽ ቢሆን "እናቴ ትሙትን" ማለት የምሬን ነው እንዴት በቃላት ልግለፅ 👉 እግዚአብሔር ባዶ እጁን ነው ያለው! ክርስቶስ ውስጥ ሁሉን ሀብቱን መዝገቡን አስቀመጠ። ያንን አማኞች ማስተዋል ያቃተን.. እርሱ ከበቂም በላይ ነው! አሁን እግዚአብሔር ጋር ለአዲስ ነገር መታገላችንን አቁመን: ይልቁንም በክርስቶስ የተሰጠንን ነገር ለማወቅ በሙሉ ልብ መራብ መጠማት ይኼ እውነት አይናችን ተከፍቶ እስኪገለጥ መፀለይ፣ እርሱ ወደሚናገረን እውነት መጥለቅ ፣ ማውጣትና ወደ አካላዊ አለም ማፍሰስ አለብን። እግዚአብሔር እንዲሰራ የመጎትጎት ሳይሆን የተሰራው ስራ እንዲገለጥ ራስህን የመጎትጎት ይሆናል ማለት ነው፣ እግዚአብሔር ምንም የሚያደርገው ነገር የለም እርሱ አስቀድሞ አድርጓል አንተ ነህ በመንፈስ ቅዱስ በኩል ለዚህ እውነት አዎንታዊ ምላሽ የምትሰጠው! እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛም እንወደዋለን እንደሚለው ማለት ነው።
ይኼ እንዴት ይሆናል? ብታምን ይሆናል መንፈስ ቅዱስ በአንተ ውስጥ አለ፣ የልዑል ኃይል ይኼ እውነት ከውስጥ ወደ ውጭ እንዲፈስ ያደርጋል!!
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ይንኩ👉@biruk351
