ልሣነ አምሐራ ሚዲያ
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ፈጣንና ወቅታዊ የአማራ ፋኖ እለታዊ ዘገባዎች እንድሁም ፈጣን ዜናዎች ይቀርባሉ። ለማንኛውም ጥቆማ በ @lisaneamhara ያናግሩን‼️
Show more1 970
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-3430 days
Posts Archive
1 970
#ሰበር ቪዲዮ ከወሎ!
#የጄ/ል አሳምነው ፅጌ ጓደኛ የነበረው አርበኛ ዋኘው!
#መኪናውንም፣ ልጁንም ይዞ ወደ ጦር ግምባር ወረደ!
https://www.youtube.com/watch?v=QWgjPTRzeCg
1 970
ከእነ ሙሉ ትጥቁ ፋኖን ተቀላቀለው የፖሊስ አዛዡ ሳጅን ተመስገን አለሙ ከመረብ ሚዲያ ጋር ባደረገው ቆይታ፦
"ቤተ ክርስትያን ቆመን እንኳን ህዝቡ ደና አደራችሁ አይለንም: እኛ ስንልም ዝም ይሉናል።
ባጃጅ የሚያሳፍረን የለም፤
ውጊያው ወቅት ቆስለን ሕዝቡ መጥቶ ሌላውን አንስቶ እኛን ይተወናል። እናንተማ ባበላናቹህ እጃችን ክዳችሁናል ይሉናል።
ቤተክርስቲያን ቁመን ቤተክርስቲን የመጡት ከአጠገባችን እነሱን አጥፋለን ብለው ሲጸልዩ እንሰማለን በአጭሩ ህዝባችን ጠልቶናል"
ሙሉ ቪዲዮውን ይመልከቱ👉
https://www.youtube.com/watch?v=GSac63kuWko
1 970
ታላቅ ጀብድ ሰከላ ግዮን ብርጌድ
በዛሬው ዕለት በቀን 03/07/2017 ፋኖ አለምነህ ፈጠነ የተባለ የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ኛ ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር የግዮን ብርጌድ አባል ወደ ሰከላ ወረዳ ግሽ አባይ ከተማ ብቻውን ዘልቆ በመግባት 2 የአገዛዙን ወታደር ገድሎ እና 2 አቁስሎ አንድ ጥቁር ክላሽ መማረክ ችሏል። ጀግናው ፋኖ አለምነህ ፈጠነ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስበት ታላቅ ጀብድ በመስራት የፋኖን ድንቅ ብቃት አሰመስክሯል።
1 970
ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ደፈጣ በመያዝ የአገዛዙ ሎሌዎችን አመድ አድርጋለች ከአዲስቅዳ ወደ አሸዋ ጉዞ ሴረግ የነበረ ዲሽቃ የጫነ 1 ፓትሮል በኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ልጆች አሸዋ ላይ በደፈጣ ሲመታ መኪናዋ ተገልብጣ 6 ሰዎች ወደ ላይኛዉ ሲላኩ ዲሽቃዉ ከጥቅም ዉጭ ሁኗል ሲል የብርጌዱ ጦር አዛዥ መቶ አለቃ ለአለም ገልፀዋል
1 970
ጠላት ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል!!!
ዛሬ በቀን 30/06/2017 ዓ/ም ለሊት 12:00 ስዓት ጀምሮ የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገው ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፪ ተርቦች ባደረጉት የተጠና ልዩ ኦፕሬሽን ብዛት ያለዉ ወራሪ የብርሀኑ ጁላ ጦርን ጨምሮ ገዘኸራ ቀበሌ ላይ የነበረዉ ተመክሮ አይድን ባንዳ አዛይ አድማ ሚሊሻ'ና ፖሊስ ሰራዊት ከእነ ተተኪ ባንዳ አዲስ ምልምል ሰልጣኞቻቸዉ ሙሉ በሙሉ እንዲደመሰሱ ተደርጓል።
ይህ ከቀናት በፊት ከእየ ቦታዉ ተለቃቅሞ ወደ ፋ/ለ/ወረዳዋ የገጠር ከተማ ገዘኸራ ገብቶ የነበረ የጠላት ሀይል ዛሬ በቀን 30/06/2017 ዓ/ም ህዝቡን ከቤተ ክርስቲያን መልስ በማስገደድ ገዘኸራ ላይ ብልፅግናን የሚደግፍ ፋኖን የሚያወግዝ ሰልፍ ለማድረግ አስቦ ሰፊ ስራ እየሰራ የነበረ ሲሆን ይህንን የጠላት እቅድ ቀድመዉ ያወቁት የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ዋና ጦር መሪ የመቶ አለቃ ለአለም ጌታነህ በሰጡት ስምሪት መሰረት ወደ ቦታዉ የተንቀሳቀሱት የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፪ ተርቦች ሰልፍና ስብሰባህ ከህዝባችን ጋር ሳይሆን ቀደም ሲል በዚህ ብርጌድ ከተሸኙት አለቆችህ ከእነ ሞገሴ እና ብዙ መሰሎቻቸው ጋር ይሁን ሲሎ ሰባ ሶስቱን የጠላት ሙጃ ሰራዊት ወደ ማይመለስበት ሸኝተዉታል።
