981
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
# የሰይዲ_ﷺ_ልብስ
ዐብዱላህ ( የአስማእ ቢንት አቢበክር ረ.ዐንሁማ ኻዲም ) :
" አስማእ.. አንዲት ጁባ ( ከላይ የሚለበስ ልብስ ) አወጣችና
እንዲህ አለችን : [ እቺ የአላህ መልክተኛ ﷺ ጁባ ናት ፤ ዓኢሻ
(ረ.ዐ) ጋር ነበረች ፤ እሷ ስትሞት እኔ ወሰድኳት ፤ ነብያችን ﷺ
ይለብሷት ነበር ፤ እኛ ለበሽተኞች እናጥባታለን ..]
በሌላ ዘገባ : " አንዳችን ህመም ሲሰማው እናጥብለትና ውሀውን
እንሰጠዋለን ፤ መዳንን ያገኛል "
ሶሒሕ ሙስሊም - 2069
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
〽️ በዚክር የተተኛ እንቅልፍ ሰላም አለው
〽️ በዱአ የተከፈተ ቀን ድል አለው
〽️ በቅንነት የተጀመረ ስራ ስኬት አለው
〽️ በምስጋና የተጀመረ ዘመን በረካ አለው
〽️ በይቅርታ የሆነ ጓደኝነት ዘለቄታ አለው
〽️ በተስፋ የሆነ ጉዞ ጉልበት አለው
〽️ በፍቅር የሆነ አገልግሎት እርካታ አለው
〽️ በእምነት የሆነ ኑሮ እረፍት አለው
〽️ እናም እነኚህን ሁሉ ያለ ቸልተኝነት እንጠቀምባቸው
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
#አጭር_ናት
ሂሻም ኢብን ዐብዱል መሊክ...
ይህን ሰው ታውቃላችሁ!!!?
ኑ ዐጀብ እንመልከት...።
ሂሻም ማለት በታቢዒዮች ዘመን የሙስሊሞች መሪ የነበረ ንጉስ ነው። እናላችሁ አንድ ቀን ይህ ንጉስ ለሀጅ ወደ መካ መጣ'ና፦
"አንድ ሰሀባ አምጡልኝ" ሲልአዘዘ።
ነዋሪያኑም፦"ሰሀባዎች ሁሉ ሙተው
አልቀዋል" በማለት መለሱለት።
ሂሻምም፦"እሽ አንድ ታቢዒይ አምጡልኝ"
ሲልም አዘዘ።
ይህን ግዜ ጣዉስ አልየማኒ የተባለውን ሊቅ ታቢዒይ ይዘውለት መጡ።
ከዝያም ይህ ጣዉስ የተባለው ታቢዒይ ንጉሱ ወደሚገኝበት ክፍል በመዝለቅ ጫማውን አውልቆ፦"
አሰላሙ ዐለይኩም ሂሻም"
ብሎ ገባ ምንም አይነት የማዕረግም ሆነ
የክብር ስም አላካተተም ነበር።
ሁኔታው ንጉሱን አናድዶታል።
አንደኛ በክብር ስሙ አሚረል ሙእሚኒን/
የምእመናን መሪ ብሎ አልጠራውም። ሲቀጥል ሳይፈቅድለት ነው ቁጭ ያለው፤
ሌላው ደግሞ ፍራሹ መዳረሻ ላይ ነው ጫማውን ሁላ ያወለቀው።
ንጉሱ እንዴት እናቃለሁ በሚል ፍፁም ተናድዶ ይህን ታቢዒይ ለመግደል
ቢወስንም በዙርያው ያሉ ሰዎች በተከበረው ሀገር እና በተከበረው ወር መግደል ተገቢ እንዳልሆነ ነግረው አረጋጉት።
ንጉሱም ንዴቱን እንደመቆጣጠር እየሆነ፦" አንተ ጣዉስ!!! ይህን ለመፈፀም ምንድነው ያነሳሳህ?" አለው።
ጣዉስም፦"ምን ፈፀምኩ?" ሲል ጠየቀው።
ንጉሱም ይልቅ ንዴቱ እየተፋፋመ፦
"አንደኛ ፍራሼ መዳረሻ ላይ ጫማህን አወለቅክ፣
ሁለተኛ የምእመናን መሪ አላልከኝም፣ ሶስተኛ ወይ በልጆቼ ስም/ የኤኬሌ አባት ብለህ አልጠራኸኝም፣
አራተኛ ደግሞ ሳልፈቅድልህ ዝም ብለህ
ቁጭ አልክ...ከዝያም እንዴት ነህ ሂሻም ብለህ አቀለልከኝ" ብሎ ጮኸበት።
ጣዉስም እጅግ ዐሊም ነበሩ'ና እንዲህ ሲሉ መለሱለት፦
=> "ፍራሼ መዳረሻ ላይ ጫማ አወለቅክ ላልከው፤ እኔ እጌታዬ ፊት ለፊት እንኳን 5 ግዜ አወልቀለሁ። አይቀጣኝም ለምን አወለቅክብኝ ብሎ ተቆጥቶኝም አያውቅም።
=> የምእመናን መሪ ያላልኩህ ባንተ መሪነት ሁሉም ምእመናን ስላልተስማሙበት ነው።
ሁሉም ሳይስማማ እኔ ብልህ ውሸታም እንዳልሆን ሰግቼ ነው።
=> የኤኬሌ አባት ብለህ አልጠራኸኝም
ላልከው አላህ ወዳጆቹን እና ነቢያቶቹን
እንኳን <<አንተ ያህያ፣ አንተ ዒሳ...>>
እያለ ነው በስማቸው የጠራው።
ግን እንደ አቡ ለሀብ ያሉ ጠላቶቹን ሲጠራ <<የለሀብ አባት ሁለት እጆች ከሰሩ>> ስለሚል ነው።
=> ያለ ፍቃዴ ቁጭ ብለሀል ላልከው ደግሞ ዐሊይ ረዐ እንዲህ ሲሉ
ሰምቻለሁ<<የጀሀነም ሰውን መመልከት ከፈለግክ እሱ ቁጭ ብሎ ከዙርያው
ሰዎችን የሚያቆም ሰው ዱንያ ላይ ተመልከት>> ለዝያ ነው።" አለው።
☞ ይህን ግዜ ሂሻም የተባለው ንጉስም በለዘበ ድምፁ፦"
ጣዉስ ሆይ ምከረኝ" አለው።
ጣዉስም፦"የምእመናን መሪ ዐሊይ ረዐ እንዲህ ሲል ሰምቻለሁ <<ጀሀነም
ውስጥ ትላልቅ አውሬ ሚያክሉ ጊንጦች እና እባቦች አሉ። እነዚህ እባቦች
ለህዝቡ ፍትህን በማያሰፍን ሰው ላይ መርዛቸውን እየረጩ ይነድፉሉ ብሎ ጥሎት ሄደ
____________________
ምንጭ፦
ﻛﺘﺎﺏ ﺍﻷﺣﻴﺎﺀ - ﺍﻟﻤﺠﻠﺪ ﺍﻟﺜﺎﻧﻲ - ﺻﻔﺤﺔ 160
#ሼር ☺️
JOIN US👇👇👇
👉@finding_hubullah
ቁርአንን የማንበብ ፍሬዎች
1- የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም በመጥፎ
ተምሳሌትነት ከገለጽዋቸው ሰዎች ከመሆን ያድናል።
ኢብን አባስ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና
እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም
እንዲህ ብለዋል፡-
‹‹ ያ በውስጡ ከቁርአን አንዳች ነገር የሌለው (ምሳሌው) እንደ
ወና ቤት ነው፡፡›› ቲርሚዚ
አቢ ሙሳ አል አሽዓሪይ አላህ መልካም ስራቸውን
ይውደድላቸውና ባስተላለፉልን ዘገባ ተወዳጁ የአላህ
መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለምእንዲህ ብለዋል፡-
‹‹ቁርአንን የሚቀራ አማኝ ምሳሌው ልክ እንደ ትርንጎ ነው፡፡
ትርንጎ መዓዛውም መልካም ጣዕሙም መልካም ነው፡፡ ቁርአንን
የማይቀራ አማኝ ምሳሌው እንደ ቴምር ነው፡፡ ቴምር መዓዛ
ባይኖረውም ጥፍጥናው ግን ልዩ ነው፡፡ ሙናፊቅ ሆኖ ቁርአንን
የሚቀራ ሰው ምሳሌው እንደ አሪቲ ነው፡፡ አሪቲ መዓዛው
መልካም ቢመስልም ጣዕሙ ግን መራራ ነው፡፡ እንዲሁም
ሙናፊቅ ሆኖ ቁርአንን የማይቀራ ሰው ምሳሌው እንደ የቅል ፍሬ
ነው፡፡ የቅል ፍሬ መዓዛም የለውም ጣዕሙም መራራ ነው፡፡››
ቡኻሪና ሙስሊም
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
#መጠጥ_የሚጠጣ_እላህ_ስላቱንም_ሆነ_መልካም_ስራውን_እይቀበለውም*።
ጃቢር ቢን እብዳላህ (ረ.ዐ) ባስተላለፉልን ሃዲስ የነብያችን( ሰ.ዐ.ወ) ሶስት ዓይነት ሰዎች ስላታቸውንም ሆነ መልካም ስራቸውን እላህ እይቀበላቸውም ብለዋል ፦
