981
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
❀ ወላሂ እጅግ በጣም ቀናሁ. . . .
☞ሰብር አድርጋችሁ አንብቡት ትጠቀማላችሁ ኢንሻ አላሁ ተዓላ !
✿መጪው ዘመን የሚል አንድ ደብዳቤ ላይ አንድ የአረብ ሀገሮች
የመኪና ፍጥነት የሚቆጣጠር ትራፊክ ይህንን ታሪክ ዘግቦታል. . .
>ለናንተ ላካፍላችሁ! ትራፊኩ እንዲህ ሲል ታሪኩን ጀመረ:- "
አንዴ የተለመደውን ስራዬን ቆሜ እየሠራሁ እንዳለ አንድ መኪና
እንዲሁ ረጋ ብሎ ሲሄድ ነበር ይህ ሰው መኪናው ተበላሸበትና
ከመኪናው ወቶ ወርዶ ለማስተካከል ልክ እንደወረደ ከሁዋላ
መጣችና አንዲት መኪና ወጣችበት ወደቀ ተገጨ
ይህ ሰው ከባድ የሆነ አወዳደቅን ወደቀ እኛም ሩጠን አነሳነውና
መኪና ላይ ሰቀልነው ይሄን ሰው ይህ ሰው ስናየው ገና ለጋ
~ወጣት ነበር ይህ ልጅ የአላህ ባሪያ መሆኑ ፊቱ ላይ ያስታውቃል
``ፂሙ ፊቱ ያበራል የኢማን ኑር ይታይበት ነበር ልክ አንቡላንስ
>መኪና ላይ ስንጭነው ይህን ወጣት አብረነው ስንሳፈር የኾነ
ቃል ይናገር ነበር የሚለውን ግን መረዳት አልቻልንም ነበር ነገር
ግን መኪና ውስጥ አድርገነው ከጎን እኔና ጉዋደኛዬ ትራፊክ
አብረን ከጎን ሁነን መሄድ ስንጀምር ለየት ያለ የሚያምር ድምፅ
መስማት ጀመርን አላሁ አክበር!!!
❀ይህ ወጣት ቁርዓን እየቀራ ነበር ይህ ወጣት በሚያምር ድምፅ
ቁርዓን እየቀራ ነበር ሱብሀንአላህ! በጣም ይገርማል እንደው
የተመታ እንደዚያ አይመስልህም ደም ልብሱን እንዳለ አካላቱን
አልብሶታል አጥንቱ ደቆ ተሰባብሮዋል ልክ ወጣቱን ስታየው ሞት
አፋፍ ላይ ያለ ነው የሚመስልህ ነገር ግን ይህ ወጣት
በሚያምር ድምፅ ቁርዓንን ይቀራ ነበር ሞት አፋፍ ላይ ያለ
ወጣት! አላሁ አክበር!
ተገርመን በጣም ማየት ጀመርን ትንሽ እንደቆየ ፀጥ አለ!ወደ
ሁዋላ ዞር ብዬ ስመለከተው እጁን ወደ ላይ አድርጎ ሸሀዳ እያለ
ነበር :- " አሽሀዱ አላ ኢላሀ ኢለላህ ወአሽሀዱ አነ ሙሀመደን
ረሱሉላህ" ያ አላህ! ሱሀነክ! ;-( ;-( ;-( ከዛም ፀጥ አለብን
ይህ ወጣት እጁን ሂጄ ነካሁት ደረቱን ዳሰስኩት ምንም
የሚንቀሳቀስ ነገር የለም ይህ ወጣት ዱንያን ለቆ ወጥቶ ነበር
ሱብሀነላህ!
ብዙ አተኩሬ ይህን ወጣት ተመለከትኩት ከአይኔ እንባ መርገፍ
ጀመረ ጉዋደኛዬ እንደው መቆም አልቻለም ለቀቀው ማልቀስ
ጀመረ እንዲህ ብሎ ቁርዓን እየቀራ ሲሞት ሆስፒታልም
እንደደረስን ስለዚህ ወጣት ሁኔታ ያገኘነውን ሰው ሁሉ ስለ
ወጣቱ ነገርናቸው አብዛኛዎቹ በጣም ልባቸው ተነካ እንባቸው
መውረድ ጀመረ አንደኛው ታሪኩን እንደሰማ በጣም ተገረመና
ይሄን የአላህ ባሪያ ሄጄ ግንባሩን ነው የምስመው ብሎ ሳመው
አብዛኛዎቹ በቃ ከዚህ ከአላህ ባሪያ ላይ ሶላተል ጀናዛ
ሳንሰግድበት አንሄድም አሉ::
`
ከዛም ከሆስፒታሉ ሰራተኞች ውስጥ አንዱ ወደ ቤተሰቡ ደወለና
ወንድሙ መጣ:- ወንድሙ ነው ይሄን የሚቀጥለውን ታሪክ
የሚናገረው:- "ወንድሜ ሁሌ ሰኞ ሰኞ አንዲት ገጠር አካባቢ
አያቱ አለች እሷን ሊዘይራት ይመላለስ ነበር:: እዛች አገር
ውስጥ ያሉ ሚስኪኖችን የቲሞችን ባል የሞተባቸውን ሴቶችን
እየሄደ ይረዳቸው ነበር:: ያቺ ከተማ ወንድሜን ታውቀው ነበር::
ለዛች አገር ሰዎች ሁሌ ሰኞ ሰኞ ካሴቶች መፅሐፎችን እየወሰደ
እሱ ነበር የሚሰጣቸው::
ሁሌም ወደዛች ሀገር ሲሄድ መኪናው ውስጥ ሩዝ ስኩዋር
ምናምን ሞልቶ ነበር የሚሄደው ለችግረኞች እዛ ሊበትንላቸው
