981
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ከዚና በላይ ከባድና አደገኛ የሆነ ወንጀል
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ዚና ክብርን የሚያሳጣ እንዲሁም ዘርን የሚያጠፋ በመሆኑ አላህ ዘንድ ከባድ ወንጀል ነው፡፡ ነብያችንም ወደ ዚና የሚያዳርሱ መንገዶችን ሁሉ እንዳንቀርብ አስጠንቅቀዋል፡፡አላህም ከዚህ አስቀያሚ ድርጊት እንድንርቅ የዛኒና የዛኒያ (የወንድና የሴት ዝሙተኛን ) ቅጣት እንዲህ ሲል ነግሮናል።
الزَّانِيَةُ وَالزَّانِي فَاجْلِدُوا كُلَّ وَاحِدٍ مِّنْهُمَا مِائَةَ جَلْدَةٍ ۖ
((ዝሙተኛይቱና ዝሙተኛው ከሁለቱ እያንዳንዳቸውን መቶ ግርፋትን ግረፉዋቸው))
ልብ በሉ ይህ የግርፋት ቅጣት ያላገቡ እንደሆነ ነው፡፡ ያገባ ከሆነ ግን ተቀጥቅጦ ይገደላል፡፡
ወደ ዋናው ርዕሳችን ስንመለስ በሙሳ ዐሰ ዘመን በአንዲት ሴት የተከሰት ታሪክ ነበረ፡፡ ይህች ሴት ከወንጀሏ ተውበት ለማድረግ ወደ ሙሳ ትመጣና
"ሙሳ ሆይ እኔ በዚና አረገዝኩ ይህ አልበቃ ብሎኝ በዚና የወለድኩትን ልጅ ገደልኩት"
ሙሳም "የፈፀምሽው በጣም ከባድ ወንጀል ነው በወንጀልሽ ሰበብ አላህ ከሰማይ እሳት ሳያዘንብብን በፊት ከዚህ ጥፊልኝ" አሏት
እሷም አዝና ተመልሳ ሄደች
ከትንሽ ቆይታ በኃላ አላህ ወደ ሙሳ መላኢካ ላከና በሴቷ ጉዳይ እንዲህ አለው
"አንተ ሙሳ ከዚች ሴት የበለጠ ወንጀለኛ መኖሩን አላወክምን?"
ሙሳ "ከዚች የበለጠ ወንጀል ማን ሊፈፅም ይችላል?"
አላህም "ሰላትን ሆን ብሎ የሚተው ሰው ወንጀሉ ከዚች ሴት ይበልጣል" ሲል መለሰለት፡፡ ሱብሐነላህ
ማንኛውም ከባኢር የሚባሉ እንደ ግድያ ዚና የየቲምን ሐቅ መብላት የመሳሰሉ ከባባድ ወንጀሎች በአላህ መሺአ ውስጥ ናቸው፡፡ አላህ ከሻ ይቀጣባቸዋል ከሻም ይምራቸው፡፡
ምንም እንኳ ይህ ከላይ የተጠቀሰው ሐዲስ ከኢስራኢልያት ቢሆንም ይህን የሚደግፉ በርካታ ሰሒሕ ሐዲሶች አሉ፡፡ ከነዚህም መካከል
ነብዩ ሰዐወ ሆን ብሎ ማይሰግድን ሰው የአላህ ጥበቃ የተነፈገ መሆኑንና "ፈቀድ ከፈረ"/ "ካፊር ነው"/ ማለታቸው የወንጀሉን ክብደት ያሳያል፡፡በተጨማሪም ነብዩ ሰዐወ ኢስራእ ባደረጉበት ወቅት ጭንቅላቶቻቸው በድንጋይ የሚጨፈለቅ ሰዎችን ተመለከቱ (ከተጨፈለቀ በኋላ ተመልሶ ደህና ይሆናል፡፡ እንደገና ተመልሶ ይጨፈለቃል በዚህ ሁኔታ እየተመላለሰ ራሱ ይጨፈለቃል)
ነብዩ "እነዚህ ሰዎች ማናቸው?" ብለው ጂብሪልን ጠየቁ
"እነዚህ ሰዎች ከሰላት የሚዘናጉ ሰዎች ናቸው" ብሎ መለሰላቸው፡፡ ማለትም ዙሁርን ሳይሰግዱ አስር የሚገባባቸው መግሪብን ሳይሰግዱ ኢሻ የሚገባባቸው ሰዎች ናቸው::
ሙሉ ለሙሉ የተዉ ሰዎችስ ምን ያህል ይቀጡ ይሆን?