➊ የኮበለለ ባሪያ ወደ ጌታው እስኪመለስ
➋ ባሏ የተቆጣባት ሚስት ይቅር ብሎ እስኪወድላት
➌ የሰከረ ከሰካሩ እስኪያገግም (እስኪበርድለት)።
በሌላ ሃዲሳቸው ላይ ነብያችን (ሰ,ዐ.ወ) ፦መጠጥን ጠጥቶ ያልስከረ እደሆነ እላህ (ሱ.ወ) ከእሱ ዘንድ ለአርባ ቀን ያህል ያርቀዋል ።መጠጥን ጠጥቶ የሰከረ እንደሆነ እላህ (ሱ.ወ) ለአርባ ቀናት ፊርዱንም ሆነ ሱናውን አይቀበለውም ።ብሎም በዚህ አቋሙ ላይ ሆኖ ከሞተ እንደ ጣኦት አምላኪ ሆኖ ነው የሚሞተው ።እላህም ነገ በጀሃነም ውስጥ የጀሃነም ሰዎች ፍሳሽ የሆነውን እዥ የተቀላቀለበት መጠጥን ያጠጣዋል።(እብኑ ሃጀር እል ሃይስሚ እል ዘዋጀር በተሰኘው ኪታባቸው ላይ ይህን ሃሳብ አስፍረዋል ።)
#መጠጥ_የሚጠጣ_የተረገመ_ነው*።
አስካሪ መጠጥ የተረገመች ናት የሚጠጣት ፤የሚያስጠጣትም ፤የሚገዛትም ፤የሚሽጣትም ፣የሚጠምቃትም ፣የሚሽከማትም ፣በእሷ የመጣን ገንዘብ የሚበላም ሁሉም የተረገሙ ናቸው በማለት ታላቁ ነብይ( ሰለላሁ አለይኺ ወሰለም )ተናግረዋል ።እንድ ስው መጠጡን ባይጠጣውም የሚጠጣን ከረዳ ፣መጠጥ ቤት ከከፈተ መኪናውን ለመጠጥ ሻጭ ማጓጓዣነት ካከራየ (ከሰጠ) ቤቱንም ለመጠጥ ቤት ካዋለ ወይም ካከራየ ፤መጠጥ የተሽከመን ለማውረድም ይሁን ለመጫን ከተባበረ ፤ለመጠጥ የሚሆኑ ቁሶችን በመግዛት የሚያቀርብ ከሆነ ባጠቃላይ ከመጠጥ ተግባር ጋር በተዛመደ እንቅስቃሴ የሚያደርግ ከሆነ ከነብያችን (ሰለላሁ አለይኺ ወሰለም) እርግማን ፈጽሞ ሊድን። አይቻለውም ።
አላህም በቁርአኑ እንዲህ ይለና👇
إِنَّمَا يُرِيدُ ٱلشَّيۡطَٰنُ أَن يُوقِعَ بَيۡنَكُمُ ٱلۡعَدَٰوَةَ وَٱلۡبَغۡضَآءَ فِي ٱلۡخَمۡرِ وَٱلۡمَيۡسِرِ وَيَصُدَّكُمۡ عَن ذِكۡرِ ٱللَّهِ وَعَنِ ٱلصَّلَوٰةِۖ فَهَلۡ أَنتُم مُّنتَهُونَ
ሰይጣን የሚፈልገው በሚያሰክር መጠጥና በቁማር በመካከላችሁ ጠብንና ጥላቻን ሊጥል አላህን ከማውሳትና ከስግደትም ሊያግዳችሁ ብቻ ነው፡፡ ታዲያ እናንተ (ከእነዚህ) ተከልካዮች ናችሁን (ተከልከሉ)፡፡
(ሱረቱል ማኢዳ 91)📖🌹
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِنَّمَا ٱلۡخَمۡرُ وَٱلۡمَيۡسِرُ وَٱلۡأَنصَابُ وَٱلۡأَزۡلَٰمُ رِجۡسٞ مِّنۡ عَمَلِ ٱلشَّيۡطَٰنِ فَٱجۡتَنِبُوهُ لَعَلَّكُمۡ تُفۡلِحُونَ
እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ ቁማርም ጣዖታትም አዝላምም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፡፡ (እርኩስን) ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና፡፡
(ሱረቱል ማኢዳ 90)📖🌹
━━━━━🍃🌸🍃━━━━
ለማንኛውም አስተያየት ይህን ይጠቀሙ
@sehih_hadith_bot
•════•••🌺🍃•••════•
ሼር 👇JoiN👇 & Share
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
@sehih_hadith
@sehih_hadith
@sehih_hadith
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
╰─•🍂•─═••••••••🍃•═─••─╯
ይ🀄️ላ🀄️ሉን
#◼️ዚክር‼️ ጥቅሙና‼️ቁጭት‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
💦ሸህ አብዱረዛቅ አልበድር አላህ ይጠብቃቸውና እንዲህ አሉ።
〰〰〰〰〰
✅ ዚክር ማለት እውነተኛ የቀልብ ህይወት ነው። ዚክር የቀልብ ምግብና ሩህ ነው። አንዲት ቀልብ ዚክር ካጣች ልክ አቅሙ እንደተጋረደበት የሰውነት አካል ነው የሚሆነው። ለቀልብ ትክክለኛ ህይወት የላትም አላህን በማውሳት (በዚክር) ቢሆን እንጂ።
📚فقه الأدعية و الأذكار صـ ١٧
💦ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።
〰〰〰〰〰
✅ በየመንገዱ፣ እቤት ውስጥ፣ ጉዞ ስንወጣም ሆነ ሀገር ኗሪ በሆንን በማንኛውም ጊዜ፣ ቦታና ሁኔታ ላይ ዚክርን ማብዛት፦ የውመል ቂያማ (በመልካም) የሚመሰክርልህ መስካሪ ይበዛልሀል። ምክንያቱም ዚክር ስታደርግ ያለፍክባቸው ቦታዎች፣ መሬት፣ ተራሮችና ሌሎችም የውመል ቂያማ መስካሪ ይሆኑልሀል።
📚 [الوابل الصيِّب : (٦٩) ]
💦ኢብኑ ኡሰይምን አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ።
〰〰〰〰〰
✅ በአላህ ይሁንብኝ‼️ከእለታት አንድ ቀን በስራ መዝገቤ ላይ ምናለ አንድ ተስቢህ (سبحان الله)፣ አንድ ተክቢር (الله اكبر)፣ ወይም አንድ ተህሊል (لا اله الا الله) በኖረኝ ብለህ የምትመኝበት ቀን ይመጣል።
📚 ابن عثيمين | اللقاء الشهري (41)
💦አቡ መህረዝ አጠፋዊይ አላህ ይዘንለትና እንዲህ አለ።
〰〰〰〰〰
✅እናንተ ከአላህ ትእዛዝና እሱን ከመገዛት ችላ ብትሉና ብትዘናጉ፦ አላህ ሌሎች ቀንም ሆነ ማታ እሱን ከመታዘዝና ከመገዛት የማይሰላቹ ምርጥ ባሮች አሉት።
📚 الزهد لابن أبي الدنيا (٤٤٧)
☑️ ምላስ የለመደውን ነገር ነው የሚደጋግመው። የዘወተረበትን ነገር ነው የሚይዘው። ስለዚህ ምላስህ አላህን በማውሳት ዚክርን አለማምደው። ዚክር ማለት፦ ውዱእ የማይጠይቅ፣ ጉልበት የማያስፈልገውና ሁኔታ የማይገድበው ቀላልና ገር ኢባዳ ሆኖ ብዙ ምንዳዎችን የሚያስገኝ ስለሆነ በዚክር ላይ እንበርታ።
💦ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።
〰〰〰〰〰
✅ ዛሬ ላይ ሰዎች የተዘናጉበት መልካም ስራና የስራቸው ምንዳ ምን ያክል እንደሆነ የውመል ቂያማ ተገልጦላቸው በሚያዩ ጊዜ ከዚክር በላይ ብዙ ምንዳ ያለው ነገር ያለ አይመስላቸውም። የዚህን ጊዜ በጣም ያዝናሉ። በጣም ቀላል ሆኖ ይህን ያክል ምንዳ ከሚገኝበት ዚክር ምናለ ባልተዘናጋን በማለት ብዙ ባለመዘከራቸው በንዴት ይቆጫሉ።
📚الوابل الصيّب ١١١
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
{{የጥዋት ዚክር}}