ማለት ነው:: ከረሜላ እንኩዋን ለዛች ሀገር ሕፃናቶች አይረሳም
ነበር:: ሁሌም ታዲያ ሰዎቹ አንተ የዚህን ያህል ጉዞ
ትመላለሳለህ እንዴ! ብለው ለሚተቹትና ሀሳብ ለሚሰጡት
ሰዎች እንዲህ ብሎ ይመልስላቸው ነበር:- " እኔኮ ወደዝች
ሀገር በመመላለሴ በረጅሙ ጉዞዬ ውስጥ ቁርዓንን ለመሐፈዝና
ቁርዓንን ሙራጃ ለማድረግ ለማስታወስ እጠቀምበታለሁ
የሚጠቅም ሸሪጦችን ሙሀደራ እሰማበታለሁ እንደኛ ሙዚቃ
ከፍቶ አይደለም የሚሄደው ይሄ ሁሉ ጎማዬ የሚሽከረከረው
መሽከርከር ከአላህ ዘንድ አጅር አኝበታለሁ ብዬ አምለናለሁ
ይለን ነበር::
እያለ ወንድምየው ነገረን:: ሱብሀን አላህ!!! ትራፊኩ ምን
ይላል:- ሀያቴ ልክ በማዕበል እንደምትናጥ መርከብ እዛ እዚ
እየዋተትኩ ነበር መዋለል ከሁሉ አቅጣጫ ወሮኝ ነበር አላህ
(ሱ.ወ) ን ከራቁት ውስጥ ነበርኩ ወጣቱን ቀብር ላይ ከተነው
በሰገድንበት ጊዜ እሱ የአኼራን የመጀመሪያን ቀን ሲገናኝ እኔ
የዱንያን የመጀመሪያዬን ቀን ተገናኘሁ ወደ አላሁ (ሱ.ወ)
ተመለስኩ አላሁ (ሱ.ወ) ያሳለፍኩትን ይምረኝ ዘንድ ይህንን
ወጣት አሟሟቱ እንዳሳመረው ሁሉ በኸይር ይወስደኝ ዘንድ
አላሁ(ሱ.ወ) እየተማፀንኩ ቶብቼ ተጸጽቼ የዱንያን
የመጀመሪያዬን ቀን ጀመርኩ ይላል::
" መጪው ዘመን በሚል ርዕስ ላይ ይህ ትራፊክ ነው ታሪኩን
የዘገበው እናቶቼ አባቶቼ እህቶቼ ወንድሞቼ ወላሂ የመጨረሻን
ሸሀዳ ማግኘት ከባድ ነው አሁን ምላሳችን ዚክር ያለመደ ከኾነ
ከቁርዓን ጋር ያልኖርን ከሆነ ያኔ ጣዕረሞት ላይ አይመጣልንም
ወላሂ !!! የቁሉላሁ (ተባረከ ወተዓላ) ፊ ሙህከሚ ተንዚሊህ:
- "አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ
ልፋትን ለፊ ነህ! ተገናኚውም ነህ!" ሱረቱ አል-ኢንሺቃቅ 6
ያ አላህ!!! ያ አረሕማን!!! ያ ዘልጅላሊ ወል ኢክራም!!! ያ
አርሀሙ ራሒሚን!!! አሟሟታችንን አሳምርልን!!! ኑሮአችንን
በኢባዳ ሞታችንን በሸሀዳ አድርግልን!!! አሚን!!! አላሁመ
አሚን!!!
ሼር ያድርጉ ለሌላውም ያስተላልፉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ላ ኸላሶ ኢላ ቢል ኢኽላስ ኢዘን
ሊላሒ_ተዓላ
🍀➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖🍀
أخرج الطبرانيّ في اﻷوسط والمستغفري بسند حسن عَنْ سُمْرَةَ بْنِ جُنْدُبٍ رَضِيَ اللهُ عَنْهُ قالَ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ ﷺ
يَقُولُ: مَنْ قالَ إذا أَصْبَحَ وَإذا أَمْسى:
اللهُمَّ أَنْتَ خَلَقْتَني وَأَنْتَ تَهْديني
وَأَنْتَ تُطْعِمُني وَأَنْتَ تَسْقيني
وَأَنْتَ تُميتُني وَأَنْتَ تُحْييني،
لَمْ يَسْأَلِ اللهَ شَيْئًا إلّا أَعْطاهُ إيَّاهُ .
🌿▬▬▭▭▭▬▬🌿
አሏሁመ አንተ ኸለቅተኒ✨
ወአንተ ተህዲኒ✨
ወአንተ ቱጥዒሙኒ✨
ወአንተ ተስቂኒ✨
ወአንተ ቱሚቱኒ✨
ወአንተ ቱህይኒ✨
🌿▬▬▭▭▭▬▬🌿
👆
በመሸና በነጋ ጊዜ ይህንን ያለ ሰውየ
አላህን አንድ ነገር አይጠይቅም አሏህም የሚሰጠው ቢሆን እንጂ ﷺ
#ጦበራኒይ_ዘግበውታል
▬▬▬▬ ―➖➖➖▬➖▬▬🍃
@eslamik_tube
አጂብ የሆነ ቂሷ!
በአንድ ወቅት ነብዩ መሐመድ ﷺ ቢላል ኢብኑ ረባህን ከኃላው በፍቅር ስሜት እቅፍ አድርገው ይይዙትና ድምፃቸውን ቀይረው
"እኔ ማን ነኝ ?" ብለው ይጠይቁታል
ቢላልም "ኡመር ነህ ?"
"አይደለሁም"
"አቡበክር መሆን አለብህ?"
"አሁንም ተሳስተሃል"
"በቃ ኡስማን ነህ"
"አላወቅከኝም"
"አሊ ነህ ማለት ነው?"....እያለ ያቀፈውን ሰው ማንነት ሲጠይቅ ይቆያል።
ከዚያ ረሱልﷺ ለቅቅ አደረጉትና ከፊት ለፊቱ በመምጣት
"ቢላል ሆይ! በእውነት እኔ መሆኔን አላወቅክም ነበር እንዴ ?" ሲሉ ጠየቁት
ቢላልም “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በደንብ አውቄዎታለሁኝ ነገር ግን ለረጅም ጊዜ እንዳቀፉኝ መቆየትን ስለፈልግኩኝ እንጂ" ሲል መለሰላቸው።
ፊዳክ አቢ ወኡሚ ወደሚ ወነፍሲ ያረሱሉሏህ!!
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ልብ የሚነኩ የአለማችን 4 ንግግሮች:-
1- በሶሪያ ጦርነት የቆሰለው ህፃን ለዶክተሩ
«እኔ ወደ ፈጣሪ መሄዴ ነው የሆነውን ሁሉ እነግረዋለው!»😢
2-ኢራቅ ሞሱል ውስጥ ቆስላ እየሮጠች ካሜራማኑ ሲቀርፃት
«አጎቴ እባክህ ቪዲዮ አትቅረጸኝ ምክንያቱም ሂጃብ አለበስኩም!»😍
3- አንድ ህፃን በፍልስጤም እጅግ በጣም ይራብና
«ፈጣሪ ሆይ እባክህ በቶሎ ወሰደኝ አንተ ከወሰድከኝ በጀነት ውስጥ አልራብም እዛ እበላለሁ»😔
4- በአፍጋኒስታን ጦርነት እጁ ክፉኛ የቆሰለው ህፃን ለሕክምና ዶክተር ጋር ወስደውት ለዶክተሩ
«ዶ/ር እጄን ስትቆርጠው ልብሴን አትቁረጠው ተጠንቀቅ ምክንያቱም እኔ ሌላ ልብስ የለኝም እና» አለው። 😢
😔😔😔😔😔😔😔😔😔😔😔😔
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
۞ وَأَقِيمُوا۟ ٱلصَّلَوٰةَ وَءَاتُوا۟ ٱلزَّكَوٰةَ ۚ وَمَا تُقَدِّمُوا۟ لِأَنفُسِكُم مِّنْ خَيْرٍۢ تَجِدُوهُ عِندَ ٱللَّهِ ۗ إِنَّ ٱللَّهَ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌۭ۞ وَقَالُوا۟ لَن يَدْخُلَ ٱلْجَنَّةَ إِلَّا مَن كَانَ هُودًا أَوْ نَصَٰرَىٰ ۗ تِلْكَ أَمَانِيُّهُمْ ۗ قُلْ هَاتُوا۟ بُرْهَٰنَكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ۞ بَلَىٰ مَنْ أَسْلَمَ وَجْهَهُۥ لِلَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌۭ فَلَهُۥٓ أَجْرُهُۥ عِندَ رَبِّهِۦ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ۞
፡
:
۞ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ ለነፍሶቻችሁም ከበጎ ሥራ የምታስቀድሙትን አላህ ዘንድ ታገኙታላችሁ፡፡ አላህ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና፡፡۞
«ገነትንም አይሁድን ወይም ክርስቲያኖችን የኾነ ሰው እንጂ ሌላ አይገባትም» አሉ፡፡ ይህቺ (ከንቱ) ምኞታቸው ናት፡፡ «እውነተኞች እንደኾናችሁ አስረጃችሁን አምጡ» በላቸው፡፡۞አይደለም (ሌላውም ይገባታል) እርሱ በጎ ሠሪ ኾኖ ፊቱን ለአላህ የሰጠ ሰው ለርሱ በጌታው ዘንድ ምንዳው አለው፡፡ በነሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡۞
(አል በቀራህ110-112)
.
.
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ምናልባት ልብህ በአንድ ነገር አዝኖ ነገሩም
ሰቅስቅ ብሎ አስለቅሶህ ተኝተህ አድረህ ይሆናል
ነገር ግን አላህ ያንተን ጉዳይ እያስተናበረ አይተኛም
ጥራት ይገባውና...
አዛኙ ጌታህ ያዘንክበትን ጉዳይ ያስተካክልልሀል
እንዴት አድርጎ ነገራቶችን እንደሚያስተካክልልህ
ብታውቅ ኖሮ የደስታ እንባን ታነባ ነበር
ነገራቶችን ይበልጥ እየተረዳን በመጣን ቁጥር ችግሮች
ሲፈጠሩ የነበሩት በሰዎች በኩን እንደነበሩ እናስተውላለን
በጎ ነገራቶች ደሞ ከ ሚወደን ጌታችን እንደሆነ እንረዳለን
ሆኖም አሁንም ሰዋች ጋር እየተቀራረብን
ከአዛኙ ጌታችን እንሸሻለን🥺
ወዴት እያመራን ነው!?
