en
Feedback
መርጌታ ይኸይስ የባሀል መድሃኒት ቀማሚ እና

መርጌታ ይኸይስ የባሀል መድሃኒት ቀማሚ እና

Open in Telegram
981
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ነብዩ መሀመድ (ሰ,ዐ,ወ) እንዲህ አሉ፡- ፡ 5 ነገሮችን ከ 5 ነገሮች በፊት ተጠቀሙባቸው አሉ፡- ፡ ➊. ወጣትነትህን~ከማርጀትህ በፊት ➋. ጤንነትህን~ከመታመምህ በፊት ➌. ሀብትህን~ድህነት ከመምጣቱ በፊት ➍. ትርፍጊዜህን ~በስራ ከመወጠርህ በፊት ➎. ህይወትህን~#ከመሞትህ በፊት ፡ ፡ አላህ ሆይ መጨረሻንን አሳምርልን ያረብ አሚን :::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

👛ለውዷ እህቴ ውድ ምክር👛 ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦ ''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''' በመጽሐፉ ውስጥ መርየምንም ከቤተሰቧ ወደ ምሥራቃዊ ስፍራ በተለይች ጊዜ (የሆነውን ታሪኳን) አውሳ፡፡ فَاتَّخَذَتْ مِن دُونِهِمْ حِجَابًا فَأَرْسَلْنَا إِلَيْهَا رُوحَنَا فَتَمَثَّلَ لَهَا بَشَرًا سَوِيًّا ከእነሱም መጋረጃን አደረገች፡፡ መንፈሳችንምም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፡፡ ለእርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት፡፡ قَالَتْ إِنِّي أَعُوذُ بِالرَّحْمَٰنِ مِنكَ إِن كُنتَ تَقِيًّا «እኔ ከአንተ በአልረሕማን እጠበቃለሁ፡፡ ጌታህን ፈሪ እንደ ሆንክ (አትቅረበኝ)» አለች፡፡ ✅ተመልከቺ👆እህቴ የአርአያሽን መርየም ጥግ የደረሰ ኢማን የሞላው ምላሽ : በዛ በረሀ ሰው ዝር በማይልበት: መልከ መልካሙ ጅብሪል በሰው ተመስሎ ገና ሳይቀርባት ባእድ ሰው በመሆኑ ብቻ አላህን ምትፈራ ከሆንክ አትቅረበኝ: በአረህማኑም እጠበቃለው ስትል ክብሯን የጠበቀችው። ታድያ ለምን አንቺስ ብትሆኚ hi እያለ በጓሮ በረ ሚሽሎከለከውን የሸይጣን ጓደኛ : በአረህማኑ እጠበቃለ እያልሽ የመርየምን ሱና ሀይ አታደርጊም!??🙏🙏👍 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

አኽላቃችን‼️ ======= ✍ከሰዎች ጋር ያለን ስነ-ምግባር እንዲስተካከል ከሚያግዙ ትልልቅ ነገሮች መካከል አንዱ፤ እራስን ዝቅ ማድረግና ጥፋተኝነትን ማመን (ልሳሳት እችላለሁ ማለት) ነው። || ይህን ያልታደለ ሰው ሁሌም እራሱን ንጹህ አድርጎ በማየቱ ሰዎችን እየበደለ ይኖራል። * ✔️የሰዎችን ጉድለት እንደምናያው ሁሉ የራሳችንን ጉድለትም የምናይበትን የልብ ዓይን አላህ ይስጠን‼️ 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

وعَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ -رَضِيَ اللهُ عَنْهُ- قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ -صلى الله عليه وسلم-: "أَكْثَرُ مَا يُدْخِلُ الجَنَّةَ: تَقْوَى اللهِ، وَحُسْنُ الخلُقِ" أَخْرَجَهُ التِّرْمِذِيُّ وَصَحَّحَهُ الحَاكِمُ (1). አቡ ሁረይራ (ረ.ዓ) እንዳሉት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል ጀነትን ብዙ የሚያስገባው የአላህ ፍራቻ(ተቅዋ) እና መልካም ስነምግባር ነው። ቲርሚዚይ ዘግበውታል وَعَنِ ابْنِ مَسْعُودٍ -رَضِيَ اللهُ عَنْهُ- قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ -صلى الله عليه وسلم-: "اللَّهُمَّ كَمَا حَسَّنْتَ خَلْقِي فَحَسِّنْ خُلُقِي" رَوَاهُ أَحْمَدُ، وَصَحَّحَهُ ابْنُ حِبَّانَ (1). ኢብኑ መስኡድ (ረ.ዓ) እንዳሉት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል አላህ ሆይ አፈጣጠሬን እንዳሳመርከው ስነምግባሬን አሳምረው። 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

ዝምታው አልበዛም ❓ ስንሄድ ስንቀመጥ ስንሰራ ለምንድነው ዝም የምንለው አስቲግፋር ከአንደበታችን ለምን ራቀ ቁርዐኑም ሊርቀን ዳር ዳር እያለ ነው!! ያ እንዲሆን አንፍቀድ ሀታ ሱረቱል ፋቲሀ ቢሆን ምንም ቁርዐን ባንሀፍዝ ሺ ጊዜ ይቀራ ኪሳራ የለውም!!! 💚 መዋደቅ መተናነስ ለእሱ የተገባ ነው ልባችን ከበላይነት ስሜት ሰበር ይበል! 💚~ የቢላል ዘሮች በዲን ጠንካራ ናቸው ፆማችሁን ያዙ ዚክራችሁን አብዙ ▪️ብዙ ማውራትን ቀንሱ ▪️ዱአችሁ ላይ በርቱ ☂እያሰባችሁኝ በዱአውም ኢን ሻ አላህ ☂ሀጃችሁም ይውጣ የሙራዳችሁ ይሙላ ☂አገራችንን ሰላም ያርግልን ☂ይህን ወረረወሽኝም አላህ በራህመቱ ያንሳልን ☂በዲናችን ላይ ያሰፈሰፉውትን ፈተናዎች ድራሻቸውን አላህ ያጥፋልን በልዩነት ውስጥ ያለውን ውብ አንድነት ይስጠን ያ ረብ ያ ረብ … ………………¶ ቢል አማና በዱዐችሁ አስቡኝ እኔ አረሳችሁም 💚 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

🍂 ጥሩ ጓደኛ ካለህ በተኛህበት አላህ ሊምርህ ትችላለህ قال كعب الأحبار رحمه الله تعالى: ከእብ አልአህባር አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል ‏【«رُب قائم مشكورٌ له، ورب نائم مغفور له؛ وذلك أن الرجلين يتحابان في الله، فقام أحدهما يصلي؛ فـ رضي الله صلاته ودعاءه، فلم يرد عليه مِن دعائه شيئًا، فذكر أخاه في دعائه من الليل، فقال:يا ربّ أخي فلان اغفر له؛ فغفر الله له وهو نائم።】 አንደኛው በሰራው የሚመሰገንና ሌላኛው ደሞ በተኛበት ወንጀሉ የሚማርለት አለ። 👇ይህም የሚሆነው ሁለት ለአላህ ብለው በጣም የሚዋደዱ ጓደኛሞች ነበሩ። አንደኛው ሌሊት ሊሰግድ ቆመ። አላህም ሶላቱና ዱአው ወደደለት። ከዱአውም ምንም ነገር ሳይመልስ አላህ ተቀበለው። በዚህ በሚሰግድ ጊዜ ዱአ ሲያደርግ የተኛው ወንድሙን አረሳውም ዱአ አደረገለት። ጌታዬ ሆይ እገሌ የሚባለው ወንድሜ ወንጀሉን ማረው አለ። በዚህ ወንድሙ ዱአ አማካኝነት በተኛበት አላህ ወንጀሉን ማረው። 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

#የጁመዓ ቀን ሱናዎች እና አዳቦች 🗣ሱረቱ ከህፍን ማንበብ፣ 🚿ሻወር መውሰድ፣ 🚰መፋቅያ መጠቀም፣ 🥋ጥሩ ልብስ መልበስ፣ 🧴ሽቶ መቀባት (ለወንድ) 🕗በጊዜ መስጂድ መሄድ፣ 👉በሀቢቡና (ሰዐወ) ላይ ሰለዋት ማውረድ፣ 🤲ዱዓ ማብዛት። ኹጥባን በዝምታ ማዳመጥ🙊 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

🦋#ጁመአ_ሙባረክ🦋 ﴿#إِنَ_الله_ومَلائكته يُصَلُّونَ على النَّبِيِّ يا أَيها الذين آَمنُوا صَلوا عَليهِ وسَلِّموا تَسلِيمًا} لبيك ا
🦋#ጁመአ_ሙባረክ🦋 ﴿#إِنَ_الله_ومَلائكته يُصَلُّونَ على النَّبِيِّ يا أَيها الذين آَمنُوا صَلوا عَليهِ وسَلِّموا تَسلِيمًا} لبيك اللهم ربي وسعديك صلوات الله البر الرحيم،والملائكة المقربين،والنبين والصديقين، والشهداء، والصالحين ،وما سبح لك من شئ يارب العالمين على سيدنا محمد بن عبد الله خاتم النبيين وسيد المرسلين، وإمام المتقين،ورسول رب العالمين، الشاهد البشير، الداعي إليك بإذنك السراج المنير ﷺ، ﷺ 🌹 ............................🌹 ﷺ📿 ﷺ ﷺ🌹 ..................🌹 ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ🌹.......🌹 ﷺ ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ🌹 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ📿 ﷺ 🌹 .............................🌹 ﷺ📿 ﷺ ﷺ🌹 ..................🌹 ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ🌹.......🌹 ﷺ ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ🌹 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ📿 ﷺ 🌹 .............................🌹 ﷺ📿 ﷺ ﷺ🌹 ..................🌹 ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ🌹.......🌹 ﷺ ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ🌹 ﷺ ﷺ ﷺ📿 ﷺ 🌹 .............................🌹 ﷺ📿 ﷺ ﷺ🌹 ..................🌹 ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ🌹.......🌹 ﷺ ﷺ ﷺ📿 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ🌹 ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ📿 በነብዩ ﷺ ላይ ሰለዋት ማውረድን እናብዛ! 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

ከእለታት አንድ ቀን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዓንሃ ለነብዩ እንዲህ ስትል ጠየቀቻቸው:- « አንቱ የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ከባለቤቶችህ ሁሉ በጣም የምትወዳት ማን ናት?» ነብዩም «ዓኢሻ ሆይ! አንቺን ነው።» አሏት! እሷም እንዲህ አለች « ስለዚህ እነሱ ጋር ሂድና(እኔን በጣም እንደምትወደኝ) ለሁሉም ንገራቸው!» ነብያችን(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ፈገግ አሉና ሳቁ ፤ በመቀጠል ቀለበት ሰጧትና እንዲህ አሏት...... ሱብሀነላህ አጃይብ የሆነ ቂሷ ነዉ😱 ሙሉዉን ማንበብ ከፈለጉ ይህን ይጫኑ ወላሂ ዉሸት አይደለም👇👇👇

አስተውይ እህቴ‼️ ✅ ለምን ይመስልሻል⁉️ በሸሪአችን ሴት ልጅ፦ ➲ነብይ ወይም ረሱል ተደርጋ ያልተላከችው ❗️ ➲ቃዲ ሆና ፍርድ ሰጪ ያልተደረገችው ❗ ➲ኢማም ሆና ሰዎችን የማታሰግደው❗ ➲ለሶላት እንድትጠራ ሙአዚን ያልተደረገችው❗ ➲የሶላት ማእዘን የሆነውን ፋቲሀ ወንዶች ባሉበት ድምፇ ከፍ አድርጋ መቅራትን የተከለከለችው❗ ➲ኢማሙ ቢሳሳት እንድታጨበጭብ እንጂ በድምፅ መመለስ ያልተፈቀደላት❗ ➲በሀጅ ተልቢያ (ለበይከላሁመ ለበይክ) ስትል ድምፃ ከፍ እንዳታደርግ የታዘዘችው❗ ➲በተከበረው ቁርአን ድምፃችሁ አታለስልሱ የተባለው❗ ➡️ለምን ይመስልሻል⁉️ ✅መልሱ፦ የሴቶች ድምፅ ወንዶችን ስለሚፈትንና ስለሚያሳስት ነው። በዚህ ሰበብ ጥፋት ላይ ላለመውደቅ በሩን ለመዝጋት ሲባል ነው። 💢 ታዳ አላፊ አግዳሚው ባለበት፣ የሴት ልጅ አዳኝ ጠላቶች በበዙበት፣ ካፊር ፋሲቅ ሙናፊቁና የሁዳ በግልፅ በሚታይበት በየ ሚዲያው ድምፅሽን የምትለቂው፣ በቪድዮ የምትቀርቢው፣ ከወንዶች ጋር ያለሀጃ እንደፈለግሽ የምታወሪው እህቴ ሆይ ተይ ተመከሪ። ነገ አላህ ፊት ቆመሽ ከመጠየቅሽ በፊት ዛሬውን ተመለሺ። ዝናው፣ ጥቅሙ፣ ዳእዋውም፣ ለሴቶች ያለሽ ተቆርቋሪነቱም ቀርቶብሽ ባንቺ ድምፅም ሆነ በሌላ ነገር ወንዶች እንዳይፈተኑብሽ ማድረግሽ ይህ ትልቅ ጅሀድ ነው። አላህም ያዘዘሽ በዚሁ ነው። ማስተማርና መምከርም ከፈለግሽ ሴቶች ብቻ ባሉበት ወንዶች በማይገኙበት ቦታ ይሁን። 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