~
أَصْبَحْنَا وَأَصْبَحَ الْمُلْكُ لِلَّهِ، وَالْحَمْدُ لِلَّهِ، لاَ إِلَـهَ إِلاَّ اللهُ وَحْدَهُ لاَ شَرِيْكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيْرُ. رَبِّ أَسْأَلُكَ خَيْرَ مَا فِيْ هَذَا الْيَوْمِ وَخَيْرَ مَا بَعْدَهُ، وَأَعُوْذُ بِكَ مِنْ شَرِّ مَا فِيْ هَذَا الْيَوْمِ وَشَرِّ مَا بَعْدَهُ، رَبِّ أَعُوْذُ بِكَ مِنَ الْكَسَلِ وَسُوْءِ الْكِبَرِ، رَبِّ أَعُوْذُ بِكَ مِنْ عَذَابٍ فِي النَّارِ وَعَذَابٍ فِي الْقَبْرِ.
▲«ማለዳ ላይ ለመድረስ ነቅተናል፡፡ በዚህ ሰዓት ሉዓላልነት የዓላማት ጌታ የሆነው አላህ ነው፡፡ ምስጋና ከአላህ ነው፡፡
💦 ከአላህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም፡፡ አንድ ነው፡፡ አጋሪ የለውም፡፡ ሉዓላዊነት የርሱ ብቻ ነው፡፡ ምስጋናም የርሱ ብቻ ነው፡፡ ጌታዬ ሆይ የዚህን ቅና የቀጠዩን /የሌሊቱን/ መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ፡፡
◆«ከዚህ ቀንና ከቀጣዩ /ከሌሊቱ/ ክፉ ነገር በአንተ እጠበቃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ ከእሳት ቅጣት ከቀብር ውስጥ ቅጣትም በአንተ እጠበቃለሁ።
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
🖐 كلام اعجبني ..................
ካስገረሙኝ ንግግሮች 🖐
🔲 عندما تولد لا تعلم
من الذي أخرجك من بطن أمك
🔲በምትወለድበት ጊዜ ከእናትህ ሆድ ያወጣህን ፈፅሞ አታውቅም።
🔳 وعندما تموت لا تعلم
من الذي أدخلك إلى قبرك
🔳 በምትሞትበት ጊዜ ማን ወደ ቀብርህ እንዳስገባህ ፈፅሞ አታውቅም።
*🔲 عجبا لك ياابن آدم*
*🔲 የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ።*
🔳 عندما ولدت تغسل وتنظف
🔳 በተወለድክ ጊዜ ትታጠባለህ፣ ትፀዳለህ።
🔲 وعندما تموت تغسل وتنظف
🔲 በምትሞትበት ጊዜ ትታጠባለህ፣ ትፀዳለህ።
*🔳 عجبا لك ياابن آدم*
*🔳 የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ።*
🔲 عندما تولد لاتعلم من فرح واستبشر بك
🔲 በተወለድክ ጊዜ በውልደት ማን እንደተደሰተ እና እንደተበረሰ አታውቅም።
🔳 وعندما تموت لاتعلم من بكى عليك وحزن
🔳 በሞት ጊዜ በመሞትህ ማን እንዳለቀና እንደአዘነ አታውቅም።
*🔲 عجبا لك ياابن آدم*
*🔲 የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ*
🔳 في بطن أمك كنت في مكان ضيق ومظلم
🔳 በእናትህ ሆድ ውስጥ በጠባብ ቦታና በጨለማ ውስጥ ነበርክ።
🔲 وعندما تموت تكون في مكان ضيق ومظلم
🔲 በምትሞትበት ጊዜ በጠባብ ቦታና በጨለማ ውስጥ ትሆናለህ።
*🔳 عجبا لك ياابن آدم*
*🔳 የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ*
🔲 عندما ولدت تغطى بالقماش ليستروك
🔲 ስትወለድ በጨርቅ ትጠቀለላህ ሊሸፍኑህ!
🔳 وعندما تموت تكفن بالقماش ليستروك
🔳 ስትሞት በከፈን ይጠቀልሉሃል ሊሸፍኑህ!
🔲 عجبا لك ياابن آدم
🔲 የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ
🔳 عندما ولدت وكبرت يسألك الناس
عن شهادتك وخبراتك
🔳 በተወለድክና በአደግክ ጊዜ ሰዎች ስለምስክር (ወረቀትህና) ስለሙያህ ይጠይቁሃክ።
🔲 وعندما تموت تسألك الملائكة عن عملك الصالح
🔲 በሞትክም ጊዜ መልዓይኮች ስለመልካም ስራህ ይጠይቁሃል።
*🔳 فماذا أعددت لآخرتك ؟*
*🔳 ለመጨረሻው ሃገርህ ምን አዘጋጀህ?*
🔲 جرب تقولها من قلب :
آشهد آن لآ آله آلآ آلله
واشهد آن محمد رسول آلله
🔲 ከልብህ ይህችን (ቃል) ለመናገር ሞክር! ።ከአላህ ሌላ በፍፁም የሚመለክ አምላክ እንደሌለ መስክር። እንዲሁም ሙሃመድ የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን መስክር።
🔳 مستحيل تقرآها بدون ما ترسلها
🔳 (ይህን መልእክት) በፍፁም ሳታነባድ እንዳትልካት!!
& & &
بسم الله الرحمن الرحیم
*{ قل هو الله أحد * الله الصمد * لم يلد ولم يولد * ولم يكن له كفواً أحد }*
*ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ*
*{ በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው። አልወለደም፤ አልተወለደምም። ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።}*
إرسل وتخيل في هالساعه 🕗
መልዕክቱን ላክ! ሰአትህን አስተውል🕗
كم شخص يقرأ ثلث القرآن 📘 بسببك لاتحرم نفسك مٍن الاجر
በአንተ ሰበብ የቁርዓን አንድ ሶስተኛን ይቀራሉ(ያነባሉ) 📘
ነፍስህ አጅር አትከልክላት!!
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
❥::::::::::ሴት ልጅ: ::::::::::::❥
❥የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ❥
لا تمنعوا إماءَ اللهِ مساجدَ اللهِ وبيوتهنَّ خيرٌ لهنَّ. متفق عليه
"የአሏህን ባርያት የአሏህን(ቤት) መስጂድን አትከልክሏቸው፡ ቤታቸው ግን ለነሱ በላጭ ናት፡፡"
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል ].