ይች በሀምሳ አለቃ ማስተዋል ታደለ ሀምሳ አለቃ ፈንታሁን እና ፋኖ ዘመን አዲስ እየተመራች ጎህ ሳይቀድ ገዘኸራ ቀበሌ ገብታ የተሰጣትን ግዳጅ በብቃት አሳክታ በለሊት ልብ የሚያሞቅ ብስራት ያደረሰችን ተርብ ሻለቃ ከዚህ ቀደም ከ31 ጊዜ በላይ ወደ ቀጠናዋ ተንቀሳቅሶ ከነበረ የጠላት ሀይል ጋር ተፋልማ 31 ጊዜ ሁሉ ከፍተኛ ድል ከማስመዝገቧ በተጨማሪ በክፍለ ጦራችን ስር ከሚገኘዉ ማለትም ከአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በዳንግላ ከተማ የቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ጋር በመናበብ በዳንግላ ወረዳ ጫራ ጊሳና ባርባሺ አካባቢዎች ሰፍሮ የነበረ ጠላትን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት በቀን 28/4/2017 ዓ/ም ጊሳ አካባቢ ከ100 በላይ የጠላት ጦር የተደመሰሰበትን ኦፕሬሽን ጨምሮ ብዙ ግዳጆችን በታላቅ ጀብድ ያሳካች የብርጌዷ ፈርጥ ናት።
ጠላት ተጨማሪ ጦር ከአዲስ ቅዳም ከተማ ማንቀሳቀስ አስቦ የነበረ ሲሆን የብርጌዷ ዋና ጦር መሪ መቶ አለቃ ለአለም ጌታነህ የመሩት የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፩ እረመጥ ጦር ከአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በሳትማ ዳንጊያዉ የቀኛዝማች ስሜነህ ደስታ ብርጌድ ግስሎች ጋር በመናበብ አዲስ ቅዳም ከተማ ድረስ በመግባታቸዉ ጠላት አድጓሚ ተራራ ምሽጉ ዉስጥ ተወስኖ በእዉር ድንብር ተኩስ ሞርተር'ና ዙ23 ብቻ እየወረወረ በአለበት ቀዝቅዞ እንዲቀመጥ ተደርጓል።
ይህ የቀዘቀዘ የጠላት ጦር አድጓሚ ተራራ ላይ ተቀብሮ በወረወረዉ የሞርተር ቅንቡላ ዛምበላ ቀበሌ ላይ ህፃን ቀረብሽ አዲሱ የተባለች ህፃንን ጨምሮ የተወሰኑ ግለሰቦች ከባድ'ና ቀላል የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
እንዲሁም በምዕራቡ አቅጣጫ በእየቦታዉ የወደቀዉን የጠላት ጦር ሰባዊነት አስገድዷቸዉ ለመቅበር በወጡ የገዘኸራና አካባቢዋ ማህበረሰባችን ላይ ከሞት የተረፈ ቁስለኛ የጠላት ሀይል በከፈተዉ የእሩምታ ተኩስ 3 ንፁሀን ወገኖቻችን በግፍ ሲረሸኑ ብዙዎች ቁስለኛ ሁነዋል።
በሌላ በኩል ጫራን አቋርጦ ወደ ገዘኸራ ሊገባ የነበረዉ ጠላት በአማራ የብረት በሮቹ የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ትንታጎች በለሊት በመዉጣት መንገዱን እሾህ ስላደረጉበት የገዘኸራ እቅዱን ዳንግላ ላይ ሁኖ እንዲያኝከዉ ተገዷል።
አጠቃላይ በዛሬዉ የለሊት ኦፕሬሽን እስከ ጥዋት 1:30 ድረስ የተረጋገጠ 29 ክላሽንኮፍ መሳሪያ የተገኘ ሲሆን ከ73 በላይ የጠላት ሀይል እስከወዲያኛው ሲሸኝ የተወሰነ ቁስለኛ በምርኮ ተይዟል።
ከሞተ ከቆሰለና ከተማረከ የጠላት ሀይል ዉስጥም አብዛኞቹ የአድማ ምሊሻ እና ፖሊስ አባላት መሆናቸዉን ማረጋገጥ እንደተቻለ የሻለቃዋ ህ/ግንኙነት ፋኖ ሰናይ ፀጋ ከቦታዉ አረጋግጦልናል።
ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙነት
ይበልጣል የዉነቱ የክ/ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ