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
◾️የሰደቃ ጥቅሞች‼️
➖➖➖➖➖➖➖
💦ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።
✅ ሶደቃ ብዙ ጥቅሞች አሉት ከነዚህ መካከል፦
➲ከመጥፎ ነገር ትጠብቃለች
➲በላእን ትከላከላለች
➲ወንጀልን ታጠፋለች
➲ገንዘብን ትጠብቃለች
➲ሪዝቅን ያመጣለች
➲ቀልብን ታስደስታለች
➲ሸይጧንን ታስቆጫለች
➲ነፍስን ታጠራለች
➲እድሜን ትጨምራለች
➲የቀብርን ቅጣት ትከላከላለች
➲የውመል ቂያማ ጥላ ትሆናለች
➲አላህ ዘንድ አስታራቂ ትሆናለች
➲የዱንም ሆነ የአሄራ ጭንቅ ታቀላለች
➲ዱአ ተቀባይነት እንዲኖረው ታደርጋለች
➲ሰጭው አላህና ፍጡር ዘንድ እንዲወደድ ታደርጋለች
➲በአላህ ላይ መተማመንና ጥሩ ጥርጣሬን ታመጣለች
📚(عدة الصابرين 《304》)
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
➺➺➺➺ ምራኝ …
ያ ረብ!!
ባንተ በትክክል ወደማመኑ ምራኝ፡፡ አንተን ወደማወቁ ምራኝ፡፡ ወዳንተ ፍራቻ ምራኝ፡፡ ቀልቤ ትጠገን ዘንድ ምራኝ፡፡ ነፍሴ ትታደስ ዘንድ ምራኝ፡፡
ራሴን ትንሽ አድርጌ ወደመመልከቱ ምራኝ፡፡ ለመቃብር ቤቴ፤ ለጨለማው አገሬ፤ ለረጅሙ መንገዴ .. ከብርሃንህ ልለኩስ ምራኝ፡፡
አንተን አግኝቼ ምን አጥቼ፤ አንተን አጥቼስ ምን አግኝቼ የኔ ጌታ፡፡
አግኝቼህ ካንተ ጋር ልኑር ምራኝ፡፡
ከጉያህ እንዳልወጣና ካንተ እንዳልነጠል ምራኝ፡፡
ስቸገር ተስፋ እንዳልቆርጥ፣ ሳገኝ ከደጅህ እንዳልጠፋ ምራኝ፡፡
በማግኘት እንዳልጃጃል፣ ማጣት ከደጅህ እንዳያስቀረኝ ምራኝ፡፡
ጠፍቼ እንዳልቀር ጥራኝ፣ ወጥቼ እንድመለስ ምራኝ፡፡
በምሰግደው ሶላቴ ፣ በሩኩዔና በሱጁዴ በትክክል አገኝህ ዘንድ ምራኝ፡፡
አንተ ያልመራኸው መንገደኛ ጠፊ ነው፡፡ አንተ ያላመላከትከው ተጓዥ ለፊ ነው፡፡
ኢላሂ … ሁሌም አገኝህ ዘንድ እርዳኝ፡፡
መመራትን ካገራህላቸው ትመድበኝ ዘንድ በትልቅነትህ ጠየቅኩህ
አንተ ካልመራኸኝ ምንም ተስፋ የለኝምና።
ምራኝ ወዱዴ።
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
#ልቤን_ነካኝና_ላካፍላችሁ_ወደድኩ
እንዲህ ነበሩ የኛ ነብይ፣የኛ ረሱል ﷺ
🥀ረሱል ﷺ ወደ መስጂድ ለመሄድ የሚጠቀሙት መንገድ ጠብቃ "ቆሻሻ" የምትወረውርባቸው አንዲት አዛውንት ነበረች። ነብያችንﷺ በየቀኑ ወደመስጂድ ሲመላለሱ እየጠበቀች "ቆሻሻውን "ትደፍባቸዋለች ነብያችንም ﷺ ችለውት በዝምታ ምንም አይነት መቆጣትን ሳያሳዩ ያልፋሉ።
ይህ የተለመደ ክስተት ሆኗል። አንድ ቀን የአሏህ መላዕክተኛ ﷺ በመንገዱ ሲያልፋ እንደ ወትሮው ቆሻሻ የምትደፍባቸው ሴት የለችም። ነብያችንﷺ በቦታው ላይ ቆመው ስለ ጤንነቷ ጎረቤቷን ጠየቁ።
የሴትዬዋ ጎረቤትም አዛውንትዋ ታማ አልጋ ላይ እንደተኛች ነገሯቸው። የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ ወደ አዛውቷ ቤት መግባት እንደሚችሉ በትህትና በመጠየቅ ሲፈቀድላቸው ገቡ።
ሴትዪዋ ነብዩ ሙሐመድ ﷺ ን ስትመለከት ለበቀል እንደመጡ በማሰብ "አቅሜ ሲደክም በሽታ አልጋ ላይ ሲያስተኛኝ ልትበቀለኝ መጣህ?" አለቻቸው።
"እርሳቸውም" የመጡት ለበቀል ሳይሆን መታመሟን በመስማታቸው አዝነው ሊጠይቋትና የምትፈልገው ነገር ካለ ሊያሟሉ ፍቃደኛ መሆናቸውን ገለጹላት።
አዛውቷም ከመገረሟ የተነሳ መናገር አቃታት። በአትኩሮት ትመለከታቸው ጀመር ከዚያም እንዲህ አለች ፦"አንተ እውነተኛ የአሏህ መልዕክተኛ መሆንህን እና አሏህም ጌታህ መሆኑን እመሰክራለሁ" በማለት እስልምናን ተቀበለች። ሱበሃን አሏህ!!