⭐️ይህ የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ታላቅ ምክር ነው። አንድ ሰው ወደ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጋ መጣና "ለዱንያም ሆነ ለአኼራ የሚጠቅም ንግግር ለመጠየቅ መጣው" አላቸው ። እሳቸውም ደግሞ "የመጣልህን ጠይቅ" አሉት። ⭐️"ከሰው ሁሉ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለው?" እሳቸውም "አላህን ፍራ" አሉት ⭐️ "ከሰው ሁሉ ሀብታመ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው። "ባለህ ነገር ተብቃቅተ አላህን አመስግን" አሉት ⭐️"ትክክለኛ ፈራጅ እና ታማኝ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "ለራስህ የምትወደውን ለሰዎች ውደድ" አሉት። ⭐️ "ከሰው ሁሉ ብርቱ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "በአላህ ተወከል"አሉት ⭐️ "በአላህ ዘንድ ብቸኛ ተመራጭ ለመሆን እፈልጋለው" ሲላቸው? "ዚክር አብዛ" አሉት። ⭐️ "ከሰው ሁሉ በላጭ ለመሆን እና ጥሩ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "ለሰው ጠቃሚ ሁን" አሉት። ⭐️"የተከበረና ቸር ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው "ችግርህን ለፍጡር አትንገር" አሉት። ⭐️"ረሱል እና አላህ እንዲወዱኝ እፈልጋለው?" ሲል "አንተም እነሱ የወደዱትን ውደድ" አሉት:: ⭐️"ከወንጀል የጠራው ሁኜ አላህንመገናኘት እፈልጋለው" ሲል "ጀናባህን በደንብ ታጥበ እስቲግፋር አብዛ ማልቀስ መተናነስ መታመም አለብህ" አሉት። ⭐️ "ከበጎ ሰሪወች ለመሆን እፈልጋለው" ሲላቸውም "አላህን ልክ እንደምታየው ሁነክ ተገዛው" አሉት። ⭐️"ኢማኔ እንዲ ሞላ እፈልጋለው" ሲል "ፀባይህን አሳምር" አሉት። ⭐️"እርዝቄ እንዲሰፋ እፈልጋለው" ሲል "ተዋዱዕ አዘውትር" አሉት። ⭐️"ዱዓዬ ሙስተጃብ እንዲሆንልኝ እፈልጋለው?" ሲላቸው "ሀራም አትብላ" አሉት:: ⭐️ "አላህን ከሚታዘዙ ሰዎች ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "ግዴታዎችህን ፈፅም" አሉት። ⭐️"በአላህ ዘንድ ትልቁ ሀሠና ወይም ደግ ሥራ የቱ ነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው "መልካም ፀባይ መተናነስ እና በበላ ላይ ሰብር ማድረግ ነው" አሉት። ⭐️"በአላህ ዘንድ የትኛው ስርዓት ነው መጥፎ ሥራ?" ሲል ሲጠይቃቸው "መጥፎ ፀባይና ፍላጎትን መከተል ናቸው" አሉት ⭐️"በዱንያም ሆነ በአኼራ የአላህን ቁጣ የሚያበርድ ምንድነው" ሲል ጠየቃቸው? "ድብቅ ሰደቃ እና ዘርን መቀጠል ናቸው" አሉት። ⭐️ "የቂያማ ቀን በአላህ ኑር ለመሰብሰብ እፈልጋለው?" ሲል "ሰውን አትበድል" አሉት ⭐️"የቂያማ እለት አላህ እንዲያዝንልኝ እፈልጋለው?" "ለአላህ ባርያዎች እዘን" አሉት። 〰 "የቂያማ ቀን የጀሀነም እሳት የሚያጠፋው ምንድነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው "በችግር ላይ ወይም በሙሲባ ላይ ትህግስት መሰድረግ ነው" አሉት። ⭐️ "የቂያማ እለት ነውሬ እንዲሸፈንልኝ እፈልጋለው?" ሲል "የወንድምህን አይብ ሸፍን" አሉት። ⭐️"የቂያማ ቀን ከአላህ ቁጣ ሰላም ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "በአንድም ፍጡር አትቆጣ" አሉት። አላህ ሱብሃን ወተአላህ ባወቅነው በስማነው የምንስራ ያድርገን አሚን! 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

#የሶላት_ማእዘናቶች #የሶላት ማእዘናቶች አስራ አራት ናቸው ፤ እነርሱም ፦  ከመቻል ጋር  መቆም, ተክቢረቱል ኢሕራም, ፋቲሓን መቅራት, ረኩዕ, ከሩኩዕ በኋላ ተስተካክሎ መቆም, በሰባት አካላቶች ላይ ሱጁድ ማድረግ, ከሱ መነሳት, በሁለት ሱጁዶች መካከል መቀመጥ, በየተግባራቱ ላይ እርጋታ መኖር, በማእዘናቶች መካከል ቅድመ-ተከተል መጠበቅ, የመጨረሻው ተሸሁድን መቅራት, ለተሸሁዱ መቀመጥ, በነብዩ - ﷺ - ላይ ሰለዋት ማውረድ, እና ሁለት ሰላማታዎች። ° ▪️ #ሩክን ማለት ፡ የአንድ ነገር ወሳኝ ወይም ጠንካራ ክፍል ነው። የሶላት ሩክን የሚባሉትን ነገሮች ረስቶም ይሁን አውቆ ካልተገበረ ሶላቱ ተቀባይነት የለውም። ° 🍃 #1ኛው ሩክን ፡ #ከመቻል_ጋር_መቆም_ነው ፡ አንድ ሰው አቅሙ ካለው ቆሞ መስገድ አለበት ፤ አቅሙ እያለው ተቀምጦ ከሰገደ ሶላቱ ተቀባይነት የለውም። ረሱል - ﷺ - እንዲህ ይላሉ ፦ [ ቁመህ ስገድ ካልቻልክ ተቀምጠህ ካልቻልክ ተጋድመህ ስገድ ] (ቡኻሪ ፥ 1117). አንድ ሰው መቆም የሚችለበትን ያክል ድረስ እና መቆሙ ኹሹዕን እስካላሳጣው ድረስ መቆም አለበት። ለምሳሌ ፋቲሓ እስኪያልቅ ድረስ መቆም ከቻለ እስከዛ ድረስ ቆሞ ይስገድ። ° 🍃 #2ኛው ፡ #ተክቢረተል_ኢሕራም ፡ ትርጉሙም እርም የሚያደርግ ተክቢራ ማለት ሲሆን ከሶላት በፊት የተፈቀዱ ነገሮችን እርም ስለሚያደርግ ነው እንዲህ የተባለው። ተክቢራውም አሏሁ አክበር በሚል ቃል ነው የሚፈፀመው ፤ ከዚህ ውጭ ባለ ቃል ለምሳሌ አሏሁ አጀል ወይም አሏሁ ከቢር ቢል ተቀባይነት የለውም። ነብዩ - ﷺ - ሶላቱን ላበላሸው ግለሰብ እንዲህ ብለውታል ፦ [ ለሶላት መቆም ባሰብክ ጊዜ ዉዱእህን ሞልተህ በደንብ አድርግ ከዛም ወደቂብላ ተቅጣጭ እና አሏሁ አክበር (በል) .. ] (ቡኻሪ ፥ 6251). ° 🍃. #3ኛው. #ፋቲሓን_መቅራት ፡ ፋቲሓን በየረከዓው ላይ መቅራት ግዴታ ነው ፤ ፋቲሓን ካልቀራ ሶላቱ ተቀባይነት የለውም። ነብዩ - ﷺ - እንዲህ ብለዋል ፦ [ የመፅሐፉ መክፈቻን (ፋቲሓን) ላልቀራ ሰው ሶላት የለውም። ] (ቡኻሪ ፥ 756 ). ፋቲሓ የቁርአን እናት በመባልም ትታወቃለች። በቀን 17 ጊዜ የምንደጋግመውን ፋቲሓ ትርጉሙን ማወቅ በጣም አንገብጋቢ ነገር መሆኑ በደርሱ ላይ ተነግሯል። ° 🍃 #4ኛው. #ሩኩዕ_ማድረግ ፡ ሩኩዕን መተው ወይም ተረጋግቶ አለማድረግ ሶላትን ያበላሻል። አሏሁ - ተዓላ - እንዲህ ይላል ፦ { يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا ارْكَعُوا ... } [| እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! (በስግደታችሁ) አጎንብሱ .. |] (ሐጅ ፥ 77) ° 🍃 #5ኛው. #ከሩኩዕ_በኋላ_መረጋጋት ፡ ነብዩ - ﷺ - ሶላቱን ላበላሸው ሰውዬ እንዲህ ይላሉ ፦ [ ከዛም ቆመህ እስክትረጋጋ ድረስ ተነስ። ] (ቡኻሪ ፥ 793). አንድ ሰው ከሩኩዕ ተነስቶ ተረጋግቶ መቆም ይኖርበታል ፤ ብዙዎቹ ሰዎች ጋር ግን ይህ ተግባር ሲጣስ ይታያል። በመሆንም ተረጋግቶ ያልቆመ ሰው ወይም ረስቶ ወደ ሱጁድ የወረደ ሰው ተመልሶ አንድ ረከዓ ማምጣት ይኖርበታል። ° 🍃 #6ኛው. #በ7_አካላት_ሱጁድ_ማድረግ ፡ ነብዩ - ﷺ - ሶላቱን ላበላሸው ግለሰብ ተከታዩን ብለዋል ፦ [ በሰባት አካላት ሱጁድ እንዳደርግ ታዝዤያለሁ። ] (ቡኻሪ ፥ 812). እነርሱም ፦ 2መዳፎች, 2ጉልበቶች, 2የእግር ጣት ጫፎች, ግንባር እና አፍንጫ (2ቱ እንደአንድ ተቆጥረው ማለት ነው።) ° 🍃 #7ኛው. #ከሱ_መረጋጋት ፡ ማስረጃውም ነብዩ - ﷺ - ሶላቱን ላበላሸው ግለሰብ ተረጋግተህ ተቀመጥ ካሉት በኋላ [ ሱጁድ አድርገህ እስክትረጋጋ ድረስ ሱጁድ አድርግ. ] ማለታቸው ነው። ° 🔻8ኛው.#በሁለት_ሱጁድ_መካከል_መቀመጥ ፡ ነብዩ - ﷺ - ሶላቱን ላበላሸው ግለሰብ ተከታዩን ብለዋል ፦ [ በመቀመጥ ላይ እክስትረጋጋ ድረስ (ከሱጁድ) ተነስ. ] ° 🍃9ኛው. #በእያንዳንዱ_ማእዘናቶች_ላይ_መረጋጋት ፡ ማስረጃውም ከላይ እንዳየነው ነብዩ - ﷺ - ሶላቱን ላበላሸው ግለሰብ መረጋጋት እንዳለበት መናገራቸው ነው። መረጋጋት የሚገለፀው የወገቡ አጥንቶች ወደቦታቸው እስኪመለሱ ደርስ ነው። በዚህ መጠን እስካልተረጋጋ ድረስ ሶላቱ ተቀባይነት የለውም። ምክንያቱም ነብዩ - ﷺ - ሶላቱን ያለመረጋጋት ለሰገደው ግለሰብ [ ሂድ እና ደግመህ ስገድ አንተእኮ አልሰገድክም። ] ብለውታል።(ቡኻሪ ፥ 793). ° 🍃 #10ኛው #በማእዘናቶች ላይ #ቅድመ-#ተከተልን_መጠበቅ ፡ ነብዩ - ﷺ - አንድም ቀን ተርታውን ሳይጠብቁ ሰግደው አያውቁም። በመሆኑም ቅድመ ተከተሉን ያዛባ ሰው ሶላቱ ተቀባይነት የለውም። ° 🍃11ኛው. #የመጨረሻው_ተሸሁድ_መቅራት ፡ ማስረጃውም ዐብደሏህ ኢብኑ መስዑድ - ረዲየሏሁ ዐንሁ - እንዲህ ለማለቱ ነው ፦ [ በሶላት ውስጥ ተሸሁድ ግዴታ ሳይሆን በፊት እኛ እንል ነበር ... ] (ነሳኢይ ፥ 1277). የመጀመሪያውን ተሸሁድ የረሳ ሰው በሱጁድ-አስሰሕው ይጠገናል ፤ የመጨረሻውን የረሳ ግን ሶላቱን መድገም ይኖርበታል። ° 🍃#12ኛው. #ለሱ_መቀመጥ ፡ ለመጨረሻው ተሸሁድ መቀመጥ ማለት ነው። ° 🍃 #13ኛው. #በመጨረሻው ተሸሁድ ላይ በነብዩ - ﷺ - ላይ #ሰለዋት ማውረድ ፡ ይህም ከኢማሙ አሕመድ መዝሀብ የታወቀው ነው።(ሙንተሃል ኢዳራት ፥ 1/63). ° 🍃14ኛው. #ሁለቱ_ሰላምታዎች ፡ 2ቱ ሰላምታዎች እንደአንድ ሩክን ነው የሚታዩት ፤ ሰላምታዎችን ከረሳ የሶላት ማእዘንን ስለረሳ ሶላቱ ትክክል አይሆንም ማለት ነው። አዟዟሩ ደግሞ ለጀርባ ላለው ሰው ጉንጩን እስኪያሳይ ድረስ መዞር ነው። 👉 { من يريد الله به خيرا يفقهه في الدين }. رواه البخاري [ አላህ ኸይርን የሻለት ሰው የዲኑን ግንዛቤ ይሰጠዋል። ] (ቡኻሪ ፥ 71) { من دلَّ على خير، فله أجر فاعله }. رواه مسلم [ ወደ ኸይር ነገር ያመላከተ ፤ የሰሪውን ያክል ምንዳ አለው። ] (ሙስሊም ፥1893) •════•••🌺🍃•••════• 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

📵ዋናው አጠቃቀምህ ነው‼ 🌐አጠቃቀሙን ላወቀበት ኢንተርኔት ከጊዜው የአላህ ፀጋዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ደዕዋ ይደረግበታል፣ መረጃ ይሠጥበታል፣ ንግድ ይነገድበታል፣ ጓደኛ ይፈራበታል፡፡ ♻️ ካልቻሉበትና አጠቃቀሙን ካላሳመሩ ጉዳቱም በዚያው ልክ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ፌስቡክ የብዙ ወጣቶችን ጊዜ እየበላ ነው፣ ዕድሜያቸውን እንክት እያደረገ ነው፡፡ ቁርኣን ተዘግቷል፣ ሐዲሥ ተረስቷል፣ ቁምነገር ተዘንግቷል፡፡ 📵ጉዳቶቹ 1- ከመጥፎ ጓደኞች ጋር ሊያገናኝ ይችላል፣ 2- እምነትና አመለካከትን የሚፈታተኑ መረጃዎች ይለቀቁበታል፣ 3- ሞራልና ሥነምግባርን ይሸረሽራል፣ 4- ከዚክር እና ከሶላት ያዘናጋል፣ 5- ይበልጥ ጠቃሚ የሆነውን ነገር ከመሥራት ወደኋላ ያስቀራል፣ 6- ለስንፍና እና ድክመት ያጋልጣል፣ 7- ጊዜና ዕድሜን ወደማባከን ያደርሳል፣ 8- ከትምህርትና ጥናት ያርቃል፣ 9- ለአልባሌ ሱስ ይዳርጋል፣ 10- የትዳር ሕይወትን ለአደጋ ያጋልጣል፣ 11- ሥራ ያስፈታል 🔆ከጥቅሞቹ መካከል 1- ወደ እስልምና ለመጣራት፣ 2- ትክክለኛውን የእስልምና አስተምህሮ ለማሳወቅ፣ 3- ወደ መልካምነትና ሰላም መጣራት፣ 4- በእስልምና ዙሪያ የሚነዙትን የሐሰት ወሬዎች ለማክሸፍ፣ 5- የዲን ዉስጥ ፈጠራዎችንና የሐሰት አስተምህሮዎችን ለመዋጋት፣ 6- ጠቃሚ ትምህርትንና መልካም ሥነምግባር ለማስፋፋት፣ 7- የተለያዩ ጠቃሚ መረጃዎችን ለመቀበልና ለማስተላለፍ፣ 8- ሌሎችም ብዙ ጥቅሞች ስለዚህ ይህን አላህን ፀጋ ጠቃሚ ነገር ላይ በማዋል እንጠቀምበት። 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

