1 167
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-1930 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
February '26
February '26
+1
in 0 channels
January '26
+5
in 0 channels
Get PRO
December '25
+5
in 0 channels
Get PRO
November '25
+4
in 0 channels
Get PRO
October '25
+5
in 0 channels
Get PRO
September '25
+8
in 0 channels
Get PRO
August '25
+16
in 0 channels
Get PRO
July '25
+30
in 3 channels
Get PRO
June '25
+42
in 0 channels
Get PRO
May '25
+24
in 0 channels
Get PRO
April '25
+42
in 1 channels
Get PRO
March '25
+34
in 1 channels
Get PRO
February '25
+107
in 0 channels
Get PRO
January '25
+794
in 0 channels
Get PRO
December '24
+295
in 0 channels
Get PRO
November '24
+933
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 20 February | 0 | |||
| 19 February | 0 | |||
| 18 February | 0 | |||
| 17 February | 0 | |||
| 16 February | 0 | |||
| 15 February | 0 | |||
| 14 February | 0 | |||
| 13 February | 0 | |||
| 12 February | 0 | |||
| 11 February | 0 | |||
| 10 February | 0 | |||
| 09 February | 0 | |||
| 08 February | 0 | |||
| 07 February | +1 | |||
| 06 February | 0 | |||
| 05 February | 0 | |||
| 04 February | 0 | |||
| 03 February | 0 | |||
| 02 February | 0 | |||
| 01 February | 0 |
Channel Posts
ሰበር ዜና!
31 የአገዛዙ ወታደሮች ሁለት የቡድን መሣሪያ እና 29 ክላሽ ይዘው ፋኖን ተቀላቀሉ!
ኦህዴድ መሩ የብልፅግና ቡድን ስልጣኔን ይጠብቅልኛል ብሎ ያሰማራው ኃይል፡ "ማን ሞቶ የማን ስልጣን ሊፀና" በሚል ከነ ሙሉ ትጥቁ ከስምሪት ቀጠናው በመጥፋት ፋኖን እየተቀላቀለ መሆኑን መረብ ሚዲያ ተመልክቷል።
የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩ 31 ወታደሮች ሁለት የቡድን መሣሪያ እና 29 ክላሽ እንደያዙ ዛሬ ህዳር 13/2018 ዓ/ም ፋኖን ተቀላቅለዋል።
ወታደሮቹ የተቀላቀሉት በአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ ኮር2 ዞብል አምባ ክ/ጦርን ሲሆን፡ በክፍለጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸውም ዕዙ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ብልፅግና በሕግ ማስከበር ስም በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፅመውን ጭፍጨፋ በመቃዎም ከስምሪት ቀጠናቸው ጠፍተው የወጡት 31 የሰራዊት አባላቱ፡ አንድ ብሬን እና አንድ ስናይፐር እንዲሁም 29 ክላሽንኮቭ መሣሪያ ከነ ሙሉ ትጥቁና ተተኳሹ እንደያዙ ነው ፋኖን የተቀላቀሉት።
ጀምበር የጠለቀችበት የብልፅግናው አገዛዝ፡ ስልጣኑን ለማቆየት የደሃ ልጆችን በግዳጅ እያፈሰ ከሁለት ወራት ያልዘለለ ወታደራዊ ስልጠና በመስጠት በአማራ ክልል ያሰማራ ቢሆንም፡ ነገር ግን ሰራዊቱ እናቶቻችን ላይ እጃችንን አናነሳም በሚል ከነ ሙሉ ትጥቁ በገፍ ወደ ፋኖ መግባቱን ቀጥሏል።
| 2 | የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ በሁለት ግንባሮች በጠላት ላይ ድል ተቀዳጅቷል ።
1/ የትመን ንዑስ ከተማ እና ማህበርብርሃን ቀበሌ ሰረጎ በመግባት ጥቃት ተሰንዝሯል!!