እንዲህ ነበሩ ነብያችን ﷺ እጅግ በጣም አዛኝ ተፈቃሪ ፦አዛውት ህጻን ሳይሉ ሁሉንም በቸርነት የሚያስተናግዱ ምርጥ ነብይﷺ !!!! Share ሼር share
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
💎ጥሩ ሚስት እረፍት ናት💎
قال الشيخ مقبل بن هادي الوادعي رحمه الله:
"أحسن ما يستريح به العبد في هذا الزمان بعد الإيمان بالله، طلب العلم: والزوجة الصالحة"
📚ሸይኽ ሙቅቢል ((ረሂመሁላህ)) እንዲህ ይላሉ፦
🌸በአሁን ጊዜ አንድን ሰው ከምንም በላይ ደስተኛ ሊያደርገው የሚችለው ነገር እውቀትን መማርና መልካም ሚስትን ማግባት ነው::
📚((الإمام الألمعي ~٢٥٣))
«ለሱ ብቻ ተዋቢ»
የአላህ መልዕክተኛ { ﷺ } እንዲህ ብለዋል፦
«መልካም ሴት ባለቤቷ ወደ እሷ ሲመለከታት የምታስደስተው ናት!»ብለዋል።
ዛሬ አብዛኛዎቹ ሴቶች የሚዋቡት ለሠርግ አሊያም ለፕሮግራም ጭራሽ ደግሞ አንዳንዶች መንገድ ላይ እንዲሁም በየሱቁ ላሉ ወንዶች ለመታየት ይዋባሉ።
እንዲህ አይነቶቹ ደግሞ ለባሎቻቸው መዋብን በቤት ውስጥ ፍፁም የዘነጉ ናቸው ።
ሷሊህ የሆነች ሴት የትና መቼ መዋብ እንዳለበት ታውቃለች።
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
🔴 ኻቲማ ከሚበላሽባቸው ምክንያቶች
፡
«ጀላሉዲን አስ‐ሲዩጢይ (ረሒመሁላህ) "ሙኽተሶር አዝካር አን‐ነወዊ" በተሰኘው መጽሀፍ ላይ እንዲህ ብለዋል: ‐ «አዛን እየተደረገ ወሬ የሚያወራ ሰው ኻቲማው እንዳይበላሽበት ያሰጋል።»
አንዳንድ ዓሊሞች እንደሚሉት ኻቲማን ከሚያበላሹ ነገሮች መካከል አራቱ ዋና ናቸው: ‐
1⃣ ሶላትን ችላ ማለት፤
2⃣ አስካሪ መጠጥ መጠጣት፤
3⃣ ወላጆችን መበደል፤
4⃣ ሙስሊሞችን ማስቸገር።»
:
📚 "ቡጀይሪሚ ዐለል‐ኸጢብ"፥ ቅፅ 2፥ ገጽ 48
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
🕌ሰ...ላ...ት...ን_ አ...ደ...ራ...🕌
🍃 ሶላት _ ያለ ራዕይ የተደነገገች ብቸኛዋ አምልኮ...)
የሶላትን ክብደት ከሚያመለክቱ ነገሮች መካከል በኢስራእና ሚዕራጅ #ሌሊት የተደነገገች ብቸኛዋ የአምልኮ ተግባር መሆኑ ነው። ያውም በመካከል አስተላላፊ መልዓክ ሳይኖር (ያለ ራዕይ)።
ሶላት በመልክተኛው ﷺ እና በሕዝቦቹ ላይ ያለ ጅብሪል (ዐ.ሰ) መልዕክት ነጋሪነት የተደነገገች ናት። መጀመሪያ ላይ ሀምሳ ሆና ነበር የተደነገገችው። ሆኖም ግን ነብዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) ለነብያችን በመከሩት መሰረት ነብያችን አላህ (ሱ.ወ) ዘንድ ተመላልሰው ወደ አምስት ዝቅ ተደረገች። የፈጠረን አምላክ አላህ (ሱ.ወ) እዝነቱ ሰፊ ነው። ታዲያ የግዴታ ሶላት በቁጥር አምስት ብትሆንም በምንዳ ግን የሃምሳ ሶላት ደረጃ የምትስተካከል መሆኗን ልብ ይሏል። ይህም አላህ ዘንድ የተፃፈ ድንጋጌ ነው። ("አቡ ዳውድ ዘግበውታል)
ወዳጆቼ ! በቀን ውስጥ ግዴታ የተደረገብን ሶላት ብዛት ሀምሳ ቢሆን ኖሮ ማን ይችል ነበር ?… ፈፅሞ አይታሰብም። ያኔ በየስላቱ መካከላቸው ሊኖር የሚችለው የሰዓት ልዩነት ግፋ ቢል ሰላሳ ደቂቃ ብቻ መሆኑን እናስተውል። ዛሬ ግን ከሁለት እና ሦስት አራት ሰዓት ከዚያም በላይ በሆነ ልዩነት መካከል የምንሰግዳቸውን ሶላቶች መሳነፋችንና ባአግባቡ መወጣት አለመቻላችን የሚገርምና የሚያሳዝን ነው።
በዚህ መልኩ የእዝነቱ አምላክ አላህ (ሱ.ወ) እዝነቱንና ርህራሄውን አሳየን። ሆኖም ግን ብዙዎቻችን እፍረትና ጨዋነት የሚባል ነገር የተፈጠረብን አንመስልም። የአምላካችንን እዝነት አስተውለን ከኛ የሚጠበቅብንን አናደርግም።
<ላ ሐውለ ወላ ቁወተ ኢልላ ቢልላህ !> አላህ ይዘንልን።
♻️ይቀላቀሉን♻️