አታላይ! ~ "አንቱን መዘከሬ ከሆነ ስህተቴ፣ እኔ አንቱን ዘክሬ ይቅርብኝ ጀነቴ!" ~ "ጀነትን አልፈልግም" ማለት የራሳችሁ ምርጫ ነው። ነብዩ ﷺ "ሁሉም ህዝቦቼ ጀነትን ይገባሉ፣ እምቢ ያለ ሲቀር" ብለዋል። እምቢታ ማለት ትእዛዝን አለመቀበል ነው። "አንቱን መዘከሬ ከሆነ ስህተቴ" የሚለው ግን ቀንዳም ውሸት ነው። በዚህ ቅጥፈት መሰረት:– ~ መውሊድ የማይጨፍር ሰው ነብዩን ﷺ በሶለዋት አያወሳም ማለት ነው። አይን ያወጣ ቅጥፈት! ~ እሳቸውን ማውሳት ማለት በመውሊድ መጨፈር ከሆነ አመቱን ሙሉ ረስታችኋቸው የምታወሷቸው በመውሊድ ቀን ብቻ ነው ማለት ነው። ~ ድግስ ካልተደገሰ፣ ጭፈራ ካልተጨፈረ ነብዩን ﷺ ማውሳት አይቻልም ማለት ነው። ~ በርካታ የመውሊድ ደጋፊዎች ቢድዐ መሆኑን ያምናሉ። የአሕባሽ ቲቪም ሰሞኑን ይህንኑ አረጋግጧል። መውሊድ ከጊዜ በኋላ የመጣ መጤ ፈሊጥ በመሆኑ ላይ ከተስማማችሁ፣ እሳቸውን ማውሳት ማለት መውሊድ መጨፈር ከሆነ ይሄ መውሊድ ከመጀመሩ በፊት ያለፉት ሶሐቦች፣ ታቢዒዮች፣ አትባዑ ታቢዒን፣ አኢማዎች ሁሉ ነብዩን ﷺ አውስተው አያውቁም ማለት ነው። ከዚህ በላይ ቅጥፈት አለ?! ~ እነዚህ ሰዎች ዘንድ ነብዩን ﷺ ማውሳት ማለት አመት ጠብቆ መደለቅ፣ መደነስ ነው። ሎጂካችሁ ጭፈራቸውና ዝላያቸው እየሱስን ከመውደድ የተነሳ እንደሆነ ከሚሞግቱት ጴንጤዎች ጋር ያመሳስላችኋል። እንዲያውም ቅጥፈት ከመሆኑም ጋር የነሱ ሎጂክ ከናንተ ሎጂክ ይሻላል። የሚያዘልላችሁ ፍቅር ከሆነ በአመት አንድ ጊዜ ከሚጨፍረው ይልቅ በየሳምንቱ የሚጨፍረው የበለጠ ያፈቅራል ማለት ነው። ይልቅ እሳቸውን በመውደድ እያመሃኘ ከፊሉ እንጀራውን የሚያበስል፣ ከፊሉ የጭፈራ ሱሱን የሚያስተነፍስ፣ ሌላው ለብልግና አጋጣሚውን የሚጠቀም፣ ሌላው ደግሞ ምኑም ሳይገባው "ሲሉ ሰማሁ ብዬ፣ እላለሁ ነብዬ" የሚል የደመቀ አጫፋሪ ነው። ~ 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

⭕️ጥሩ ሰው እንዳልሆንኩ እኔው ራሴ አውቃለሁና አስረጂኝም ሆነ ምስክር አያሻኝም፤ ሁኔታዬ አላህ (ሰ.ወ) ስለ አንዳንድ ባሮቹ እንዳለው “ኸይርና ሸርን ከሚቀላቅሉት፣ ጥፋታቸዉንም ከሚያምኑት” ነው፡፡ 📌 ወደ አላህ በመቅረብና በመራቅ መካከል ዘመናትን ኖሬያለሁ፤ እየኖርኩም ነው፡፡ ግና ባጠፋችበት ቅጽበት ራሷን የምትወቅስ፣ ከአምላኳ ከራቀች ዳግም ለመመለስ የምትታገል ነፍስ ሠጥቶኛልና ጌታዬን በብዙው አመሰግናለሁ፡፡ ብታምፅ እንኳ ጠፍታ አትቀርም፣ ብታጠፋ ሸሽታ እዉጭ አታድርም፣ ብትወድቅ ወድቄያለሁ ብላ ተስፋ አትቆርጥም፡፡   በኃጢኣት ፊት ይጠቁራል፣ ደረት ይጠብባል፣ ኑሮ ይጨንቃል፤ በተውባ ግን ፊትም ልብም ይበራል፡፡ 📍 ዋናው ቁምነገር በሕይወት እስካለሁኝ ድረስ መታገሌ ነው፣ እስትንፋሴ እስካለችና በሞት ወደርሱ እስኪወስደኝ ድረስ ራሴን ለማስተካከል መልፋቴ ነው፡፡  ጨለማዎችን ሁሉ ባበራው ብርሃንህ እማፀንሃለሁ፤ ያ ረብ ዘላለማዊ ፀፀትን ከሚያስከትል ወንጀል ሁሌም ጠብቀኝ፡፡ 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

♻️🔺 የጥሩ ባል መገለጫዎች♻️🔺 ➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️🔺 ጥሩ ትዳር መስርቶ መኖር የማንኛዋም ሴት ምኞት ነው፣የጥሩ ትዳር መሰረቱ ጥሩ ባል ነው፣ከጥሩ ባል መገለጫዎች በጥቂቱ እነሆ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ⏬ በሁሉም ነገር አላህን ይፈራል ⏬ ከሚስቱ ጋር በጥሩ ስነ-ምግባር ይኗኗራል ⏫ በተቻለው ያክል ቃሉን ይሞላል ↕️ ለሚሰትና ለልጆቹ መልካም አርዓያ ይሆናል ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ⏬ንግግርና ተግባሩ አንድ ነው (አታላይ አይደለም) ↕️ ሚስቱን ያከብራል ለሷ ያለውንም ፍቅር ይገልጻል ↕️ ሸሪዓ የሰጣትን ሐቅ ይጠብቃል ↕️ዘመድና ቤተሰቦቿን ያከብራል ↕️በሆነ ባልሆነው አይጨቃጨቅም ↕️ ትርፍ ቃል ከመናገር በመታቀብ በመልካም ንግግሮቹ ሚስቱን ያስደስታል 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ↕️ ሚስቱ አላህን እንድትታዘዝና ዲኗን እንድታውቅ ይገፋፋል ያግዛታልም ↕️ስትደሰትም ይሁን ስትከፋ ስሜቷን ይጋራል 〰〰➰➰➰➰➰〰〰〰〰 ↕️ቤቷን ሳትጎዳ ቤተሰቦቿን መጠየቅ ስትፈልግ ከመፍቀድም አልፎ የሚያስፈልጋትን ነገር እንደ አቅሙ ያሟላላታል ↕️ለቤቱ በቂ ወጪ ያደርጋል ለልጆቹና ለሱ በምታደርጋቸው ነገሮች ሁሉ ያመሰግናታል ድምበር ሳያልፍ፥ አለባበሷን፣ ገጽታዋንና የምትሰራቸውን ምግቦች ያደንቃል ↕️ በሁሉም ነገር ላይ እርጋታና ትዕግስትን ተላብሶ ይኖራል ↕️አለመግባባትና ግጭቶች ሲፈጠሩም ሚስቱን እንደ እህቱ በመቁጠርና ለሷ በማዘን ችግሩን ለመፍታት ብዙ ነገሮችን በመተውና ቁጣውን ዋጥ በማድረግ መፍትሄ ይፈልጋል:: ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ↕️ ከሚስቱ ጋር በመተባበር ልጆቹን በኢስላማዊ አደብና እውቀት ቀርጾ ያሳድጋል ↕️ ሚስቱ ጥሩ እንድትለብስለትና ጥሩ እንድትሸት እንደሚፈልገው ሁሉ እርሱም ከሷ ጋር ሲሆን ይሄን ያደርጋል የመላ ሰውነቱን ንጽህናም ይጠብቃል ወንድሞች አላህ መልካም ወንድ ያድርጋችሁ 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