ቤታቸው ለነሱ በላጭናት ከሁሉም ነገር፡፡ እንዲሁም ከመስጂድ ሁላ ቤታቸው በላጭ ናት ከተባለ እንዴት ሊሆን ነው ታዲያ ሱቅን ተገላልጠው መውጣታቸው?
አሏህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል
وَٱلْقَوَٰعِدُ مِنَ ٱلنِّسَآءِ ٱلَّٰتِى لَا يَرْجُونَ نِكَاحًۭا فَلَيْسَ عَلَيْهِنَّ جُنَاحٌ أَن يَضَعْنَ ثِيَابَهُنَّ غَيْرَ مُتَبَرِّجَٰتٍۭ بِزِينَةٍۢ ۖ وَأَن يَسْتَعْفِفْنَ خَيْرٌۭ لَّهُنَّ
ٌۭ
እነዚያም ከሴቶች እድሜየቸው የገፋ የሆነ እንዲሁም ጋብቻን የማይፈልጉት ተቀማጮች (ባልቴቶች)፤ በጌጥ የተዋቡ ሳይኾኑ የላይ ልብሶቻቸውን ቢጥሉ በእነሱ ላይ ኀጢአት የለባቸውም፡፡ ነገር ግን መጠበቃቸው ለእነርሱ ጥሩና የተሻለ ነው፡፡
አሮጊት-በእድሜ የገፋች- የሆነች ሴት በጌጥ መገላለጥን ከተከለከለች፡ እንዴት ይሆናል ታዲያ በወጣቷ ያቺ የፊትናን በር ከፋች የሆነችዋ ተውባና አምራ ከቤት መውጣቷ?
አሏህ እንዲህ ይላል
وَلَا يَضْرِبْنَ بِأَرْجُلِهِنَّ لِيُعْلَمَ مَا يُخْفِينَ مِن زِينَتِهِنَّ
"እግሮቻቸውንም ከምድር ጋር አይምቱ ከእግራቸው ስር ያለው ጌጥ እንዲታወቅ ብለው፡፡"
ሴት ልጅ ከእግሯ ውስጥ ያለውን እንዳታሰማ አሏህ ከከለከላት እንዴት ልትሆን ነው ታዲያ ያቺ እግሯን ሳይቀር የምታሳየው?
ለምን ከተባለ የእይታ ፈተና ልክ እንደሚታወቀው ከመስማት የበለጠ ስለሆነ ነው፡፡
የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ
"ሁለት አይነት ባህሪ ያላቸው የእሳት ሰዎች እኔም በፍፁም የማላያቸው የሆኑ...ከነዚህም ሴቶች ናቸው ለብሰው እንዳለበሱ፤ተዘንብለው ሌሎችን የሚያዘነብሉ፤ጸጉራቸውንም እንደ ግመል ሻኛ የቆለሉ የሆኑ እነዚህ ጀነትን አይገቡም፡ከሽታዋም ምንንም አያገኙም፡፡"
እንዲሁም በሌላ ሀዲስ የአሏህ መልእክተኛ ﷺእንዲህ ብለዋል
" የትኛዋም ሴት ጭስን(እጣን) የነካች የሆነች ከእኛ ጋር እንዳትጣድ፡፡"
የአሏህ መልእክተኛ ጭስን ወይም እጣንን በመንካቷ ሶላት እንዳትጣድ ካሉ እንዴት ሊትሆን ነው ታዲያ ከጭስ የበለጠ ሽታ ያለውን ሽቶ ተለቅልቃ የምትወጣው?
ከአሏህ መልእክተኛ ﷺተዝግቧል እንዲሁ እንዲህ እንዳሉ
" ለሴቶች ጥሩ የሚባለው ሰፋቸው(በሶላት ላይ) ኀላ መሆናቸው ነው፡ መጥፎዎቸው ደግሞ ፊት መሆናቸው ነው።
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
📜
[ዝምታ ወርቅ ነው] 📣
💰 ሰለፎቻችን ስለ ዝምታ እና ንግግርን መቀነስ ብዙ ብዙ ብለዋል ፤ ከእዚያ ውስጥ ሁለት አሣሮች ልጥቀስ ፡
🎙ኢማም አልአውዛዒይ (አሏህ ይዘንለትና) እንዲህ ብሎ ነበር ፦
« قال سليمان بن داود صلى الله عليهما وسلم : إن كان الكلام من فضة ، فالصمت من ذهب »
« (ነብይ) ሱለይማን ኢብኑ ዳዉድ (ﷺ) እንዲህ ብሏል ፦
"ንግግር ከብር(silver) ቢሆንም ዝምታ ደግሞ ከወርቅ ነው።»
[📙 ኢብን አቢ አድዱንያ "አስሶምት" ቁ 47]
🎙ኻቃን ኢብኑ ዐብዲላህ (አሏህ ይዘንለትና) እንዲህ ብሏል ፦
سمعت ابن المبارك ، وسئل عن قول لقمان لابنه: إن كان الكلام من فضة ، فإن الصمت من ذهب .
« ኢብኑ አልሙባረክ ሉቅማን ለልጁ ፡ " ንግግር ከብር(ብር) ቢሆን ዝምታ ከወርቅ(ወርቅ) ነው" ብሎ ስለተናገረው ንግግር ሲጠየቅ ሰማሁ »
فقال عبد الله :
» لو كان الكلام بطاعة الله من فضة ، فإن الصمت عن معصية الله من ذهب «
«እንዲህም ብሎ መለሰ ፡
"አሏህን መታዘዝ በሆነ ነገር መናገር ከብር(ብር) ከሆነ ፤ አሏህን ከማመፅ ዝም ማለት(መቆጠብ) ደግሞ ከወርቅ ነው።" »
[📙 ኢብኑ አቢ አድዱንያ "አስሶምት" ቁ 744]
፨ አሏህ የሚጠቅማቸውን ነገር ብቻ መርጠው ከሚናገሩት ያድርገን።
أبو عاصم النبيل
هذا وصل اللهم على محمد وعلى آله وصحبه وسلم
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ሰላት#
ሰላት የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ ዱዓእ (ልመና) ማለት ሲሆን ሸሪዓዊ ትርጉሙ ደግሞ፦ በተክቢራ የሚጀመርና በማሰላመት የሚጠናቀቅ ለየት ያሉ ንግግሮችና ተግባሮች ማለት ነው፡፡ ሰላት ከእስልምና ማዕዘናት አንዱ ሲሆን ከቃለ ተውሂድ (ከሁለቱ ቃል ምስክርነት) በኃላ በጣም ጥብቁ የእስላም ማዕዘን ነው፡፡
ሰላት ግዴታ መሆኑ በቁርአን በሀዲስና በዑለማዎች ስምምነትም (ኢጅማዕ) የተረጋገጠ ነው፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል፡-
<<ሶላትንም ደንቡን ጠብቃችሁ ስገዱ፡፡>> (አል በቀራህ 43
በዚህ መልኩ በብዙ አንቀፆች ላይ ተናግሯል፡፡ በሌላም አንቀፅ አላህ እንዲህ ብሏል፡-
<<ለእነዚያ ላመኑት ባሮቼ በእርሱ ውስጥ ሽያጭና ወዳጂነት የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ሶላትን በደንቡ ይሰግዳሉ፡፡>>
(አል ኢብራሂም 31)
ከሀዲስ ማስረጃዎች ውሰጥም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-
<<ሰላቶች አምሰት ምንዳቸው ግን ሀምሳ ነው፡፡>> (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ቡኻሪና ሙሰሊም በዘገቡት ሀዲስ ስለ ኢስላም ለጠየቃቸው ግለሰብ እንዲህ ብለውታል፡-
#በቀንና በሌሊት ውስጥ አምስት ሰላቶችን መስገድ…ጠያቅውም ከዚህ ሌላ አለብኝን? ሲላቸው አይ በራስህ ፈቃድ ከሰገድክ እንጂ ሌላ ግዴታ ሰላት የለምብህም ብለውታል፡:>>
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ሱብሀነላህ
ከአቡ ሁረይራህ - ረዲየሏሁ ዐንሁ - ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ ይላሉ፡-
“ከበኒ ኢስራኢል (ህዝቦች) አንድ ወንጀል የሚያበዛና ሌላ በዒባዳ (በአምልኮ) ላይ የሚታገል ሁለት ጓደኛሞች ነበሩ፡፡ ዒባዳ ላይ የሚታትረው ያንኛውን ሁሌ ወንጀል ላይ ስለሚመለከተው ‘ተው’ ይለዋል፡፡ የሆነ ቀን ወንጀል ላይ አገኘውና ‘ተው’ አለው፡፡
(ወንጀለኛው): ‘ተወኝ (እባክህ) በጌታዬና በእኔ መሀል አትግባ! በእኔ ላይ ተቆጣጣሪ ሆነህ ተልከሀል?’ ሲል መለሰለት፡፡ ያንኛው በዚህን ጊዜ፡
‘ወላሂ! አንተን አላህ አይምርህም!! ወይም አላህ አንተን ጀነት አያስገባህም’ አለ፡፡
የሁለቱም ሩሕ ተወሰደ (ሞቱ፡፡) ከአለማቱ ጌታ ዘንድ ተገናኙ፡፡ ለዚያ ታታሪ ሰውም (አላህ) እንዲህ ሲል ጠየቀው፡-
‘በእኔ ላይ (እንደማልምረው) አዋቂ ነበርክ?! በእጄ ላይ ባለውስ ቻይ ነበርክ?!’