አላህ ሰላት የሚተዉ ሰዎች አስመልክቶ
۞ فَخَلَفَ مِن بَعْدِهِمْ خَلْفٌ أَضَاعُوا الصَّلَاةَ وَاتَّبَعُوا الشَّهَوَاتِ ۖ فَسَوْفَ يَلْقَوْنَ غَيًّا
"ከእነሱም በኋላ ሶላትን ያጓደሉ (የተዉ) ፍላጎቶችንም የተከተሉ መጥፎ ምትኮች ተተኩ! የገሀነምንም ሸለቆ በእርግጥ ያገኛሉ፡፡" ይለናል አላህ ይጠብቀን
ይህንን አንተ እንዳነበብከው ሌሎችም የዚ ኸይር ተካፋይ እንዲሆኑ ላክላቸው፡፡ በርካታ ሰዎች ከሰላት ይዘናጋሉ ፕለስ
Join us on
telegram channal
⇩⇩⇩ ⇩⇩⇩ ⇩⇩⇩
https://t.me/susui_slamic_channal
አንድ ጊዜ መላኢካዎች በተራራ ጥንካሬ ተገረሙ እና አላህን(ሱ·ወ) እንደዚህ ብለው ጠየቁ።
“ከተራራ በላይ ጠንካራ አድርገህ የፈጠርከው አለ እንዴ“? ብለው ጠየቁት አላህም(ሱ·ወ) “አለ ብረትን ፈጥሪያለሁ ከተራራ በላይ ጠንካራ ነው።ብረት ተራራን እንዳልነበር ያደርጋል“።አላቸው “ከብረትስ በላይ ጠንካራ አድርገህ የፈጠርከው
አለ?“ አሉ። “አዎ እሳትን ፈጥሪያለሁ እሳት ብረትን ማሸነፍ ይችላል“ አላቸው።
“ከእሳትስ በላይ ጠንካራ አድርገህ የፈጠርከው አለ እንዴ?“ ብለው ጠየቁ አላህ (ሱ·ወ) “አዎ ውሀን ፈጥሬያለሁ።“ውሀ እሳትን ማጥፋት ይችላል አላቸው።ከውሀ
በላይ ደሞ አለ ነፋስን ፈጥሪያለሁ ነፋስ ውሀን ይበተናል“።ከነፋስ በላይ ጠንካራ የሆነነገር አልነግራችሁምን ከነዚህ ሁሉ ጠንካራ የሆነ ነገር የኔ ቁጣ አለ“።(ያአላህ ካንተ ቁጣ አንተው በራህመትህ ጠብቀን እኛ አቅመ ደካሞች ነን።) ከኔ ቁጣ በላይ ጠንካራ
የሆነ ነገር አልነግራችሁምን ሶደቃ ናት።ሶደቃ የኔን ቁጣ መመለስ ትችላለች“።
https://t.me/susui_slamic_channal
#አንዲት የ 18 አመት ልጅ ድንገት ከትምህርት ቤት እየተመለሰች ሳለ አንድ ባለ መኪና አፍኖ ይዞ ከመኪናው የሗላ ኪስ ይከታታል ከዛው ወደ ጫካ ይዞዋት ይሔዳና ኬሱን ለመክፈት ሲሞክር እምቢ ይለዋል ቢታገል ቢታገል እምቢ ይለዋል አረ ጉድ ሐገር አየኝ ብሎ እዛው አቅራቢያ ወዳለ ገራጅ መኪናውን ይዞ በመሔድ አረ ከጉድ አውጡኝ ይላል: እነሱም በተራቸው ለመክፈት ይታገሉ ጀመር ሊሳካላቸው አልቻለም ከዛው