@ማን ናት ኸዲጃ?@ ____ በሞባይል ስልኬ ላይ የባለቤቴን ስም ኸዲጃ ብዬ ነበር save ያደረኩት። ለሷ ግን አልነገርኳትም ነበር። አንድ ቀን ድንገት ስልኬን ስትጎረጉር ኸዲጃ ከምትባል ሴት ጋር በተደጋጋሚ መደዋወሌን ተመለከተች። በንዴት አይኖቿ ቀልተውና ደም ስሯ ተወጥሮ “ኸዲጃ ማን ናት?” አለችኝ። የደነገጥኩ አስመስዬ ዝም ብዬ አየኋት። በዚህን ጊዜ ንዴትዋ ጨምሮ ጮክ ብላ መናገር ጀመረች። አትናገርም? .................. አትመልስልኝም?...... ........................ አንተን መስሎኝ የማናግረው! ............... .......... ማን ናት ኸዲጃ? እያለች የሸሚዜን ኮሌታ ይዛ ትወዘውዘኝ ጀመር። ሳይታወቃት እንቅ............አደረገችኝ። ኸ.....ዲ......ጃ ማን ናት? በል ፍጠን ተናገር! ለምን እሷን እራሷን ማን እንደሆነች አትጠይቂያትም? አልኳት እጆቿን ለማስለቀቅ እየሞከርኩ። እሺ እንደሱ ሳይሻል አይቀርም እኔው እራሴ እጠይቃታለሁ በማለት ወደ ኸዲጃ ደወለች። የራሷ ስልክ ሲጠራ ሰምታ ደዋዩን ስታጣራ ባለቤቷ (እኔ) መሆኑን አወቀች። ግራ በተጋባ ሰው ስሜት “ታዲያ ለምን? እኔ ስሜ ኸዲጃ አይደለም” አለች። ባህሪሽ፡ እዝነትሽ፡ ለኔ ማሰብሽ፡ መጨነቅሽ፡ ፍቅርሽ፡ ቤሳ ቤስቲን ሳይኖረኝ እኔን ለማግባት መፍቀድሽ፤ ..................... አንቺ ለኔ በዱኒያ ላይ ያለሽኝ መተኪያ የሌለሽ ሀብቴ ነሽ፡ አንቺ ለኔ ክብሬ፡ ፍቅሬ፡ መሰተሪያዬ፡ የህይወት አጋሬ ነሽ። በአላህ ፍቃድ በፊርደውሰል አእላ ውስጥም ሚስቴ እንድትሆኚ እፈልጋለሁ። እናታችን ኸዲጃ (ረዲየላሁ አንሃ) የፍቅርና የመልካም ትዳር ተምሳሌት ስለሆነች ነው በርሷ ስም የሰየምኩሽ አልኳት። አይኖቿ እምባ እንዳቀረሩ እሺ በአላህ ፍቃድ ሁሌም መልካም የትዳር አጋርህ ለመሆን እጥራለሁ አንተም ጥሩ በመሆን አግዘኝ አለችኝ። ========================== አንቸኩል፡ በመጥፎ ከመጠርጠር እንቆጠብ share 🌸መልካም ምሽት 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

🌸ትዳር🌸 ትዳር ሃላፊነት ነው መስዋዕትነት ይጠይቃል 📌✍! #ትዳር ማለት መስወዕትነት፣ ቀሪ ህይወታችንን ከአንድ ሰው ጋር ለማሳለፍ የምንወስንበት ትልቅ የህይወት ዘርፍ ስለሆነ ነው ። የትዳር አጋራችንን በምን መመዘኛ እንምረጥ ??❓❓ #ትዳር ትልቅ ሃገር የሚገነባበት መሰረት ነው፣ መሰረቱ ያላማረ ነገር እድሜ የለው ቶሎ ነው የሚፈርሰው ስለዚህ ኢስላም የትዳር መሰረቱ ጠንካራና በቀላሉ የማይፈር ለማድረግ መሰረቱን በዲን እና አኽላቅ ላይ እንዲገነባ ያስተምራል። በርግጥ የትዳር መሰረቶች የተለያዩ ናቸው ነገር ግን ከዲን እና አኽላቅ ውጪ ያሉት መሰረቶች እድሜ የሌላቸው የትዳር ጠንቅ ናቸው። ነገር ግን ዲን እና አኽላቅ የተቀሩትን መሰረቶች ይዘው ይመጣሉ። ﻭﻗﺪ ﺃﺧﺒﺮ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ، ﻋﻦ ﺫﻟﻚ ﺑﻘﻮﻟﻪ : « ﺗﻨﻜﺢ ﺍﻟﻤﺮﺃﺓ ﻷﺭﺑﻊ ﺧﺼﺎﻝ : ﻟﻤﺎﻟﻬﺎ، ﻭﺟﻤﺎﻟﻬﺎ، ﻭﻟﺤﺴﺒﻬﺎ، ﻭﻟﺪﻳﻨﻬﺎ، ﻓﺎﻇﻔﺮ ﺑﺬﺍﺕ ﺍﻟﺪﻳﻦ ﺗﺮﺑﺖ ﻳﺪﺍﻙ» ረሱል صلى الله عليه السلام እንዲህ ብለዋሉ፦ “💯ሴት ልጅ ለአራት ነገሮች ትገባለች። 📌ለገንዘቧ፣ 📌ለዘር ክብሯ፣ 📌ለውበቷና 📌ለዲኗ። ✍የዲን ባለቤት የሆነችውን ምረጥ።👌 (ይህን ላደረግክ) እጅህ አመድ አፋሽ ትሁን።” (ቡኻሪና ሙስሊም) ﺃﻓﻀﻞ ﻣﺎ ﻳﻨﺒﻐﻲ ﺗﻮﻓﺮﻩ ﻓﻲ ﺍﻟﺰﻭﺟﻴﻦ، ﻣﻠﺘﺰﻣﺎ ﺑﺸﺮﺍﺋﻊ ﺍﻹﺳﻼﻡ ﻓﻲ ﺣﻴﺎﺗﻪ ﻓﻼ ﻳﻈﻠﻢ ﺯﻭﺟﺘﻪ، ﻓﺈﻥ ﺃﺣﺒّﻬﺎ ﺃﻛﺮﻣﻬﺎ ﻭﺇﻥ ﻟﻢ ﻳﺤﺒﻬﺎ ﻟﻢ ﻳﻈﻠﻤﻬﺎ ﻭﻟﻢ ﻳُﻬﻨﻬﺎ እጅግ በላጩ ምርጥ ባል ማለት የአላህ ዲን በሚገባ የሚያውቅና ስነ ምግባሩ ያማረ ነው። ዲኑን የሚያውቅ ካገባሽ ከወደደሽ በእጅጉ ያከብርሻል፤ የማይወድሽ ከሆነ አያዋርድሽም ክብርሽን በሚገባ ይጠብቅልሻል። ስለዚህ ዲን ያለው የስነ ምግባር ባለቤት ምርጫሽ ሊሆን ይገባል። በዲናቸው እኩል የሆኑ ሰዎች ለትዳር እጅሽን ከጠየቁ ቤተሰቦቹ መልካም የሆኑትን ምረጪ ምክኒያቱም የእሱ ቤተሰቦች ወደ አንቺ የቀረቡ ናቸውና። ﻟﻘﻮﻝ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﻣﺤﻤﺪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : (ﺧﻴﺮ ﺍﻟﻨﺴﺎﺀ ﻣﻦ ﺇﺫﺍ ﻧﻈﺮﺕ ﺇﻟﻴﻬﺎ ﺳﺮﺗﻚ، ﻭﺇﺫﺍ ﺃﻣﺮﺗﻬﺎ ﺃﻃﺎﻋﺘﻚ، ﻭﺇﺫﺍ ﺃﻗﺴﻤﺖ ﻋﻠﻴﻬﺎ ﺃﺑﺮﺗﻚ، ﻭﺇﺫﺍ ﻏﺒﺖ ﻋﻨﻬﺎ ﺣﻔﻈﺘﻚ ﻓﻲ ﻧﻔﺴﻬﺎ ﻭﻣﺎﻟﻚ ) }ﺃﺧﺮﺝ ﺍﻟﻨﺴﺎﺋﻲ . የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም “ከሴቶች ሁሉ በላጯ የትኛዋ ናት?” ተብለው ተጠይቀው “ሲያያት የምታስደስት፣ ሲያዛት የምትታዘዝ፣ በነፍሷም በገንዘቡም እርሱ የማይፈልገውን የማትፈጽም” ሲሉ መለሱ። # ትዳር ማለት ሃላፊነት ነው፣ መስዋዕትነት ይጠይቃል! መለያየት የሌለበት ሰላም የሰፈነበት የነፃነት አለም ነው። ትዳር ልክ እንድ ሁለት እጅ ነው። አንድ እጅ ብቻውን አያጨበጭብም ስለዚህ የጭብጨባው ድምፅ ፈፅሞ ወደ ልብ አይደርስም፣ ሁለቱም በጋራ ከተደጋገፉ ግን ፈፅሞ ሊጠፋ የማይችል የደስታ ድምፅ በልባቸው ይገባል፣ በደምስራቸው ይዞራል። ነገ ለሚፈጠረው ጀግና ትውልድ ዛሬ ላይ የሁለታቹ ትልቅ ተፅኖ እጅግ አስፈላጊ ነው ትዳር የጭቅጭቅ መፍትሄ፣ ከጭንቀት ማረፊያ የአይምሮ ሰላም አንድ አዕምሮ ከሚሰራ ሁለት አዕምሮ በጋራ ቢሰራ የሚደመር እንጂ የሚቀነስ ነገር የለውምና 📌ትዳር ማለት ችግርን ወይም ተግዳሮትን ለሁለት የሚያካፍል ፣ ደስታ እና ስኬትን ደግሞ በሁለት የሚያበዛ የልብ ወዳጅ ማግኘት ማለት ነው ትዳር / መጣመር አላህ ከዋለልን ፀጋ አንዱ ነው ስለዚህ አዩሀሙስሊሙን ትዳር እጅግ ከሚያስፈልገን ከዱንያ ነገሮች አንዱ በመሆኑ በፍጥነት ለትዳር እጅ ልትሰጡ ይገባል። ትዳር (ኒካህ) እጅግ ቀለል ያለ እራስን ከዝሙት የመጠበቂያ መንገድ ነው። #ትዳር መመስረት እጅግ ቀላል ነው፣ ዘላቂ ለማድረግ ግን ከፍተኛ ትግል ያስፈልጋል. ስለዚህ ትዳራችን ስኬታማ እንዲሆን አቂዳውን ፣ ዲኑ መስፈርታችን መሆን አለበት። ✍✍✍✍✍✍✍ 👇👇👇👇👇👇👇 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channa