የአ.ፋ.ብ.ኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 8ኛ በላይ ዘለቀ ክ/ጦር አባ ኮስትር ብርጌድ በየትመን ንዑስ ከተማ የትመን የመጀመረያ ደረጃ ት/ቤት መሽጎ የሚገኜው የአረመኔው አገዛዝ ቅጥረኛ የሚኒሻ አባላት ጳጉሜ 03/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 5:00 ሰዓት ሰርጎ በመግባት በF1 ቦንብ መድረሻ ሲያሳጣው አድሯል።
አባ ኮስትር ብርጌድ በየትመን ከተማ የመሸገውን የአረመኔው አገዛዝ ይጠቀምበት የነበረውን ሁለት ኮፒውተር እና የተለያዩ ማቴሪያል በማውጣት የአረመኔው አገዛዝ ቅጥረኛ ሰራዊትን ሙት እና ቁስለኛ አድርጓል። በዚህ የተበሳጨው የአረመኔው ሰራዊት ተጨማሪ ኃይል በማስገባት በእነማይ ወረዳ የፈለገ ሰላም ቀበሌ/ዘብች እየሱስ የንፁሃን አርሶ አደሮችን አንድ በሬ እና አንድ ላም በመዝረፍ እንዲሁም ማህበረሰቡ ይጠቀምበት የቀበሌ ሰነድ አቃጥሎ ወደ መጣበት ቦታ እግሬ አውጭኝ ብሎ ፈርጥጦ ሄዶል።
ከደጀን ከተማ ወደ ቢቸና ከተማ የአገዛዙ ካዲሪዎችን በዙ 23፣ብረት ለበስ ፔንፔ እና የቡድን መሳሪያዎች በመያዝ አጅቦ ይንቀሳቀስ የነበር የአረመኔው ሰራዊት ጵጉሜ 04/2017 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ዲቢሳ ቀበሌ አባ ኮስትር ብርጌድ ደፈጣ በመጣል ሙት እና ቁስለኛ አድርጓል ።
2/ ወምበርማ ብርጌድ የተሳካ ጥቃት ፈፀመ‼
አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴውድሮስ ዕዝ ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም 5ኛ ክፍለ ጦር የወምበርማ ብርጌድ ከጥዋቱ 1:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 7:00 ሰዓት የአረመኔው ስርዓት ወንበር ጠባቂዎችን ልዩ ስሙ ኮኪ መገንጠያ ላይ ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
አይበገሬዎቹ የወምበርማ ብርጌድ ንስር ሻለቃ፣ ቆምጠው ሻለቃ እና ነበልባል ሻለቃ በጋራ በመሆን ወደ ወገዳድ ኮኪ መገንጠያ ላይ የአረመኔውን ጦር አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት በርካታ ወንበር ጠባቂዎች ወደ ላይኛዉ ሲሸኙ ቀሪዎችነሰ ቁሰለኛ በማድረግ ቀጥተውታል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ! | 345 |
| 3 | No text... | 340 |
| 4 | የሻምበል አዛዡ የሻለቃ አዛዥ የሆነ የበላይ አመራሩን ገድሎ ፋኖን ተቀላቀለ!
በራያ ቀጠና በርተክላይ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ተመድበው ከነበሩ የፌደራል ፖሊስ አባላት መካከል ሳጅን ኤፍሬም ከበደ የተባለ የሻምበል አዛዥ የሻለቃ አዛዥ የሆነ የበላይ አመራሩን ገድሎ ፋኖን መቀላቀሉን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
የሻምበል አዛዡ፡ የሻለቃ አዛዥ በሆነው የበላይ አመራሩ ላይ ግድያውን ከፈፀመ በኋላ ለቀናት በእግሩ ተጉዞ አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝን የተቀላቀለ ሲሆን፡ የዕዙ ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ ምክትል ኃላፊ በሆነው በአርበኛ ኮማንዶ ጌታቸው ሲሳይ የተመራ ልኡክ ደማቅ አቀባበል እንዳደረገለት ታውቋል።
ግድያው የተፈፀመበት በፌደራል ፖሊስ 5ኛ መምሪያ ስር የ1ኛ ሻለቃ አዛዡ፡ አስከሬኑ ወደ አላማጣ ተወስዶ ስርዓተ ቀብሩ እንዲፈፀም ተደርጓል ነው የተባለው።
የሻምበል አዛዡ ሳጅን ኤፍሬም ከበደ፡ የሻለቃ አዛዡ የሆነው የበላይ አመራሩ "በንፁኋኖች ላይ የሚፈፅመውን ግፍና በደል ቆሜ ማየት ስላልቻልኩ እርምጃውን ወስጄበታለሁ" ሲል ቃል በቃል ተናግሯል።
በ5ኛ መምሪያ ስር የ1ኛ ሻለቃ አዛዡ የአከባቢው ነዋሪዎችን በጅምላ በማሰር ከ50 ሺ ብር ጀምሮ እስከ አንድ መቶ ሺ ብር የሚቀበል ሲሆን፡የተጠየቀባቸውን ገንዘብ መክፈል ያልቻሉትን ደግሞ "የፋኖ ደጋፊ ናቸው" በሚል አንዳንዶቹን ይገድላል፡ አንዳንዶቹን ደግሞ "ለፋኖ ስንቅ ሲያቀብሉ እጅ ከፈንጅ የተያዙ ናቸው" በሚል አላማጣ ከተማ ለሚገኘው ለሪፐብሊካን ኮማንዶ ክ/ጦር አሳልፎ ይሰጣል ሲል ነው እርምጃውን የወሰደው የሻምበል አዛዥ የተናገረው።
የሻለቃ አዛዡ በተጨማሪም፡ በአከባቢው ልጃገረዶችን ጨምሮ የአባወራ ሚስቶችን ወደ ካምፕ እያስመጣ የአስገድዶ መድፈር ድርጊት ይፈፅም እንደነበር ተነግሯል።
ይሄንን ግፍና በደል ቆሞ መመልከት ያልፈለገው በሻለቃዋ ስር የአንድ ሻምበል አዛዡ ሳጅን ኤፍሬም ከበደ፡ በግፈኛው የሻለቃ አዛዥ ላይ ነፃ እርምጃ በመውሰድ ከነ ሙሉ ትጥቁ ፋኖን መቀላቀሉን ነው መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው።
የሻምበል አመራሩ ሳጅን ኤፍሬም ከበደ እንደገለፀው፡ "የፅንፈኛ ደጋፊ ናችሁ" በሚል በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት ትጥቅ እንዲያወርዱ ተደርገው የተወሰዱበት ደብዛ ጠፍቷል፡ ስለታሰሩ አባሎች የትና እንዴት እንዳሉ የሚጠይቅ ደግሞ "አንተም የፅንፈኛ ደጋፊ ነህ" ተብሎ ለእስር ይደረግና የቀድሞዎቹ እጣ ፈንታ ይደርሰዋል ያለ ሲሆን፡ በርካታ የተቋሙ አባላትም ከእስርና ከእርሸና ለማምለጥ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በገፍ እየከዱ መሆኑን ተናግሯል።
ሳጅን ኤፍሬም ከበደ አክሎም፡ ሰራዊቱ ተመናምኗል፡ የቀረውም በተስፋ መቁረጥ ተሞልቶ ነው ያለው ያለ ሲሆን፡ በአሁን ሰዓት በአንድ ሻምበል ውስጥ ከ20 የማይበልጡ አባላት ብቻ ይገኛሉ፡ በአንድ ሻለቃ ስር ደግሞ የስታፍ አባላትን ጨምሮ 70 የማይሞሉ አባላት ይገኛሉ ሲል የፌደራል ፖሊስ ተቋም ምን ያህል ባዶ ቀፎውን እንደቀረ በዝርዝር አስረድቷል።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅ ለብዙዎች ተደራሽ ይሆን ዘንድ ሼር ያድርጉ!