አማራጭ ሲያጣ ልጅቷ ሙታ እንዳይሆን በማለት እጁን ለፖሊስ ለመስጠት ተገደደ ከዛው ፖሊሶቹም ለመክፈት ሲታገሉ ነቀነቅ አላላም ከዛው አንድኛው ፖሊስ አንድ ሐሳብ አመጣ ለኡለማኦች ይነገርና በኪሱ ላይ ቁርአን ይቀራበት አለ በዚሐሳብ ተስማምተው ለአንድ አሊም ተነገራቸውና መጥተው ቁርአን ሲቀሩበት የመኪናው ኪስ ተከፈተ ይሔን ጊዜ ልጅቱ በአፏ ይሆነ ነገር ትላለች በመቀጠል ሸኺየው ለመሆኑ ሰውየው ካፈነሽ ጊዜ ጀምሮ ምን እያልሽ ነበር አሉዋት እሷም እንዲህ አለች:
(አየተልኩርሲይና)
(ሙአወዘተይን)
ማለትም ቁል አኡዙ ቢረቢል ፈለቅ እና ቁል አኡዙ ቢረቢናስ እየቀራሁ ነበር እስከአሁኖ ሰአት ደጋግሚ ሳላቆም እየቀራሁ ነበር ይሔንን ደግሞ "ያስተማረቺኝ እናቴ ናት በማንኛውም ጊዜ ምንምአይነት ችግር ሲገጥመኝ እንድቀራው ትመክረኝ ነበር" አለች::
አላሁ አክበር
#ከአላህ ጋር የሆነ አላህ ከሱጋር ይሆናል
ወንድምና እህቶች
አንድ ነገር ታውቃላችሁ ሁል ጊዜ ከሰላት በሗላ አየተል ኩርሲይ የቀራሕ እንደሆን ጀነት ለመግባት ባንተና በጀነት መሐከል ያለው ሞት ብቻ ነው ስለዚሕ ውዶቼ ሁልጊዜ አየተል ኩርሲይ እንቅረ!
አላህ ተጠቃሚ የድርገን አሚን!!!
https://t.me/susui_slamic_channal
#ይህችን #ምርጥ #ቂሳ #ጋበዝኳችሁ!!
✍አንድ ጥበበኛ ሽማግሌ የወንዝ ዳር ላይ ቁጭ ብሎ ሳለ፤ ድንገት አንድ #ድመት ወንዝ ውስጥ ሲወድቅ ይመለከታል። ድመቱም ራሱን ከመስመጥ ለማዳን መንፈራገጥ እና ወደ ላይ ለመዝለል መሞከሩን ተያያዘው። ጥበበኛውም ሰው ይህን ድመት ለማትረፍ ይወስንና ለድመቱ እጁን ዘረጋለት።ድመቱም የሰውየውን እጅ ባጨረው። ሰውየው እጁ ሲቧጨር ጮኅ እና እጁን ቶሎ መለሰ። በጣም አመመው።
ጥቂት ደቂቃ ቆይቶም፤ ለ2ኛ ጊዜ እጁን ድመቱን ለማትረፍ ዘረጋለት። በድጋሚ ድመቱ የሰውየውን እጅ በሃይል ቧጨረው። እጁን እያመመው ጮሆ ወደ ኋላ መለሰው። ከመጀመርያው የበለጠ በጣም አመመው። አሁንም ጥቂት ሰከንድ ቆይቶ እጁን ለ,3ኛ ጊዜ ዘረጋለት።
የሆነ ሌላ ወጣት ይህን ድርጊት ከቅርብ ይከታተል ነበር። ወጣቱም ለሰውየው ድምፁን ከፍ አድርጎ በመጮህ እንዲህ አለው "አንተ ጥበበኛ ሆይ! ለምን ከ1ኛው እና ከ2ኛው ድርጊትህ አትማርም። ድጋሚ ለ3ኛ ጊዜ እጅህን ትዘረጋለህ!? ስትሞክር እየቧጨረህ አይደል እንዴ!!?" አለው። ሰውየውም የወጣቱን ንግግር ችላ ብሎ በተደጋጋሚ መሞከሩን ቀጠለበት። በስተመጨረሻም #ድመቱን ማትረፍ ተሳካለትና ከወንዙ ውስጥ አወጣው።
በመቀጠልም ጥበበኛው ወደ ወጣቱ ተጓዘና እንዲህ አለው "አንተ ልጄ! ድመት በባህሪው ይቧጨራል፤ እኔ ደግሞ በባህሪዬ ትሁትና አዛኝ ነኝ። ታዲያ የሱ ባህሪ የኔን እንዲያሸንፍ እንድፈቅድለት ለምን ትፈልጋለህ!? አንተ ልጄ! ሰዎችን በባህሪህ እንጂ በባህሪያቸው አትኗኗር፤ ምንም ቢሆኑ፤ አንተን የሚጎዳ ብልሹ ምግባራቸው ቢበዛ እንኳ። ለነዚያ ያንተን ጥሩ ባህርይ እንድትተው ለሚፈልጉ ብልሹ ምግባሮች ቦታ አትስጥ። አንተ ሰዎችን ለማስደሰት ስትኖር፤አላህ አንተን የሚያስደስትህን ይልክልሃል። { የበጎ ምግባር ምንዳ ከበጎ ውጭ ሌላ ነውን!? }። አንተ የውብ ምግባር ባለቤት ሁን። ሰዎችን ያስደሰትክባቸውን ሁኔታዎች እያስታወስክ ሰውየው ትህትና የማይገገባው ቢሆን እንኳ አትፀፀት።
በሚያውቅህ ሰው ህይወት ውስጥ ቆንጆ ነገር ሁን። በመልካም መልካምን የሚመነዳው ጌታ አላህ በቂህ ነው!!"
መልዕክቱ....
✍ #ኢብኑል #ቀይም እንዲህ ይላሉ " ዲን ሁሉም ስነ-ምግባር ነው፤ በጥሩ ምግባር የበለጠህ በርግጥ በዲንም በልጦሃል"
ይህን አስተማሪ ታሪክ ሼር ማረግ አትርሱ!
https://t.me/susui_slamic_channal
#አስገራሚ_ታሪክ_ነው
አንዱ ሚስቱን ይመታታል። በአጋጣሚ ሊገድላት ሳያስብ በእጁ ትሞትበታለች። ጉዳዩ ይፋ ወጥቶ ዕዳ እንዳይኾንበት ምን ማድረግ እንዳለበት ያስባል። አስቦ አሰላስሎ በስተመጨረሻም አንድ ሀሳብ መጣለት። እርሱም ወደ ሰፈራቸው አዋቂ ነኝ ባይ ሰው ጋር መሄድ ነበር። ታዲያ ይሄ አዋቂ ተብዬ ሰውም መፍትሄ የሚለውን ሀሳብ እንዲህ ሲል ይመክረዋል ። ደጅህ ላይ ተቀምጥና ቆንጆ ወጣት ሲያልፍ ካየህ "አንዳች የምታግዘኝ ነገር አለ" በለውና ወደ ቤትህ አስገባው።
ከዚያም ግደለውና ከባለቤትህ እሬሳ ጋር አጠገብ ለአጠገብ አጋድመው ። የርሷን ቤተሰቦች ጥራና " ከዚህ ወጣት ጋር ሲያመነዝሩ ስመለከት እራሴን መቆጣጠር ተስኖኝ እርምጃ ስወስድባቸው በእጄ ሞቱ" ብለህ ንገራቸው አለው።
አባ ውራውም መላ ነው ተብሎ የተነገረውን ተቀብሎ ደጃፉ ላይ ሄዶ ቁጭ ብሎ መጠባበቅ ይጀምራል። ብዙም ሳይቆይ አንድ ወጣት በአጠገቡ ሲያልፍ ተመለከተና "ወንድም አንዴ ላስቸግርህ? የሆነች ነገር እንድታግዘኝ ፈልጌህ ነበር" ብሎ አስማምቶ ወደ ቤት ያስገባዋል።
እንደተመከረውም ይገድለውና ከሚስቱ ጀነዛ አጠገብ ያጋድመዋል ። የሚስቱ ቤተዘመዶች ሲመጡም በዝሙት ላይ አግኝቷቸው ራሱን መቆጣጠር አቅቶት እርምጃ እንደወሰደባቸው ይነግራቸዋል። እነርሱም ጥፋተኛ ሳያደርጉት ምክኒያቱን ይረዱትና ይተዉታል።
ይሄንን የማምለጫ ዘዴ ነግሮት የነበረው ሰውዬ ገዳዩ ከምን
እንደደረሰ ሊጠይቀው ቤቱ ይከሰታል። ገዳዩ ሰውዬም የመከረውን እንዳደረገና እንደተሳካለት በኩራትና በምስጋና ይነግረዋል። እስኪ የገደልከውን ልጅ አሳየኝ ብሎ አዋቂ ተብዬው ይጠይቀዋል። ገዳዩ ወስዶ ሲያሳየውም ለካስ የተገደለው የራሱ የአዋቂ ነኝ ባዩ ልጅ ኖሯል! በሳሉት ቢላ
መቆረጥ ይሉሃል እንደዚህ ነው!
ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ (ረ ዐ) እንዲህ ይላሉ ። ለተንኮል ሰይፉን የሳለ እራሱ ይቆረጥበታል። ለወንድሙ ጉድጓድ
የቆፈረ ራሱ ይገባበታል። የሌሎችን ነውር አደባባይ የሚበትን የራሱ ነውር አደባባይ ይታይበታል።
#ለወዳጅ_ዘመዶ_ሼር_ያድርጉ
https://t.me/susui_slamic_channal
#ልብ_የሚነካ_ቂሷ//
አንድ በጣም እናቱን የሚወድ ህፃን ልጅ ነበረ...
እናም የአላህ ፍቃድ ይሆንና እናት ወደ አኸራ ትሄዳለች።
ያው የሆነው ሆኗል አባትም ሌላ ሚስት አገባ።
ነገር ግን አባት ምንም እኳን ሌላ ሚስት ቢያገባም
ለልጁ ያለው ቦታ ከበፊቱ ይብሳል...
በገባ በወጣ ቁጥር ስለሱ ይጠይቃል
እናም አባት አንድ ቀን ልጁን ስለ አዲሷ ሚስቱ ሊጠይቀው ይወስንና...
እንዲህ ይለዋል፦
"እስቲ በመጀመሪያዋ እናትህ እና በአዲሷ እናትህ ያየከውን ለውጥ ንገረኝ?"
ልጁም፦"አዎ አባዬ ልዩነት አለ።የመጀመሪያዋ እናቴ ውሸታም ነበረች በቃሏ አትገኝም አዲሷ ግን ሁሌም ቃሏን ትሞላለች።"ይለዋል።
አባትም በልጁ ንግግር በጣም ግራ በመጋባት
"እንዴት?" አለው።
ልጁም፦"የመጀመሪያዋ እናቴ
1፦ምግብ ካልበላህ እገርፍሀለሁ
2፦በአዋራ ከተጫወትክ እገርፍሀለሁ....
እያለች ትዝትብኛለች ግን አታደርገውም/ቃሏን አትሞላም።
አዲሷ እናቴ ግን ትዕዛዟን ካላከበርኩ ምግብ እንደማትሰጠኝ ትዝትብኛለች ዛቻዋንም ትፈፅመዋለች/ቃሏን ትሞላለች።
ይኸው እኔ ከሁለት ቀን አንስቶ እርቦኛል።ብሎ መለሰለት።
#እናት በምንም አትተካም ግዜ ስጣት እሷ ከንተ ሌላ ምንም አትፈልግም እን!!!
አላህ እናቶቻችንን ያቆይልን
የሞቱትን ይማርልን።
https://t.me/susui_slamic_channal
#ራስ_ወዳድ_አንሁን!
አህመድ እና መርየም የሚባሉ ባልና ሚስት ነበሩ። በጣም ደስ የሚል ቤትና ሁለት የሚወደዱ ልጆችም አሏቸው፤ አንድ ወንድ እና አንድ ሴት። ከዕለታት አንድ ቀን አሕመድ ለሥራ ጉዳይ ወደ ሌላ ከተማ እንዲሄድ በአለቆቹ ይነገረዋል። ለበርካታ ቀናት ሊቆይ እንደሚችልም ይገለጽለታል። ሚስቱ መርየም ይህንን ስትሰማ እርሷም ከከተማ ወጣ ብሎ ትንሽ የመቆየት ፍላጎት ስለደረባት አብራው ለመሄድ ጥያቄ ታቀርብለታለች። እርሱም በደስታ እሺታውን ይገልጽላትና ለጉዞ ዝግጅት ይጀምራሉ። ከሁሉም በፊት ግን ሁለቱ ልጆቻቸውን በቅርበት የምትጠብቅላቸው አንዲት ታማኝ ሴትን ይቀጥራሉ። ባልና ሚስት ለጉዞ የሚያስፈልጋቸውን ዝግጅት አጠናቀው ወደ ተባለው ከተማ ይሄዳሉ። አሕመድና መርየም ወደ ቤታቸው መመለስ ከሚገባቸው ቀን ዘግይተው ነበር የተመለሱት። መኖሪያ ከተማቸው ሲደርሱ ሁለቱም ደስ አላቸው። ነገር ግን ከሚኖሩበት ሰፈር አከባቢ አቅጣጫ ጭስ መሰል ነገር ሲመለከቱ ምን እንደሆነ ለማጣራት በቀጥታ ወደ ቦታው ያመራሉ። አንድ ቤት ተቃጥሎ በእሳት እየነደደ ነበር። መርየምም "የሚገርም ነው የእኛ ቤት አይደለም ወደ ቤታችን ሄደን ልጆቻችንን እንይ" ትላለች። አሕመድ ግን መኪናውን እየነዳ ወደተቃጠለው ቤት ቀርቦ ተመለከተ። በጣም በማዘንም "የማን ቤት እንደሆነ አወቅሽ? እዚያ ትልቅ ፋብሪካ ውስጥ የሚሠራው የጀማል ቤት እኮ ነው። እስካሁን ከሥራ የተመለሰ አይመስለኝም። አንድ ልናደርገው የምንችለው ነገር ይኖራል ብዬ አስባለሁ" በማለት ተናገረ። ሚስት ግን ተቃወመችው "እኛን የሚያገባን ምንም ነገር የለም። ይህ የለበስከው በጣም ውድና የሚያምር ለብስ መበላሸት የለበትም። ወደ እሳቱ ከቀረብክ ግን ይህ ልብስህ ከጥቅም ውጭ ነው የሚሆነው" በማለት ወደቤት እንዲሄድ ገፋፋችው።