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ሼር‼️ሼር‼️ሼር‼️ሼር❗️
:
ማሳሰቢያ‼️ ለሚመለከተው ሁሉ❗️
ሙስሊም እህት ወንድሞች *810# ምን እንደሆነ ታውቃላችሁን? *810# ማለት ሁላችንም እንደምናውቀው ከቴሌ ብድር መጠየቂያ የሜሴጅ ኮድነው እኔ ለምሳሌ ከቴሌ 5.00 ብር ብበደር ለቴሌ 5.50 ሣ.ም መመለስ አለብኝ ፡፡እንደዛው 10.00 ብር ብበደር አሁንም ለቴሌ 11.00 ብር መመለስ አለብኝ፡፡አልበቃ ብሎኝ 100.00 ብር ብበደር እንደዛው 110.00 ብር መመለስ አለብኝ ፡፡ እና ሙስሊም እህት ወንድሞቼ ይሄ ማለት እኮ ሪባ (ወለድ) ማለትነው
የአሏህ መልእክተኛ (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል ትንሹ ሪባ ከመስራት እኮ ከእናታችሁ ጋር ብትገናኙ ይቀላችኀል ብለዋል ትልቁን ሪባ መስራት እኮ በአሏህ(ሱብሀነ ወተአላ እና በመልዕክተኛው (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ላይ ጦርነት እንዳወጀ ይቆጠራል ብለዋል አሏሁ አእለም
እና ሙስሊም እህት ወንድሞቼ *810# ማለት ወለድ ያለው ብድርን ቴሌ የሚያበድርበት የቁጠባ አሰራር ነው፡፡ እና ባለማወቅ ይህን ወንጀል ስንሰራ የነበርን ሙስሊሞች ከዚህ ተግባር ልንቆጠብ እና ላለፈው ወንጀላችን አሏህ እንዲምረን ተፀፅተን አሏህን ማሃርታ መጠየቅ አለብን ኢንሻ አሏህ አሏህ ባሪያውን ማሃሪ ጌታ ስለሆነ ይምረናል ለሙስሊም እህት ወንድሞቻችን ሼር በማድረግ ያወቅነውን እናሳውቅ ባፋጣኝ‼️ ሼር‼️
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
😱 አሰተማሪ ቂሳ እንዴት ያለ ባል
👉ባልና ሚስት ከተጋቡ አራት አመታት ተቆጥረዋል ግን ልጆችን መውለድ አልቻሉም ነበርና ወደ ሀኪም ቤት ችግሩን ለማወቅ ይሄዳሉ አስፈላጊውንምርመራ ማድረግ እንዳለባቸው ተነግሯቸው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ፣ የምርመራውን ውጤት ለመስማት ባል ወደ ሃኪም ቤት ቀድሞ ያመራል ዶክተሩ ጋር ሲገባ የተነገረው ውጤት እጅጉን አሳዛኝ ነበር ባለቤቱ መውለድ አትችልም መሃን ናት ባል የሰማውን ዋጥ በማድረግ አላህን ያመሰግናል ፣ ለዶክተሩም እንዲህ ይለዋል.......
ሙሉዉን ማንበብ ከፈለጉ ከስር ያለዉን ይጫኑ ወላሂ ልብ ሚነካ ታሪክ ነዉ👇👇👇👇
ኢብራሂም ዓለይሂ ሰላም አባታቸው ሙስሊም
እንዲሆንላቸው ተመኙ ...
ኑህም ዓለይሂ ሰላም ልጁ ሙስሊም
እንዲሆንላቸው ተመኙ...
የኛው ነብይም ﷺ አጎታችው ሙስሊም
ቢሆን ብለው ተመኙ...
ነገር ግን አላህ አልፈለገውምና አልሆነም
አላህ ግን ለኔና ላንተ/ላንቺ ሳንጠይቀው
እስልምናን ሰጠን
ለኢብራሂም አባት ፣ ለኑህ ልጅ ፣ ለረሱሉ ﷺ አጎት
ያልሰጠውን ውብ እስልምናን ለገሰን አናመሰግንምን!!
ۚ إِنَّ اللَّهَ لَذُو فَضْلٍ عَلَى النَّاسِ وَلَٰكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَشْكُرُونَ
{አላህ በሰዎች ላይ በእርግጥ የችሮታ ባለቤት
ነውና፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያመሰግኑም፡፡}
[ሱረቱል ጋፊር: 61]
እንዴት ታዝናለህ!...
ሌላው ለሌላ አካል እያጎበደደ፤አላህ አንተን መርጦ
እስልምናን ሰጥቶ ለርሱ ብቻ እንድታጎበድድ ፈቀደልህ!
እንዴት ታዝናለህ!...
ስንቱ በተከበረበት ተዋርዶ፤ረበል ዓለሚን ያንተን ወንጀልህንና ነውርህን ደብቆልህ
ለምን ታዝናለህ!...
ስንቱ ነው አንድ አፉን ሚመገበው ጎኑን
ሚያሳርፍበት ማደሪያ የሌለው፤አዛኙ ጌታህ ቤትህን በምግብና በመጠጥ ሞልቶልህ ማደሪያ ሰጠህ
ስለምንስ ታዝናለህ!
ስንቱ ጤናውን አጥቶል ፤ራህማኑ አንተን ሰላም አደረገህ
አትዘን!
የሰው ፊት የሚገርፈው ሚለምን ስንቱ መሰለህ!?