ለወንጀለኛው፡- ‘ሂድ በእዝነቴ ጀነት ግባ’ አለው፡፡ ያንኛውን ደግሞ ‘ወደ እሳት ውሰዱት’ አለ፡፡”
አቡ ሁረይራ - ረዲየሏሁ ዐንሁ ከዚህ ሐዲሥ በመቀጠል እንዲህ አሉ፡- “ነፍሴ በእጁ በሆነችው እምላለሁ! በርግጥም ዱንያ አኺራውን የምታጠፋ ንግግርን ተናገረ፡፡” [ሶሒሕ ኢብኑ ሒባን፡ 5712]
……………………………………………..
ከሐዲሡ የሚወሰዱ ቁም-ነገሮች
በመጀመሪያ የዚህን ሐዲሥ መልእክት ምን ያክል እናውቀዋለን? ምን ያክልስ አደጋው ይታየናል? ምን ያክልስ ጥንቃቄው አለን? ከዚህ ጥፋት ያለንስ ርቀት ምን ያክል ነው?
1. በሐዲሡ እንደተገለፀው
1.1. አንደኛው ሰው ወንጀል የሚያበዛ ነው፡፡ በዚያ ላይ ምክር አልተቀበለም፡፡
1.2. ሁለተኛው ሰው ዒባዳ የሚያበዛ ነው፡፡ በዚያ ላይ ከመጥፎ ለመመለስ የሚመክር አስተማሪ ነው፡፡
2. ውጤቱ ግን አስደንጋጭ ነው፡፡ ወንጀለኛው ወደ ጀነት፣ ዓቢዱና መካሪው ወደ እሳት!!!
3. ምክንያቱ ደግሞ፡-
3.1. የመጀመሪያው ወንጀሉ ከሺርክ በታች እስከሆነ ድረስ ከአላህ መሻት ስር ነው፡፡ “አላህ የሚያጋራበትን አይምርም፡፡ ከዚያ በታች ያለውን ግን ለፈለገው ይምራል” ማለቱ አይዘንጋ፡፡ ስለዚህ ሰውየው የተማረው ስላላጠፋ ሳይሆን በአላህ እዝነት ነው፡፡ “ሂድ በእዝነቴ ጀነት ግባ” እንዳለው ይታወስ፡፡
3.2. ሁለተኛው በማያገባው ገብቶ “ይህን አያደርግም” እያለ በአላህ ላይ እየማለ ነው፡፡ ይህን ወንጀለኛ ይምረዋል ወይስ አይምረውም የሚለውን የሚያውቀው ባለምህረቱ ብቻ ነው፡፡ ስልጣኑም ችሎታውም የሱው ነውና፡፡ ስለዚህ አቶ ዐቢድና መካሪ የአላህን ሐቅ ነው እየተጋፋ ያለው፡፡
4. ከሳሽ ማን ነው?!
በቂያማ ቀን ታዲያ የዚህ ሰውየ ከሳሽ የሆነው ያ ወንጀል የሚያበዛው አካል አይደለም፡፡ እህሳ ከሳሹም ዳኛውም የአለማቱ ጌታ አላህ ነው!! አያስፈራም?! “በእኔ ላይ (እንደማልምረው) አዋቂ ነበርክ?! በእጄ ላይ ባለውስ ቻይ ነበርክ?!” ሲል አፋጠጠው፡፡
5. ቀይ መብራት!
እንዳቅሚቲ በዲን ላይ የምትታትረው ወንድሜ ሆይ! እንዳቅሚቲ ሸሪዐውን ለመተግበው ተፍ ተፍ የምትይዋ እህቴ ሆይ! የምናውቃትን ከማስተላለፍ ባለፈ፣ ስለ ሰዎች መፃኢ እድል ከመዳፈር በእጅጉ ልንቆጠብ ይገባል፡፡ ይሄ ሐዲሥ እጅግ አስፈሪ የሆነ መልእክት ነው የያዘው፡፡ ድንበር ማለፍ በዲን ስም ስለተፈፀመ ከተጠያቂነት አያተርፍም፡፡ አላህ መጨረሻችንን ያሳምረው፡፡
(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 16/2009)
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ሰላት ከሰገዱ ቡኋላ መስገጃዎ ላይ መፅናት ምን ያህል አጅር እንደሚያስገኝ ያውቃሉን?
✒ የአላህ መልክተኛ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦ "ከእናንተ መካከል አንዳቹ ሰላት የሰገደበት መስገጃው ላይ እስካለ እና ውዱእ እስካላጠፋ ድረስ መላኢካዎች በርሱ ላይ ሰለዋት ያወርዱለታል። "አላህ ሆይ! ወንጀሉን ማረው፣ አላህ ሆይ! እዘንለት።" ይላሉ።"
(ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል)
☞ ኢብኑ በጣል(ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ "እጅግ ብዙ ወንጀል ያለበት ያለ ብዙ ልፋት ወንጀሉን አላህ እንዲያራግፍለት የሚፈልግ ሰው ካለ፦ መላኢካዎች እርሱ ላይ የሚያደርጉት ዱዓእና ኢስቲግፋር ይበዛለት ዘንድ ሰላት ከሰገደ ቡኋላ መስገጃው ላይ በመፅናት እድሉን ይጠቀም።"
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
አስተማሪ ቂሳ
ሪያድ በሚገኝ አንድ መስጂድ ውስጥ ሙአዚን ነው ጀናዛ በማጠብ መልካም ስራው ይታወቃል ከእለታት በአንደኛው ቀን የገጠመውን ይተርክልናል:
《ለሊት ስምንት ሰአት ላይ የቤቴ በር በሀይል ተንኳኳ ደንግጬ ተነሳሁ ሶስት ወጣቶች ሞተው ጀናዛቸውን እንዳጥብላቸው ፈልገው ነበር የመጡት ከቤት ወጥቼ ጉዞ ጀመርን ወደ ማጠብያው ስፍራ ደረስን ክፍሉ ማብራት ስላልነበረው ፋኖስ እንዲመጣ አዘዝኩና ጀናዛውን መክፈት ጀመርኩ በአላህ እምላለሁ ከሶስቱ ወጣቶች አካል በሚወጣው ኑር (ብርሀን) ቤቱ በራ ያለ ፉኖስ ጀናዛውን ማጠብ ጀመርኩ እንደጨረስኩም ስለ ልጆቹ ባህሪ ጠየቅኩ ሰላተል ጀማአ አምልጧቸው እንደማያውቅ ተነገረኝ ።》
ሰኢድ ኢብኑ ሙሰዩብ ተክቢረተል ኢህራም አርባ አመት አምልጦት አያውቅም ነበር
አላህ ብርሀን ያላደረገለትን ሰው ማንም ብርሀን አያደርግለትም
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
🌍🌙🌙🌙
🌙
🌙
🌙
┈┈•••✿❒②❒✿•••┈┈
⇩⇩
❒ ጥልቅ ፍቅር
በአንድ ወቅት ነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ቢላል ኢብኑ ረባህን ከሗላው በፍቅር ስሜት እቅፍ አደረገው ይይዙትና።
ድምፃቸውን ቀይረው "እኔ ማን ነኝ ?" ብለው ይጠይቁታል.....