https://t.me/MerebMedia24 | 327 |
| 5 | https://youtu.be/rH1xGf8re04?si=Lbo6ZikG0Ga79Qhq | 237 |
| 6 | No text... | 251 |
| 7 | አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ንጉስ ሚካኤል አሊ ኮር ሸዋንግዛው ክፍለጦር ከላላ ወረዳ ላይ ተጋድሎ በማድረግ ድል ተጎናፀፉ::
አፋብኃ ንጉስ ሚካኤል ኮር ሸዋንግዛው ክፍለጦር ከላላ ወረዳ ሻፊ ቀበሌ እና ቲርቲራ ከተማ በመግባት ጭምር ታላቅ ተጋድሎ በማድረግ በርካታ የጠላት ጥምር ጦር በመደምሰስ ታላቅ ጀብድ ፈፅመዋል::
ተጋድሎው ጳጉሜ 1/2017 ዓ.ም ከጧቱ 2:00-9:30 ድረስ የዋለ ሲሆን ሸዋንግዛው ክፍለጦር ተመም ሻለቃ እና ሁንያለው ሻለቃ ከላላ ወረዳ ዙሪያ ልዩ ስሙ ሻፊ የተባለ ቦታ ላይ በርካታ የጠላት ሃይል በመደምሰስና በማቁሰል ጠላትን ወደመጣበት መልሰውታል::
በተመሳሳይ በዚሁ ተጋድሎ ሸዋንግዛው ክፍለጦር ሁንያለው ሻለቃ ቲርቲራ ከተማ ዘልቆ በመግባት አንድ ጓድ የጠላት ሃይል ላይ ጥቃት በመፈፀምና በመደምሰስ ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ጠላትን ወደመጣበት በመመለስ ድል ተጎናፅፈዋል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም | 255 |
| 8 | https://youtu.be/P5wbN8Hk2lI?si=-MVpuW0iMrS4MoJO | 258 |
| 9 | አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ
ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር
ጉና ክፍለ ጦር/መቅደላ አምባ ብርጌድ/ናደው ሻለቃ
ጳጉሜ 01/2017ዓ.ም
የአገዛዙ አራዊት ሠራዊት መነሻውን ደብረ ታቦር ከተማ አድርጎ ወደ እሥቴዋ መዳረሻ መካነ ኢየሡሥ ከተማ እየተንቀሳቀሰ እያለ ''አቄቶ'' የተባለ ቦታ ላይ ጥበበኛው የጥበብ ልጅ የታላቁ ጉና ክፍለ ጦር አካል የሆነው መቅደላ አምባ ብርጌድ/ናደው ሻለቃ በፈጸመችው የታቀደ የደፈጣ ውጊያ በጠላት ላይ ከፍተኛ ድልን ተቀዳጅታለች። በዚህ የደፈጣ ውጊያ በቁጥር 13 ሢደመሠሥ 07 የሚሆኑት ቁሥለኛ ሆነዋል። ከተደመሰሱት የጠላት አካላት መሐከል አገዛዙን ምሕረት ጠይቀናል ብለው ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተሐድሶ ወሥደው ከጎንደር-ደብረ ታቦር-እሥቴ ሢመለሡ ነው።
ድላችን በተባበረ ክንዳችን👊
ዝንተዓለም ዐምሐራ Forever Amhara
ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር
ኃቅአለው ፀጋ አለባቸው | 339 |
| 10 | አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፍብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ንጉስ ሚካኤል ኮር መብረቅ ክፍለ ጦር እና ሌሎች የኮሩ አሃዶች ጠላት መሸጐበት የነበረውን ምሽግ በመስበርና በመደምሰስ ታላቅ ድል ተጎናፀፈ::
ዛሬ ነሀሴ 29 2017 ዓ.ም መብረቅ ክ/ጦር ፣ንጉስ ሚካኤል ኮር ቃኝ ሻለቃ፣ ልጅ እያሱ ኮር ቤተ አምሓራ ክ/ጦር በጋራ በመሆን 105ኛ ክ/ጦር ልዩ ዘመቻ ብሎ በሚጠራቸው የአገዛዙ ወንበር ጠባቂዎች ላይ በወግዲ ወረዳ ማከፍታ ቀጠና ጠላት መሸጎበት የነበረውን ቦታ ሌሊት 11፡00 ሰዓት ከበባ በማድረግ በቦንብ ምሽግን እያጋዩ በመግባት 37 የብርሀኑ ጁላ ጦር መደሰስ ተችሏል።
ከዚህም ተያይዞ ጠላት አስከሬን ለማንሳት ከወግዲ ያለውን ሀይል አጠናክሮ ወደ ማከፍታ ለመግባት ሲሞክር ወልዮች ቀብር ከተባለ ቦታ ላይ ደፈጣ በማድረግ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ከ32 በላይ አስከሬን ማሳ ላይ ሳይነሳ ጥሎ የተመለሰ ሲሆን ማከፍታ የተደመሰሰው ሙትና ቁስለኛ በየጥሻው ወድቆ ለማንሳት እንኳ ማህበረሰቡ የተቸገረበት ሁኔታ ላይ ይገኛል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ነሐሴ 29/2017 ዓ.ም | 367 |
| 11 | https://youtu.be/O9S9nDgb-ts?si=4yvdFVSoxGFUEjCl | 310 |
| 12 | No text... | 366 |
| 13 | የአማራ ክልል ታርጋ ያላቸው ተሽከርካሪዎች በአዲስ አበባ ተንቀሳቅሰው ስራ እንዳይሰሩ መታገዳቸው ተገለፀ!