#የወንጀል መዘዝ •••••••🔄••••••• ↗ማንንም ከመውቀሳችን በፊት ራሳችንን እንመልከት ጌታችን አላሁ ሱብሃነሁ ወተዓላ [وَمَا أَصَابَكُمْ مِنْ مُصِيبَةٍ فَبِمَا كَسَبَتْ أَيْدِيكُمْ] «ከአደጋዎች ማንኛዋም አደጋ የምትደርስባችሁ በገዛ እጃችሁ በሰራችሁት ነው።» በማለት በሰራነው ጣጣ ለዱንያዊ መከራም እንደምንዳረግ በግልፅ ነግሮናልና ጠንቀቅ ይበጃል። ▫➖➖◽➖➖▫    ↗ #ስለዚህ ኑሯችንን የሚያናጋው ቤታችን የሚያምሰው ወንጀላችን ቢሆንስ ? እንደ ደጋጎቹ አስተውለናልን ! ? قال الفُــضيل بن عياض -رحِــمُه الله-: «እኔ አላህን ያመፅኩ እንደሆን፣ የወንጀሌን ነፀብራቅ በአህያዬ፣ በአገልጋዬና በባለቤቴ ባህሪ እንዲሁም በቤቴ አይጥ የባህሪ ለውጥ አውቃለሁኝ።» ይላሉ ⚂ #ፉደይል ኢብኑ ዒያድ ረሂመሁላህ 📚(البداية والنهاية) (10/215) ሀቅ ነው አብዛኞቻችን ጣቶቻችንን የምንቀስረው በሌላው ላይ ስለሆነ ጥፋታችን አይታየንምና በየደቂቃው ኪሶቻችንን እንደምንፈትሸው ሁሉ ተግባሮቻችንም ተራ ይድረሳቸዋ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ↗ #በተለይ ወላጆቻችንን ባናሳዝን መልካም ነው። ካለፉም ለሀቃቸው እንታገል። ከሠለፎች قال أبــو الحسن القطان -رحِــمُه الله- : «ዐይኔ ላይ አደጋ ደረሰብኝ። ሐዲስና ዒልምን ፍለጋ ከእናቴ በተለየኋት ግዜያት ስለኔ ታለቅስ ነበርና ከሷ ለቅሶ ብዛት የተነሳ እንደተቀጣሁ እገምታለሁ።» ይሉ ነበር ⚂አቡል ሀሰን አልቀጣን ረሂመሁላህ 📚(معجم الأدباء) ( 12 / 220) •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ↗ #ስለዚህም ወደ ሃኪም ሳንሮጥ ራሳችንን እንመርምር   قال الضحاك -رحِــمُه الله- : ደሃክ ኢብን መዛሂም ረሂመሁላህ «አንድ ሰው በፈፀመው ወንጀል ካልሆነ በስተቀር ቁርኣንን ከተማረ በኋላ አይረሳውም። ካሉ በኋላ “ከአደጋዎች ማንኛዋም አደጋ የምትደርስባችሁ በገዛ እጃችሁ በሰራችሁት (ጥፋት) ነው።” የሚለውን የአላህ ቃል አነበቡ። ከዚያም "ቁርኣንን ከመርሳት የባሰ ምን ሙሲባ ኣለ ?!"» ኣሉ። 📚(الجامع لأحكام القرآن)(16/30) ተመልከት በኃጢኣትህ መነባበር የተነሳ ለዱንያም ለኣኺራም ታላቁ ሃብትህን በቀላሉ ታጣለህ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ↗ #ብዙውን ግዜ እያጠፋንም እንታለፋለን። ግን ወዲያው ኣለመቀጣታችን እንዳያዘናጋን፣ ለነገ ክፉ ስንቅ ሆኖ ይጠብቀናልና ከወዲሁ ተውበት እናድርግ። አል አልላማ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁላህ “አንድ ግለሰብ በሆነ በሽታ ወይም ክፉ የሆነ ሌላ ነገር በህይወቱም ሆነ በንብረቱ ላይ ደርሶበት ቢፈተን ይህ ነገር የፈተና መከራ መሆኑን ወይም ከአላህ ዘንድ የመጣበት ቁጣው መሆኑን እንዴት ሊያውቀው ይችላል? ” ተብለው ተጠየቁና ቀጣዩን ጥበባዊ ምላሽ ሰጡ  الجَـــ☟ـــوَابُ: ⚄ #አላህ ባሮቹን በደስታም በጉዳትም በጭንቅም በምቾትም ይፈትናቸዋል። ልክ ለነቢያቱ አለይሂሙ ሰላቱ ወሰላም እና ለደጋግ ባሮቹ እንዳደረገው ደረጃቸውን ከፍ ሊያደርግላቸው፣ ዝናቸውን አጉልቶ ሊያወሳቸውና መልካም ምንዳቸውን ሊያነባብርላቸው ሲል በእርግጥም ይፈትናቸዋል። ይህም ነቢዩ ﷺ «أشد الناس بلاء الأنبياء ثم الأمثل فالأمثل » “ከሰዎች መካከል ፈተና የሚጠናባቸው ነቢያት ሲሆን ከዚያም አምሳያዎቻቸውን፣ አምሳያዎቻቸውን” እያለ በየደረጃው እንደሚቀጥል ተናግረዋል።   በሌላ በኩል ደግሞ ይህን መከራ እንከን አልባው አምላካችን አላህ በኃጢኣትና በወንጀል ሰበብ ያደርሳል። ይህም ልክ “ከአደጋዎች ማንኛወዋም አደጋ የምትደርስባችሁ በገዛ እጃችሁ በሰራችሁት (ጥፋት) ነው።” ብሎ አላህ ሱብሃነሁ እንደተናገረው እዚህቹ ምድር ላይ ሳለን የምንቀጣባት ትሆናለች።  በአብዛኛው የሰው ልጅ ላይ የሚስተዋለው ግዴታውን ያለመወጣት ጉድለቱ ነው። የደረሰበት አደጋም በወንጀሉና የአላህን ትእዛዛት ካለመፈፀሙ ጉድለቱ የተነሳ ነው። ከአላህ መልካም ባሮች መካከል በበሽታና በመሳሰለው ነገር አንዳቸው የተፈተኑ እንደሆነ ግን ይህ ልክ ለነቢያቱና ለመልእክተኞቹ  ደረጃቸውን ይበልጥ ከፍ ለማድረግና ምንዳቸውንም እጅግ የበዛ ለማድረግ እንዲሁም በትዕግስታቸውና ከአላህ ምንዳን ከመተሳሰብ አንፃር ለሌሎቹም አርዓያ እንዲሆኑ በነሱ ላይ እንደ ደረሰው ፈተና ብጤ መሆኑ ነው።     በአጠቃላይ የሚደርሱት መከራዎች ልክ ነቢያቱና አንዳንድ ደጋግ ባሮቹ ላይ እንደደረሰው ደረጃዎችን ከፍ ለማድረግና ምንዳዎችንም ለማብዛት ሲሆን በአንፃሩም አላህ { مَن يَعْمَلْ سُوءًا يُجْزَ بِهِْ } “መጥፎን የሰራ ዋጋውን ያገኝበታል” እንዳለው  ኃጢኣትን ለማበስም ይሆናል።  ነቢዩም ﷺ « ما أصاب المسلم من هم ولا غم ولا نصب ولا وصب ولا حزن ولا أذى إلا كفر الله به من خطاياه حتى الشوكة يشاكها » “ሙስሊሙ ላይ አስጨናቂም ሆነ አሳሳቢ፣ አድካሚም ሆነ አንከራታች፣ አሳዛኝ ሆነ ሌላ ጎጂ ነገር ቢደርስበት በተወጋው እሾህ እንኳ ቢሆን በዚህ ሰበብ ኃጢኣቱን አላህ ሳያብስለት አይቀርም።” ብለዋል። በሌላም ሀዲሳቸው ﷺ « من يرد الله به خيرا يصب منه »  “አላህ መልካም የሻለትን ሰው ፈተናን ያደርስበታል።” ብለዋል።  በሌላም ሀዲሳቸው ـﷺـ « إذا أراد الله بعبده الخير عجّل له العقوبة في الدنيا وإذا أراد الله بعبده الشر أمسك عنه بذنبه حتى يوافي به يوم القيامة » خرّجه الترمذي وحسنه 》. “አላህ ለባርያው መልካምን ሲሻለት በዱንያ ላይ እንዲቀጣ ቀደም ያደርግለታል። በባርያው ላይ ሸርን ሲፈልግ ግን በወንጀሉ እንዲቀጣበት የትንሳዔዋ እለት ድረስ ያቆየዋል።” ባሉት መሰረትም በኃጢኣት ሰበብና ለተውበት ካለመፋጠን የተነሳ አፋጣኝ የሆነ የመከራ ቅጣት ሊደርስ ይችላል።»⚄ ብለዋል ረሂመሁላህ። 📚 [مجموع فتاواه] ( ٤/٣٧٠-٣٧١) #ስለሆነም ወንድም እህቶቼ ባለንበት ሁኔታ እኔ ልክ ነኝ፣ እኛ ልክ ነን ብቻ እያልን ከመኩራራት እንጠበቅ። ራሳችንን ዘንግተን የሰው ጓዳን ከመዳሰስም እንራቅ። ላጠፋነው ኢስቲግፋርና ተውበት አይለየን። በመላው የሙስሊሙ ዓለም የሚስተዋለው እልቂት፣ ቸነፈር፣ ውድቀትና ውድመትም ያለ ምክንያት አይምሰለን። والله اعلم የኃጢኣት መዘዝ ከባድ ነውና አላህ ይጠብቀን። አላሁመ አሚን ሼር ሼር 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal

ላ ኸላሶ ኢላ ቢል ኢኽላስ ኢዘን ሊላሒ_ተዓላ 🍀➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖🍀 أخرج الطبرانيّ في اﻷوسط والمستغفري بسند حسن عَنْ سُمْرَةَ بْنِ جُنْدُبٍ رَضِيَ اللهُ عَنْهُ قالَ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ ﷺ يَقُولُ: مَنْ قالَ إذا أَصْبَحَ وَإذا أَمْسى: اللهُمَّ أَنْتَ خَلَقْتَني وَأَنْتَ تَهْديني وَأَنْتَ تُطْعِمُني وَأَنْتَ تَسْقيني وَأَنْتَ تُميتُني وَأَنْتَ تُحْييني، لَمْ يَسْأَلِ اللهَ شَيْئًا إلّا أَعْطاهُ إيَّاهُ . 🌿▬▬▭▭▭▬▬🌿 አሏሁመ አንተ ኸለቅተኒ✨ ወአንተ ተህዲኒ✨ ወአንተ ቱጥዒሙኒ✨ ወአንተ ተስቂኒ✨ ወአንተ ቱሚቱኒ✨ ወአንተ ቱህይኒ✨ 🌿▬▬▭▭▭▬▬🌿 👆 በመሸና በነጋ ጊዜ ይህንን ያለ ሰውየ አላህን አንድ ነገር አይጠይቅም አሏህም የሚሰጠው ቢሆን እንጂ ﷺ #ጦበራኒይ_ዘግበውታል ▬▬▬▬ ―➖➖➖▬➖▬▬🍃 💌:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @susui_slamic_channal