ቢላልም
"ኡመር ነህ ?"
"አይደለሁም።"
"አቡበክር መሆን አለብህ?"
"አሁንም ተሳስተሃል።"
"በቃ ኡስማን ነህ።"
"አላወቅከኝም።"
"አሊ ነህ ማለት ነው?"
....እያለ ያቀፈውን ሰው ማንነት ሲጠይቅ ይቆያል።
°
ከዚያ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ለቅቅ አደረጉትና ከፊት ለፊቱ በመምጣት
"ቢላል ሆይ! በእውነት እኔ መሆኔን አላወቅክም ነበር እንዴ ?" ሲሉ ጠየቁት።
°
ቢላልም “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በደንብ አውቄዎታለሁኝ ነገር ግን ለረጅም ጊዜ
እንዳቀፉኝ መቆየትን ስለፈልግኩኝ እንጂ"
ሲል መለሰላቸው።
ምን አይነት ፍቅር ነው? ያ ረብ!
ፊዳክ አቢ ወኡሚ ወደሚ ወነፍሲ ያረሱሉሏህ!!
ያአሏህ የእሳቸውን ፊት በጀና ለማየት አብቃን!!!
🌹اللهــم صــــل وسلــــم
علـــى نبينـــا محمــــدﷺ🌹
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ሙሉዉን አንብቢዉ ከዚያም በመጨረሻ ላይ ያለዉን ቁጥር እይ
ከዚያም ወስኚ
የአላህ መልእክተኛ ሰለላህ አለይህ ወሰለም እንዲህ ብለዋል ⇣
በሚዛን ላይ ከባድ የሆነች አላህ ዘንድ የተወደደች ንግግር ⇣
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ሱበሃን አላህ ወቢ ሃምዲህ ሱበሃን አላህ አል አዚም
ከዚያም ቢያንስ ለ30 ሰዎች ላክላቸዉ ቢሉትም(ቢያነቡትም)
አምስመቶ ሺ ሚሊዮን ሃሰናትን በአላህ ፈቃድ ታገኛለህ
እንደዚሁ ደግሞ ከላክላቸዉም ሰዎች እያንዳንዳቸዉ ቢያንስ ለ30
ሰዎች ከላኩ አሁንም 4.680.000.000 ሃሰናትን ታገኛለህ
አታዉቅም መቼ እንደምትሞት ስለዚህ ሰደቀተል ጃሪያ አድርጋት
አሰራጫት ደቂቃ እንኳን ያህል አትወስድብህም የዉመል ቅያማ
#አስተማሪ_ታሪክ_ለኛ_እውነትን_መናገር
እውነትን መናገር በጣም የሚወደድ መልካም ልማድ ነው። ሁልጊዜም እውነትን የምንናገር ከሆነ እራሳችነን ከብዙ ችግሮች መጠበቅ እንችላለን። ይህ ብዙ መጥፎ ነገሮችን የሰራ ሰው ታሪክ ነው። ነገር ግን እውነትን ለመናገር ቃል በመግባቱ ከመጥፎ ነገር ጠብቆታል።
አንድ ጊዜ አንድ ሰው ወደ ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) መጣና እንዲህ አላቸው: የአሏህ ነብይ ሆይ ብዙ መጥፎ ልማዶች አሉብኝና መጀመሪያ የትኛውን መተው አለብኝ? ሲል ጠየቃቸው። ነብዩም ውሸት መናገርን በመጀመሪያ ተው አሉት።
ሰውየውም ይህን እንደሚያደርግ ቃል ገብቶላቸው ወደ ቤቱ ሄደ። በምሽት ሊሰርቅ ሊሄድ ነበርና ከመሄዱ በፊት ለተወሰነ ጊዜ ከነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ጋር የገባውን ቃልኪዳን አሰበ። ነገ ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) የት ነበርክ? ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላለሁ ልሰርቅ ሂጄ ነበር እላቸዋለሁ? አይሆንም እንዲህማ ልላቸው አልችልም፤ እንዲሁም ልዋሻቸው አልችልም። እውነቱን የምናገር ከሆነ ሰዎች እኔን መጥላት ይጀምራሉ፤ ሌባ ብለውም ይጠሩኛል። በመስረቄም እቀጣለሁ አለ።
ሰውየው በዚያን ለሊት ላለመስረቅ ወሰነና ይህን መጥፎ ልማዱን ተወ። በቀጣዩ ቀን ወይን(አስካሪ መጠጥ) ለመጠጣት ፈልጐ ይህን ለማድረግ ባሰበ ጊዜ ለራሱ እንዲህ አለ:- ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) በዚህ ቀን ምን አደረክ ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላቸዋለሁ ልዋሽ አልችልም ደግሞ እውነታውን ብናገን ሰዎች ይጠሉኛል። ምክኒያቱም ሙስሊም ወይን (አስካሪ መጠጥ) መጠጣት አይፈቀድለትም። እናም ወይን(አስካሪ መጠጥ) የመጠጣት ሀሳብን(ፍላጐቱን) ተወ። በዚህ መንገድ ሰውየው መጥፎ ነገሮችን ለመስራት ባሰበ ጊዜ እውነትን ለመናገር የገባውን ቃል ኪዳን ያስታውሳል። እያለያለ አንድ በአንድ መጥፎ ልማዶቹን ሁሉ ተወ። ጥሩ ሙስሊምና ጥሩ ሰው ሆነ።
ሁልጊዜም እውነትን የምንናገር ከሆነ ጠንካራ ሙስሊም መሆን እንችላለን። የአሏህ ውዴታን ያስገኝልናል። የአሏህን ውዴታ ካገኘን አሏህ በጀነት ይመነዳንና።
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
〰〰😔 #ዋ_ነብሴ〰〰〰
✍ #ገጣሚ ☞ ሀያት ሁሴን
ዋ ነብሴ . . .
አንቺ አኼራን የረሳሽ ለአዱንያ የሞትሽ
ለዚች ጠፊ አለም እራስሽን የሸጥሽ
ነብሴ ቓመጥሽላት ዱንያ መሆኇን ዘንግተሽ
ረህማንም ብሎሽ ይች አለም ጠፊ ናት
ታዲያ ለምን ይሁን እዲህ የወደድሻት
በምን ምክንያት ይሁን ቦታ የሰጠሻት
ዋ . . . . . ነብሴ ፈራሁልሽ
ለዚች ጠፊ አለም በፍቅሯ ወድቀሽ
ማጠቅምሽ ማትጎዳሽ የማትበጅሽ
ንቂ ዕጂ ነብሴ አትቃዢ ቁመሽ
ይች አለም ከንቱ ናት የማታዛልቅሽ
ዕናማ . . . . .
እናማ አድምጪው ፋጣሪሽን
አታወላውዪ ታዘዢው ጌታሽን
አዎ አታመንቺ ተግብሪ ያለሽን
ሠላም ትገቢ ዘንድ አኼራ ቤትሽን
ነብሴ . . . . .