ተሽከርካሪዎቹ እስከ 50 ሺ ብር ድረስ ወጭ በማድረግ የአዲስ አበባ ወይም የኦሮሚያ ክልል ታርጋ እንዲያወጡ ተገደዋል ነው የተባለው።
ገዢው የብልፅግና ቡድን በአማራ ክልል ሕግ ማስከበር በሚል ስም የዘር ፍጅት ለመፈፀም የከፈተው ጦርነት ሁለት ዓመት አልፎታል።
ጦርነቱ ከተጀመረበት እለት ጀምሮ እስከ እሩብ ዓመት ድረስ የአገዛዙ ጦር ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ የነበረው የራሱ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ቢሆንም፡ ነገር ግን ከወደ ፋኖ በሚሰነዘረው ጥቃት እነዚህ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ለውድመት ተዳርገዋል።
በርካታ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎቹ የወደሙበት አገዛዙ፡ ይሄንን ችግር ለመቅረፍ በሚል በአማራ ክልል የተሰማራው ወታደሩ፡ የመከላከያ ሰራዊት ተቋም ንብረት የሆኑ ተሽከርካሪዎችን ከመጠቀም ይልቅ የግለሰብ ተሽከርካሪዎችን በማስገደድ እንዲጠቀም እንዲሁም የፋኖ ደጋፊ ናቸው ወይም ከመንግስት ጎን ቆመው ጦርነቱን በገንዘብ አይደግፉም የተባሉ ባለሀብቶች ንብረት የሆኑ ተሽከርካሪዎችን እንዲወርስ አቅጣጫ ካስቀመጠ አንድ ዓመት አልፎታል።
የአገዛዙ ወታደሮች ከበላይ አመራሮቻቸው በተሰጣቸው አቅጣጫ መሠረት፡ የግለሰብ ወይም የማህበራት ንብረት የሆኑ የደረቅ ጭነት እና የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎችን "ግዳጅ" በሚል በመያዝ ወታደሮቻቸውንና ወታደራዊ ንብረቶቻቸውን ከቦታ ቦታ ያንቀሳቅሱባቸዋል፡ በተጨማሪም በውጊያ ወቅት የቆሰሉ የራሳቸው ቁስለኛ ወታደሮችንና አስከሬን ይጭኑባቸዋል።
መረብ ሚዲያ ባሰባሰበው መረጃ መሠረት፡ ተጓዦችን አሳፍረው ሲጓዙ የነበሩ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ያሳፈሩትን ሕዝብ አውርደው ወታደር እንዲጭኑ ተገደዋል፡ እህል የጫኑ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎችም የጫኑትን እህል መንገድ ላይ አራግፈው ወታደር ጭነው ወደ ጦርሜዳ እንዲጓዙ የተገደዱ ሲሆን፡ የጫኑትን እህል ማውረድ ያልቻሉ ደግሞ ከ15 ሺ ብር ጀምሮ እንዲከፍሉ ተገደዋል።
ፋኖ ከሚጠቀምባቸው የውጊያ ስልቶች መካከል አንዱና ዋናው የሽምቅ ጥቃት/የደፈጣ ማጥቃት/ በመሆኑ፡ ተዋጊ ኃይል እንዲሁም ሬሽንና ተተኳሽ በተሽከርካሪ ጭነው ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱ የአገዛዙ ወታደሮች ላይ በሚፈፅመው ጥቃት፡ ወታደሮቹን ጨምሮ ተሳፍረውባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎች ይወድማሉ።
በዚህም በአማራ ክልል በመቶዎች የሚቆጠሩ የግለሰቦችና የማሕበራት ተሽከርካሪዎች የወደሙ ሲሆን፡ ባለንብረቶቹም ምንም አይነት ካሳ ሳያገኙ፡ ይባስ ብሎም ስለንብረታቸው ሲጠይቁ "እኛ በርካታ ወታደሮች እየሞቱብን እናንተ ስለ ንብረት ታወራላችሁ" በሚል ለእስር የተዳረጉ ስለመኖራቸውም ጣቢያችን መረብ ሚዲያ ባደረገው ማጣራት ለማረጋገጥ ችሏል።