ጀሊሉ ግን አንተን ከሰዎች አብቃቃህ!
በፍፁም እንዳታዝን!
ከህመም ብዛት በስቃይ አይኑን ሳይከድን የተኛ ስንቱ መሰለህ!? ...ወዱዱ ግን ላንተ ሰላማዊ እንቅልፍን
ሰጠህ
ያጣሀውን አትመልከት ፤ያለህን ተመልከትና
(አልሃምዱሊላህ) በልና አላህም እንዲህ
ካላቸው ሰዎች ሁን....
" وَقَلِيلٌ مِّنْ عِبَادِيَ الشَّكُورُ"
"ከባሮቼ በጣም አመስጋኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡"
[ሱረቱ ሰበዕ:13]
JOIN US SHEAR
@susui_slamic_channal
አንድ ቀን ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ለዐሊይ (ረዐ) እንዲህ አሉት:: አንተ ዐሊይ ሆይ ከመተኛትህ በፊት አምስት ነገሮችን ተግብር፡፡
1,ስትተኛ አራት ሺ ዲናር ሶደቃ ስጥ
2,ቁርዐን አኽትም
3,ለጀነት ዋጋዋን ክፈል
4,ሁለት ሰዎችን አስታርቅ
5,ከዚያም አንድ ጊዜ ሐጅ አድርገህ ተኛ፤
ዐሊይም(ረዐ)እንዲህ በማለት ጠየቁ፦ያ ረሱለላህ ይሄን በአንድ ለሊት እንዴት ማረግ ይቻላል? ብሎ ጠየቃቸው ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) የሚከተለውን ተናገሩ።
1,አራት ጊዜ ሱረቱል ፋቲሀን የቀራ 4000 ዲናር ሰደቃ ከሰጠው ጋር እኩል ነው።
2,ሶስት ጊዜ ሱረቱል ኢኽላስን(ቁል ሁ ወላሁ አሀድ) የቀራ አንድ ጊዜ እንዳኸተመ ይቆጠርለታል።
3,ሶስት ጊዜ ላ ሀውላ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላሂል ዐሊዩል ዐዚም ያለ የጀነት ዋጋዋን ከፍላል።
4,አስር ጊዜ እስቲግፋር ያረገ ሁለት ሰዎችን እንደ ማስታረቅ ነው።
5,አራት ጊዜ ሸሀዳ ያደረገ አንድ ጊዜ ሀጅ እንዳደረገ ነው።
አስብ ይሄ መልእክት አንተ ጋር ብቻ እንዲቆይ አትፍቀድ ለሌሎችም አጋራ ባንተ ምክንያት ሌላ ሰው አንብቦ ቢጠቀም አንተም የሱ ምንዳ ተካፋይ ነህና።
አላህ ባነበብነው ባስተላለፍነው ተጠቃሚ ያድርገን!
JOIN US👇👇👇
https://t.me/susui_slamic_channal
አቡ ሁረይራ [رضي الله عنه ] እንዳስተላለፉት ነቢዩ [صلى الله عليه وسلم] እንዲህ ብለዋል፡- “የቁርኣን እናትን (ፋቲሐን) ሳያነብ የሰገደ ሰው፣ ሶላቱ ጎደሎ ነው፡፡” (ቃሉን ሦስት ጊዜ ደጋግመውታል)፡፡ አንድ ሰው ለአቡ ሁረይራ “ከአሰጋጁ በኋላ ብንሆን እንኳ” አላቸው፡፡ እሳቸውም “ለራስህ አንብብ፤ ምክንያቱም ነቢዩ [صلى الله عليه وسلم] እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁና፤ “ኃያሉና የተከበረው አላህ እንዲህ ብሏል፡- ሶላትን በኔና በባሪያዬ መካከል ለሁለት ከፍየዋለሁ፤ እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል፡፡ ባሪያው ‹አልሐምዱ ሊልላሂ ረብቢል ዓለሚን› ሲል አላህ (ሱ.ወ) ‹ባሪያዬ አመሰገነኝ› ይላል፡፡ ‹አር-ረሕማኒ -ረሒም› ሲል ደግሞ አላህ (ሱ.ወ) ‹ባሪያዬ አሞገሠኝ› ይላል፡፡ ‹ማሊኪ የውሚዲ-ዲን› ሲል አላህ ‹ባሪያዬ አላቀኝ› ይላል፡፡ (ወይም ደግሞ) ‹ባሪያዬ ለኔ ኃይል ራሱን አስገዝቷል› ይላል፡፡ ‹ኢይያከ ነዕቡዱ ወኢያከ ነስተዒን› በሚል ጊዜ ‹ይህ በኔና በባሪያዬ መካከል ነው፤ እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል› ይላል፡፡ ‹ኢህዲነስ-ሲራጠ-ል-ሙስተቂም፣ ሲራጠል-ለዚነ አን ዐምተ ዐለይሂም፣ ገይሪ-ል-መግዱቢ ዐለይሂም ወለድ-ዷሊን› በሚል ጊዜ ደግሞ፣ ‹ይህ ለባሪያዬ ነው፣ እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል› ይላል፡፡
ሙስሊም ዘግበውታል
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