እሱን ልትገዢ እሱ ፈጥሮሽ
ልትድኚ ላትከስሪ ኢስላምን መርጦልሽ
እና ለምን ይሁን የምታመነቺው
አኼራን ትተሽ ዱንያን የልሽው
እባክሽን ሩሄ ተገዢው ጌታሽን
ከአላህ ታገኚው ዘንድ ሰላምሽን ።
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
〰🍃#ነብዩሏህ #ዩኑስ ዐ.ሰ🍃〰
በድሮ ዘመን አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ ነይነዋ ወደተባለች ምድር ዩኑስ የተባለን ሰው በነቢይነት ይልከዋል።
ዩኑስም አላህ እሱን ነቢይ አድርጎ ስለመረጠውም በጣም ተደስቶ ተልዕኮውን መፈፀም ጀመረ።
ምንም እንኳም ዩኑስ ያለ እረፍት የነይነዋን ህዝቦች ወደ አላህ ቢጣራም ለጥሪው ምላሽ የሰጠ አንድም ፍጥረት አላገኘም።
ዩኑስ ተስፍ ቆረጠ...የህዝቡን አመፅ እና እንቢተኝነት ሲመለከት የነይነዋን ምድር ትቶ ወደማያውቅበት ሀገር ለመሄድም ወሰነ።ነገር ግን የአላህን ፍቃድ አልጠየቀም ነበር እንዲሁ በብስጭት ነበር ዩኑስ ሀገሩን ሊለቅ የወሰነው።
ዩኑስም በማግስቱ ባህር ዳርቻ በመሄድ መርከብ ጠብቆ መርከቢቱ የትም ትሂድ የት ብቻ መርከቢቱ ወደምትሄድበት ሊሄድ ሂሳብ ከፍሎ ተሳፈረ።
ሰዐቱ ፀሀይ ልትጠልቅ ጀንበርን በመሰነባበት ላይ ነበረች....ጨለማውም ምድርን ሊሸፍን ዝግጅት ላይ ነው።ይሄን ግዜ ዩኑስን እና በርካታ ተሳፋሪዎችን የጫነችው መርከብ በጨለማ ባህሩን እየሰነጠቀች መጓዝ ጀመረች።
ሁሉም ነገር በመርከቢቷ ረግቷል..ሰላም እና ሰጥታም እጅጉን ሰፍኗል።በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ መርከቢቷ ብዙ ከተጓዘች በኋላ ባልታሰበ መልኩ በድቅድቅ ጨለማ መርከቢቷን ከየት እንደመጣ ያልታወቀ ማዕበል ከየአቅጣጫው ያናውጣት ጀመር።
ሁሉም ግራ ተጋባ የመርከቧ ሰራተኞች ሁኔታውን ሊያረጋጉ ቢሞክሩም ምንም ሊረጋጋ ባለመቻሉ የመርከቧ ክብደት እንዲቀንስ እያንዳንዱ ሰው የጫነውን ጭነት ከመርከቧ እንዲጥል አዘዙ።
ምንም እንኳን ተሳፋሪው ሁሉ የያዘውን እቃ ወደ ባህር ቢወረውርም የመርከቢቷ መናወጥ ሊቆም አልቻለም።በመጨረሻም መርከቧ ላይ ያሉ ተሳፋሪዎች፦"እዚህ መሀከላችን አንድ ከአሳዳሪው ያመለጠ ባሪያ አለ ማለት ነው።ስለዚህ ያን ወንጀለኛ ለማወቅ እጣ እንጣል" በማለት ተስማሙ።
እጣው ተጀመረ....ወረቀቱ ሲከፈት ዩኑስ የሚል ስም ወጣ።ዳግም እጣ ጣሉ፤አሁንም ዩኑስ የሚል ስም ወጣ። ለሶስተኛ ግዜም እጣ ሲጥሉ የዩኑስ ስም ወጣ...። ያን ግዜ ዩኑስ እራሱን ከመርከቢቱ ሲወረውር አንድ አሳ ነባሪ አፉን ከፍቶ ጎረሰው'ና ወደ ባህሩ ዝቅተኛ ክፍል ይዞት ወረደ።
አላህም አሳ ነባሪውን፦"አንድም አጥንት እንዳትሰብር አንድም ስጋ እንዳታኝክ" አለው።
ዩኑስም በአሳነባሪው ጉሮሮ ተሽሎክልኮ ሆዱ ላይ እንዳረፈም ያን አሳ ነባሪ እራሱ ሌላ አሳ ነባሪ ዋጠው።ዩኑስም እራሱን የአሳ ነባሪው ሆድ ውስጥ ሲያገኝ የሞተ መስሎት ነበር፤ ድንገት እግሩን ሲያንቀሳቅስ በህይወት እንዳለ ተረድቶ መዘከር ጀመረ።
አስቡ ሌሊት ነው፣በዛ ላይ ዩኑስ አሳ ነባሪው ሆድ ውስጥ ነው፣በዛ ላይ ዩኑስን የዋጠው አሳ ነባሪ እራሱ ሌላ አሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ገብቷል፣ ጨለማ ላይ ጨለማ ተደራርቧል።
ዩኑስ እዛው በአሳ ነባሪዎቹ ሆድ ውስጥ ሆኖ የሆነ ጫጫታ ይሰማል...እና በልቡ፦"የምን ጫጫታ ነው ምሰማው ...!!!" እያለ ሲያሰላስል
አላህም፦"የባህር ውስጥ ፍጥረታት ለኔ የሚያደርጉት ውዳሴ ነው" ብሎ ወህይ አወረደለት።
ያን ግዜ ዩኑስ፦"ላ ኢላሀ ኢላ አንተ ሱብሀነከ ኢኒ ኩንቱ ሚነ ዛሊሚን (ከአንተ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጥራት ይገባህ፡፡ እኔ በእርግጥ ከበዳዮቹ ነበርኩ)" ሲል ወደ አላህ ተጣራ።
ዩኑስ እንዲህ ሲል ከሰባት ሰማያት በላይ ያሉ መላዕክት ይሄን ጥሪ ሰምተው አላህን
እንዲህ አሉት፦ያ አላህ አንድ የሚታወቅ ደካማ ድምፅ ከሩቅ ቦታ ይሰማናል"
አላህም፦"እሱ እኮ ዩኑስ ነው። አምፆኝ በአሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ አስሬው ነው" አላቸው።
መላዕክቱም፦"እንዴ! ያ ቀን እና ማታ መልካም ስራዎቹ ወደ ሰማይ የሚወጡለት ዩኑስ?"ብለው ሲጠይቁት
አላህም፦" አዎን" አላቸው።
ያን ግዜ መላዕክቱ ለዩኑስ አማላጅ ሆኑለት'ና ዩኑስን የዋጠው አሳ ነባሪ ከአንድ ደሴት ዳርቻ ሄዶ በአላህ ትዕዛዝ ዩኑስን ተፋው።
ዩኑስ ከአሳ ነባሪው ሆድ ወጥቶ ሲወድቅ የአሳ ነባሪው የሆዱ ሙቀት ዩኑስን እጅጉን አሞቅሙቆት ስለነበር ዝንቦች ይረባረቡበት ጀመር።ያን ግዜ አላህ የዱባ ቅጠልን ዩኑስ በተኛበት ቦታ አበቀለለት።
አላህም ዩኑስ እዛው ሳለ ተውበቱን እንደተቀበለው ወህይ አወረደለት'ና ወደ ህዝቡ እንዲመለስ አዘዘው።
(እሺ አሁን አንዴ ወደኋላ ልመልሳችሁ ነው...አንድም ሰው እንዳይቀር ግርርር ብላችሁ ኑ።)
ዩኑስ መጀመሪያ ህዝቡን ትቶ ሲወጣ አላህ በእነዚያ ህዝብ ላይ ከባድ ቅጣትን አምጥቶ አንዣበበባቸው።ሰማዩ ጠቁሯል...ብቻ ከባድ ቅጣት እንደመጣባቸው ታውቋቸዋል ዩኑስን ማስተባበላቸው በጣሙን ፀፅቷቸዋል።