ተሽከርካሪዎች በክልሉ አንድ ኪሎ ሜትር በማይሞላ ርቀት ላይ በተጣሉ ኬላዎች የሚከፈለውን የቀረጥ ክፍያ ተቋቁመው ለመስራት ሙከራ እያደረጉ ቢሆንም ነገር ግን ግዳጅ ተይዘው ንብረቶቻቸው በጦርነቱ ወድመዋል፡ በዚህም በርካታ ባለንብረቶች በብድር ጭምር የገዙት ተሽከርካሪ በመውደሙ የተበደሩትን ገንዘብ መመለስ አቅቷቸው የራሳቸውና የቤተሰቦቻቸው ሕይወት ተመሰቃቅሏል።
በርግጥ በውጊያ ወቅት በፋኖ የተማረኩ ተሽከርካሪዎች፡ ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው ባለንብረቶቹ የንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫ አቅርበው ንብረታቸውን ከፋኖ እንደተቀበሉ ለመረብ ሚዲያ የገለፁ አንዳንድ እድለኞችም አልጠፉም።
ክልሉ በአራቱም ማዕዘናት በጦርነት በሚታመስበት በዚህ ወቅት መስራት ያልቻሉ ተሽከርካሪዎች፡ ስራ ፍለጋ ወደ አዲስ አበባና ወደ ሌሎች አከባቢዎች ለመንቀሳቀስ ተገደዋል።
ቢሆንም ግን እነዚሁ ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የገቡት ተሽከርካሪዎች በመዲናዋ ለመስራት የአዲስ አበባን ወይም የኦሮሚያ ክልል ታርጋ ማስቀየር እንዳለባቸውና ይሄንንም ለማድረግ እስከ 50ሺ ብር እየተጠየቁ መሆናቸውን ለመረብ ሚዲያ ተናግረዋል።
ከአማራ ክልል ውጭ የሌሎች ክልሎችን ታርጋ የለጠፉ ተሽከርካሪዎች በመዲናዋ ያለማንም ከልካይ እየሰሩ ነው የሚሉት ምንጮቻችን፡ ነገር ግን የአማራ ክልል ታርጋ ያላቸው ተሽከርካሪዎች ተመርጠው እንዳይሰሩ ታግደዋል ብለዋል።
መረጃውን ለመረብ ሚዲያ ያደረሱ ምንጮች እንደገለፁት፡ የአማራ ክልልን ታርጋ ሳይቀይሩ ወደ አዲስ አበባ ገብተው የተገኙ ተሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ እስከ አምስት/5/ ሺ ብር የደረሰ ቅጣት ይቀጣሉ፣ አለፍ ሲልም አሽከርካሪው ከነተሽከርካሪው ለእስር ይዳረጋሉ፣ በከተማዋ እንዲሰሩም የግድ የኦሮሚያ ክልል ወይም የአዲስ አበባ ታርጋ እንዲያወጡ ተገደዋል ሲሉ ቃል በቃል ተናግረዋል።
ታርጋ ሳይቀይሩ አዲስ አበባ ገብተው እስከ አምስት ሺ ብር ከተቀጡ በኋላ የአዲስ አበባ ወይም የኦሮሚያ ታርጋ እንዲያወጡ ያለበለዚያ ድጋሚ በከተማዋ እንዳይንቀሳቀሱ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው አንዱ የሆኑት የመረብ ሚዲያ ምንጭ፡ ለምን ብለን ስንጠይቅ "ከትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር የተሰጠን መመሪያ ነው" የሚል ምላሽ ብቻ ነው ያገኘነው ብለዋል።
ግዳጅ ከተያዙ በኋላ ወደ ጦር ሜዳ ተወስደው በመውደም፣ አንድ ኪሎ ሜትር በማይሞላ ርቀት የተዘረጉ ኬላዎች ላይ በሚከፈለው የቀረጥ ገንዘብ እንዲሁም በተደጋጋሚ በሚታወጁ የእንቅስቃሴ ገደቦችና የፋኖን ስም ለማጥፋት የአገዛዙ ሰዎች ባደራጇቸው ቡድኖች በአሽከርካሪዎች ላይ በሚፈፀሙ እገታዎች ምክኒያት ከባድ ፈተና ውስጥ የወደቁት ባለንብረቶች ከክልሉ ወጥተው ስራ እንዳይሰሩም በተሽከርካሪዎቻቸው ላይ እገዳ ተጥሎባቸው ኪሳራ ላይ ወድቀዋል።
መረብ ሚዲያ | 336 |
| 14 | No text... | 300 |
| 15 | የቅማንት ተወላጆችን አግተው ገንዘብ ሲጠይቁ የነበሩ አጋቾች በፋኖ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነገረ!
በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ዮሐንስ ወረዳ ፋኖ ነፃ ካወጣቸው ቀጠናዎች መካከል አንዱ በሆነው በሽመለጋራ አከባቢ ሰርገው በመግባት የቅማንት ተወላጅ የሆኑ አራት አርሶ አደሮችን በማፈን የፋኖን ስም ለማጥፋት ብሎም በቅማንትና በአማራ ተወላጆች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ ሲሰሩ የነበሩ አጋቾች ከነ ጦር መሣሪያቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መረብ ሚዲያ በአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ካወጣው መረጃ ተመልክቷል።
1ኛ፦ አቶ አደራጀው ሲሳይ
2ኛ፦ አቶ አማረ ስመኘው
3ኛ፦ አቶ ብርሀን ነጋ
4ኛ፦ አቶ መንግስቴ አስማረ የተባሉ የቅማንት ተወላጅ አርሶ አደሮች ታግተው እስከ 8 መቶ ሺ ብር ድረስ የተጠየቀባቸው ቢሆንም፡ ቀጠናውን የተቆጣጠረው የበላይ ዘለቀ ዕዝ ሰራዊት ባካሄደው የተጠና ልዩ ኦፕሬሽን አጋቾቹን እጅ ከፈንጅ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው አስታውቋል።
ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብለው የእገታ ድርጊቱን የፈፀሙት ጋሻው ገብሬ፣ባሻ ግደቡ፣ስማቸ ሞላ የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ሲውሉ፡ 1መቶ 50ሺ በጥሬ ብር፣ ሦስት ክላሽንኮቭ መሣሪያ ከነ ተተኳሹ፣ ቦምብና ትጥቆችን እንደያዙ ነው ሲል ዕዙ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ባወጣው መረጃ ገልጿል።
ከወራት በፊት በተመሣሣይ የቅማንት ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ የእገታ ተግባር ሲፈፅሙ በነበሩ እጋጆች ላይ እርምጃ መውሰዱን የጠቀሰው ዕዙ፡ በዚህም በእገታ ድርጊት ተሰማርተዋል ተብለው የተጠረጠሩ 50 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ከ35 በላይ የቤት እንስሳትን ለባለቤቶቻቸው አስመልሻለሁ ማለቱን መረብ ሚዲያ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያው ካወጣው መረጃ ተመልክቷል።
ከየትኛውም አካባቢ እና ከየትኛውም ወገን የሚፈፀሙ መሰል ዕኩይ ተግበራትን የማይታገስ መሆኑን የገለፀው በላይ ዘለቀ ዕዝ፡ በተለይ በአማራና ቅማንት ህዝብ መካከል ግጭት ቀሽቃሽ ተግበባራትን ለመፈፀም የሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ ጥብቅ እምጃ እንደሚዎስድ አሳስቧል።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅ ለብዙዎች ተደራሽ ይሆን ዘንድ ሼር ያድርጉ!
https://t.me/MerebMedia24 | 346 |
| 16 | No text... | 313 |
| 17 | የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል የትግሉን አጠቃላይ ገጽታ የተመለከተ ሲምፖዚየም አዘጋጅቷል።
በአማራ ህዝብ ላይ የተጋረጠውን የህልወና አደጋ ለመመከት ላለፉት ሁለት ዓመታት ታላቅ ተጋድሎ እየተደረገ መሆኑ የሚታወቅ ነው። በተበታተነ ሁኔታ የሚደረገውን ተጋድሎ ወጥ በሆነ ድርጅታዊ መዋቅር ስር ለማድረግ በተጀመረው ጥረት የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሃይል የተወለደና ትግሉን በተሻለ ቁመና እየመራ የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል። በጥቂት ታጋዮች ከኋላ ቀር መሳሪያ የተነሳው የአማራ ፋኖ ትግል በሁለት ዓመት ውስጥ ያስመዘገበው ድልና የገነባው ግዙፍ ወታደራዊ ሃይል የተጀመረውን የህልውና አደጋ ለመመከት በሚያስችል ቁመና ላይ እንዲገኝ አድርጎታል። ምንም እንኳን ትግሉ ከሚፈልገው አቅምና ብቃት እንዲሁም የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ካለው መከራና ስቃይ አንጻር የምንገኝበት ምዕራፍ ገና ብዙ እንደሚቀረን የሚያሳይ ቢሆንም በቁርጥኝነትና በተባበረ ሃይል ከቀጠልን በቅርብ ጊዜ የአገዛዙን የጭቆና ቀንበር በጣጥሰን እንደምንጥል ጥርጣሬ የሚያስፈልገው ጉዳይ አይደለም።