አቡ ሁረይራ [رضي الله عنه ] እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ [صلى الله عليه وسلم] እንዲህ ብለዋል፡- “አላህ ጀነትና ጀሀነምን በፈጠረ ጊዜ ጂብሪልን “ጀነትንና በውስጡ ነዋሪዎ ለሚሆኑት ያዘጋጀሁትን” ተመልከት፡፡ በማለት ላከው፡፡ ከዚያም ወደ ጀነት ሄዶ አላህ ያዘጋጀውን ተመለከተ፡፡ ወደ እሱ (አላህ) ዘንድ በመመለስም፡- “በአንተ ልዕልና እምላለሁ፣ ስለጀነት የሚሰማ ሁሉ እንደሚገባበት (እርግጠኛ) ነኝ” አለ፡፡ ከዚያም አላህ (ሱ.ወ) ጀነት ዙሪያው በአዳጋች ነገሮቸ እንዲከበብ አዘዘና “ወደ ጀነት ተመልሰህ በውስጡ ነዋሪዎች ለሚሆኑት ያዘጋጀሁትን ተመልከት” አለው፡፡ ዳግም በሚሄድበት ጊዜ ዙሪያው በአዳጋች ነገሮች ተከብቦ አገኘው፡፡ ከዚያም ወደ (አላህ) በመመለስ “በአንተ ልዕልና እምላለሁ፤ አንድም ሰው እንደማይገባበት እሰጋለሁ” አለ፡፡ እሱም “ወደ ጀሀነም እሳት ዘንድ ሂድና እሱንና በውስጡ ነዋሪዎች ለሚሆኑት ያዘጋጀሁትን ተመልከት” አለው፡፡ ጂብሪልም የጀሀነም እሳት አንዱ በሌላው ላይ ተነባብሮ አገኘው፡፡ ከዚያም ወደ እሱ ዘንድ ተመልሶ “በአንተ ልዕልና እምላለሁ፣ ስለእሱ የሚሰማ አንድም አይገባበትም” አለ፡፡ ከዚያም አላህ (ሱ.ወ) (የጀሀነም) ዙሪያ በሥጋዊ ፍላጎቶች እንዲከበብ አዘዘ፡፡ ከዚያም ጂብሪልን “(ወደ ጀሀነም) ተመለስ” አለው፡፡ እሱም ተመለሰ፡፡ “በአንተ ልዕልና እምላለሁ፤ አንድም ከመግባት እንደማያመልጥ እሰጋለሁ” አለ፡፡
ቲርሚዚይ፣ አቡዳውድና ነሳኢይ ዘግበውታል
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ቂያማ ሲቃረብ ቁርአን ከምድር ላይ ይነሳል ከዛም ወደሰማይ ይወሰዳል !!
አዎ ይህ ጉዳይ ከእለታት አንድ ቀን እውነታ ይሆናል
ቂያማ ሲቃረብ ቁርአን ከምድር ላይ ይነሳል
ያኔ ቂያማ ሲቃረብ ቁርአን ወደ ሰማይ ከተነሳ ቡሀላ ሰወች በእጃቸው ላይ ይዘውት የነበረውን ቁርአናቸውን እንደለመዱት ለመቅራት ልክ ሲከፍቱት ንፁህ ባዶ ወረቀት ብቻ ሁኖ ያገኙታል የቁርአን አያዎቹ ሙሉበሙሉ ጠፍተው ያያሉ
እጅግ በጣም ይደነግጣሉ
ይሄን ነገር ለመጀመሪያ ግዜ የሚያዩት ሰወች ሌላ ቁርአን ፍለጋ ይሄዱና ያንንም ገልጠው ሲመለከቱት ልክ እንደመጀመሪያው ባዶ ንፁህ ወረቀት ብቻ ሁኖ ያገኙታል
ሁሉም ይሄን እውነታ ይደርሱበታል በቃ ከምድር ላይ ቁርአን እንደተነሳ ያምናሉ
ከዛም ከመካከላቸው አንዱ በሒፍዙ ሀፍዞት የነበረውን ቁርአን ለመቅራት ይሞክራል
ግና መቅራት አይችልም ! አዎ በፍፁም መቅራት አይችልም እንዳለ ሁሉንም የሀፈዘውን አላህ ከጭንቅላቱ ውስጥ አንስቶበታል አንዲትም የቁርአን አንቀፅ እንኳን አስታውሶ መቅራት አይችልም
ምክኒያቱም ከሰው ልጆችም አይምሮ ላይ ቁርአን ተንስቷል ያኔ
ያኔ ምድር ላይ አንድም ሰው አንዲትን እንኳን የቁርአን አንቀፅ ማስታወስ አይችልም
ከዛም አለም ላይ ያሉ ሰወች ሁሉ "ቁርአን ሙሉበሙሉ ወደሰማይ እንደተነሳ ያምናሉ
ታላቁ ሶሀባ አብደላህ ኢብኑ መስዑድ እንዲህ አሉ፦ ልክ ቂያማ ሲቃረብ የሆነች ሌሊት ላይ ቁርአን ወደሰማይ ይነሳል ፡ ያኔ ምድር ላይም ሆነ በሰወች አይምሮ ላይ አንዲት የቁርአን አንቀፅ ሳትቀር ይነሳል።
📒📔📘 ሱነን አድ ዳሪሚይ
አቡ ሁረይራ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና እርሳቸው እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ አሉ፦ ቂያማ ሲቃረብ የሁለት ወልጋዳ እግሮች ባለቤት የሆነ ሀበሻዊ ሰው ካዕባን ያፈርሰዋል፣ ከምድር ላይ አላህ ቁርአንን ያነሳዋል ፡ አጠቃላይ ምድር ላይም በሰወች ልብ ውስጥም አንዲት እንኳን የቁርአን አንቀፅ አትቀርም ያኔ።
📒📕📔📘 አል ቡኻሪ
💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
