ዕሴተ ✞ያሬድ Tube
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ውስጥ 👉መጻሕፈ ግጻዌ 👉የእለት ምስባካት 👉ውዳሴ ማርያም ዜማ 👉መስተጋብ ዜማ 👉ሥርአተ ማህሌት እና ዋዜማ 👉 ሃሳብ አስተያየት ጥቆማ👇 @St_gibereale ወይም @Menekrebot ☝☝☝☝☝☝ ይጦቅሙን እናመሰግናለን!!!
Show more750
Subscribers
+3224 hours
+1027 days
+42130 days
Posts Archive
Repost from ሐመረ ኖኅ ሚዲያ
#አናቅልለው
መዳናችን ከኛ የሆነ ሳይሆን ከሁሉ በላይ ከሆነው ከጌታችን ከኢየሱስ ነው።
ኢየሱስ ከከፍታ ክብሩ የወረደው እንደ ህጻናት ተመላልሶ ያደገው በመጨረሻም #በእንጨት_መስቀል የሞተው ለእኛ ለክርስቲያኖች ነው። መዳናችን ኀያል ጥበብ ነው። ጥበቡም ግን እዚህ ዓለም ላይ እንዳለ ተራ የሆነ የሰዎች የፊደል፣የቃላት ፣የሆሄያትና የሐረጋት ስደራ አይደለም።በፍቅር ብሩሽነት በደም ቀለም በልባችን ሸራ ላይ የተጻፈ እንጂ
ኢየሱስ የሞተው እኛ የእግዚአብሔር ልጆች እንሆን ወንድ ነው።
ኢየሱስ እኮ በዘመናት ሲኖ የነበረ እግዚአብሔር እኮ ነው።ለፍጥረታቱም የራራ ቅዱስ መሲህ ነው።
መዳናችን በደም የተከፈለ የፍቅር ጥግ ነው።
ይህን ስንል ለቃላት ማሳመሪያ፣ለንግግር ማድመቂያ ወይንም ለሞቅታና ለሰው ጭብጨባ አይደለም። ጥልቅ የሆነው የኢየሱስ ፍቅር ማለዳ ማለዳ ሁሌ እንደ አዲስ እንድናመልከው፣ እንድንባርከው፣እንድንዘምርለት ስለሚቀሰቅሰን እንጂ
በመሆኑም መዳናችን አይቅለልብን በውዳችን በኢየሱስ ከባርነት ከዲያብሎስ ልጅነት ነጻ ሆነናል። አንድ አባት ሀብቱን ለልጁ እንደሚያወርስ እርሱም በአባቱ ቤት ብዙ መኖሪያ በመኖሩ ሊያወርሰን ፍጹም ቸል አይልም።
የከፈለልን፣ ቀራኒዮ ላይ ምንም ሳያፍር እርቃኑን ስለኛ የሆነልን፣በክፉ ባሪያ በጥፊ የተመታልን፣መራራ ሃሞትን የጠጣልን፣ እነዚህንና ሌሎችን ሁሉ ውለታዎች ያደረገልን እኛ በህይወት መጽሐፍ እንጻፍ ዘንድ ነው።
አባት ሲሆነን በምድራዊ ሀብት ወስኖን አይደለም። ማንም ባላያት ጆሮ ያልሰማት ዓይን
ያላያትን ክቡር መንግስቱን ሊሰጠን ነው እንጂ
ስለዚህ መዳናችንን የጌታን የመስቀል ሥራ አናቅልለው በዓለም ሁካታ በኀጢአት ሰንሰለት
በክፉ ምግባር በስሙ ላይ አንሸቅጥ
እለት እለት ወደ መስቀሉ ወደ ቀራኒዮ እንመልከት
መልካም ውሎ
#ኢየሱስ_ሰላማችን_ነው
ሰላሙም ዓለም እንደሚሰጠን ሰላም አይደለም።
ዲያቆን የኋላሸት
ናዝሬት(አዳማ)
27/12/2015
🛑አዲስ ዝማሬ " መንፈስ ቅዱስ " ዘማሪት እየሩሳሌም ጌታቸው እና ዘማሪ ኤፍሬም ፀጋዬ || Holy Spirit_New ortodox song 2023||
🛑አዲስ ዝማሬ " መንፈስ ቅዱስ " ዘማሪት እየሩሳሌም ጌታቸው እና ዘማሪ ኤፍሬም ፀጋዬ || Holy Spirit_New ortodox song 2023||