ለዚህም የተጀመረውን የአንድነት ጉዞ ማፋጠንና ወደኋላ የማንመለስበት የፋኖ ወጥ መዋቅር ለመገንባት ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረግን እንገኛለን። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ለዚህ የአንድነት ጉዞ የሚረዳና የተጋረጡብንን ችግሮች በውይይት ለመፍታት የሚያስችል ታላቅ ሲምፖዚየም ማዘጋጀቱን ሲገልጽ በደስታ ነው።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ( አፋብኃ) ከዚህ አቅሙ የበለጠ ጠንካራ እንዲሆንና የትግሉ ጊዜ ባጠረ መልኩ ለመቋጨት ያስችል ዘንድ እና ለአለማቀፉ ማህበረሰብ የትግሉን ሂደትና ዓላማ ግልፅ ለማድረግ፣ ለማስተዋወቅ እና በጎ ፈቃደኛ ደጋፊዎችን ለመጨመር ያለመውን ይህን ሲምፖዚየም ጷጉሜ 01 እና 02 ቀን 2017 ዓ.ም ወይም በፈረንጆቹ አቆጣጠር September 06,2025 Saturday Starting 12 Noon and September 07,2025 Sunday Starting 12 Noon በቀጥታ ስርጭት የሚያካሂድ መሆኑን ያስታውቃል።
በሲምፖዚየሙ ላይ የአፋብኃ ማዕከላዊ ኮማንድ አመራሮች በጋዜጠኞች ቃለመጠይቅ ይደረግላቸዋል፣ ዝግጅቱም በቴሌቪዥንና በዩቲዩብ፣ ቲክቶክ እና የX (Twitter ) ማህበራዊ ሚዲያዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛል።
በዚህ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ( አፋብኃ) ሲምፖዚየም ተሳታፊ በመሆን የአማራ ህዝብ የታወጀበትን እልቂት ለመመከት እየታገለ ያለውን የአማራ ፋኖ በመደገፍ፣ ከአማራም አልፎ በየተራ ሁሉንም ብሄሮች በማጥቃት የጭቆናና የባርነት ስርዓቱን ለማስቀጠል እየሰራ ያለውን "ብልፅግና" የተሰኘውን ጸረ ሕዝብ አገዛዝ እንድንታገልና ሀገርን ከመፍረስ እንድንታደግ ጥሪ እናቀርባለን።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል - አፋብኃ | 349 |
| 18 | የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ሰበር ዜና💪
ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር በላስታ ሰማይ ስር ከጠላት ኃይል ጋር ከባድ ትንቅንቅ በማድረግ አንድ ድሽቃ ሲማርክ ከ65 በላይ የጠላት ኃይልን ደመሰሰ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል(አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ፣ተፈራ ማሞ ክፍለጦር፣ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር እና ጄኔራል ኃይሉ ከበዴ ክፍለጦር አንዳንድ ሻለቃዎች የተሳተፉበት 3ኛ ቀኑን የያዘው ከብልባላ ከተማ በባውሽ እስከ ሰኞ ገበያ ባለው ቀጠና ከጠላት ጋር እየተደረገ ባለው ትንቅንቅ ከፍተኛ ድል ተመዘገበ።
ነሐሴ 26/2017ዓ.ም ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ እና ተፈራ ማሞ ክፍለጦር ከገንጅ ዋርካ በጉርዱ በር እስከ መረዝ በር በመዘርጋት የገባውን የጠላት ኃይል ለወሬ ነጋሪ ሳይቀር የደመሰሱት ሲሆን ማረጉ ተማረ ክፍለጦር ከአርጨቆ በጋሸና እስከ ደረቅማ ድረስ ያለውን ቦታ በመሸፈን በጠላት ላይ ከፍተኛ ተጋድሎ ፈፅመዋል። በተያያዘም ተወርዋሪው ጄኔራል ኃይሉ ከበዴ ክፍለጦር በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በመግባት ጠላት መሽጎበት የነበረውን የወርቃምባና አሞራ ተራራ በሜካናይዝድ በተደገፈ አውደ ውጊያ ጠላት ከምሽጉ ሳይወጣ ለዱር አውሬ ቀለብ እንዲሆን አድርገውታል፤ እሸት ክፍለጦር አንዷ ሻለቃም ከላሊበላ የሚመጣውን ኃይል ሰኞገበያ ላይ በመዝጋት ወገን በጠላት ላይ የበላይነትን እንዲቀዳጅ ሰርግና ምላሽ አድርጋለታለች።
በዚህ አውደ ውጊያም በጠላት ኃይል ላይ የደረሰ ጉዳት ከ65 በላይ ሙት፣ 42 ቁስለኛና 5 ምርኮኛ ሲሆን እንዲሁም አንድ ዲሽቃ፣10 ጥቁር ክላሽ፣ 850 የክላሽ ተተኳሽ፣ 25 የደረት ትጥቅ፣ 16 የወገብ ትጥቅ፣42 የእጅ ቦምብ፣25 የክላሽ ካዝናና 20 የዝናብ ልብስ ሊማርክ ችሏል።
በመጨረሻም አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ስር የሚገኘው ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር በየትኛውም ሁኔታና በማንኛውም ጊዜ በጠላት ላይ የመደበኛና የሽምቅ ውጊያ በማድረግ በጠላት ሀይል ላይ የበላይነትን እንደሚቀዳጅና በሙሉ ዝግጁነትና ቁመና ላይ እንደሚገኝ የኮሩ ዋና አዛዥ አርበኛ 50አለቃ ኮማንዶ ወንድሙ ማሩ አሳስቧል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ነሐሴ 26/ 2017 ዓ.ም | 309 |
| 19 | No text... | 289 |
| 20 | የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙን ጨምሮ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አመራሮች በአፋር ዝግ ስብሰባ ሲያካሂዱ መሰንበታቸው ታወቀ!