አሁን ሁሉም ጥፋቱን አምኖ የሀዘን ልብስ ለብሰ፣ላሞችን ከጥጃዎቻቸው ለይተው፣በጎችን እና ፍየሎችን ከግልገሎቻቸው ለይተው፣ ግመሎችንም ከግልገሎቻቸው ልይተው፣ ህፃናት ልጆችንም ከእናቶቻቸው ለይተው ሁሉም ኡኡኡ ብሎ ሲጮህ አላህ ያዝንልናል በሚል ሚዳ ላይ ወጥተው ኡኡኡ...እያሉ አላህን በፀፀት እንባ ለመኑት።
አላህም ተውበታቸውን ተቀብሎ ያመጣባቸውን መቅሰፍት መለሰላቸው። ከዚያም ያ የጠፋውን ነቢያቸውን ይቅርታ ሊጠይቁት በጉጉት ይጠባበቁት ጀመር።
(እሺ አሁን ወደ ቅድሙ ቦታ ኑ...አንድም ስው እንዳይቀር...፤ዩኑስን አጅበን እንመጣለን።)
ከዚያም ዩኑስ እዛች የዱባ ቅጠል ስር ሆኖ ካገገመ በኋላ የቀድሞው ህዝቡ ወደሚገኝበት የነይነዋ ምድር ዳግም ዳዕዋ ለማድረግ ጉዞ ጀመረ።
ዩኑስም ልክ ነይነዋ ከተማ ውስጥ ሲገባ ከ 100,000(መቶ ሺህ) ህዝብ በላይ ተገልብጦ በመውጣት ደማቅ አቀባበል አደረጉለት።በህዝቡ መለወጥ በጣምም ተገረም....እነሱም የተከሰተውን ሁሉ በዝርዝር ነግረውት ይቅርታም ጠየቁት።እሱም ሰላሳለፋቸው አሰቃቂ ግዜያት አወጋላቸው።
ከዚያ በኋላ የዩኑስን ትምህር እየተቀበሉ ለረጅም አመታት በሰላም ከኖሩ በኋላ ዩኑስ ይህ ነው ተብሎ በማይታወቅ እድሜው ይህችን አስቸጋሪ አለም በሞት ተገላገለ።
(የአላህ ሰላም እና እዝነት በዩኑስ ላይ ይሁን)
_________________________________
ምንጮች፦
القرءان الكريم
ﺍﻟﺒﺪﺍﻳﺔ ﻭﺍﻟﻨﻬﺎﻳﺔ /ﺍﻟﺠﺰﺀ ﺍﻷﻭﻝ /
صحيح مسلم
مسند الإمام أحمد
✍ ምንጭ ☞ፍትህ ለእየሱስ
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ይነበብ ከዛም ሼርርር 🌺🌺🌺🌺🌺
⇛ቢስሚላሂረ— ረህማኒረ— ረሂም
አልሀምዱሊላሂ ረብቢል አለሚን
ወሶለዋቱ ወሰላሙ አላ አሽረፈል, ኸልቅ, ሰይድና ፣ሙሀመዲን ፣ወአላ ፣አሊሂ ፣ወአሳሀቢሂ ፣አጅማኢን፣ወመን ተቢአሁ ፣ቢኢህሳኒን ኢላ "የውመዲን "አሰላሙ "ወአለይኩም "ወራህመቱላሂ "ወበረካትሁ።
❁❁❁❁❁❁❁❁❁❁❁❁❁
❂አንድ "ወቅት, ነቢዩ (ሶ, ዐ, ወ) ዘንድ "ያ በአላህ "ፍፁም "የማያምፀው "ውድ "ዘያሪያቸው "ጅብሪል (አ, ሰ) ብቅ አለ "የጅብሪል "ሁኔታ "ግን "እንደበፊቱ, አልነበረም።
ገፅታው "ያሸብራል "ሁኔታው ፣ያስደነግጣል።ያ ጅብሪል "አሉ ነቢዩ (ሶ, ዐ ወ) ምክኒያቱ ""ምንድን ነው።እደዚህ "የቀየረህ "አሉት ።ጅብሪልም "ያ ሙሀመድ " (አተ ሙሀመድ) ወደአንተ "የመጣሁት
🔥"አላህ "የእሳትን "መቀጣጠያ💥 "ወናፍ"እንድትነፈ "ባዘዘበት "ወቅት ነው።
🔥እሳት "እማይቀር "እንዲሁም "የቀብር "ቅጣት, እውን "መሆኑን, ማንም "መዳኑን "እስከሚያረጋግጥ "ሊረጋጋ "አይገባውም "በማለት ""ያሸበረውን "ሁኔታ "ነገራቸው።
✰✰✰✰✰✰✰✰✰✰✰✰✰
ነቢዩ ሙሀመዲ (ሶ, ዐ, ወ) ጥያቄ, ቀጠሉና,
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃
↳↳ያጅብሪል "ያሸበረህን "ጂሀነም "ምን "ይመስላል "እስኪ "አስረዳኛ ? አሉት
✫✫✫✫✫✫✫✫✫✫✫✫✫
💭ጅብሪልም ፣የጂሀነም "ሁኔታ "ያብራራላቸው "ገባ "
❃❃❃❃❃❃❃❃❃❃❃❃❃
🔥🚪ጀሀነም 7 በሮች አሉት, ከመጀመሪያው "እስከ 6ኛው "የሚገቡት "ፍጥረታት "እነዚህና "እነዚህ "ይመስላሉ "አለና " ገለፀላቸው ።
✵✵✵✵✵✵✵✵✵✵✵✵✵
💥7ኛው "ጂሀነም "የሚገባውን ፣ግን "ማውጣት "ከበደው "
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
⛔ጅብሪል "7ኛው በር "የሚገባውን "አነግረኝምን "አሉት "
👉🚪በዚህ "በር "እማ የሚገቡት "ከአንተ "ኡመት "ከባድ ወንጀል "ሰርተው "ተውበት "ሳያደርጉ "የሞቱት "ሰዎች ናቸው ።
አላቸው, ይሄኔ "የኛ "ታላቅ "ነቢይ "ረሱለል "አሚን "ሀቢበል ሙስጠፋ "ሶለልሏሁ "አለይሂ "ወሰለም "እራሳቸውን "ስተው "ወደቁ ፣
🍥ጅብሪል (አ, ሰ) እስከሚነቁ "እጁን "እራሳቸው ላይ "አደርገና "ጠበቃቸው "ሲነቁም
❉❉❉❉❉❉❉❉❉❉❉❉❉
↬ጅብሪል "መከራየየም "በዛ "ሀዘኔም "በረታ ፣ከእኔ "ኡመት "ጂሀነም ፣የሚገባ አለን "አሉ "
↳↳ጅብሪልም "ታላላቅ "ወንጀል "የሚሰሩ "አላቸው።
እና "አብሩዋአቸው "ያለቅስ "ጀመረ "
➲ረሱል (ሶ, ዐ, ወ) ያጅብሪል "አተም "ታለቅሳለህን ? አሉት ⇲⇲⇲⇲⇲⇲⇲⇲⇲⇲⇲⇲
⇰ጅብሪልም "እደት አላለቅስ "የኔንስ መጨረሻ "በምን, አውቀዋለሁ? "እብሊስ "እኮ
""ከመላእክት "በላይ "አላህን "ይገዛ ነበር።
አላቸው, ቺሎታው "እጂግ "የላቀው "(600) ክፍች "ባለቤት "የሆነው "በአንድ "ክንፍ "መሬትን "ሊገለብጥ "የሚቺል "ግዙፍ "ቅዋ "ያለውና "የመጪውም "ያለፈውም, ወንጀል "የተማረላቸው "ነብይን "ያሰጋች "እሳት "ምንኛ "ትከብድ "ይሆን "
✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾
➧ወንድሜ "እኔስ "አንተስ "እህቴ "አቺስ
☝ አላህ "ይጠብቀን " አላሁመ "አኡዙቢከ " ሚነናር ⇼⇼⇼⇼⇼⇼⇼⇼⇼⇼⇼⇼
🙏🙏🙏ጌታየ 🙏🙏🙏
"እኛንም "ቤተሰቦቻችንንም "ከጂሀነም "እሳት በረህመቱ ይጠብቀን ።
⛔ማሳሰቢያ⛔
☝ ይሄንን ሸር ብናደርግ አላሁ ሱብሃነሁ ወተዐላ ጀነት ሊሰጠን ይችላል
ሰው ትንሽ ናት ብሎ በሚንቃት ሰራ ነፍስያውን አሸንፎ ሸር ብናደርግ ጀነትን
ኢንሻአሏህ 📖📖📖 ወቢላሂል ተዉፊቅ
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