በስብሰባው ከሣምንታት በፊት በፋኖ ስለተማረከው ዙ23 ተነስቶ፡ ጣት እስከመጠቋቆም የደረሰ ግምገማ የተደረገ ሲሆን፡ ቀሪ የዕዙ ሜካናይዝድ መሣሪያዎች ለአማራ ክልል አጎራባች በሆኑ የአፋር ክልል አከባቢዎች ተወስደው እንዲቀመጡ ውሳኔ ተላልፏል ተብሏል።
አገዛዙ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመው የዘር ማጥፋት ድርጊትን ከሚመሩና በዋናነት ከሚያስተባብሩ ሆድ እንጂ ሕሊና አልባ ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆነው የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄነራል አበባው ታደሰን ጨምሮ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል አሰፋ ቸኮል እንዲሁም ሌሎች የዕዙ ከፍተኛ አመራሮችና በዕዙ ስር የሜካናይዝድ ክፍሉ አዛዦች፣ በተጨማሪም የአፋር ክልል ከፍተኛ አመራሮች የተሳተፉበት ዝግ ስብሰባ በአፋር ሰመራ ከተማ መካሄዱን የመረብ ሚዲያ ወታደራዊ ምንጮች ገልፀዋል።
የስብሰባው ዋና አጀንዳ የኤርትሪያ መንግስት ጦር የኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ አዳዲስ የምሽግ ስራ እያከናወነ መሆኑን በሚመለከትና የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ሜካናይዝድ ክፍል አሁናዊ አቋምን መገምገም እንደሆነ ታውቋል።
የኤርትራ ጦር በቡሬ የኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ አዳዲስ የምሽግ ስራ እያከናወነ መሆኑን የሚያሳዩ የሳተላይት ምስሎች ሰሞኑን መታየታቸውን የአገዛዙ የሚዲያ ሰራዊት ምስሎቹን ሲያሰራጭ ሰንብቷል።
በተመሣሣይ የብልፅግናው ቡድን ጦር ከኤርትራ ድንበር 40 ኪሎ ሜትር በማይሞላ ርቀት ላይ በሚገኘው ቡሬ ማንዳ ሱላ አከባቢ ምሽግ እየቆፈረ ስለመሆኑ ተነግሯል።
ቡሬ ማንዳ ሱላ ላይ የብልፅግናው ቡድን ጦር፡ ምሽግ እያስቆፈረ ያለው በራሱ ሰራዊት ሳይሆን አማራ በመሆናቸው ብቻ "ፋኖን ሊደግፉና ሊቀላቀሉ ይችላሉ" በሚል ምክኒያት ብቻ ተጠርጥረው ከዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ ያለ ምንም ፍትሕ በቡሬ ማንዳ ሱላ ታስረው በሚገኙ የግፍ እስረኞች ነው።
እስረኞቹ ከዚህ ቀደም በመከላከያ ሰራዊት ተቋም ከከፍተኛና መካከለኛ አመራርነት ጀምሮ በተለያዩ ክፍሎች ሲያገለግሉ የነበሩ ሲሆን፡ የአማራ ክልሉ ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ ፋኖን ሊቀላቀሉ ይችላሉ በሚል ተጠርጥረው በተለያዩ ጊዜ ለእስር የተዳረጉ ናቸው።
እነዚሁ የአማራ ተወላጅ እስረኛ ወታደሮች፡ አይቀሬ በሚመስለው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት በፈንጅ ማምከን እንዲሳተፉ ከወራት በፊት ጀምሮ ተገደው የፈንጅ ማምከን ስልጠና እየተሰጣቸው እንደነበር ወታደራዊ ምንጮቹን ዋቢ በማድረግ መረብ ሚዲያ መዘገቡ አይዘነጋም።
የአገዛዙ ሰዎች "ቀጣይ ዓመት ኢሬቻን ቀይ ባህር ላይ እናከብራለን" በሚል መፈክር እንደለመዱት የደሃ ልጅን እሳት ለመማገድ ቋምጠዋል።
ገዢው ቡድን ከኤርትራ ጋር አደርገዋለው ለሚለው ጦርነት ከወራት በፊት ጀምሮ ዝግጅት እያደረ እንደሆነ የተሰማ ሲሆን፡ በተለይ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ሜካናይዝድ ክፍል የመሣሪያ ማዘጋጀትና ቦታ ማስያዝ ስራዎችን ሲሰራ ሰንብቷል።
በኤርትራ በኩልም ከምሽግ መቆፈር ጀምሮ ተመሣሣይ የሆነ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፡ ይሄንን በሚመለከት ከነሐሴ አጋማሽ/2017 ዓ/ም/ ጀምሮ በምክትል ኢታማዦር ሹሙ የተመራ ዝግ ስበሰባ በሰመራ ከተማ ተካሂዷል።
ሰሜን ምስራቅ ዕዝን ጨምሮ አገዛዙ አሉኝ የሚላቸው የጦር አዋጊዎች ነሐሴ 03/2017 ዓ/ም በራያ ቆቦ ወረዳ ከፋኖ ጋር ባደረጉት ውጊያ በርካታ ወታደሮቻቸውን አስገድለው፡ አንድ ዙ23ን ጨምሮ ሁለት ሞርተርና ሌሎች ከባባድ መሣሪያዎችን በፋኖ አስማርከው መፈርጠጣቸው ይታወቃል።
በስብሰባው በፋኖ ስለተማረከው ዙ23 ተነስቶ፡ ጣት እስከመጠቋቆም የደረሰ ግምገማ ተደርጓል ያሉት ወታደራዊ ምንጮቻችን፡ ቀሪ የዕዙ ሜካናይዝድ መሣሪያዎች ለአማራ ክልል አጎራባች በሆኑ የአፋር ክልል አከባቢዎች ተወስደው እንዲቀመጡና በውጊያ ወቅት ብቻ ከፍተኛ እጀባ ተደርጎላቸው ጥቅም ላይ እንዲውሉ ውሳኔ ተቀምጧል ብለዋል።
(ምልስ፣ ወታደራዊ አመራሮቹና የክልሉ ባለስልጣናት ከስብሰባው በኋላ የተነሱት ፎቶግራፍ)
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅ ለብዙዎች ተደራሽ ይሆን ዘንድ ሼር ያድርጉ!
https://t.me/MerebMedia24 | 268 |