አሕመድ ለመርየም ንግግር ምንም ምላሽ ሳይሰጥ መኪናዋን እያሽከረከረ የሚቀጣጠለው ቤት ደረጃ አጠገብ አቆማት። ቤቱ ሙሉ በሙሉ በእሳት ተያይዟል። አንዲት ሴት ከቤቱ ውስጥ የስቃይ ድምጽ ታሰማለች። "ልጆቹ! ልጆቹ! በማለትም ታለቅሳለች። ባልና ሚስት ከሚገባው በላይ ደነገጡ። አሕመድ በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ የወደቀችውን ሴት ትከሻ ክንድ በመያዝ ካነሳት በኋላ ልጅቹ የት እንደሆኑ ጠየቃት። ሴትየዋም ልጆቹ ምድር ቤት ውስጥ መሆናቸውን እያቃሰተች ተናገረች። አህመድ እየተጣደፈ አጠገቡ ያገኘውን ባልዲ ሙሉ ውሃ በለበሰው ልብስ ላይ በማፍሰስና በውሃ የተነከረ ፎጣ አናቱ ላይ በማሰር ወደምድር ቤቱ ይገባል። ምድር ቤቱ በጭስ ታፍኗል። ሙቀቱ ሰው አያስቀርብም። እንደምንም ብሎ ልጆቹን በትከሻው ተሸክሞ ሲወጣ ሌላ የሕጻናት የጭንቀት ድምጽ ይሰማዋል። በትከሻው የተሸከማቸውን በፍርሃት የሚንቀጠቀጡ ልጆች ይዞ ከወጣ በኋላ ቤቱ ውስጥ ሌሎች ሕጻናትም እንዳሉ ይነገረዋል።
በድጋሚ ተመልሶ ሊገባ ሲንቀሳቀስ ሚስቱ እጁን ይዛ ልትከለክለው ትሞክራለች። "መሞት ትፈልጋለህ እንዴ? ተመልሰህ እንዳትገባ!" በማለት ስትናገር አህመድ የያዘችውን እጇን መንጭቆ እሳቱ ወደሚነድበት ቤት ሮጦ ይገባል። በጭስ ታፍነው ለመሞት የተቃረቡ የሚመስሉ ሁለት ሕፃናትን ያገኛል። ወዲያውኑ በጎንና ጎኑ አንገቱን በደንብ እንዲይዙ አደረጋቸው ከቤቱ በመውጣት ላይ እያለ አንዳች የሚያውቀው የሚመስለው ነገር ሰውነቱን ያወረዋል። ጎንና ጎኑ አንገቱን በሁለት እጆቻቸው ጨምድደው የያዙት ልጆች የሚያውቃቸው መሰለው። እየሮጠ ከሚቃጠለው ቤት እንደወጣ የተመለከተው ነገር የማይታመን ሆነበት። ሳያስበው ጉንጩ በእንባ ተሞላ። ሁለቱ ሕፃናት የራሱ ልጆች ነበሩ። እንድትጠብቃቸው የተቆጠረችው ሴት ገቢያ ስትሄድ በአደራ ጎረቤት አስቀምጣቸው ነበር።
ሚስቱ ስትከለክለው የሷን ሃሳብ ተቀብሎ ቢሆን ምን አንደሚፈጠረ መገመት አያስቸግርም። በጎ ነገር ስን ሰራ እራሳችንንም እንደሚጠቅመን እንወቅ!
https://t.me/susui_slamic_channal
ًﻗﺎﻝ ﺍﻹﻣﺎﻡُ ﺍﺑﻦُ ﺍﻟﻘﻴﻢ : (ﻭﺃﻣﺎ ﺍﻟﺘَّﻬْﻨِﺌَﺔُ ﺑِﺸَﻌﺎﺋﺮِ ﺍﻟﻜُﻔﺮ ﺍﻟﻤُﺨْﺘﺼَّﺔ ﺑﻪ ﻓَﺤﺮﺍﻡٌ ﺑﺎﻻﺗِّﻔﺎﻕ، ﻣِﺜﻞ ﺃﻥ ﻳُﻬَﻨِّﺌَﻬﻢ ﺑِﺄﻋﻴﺎﺩِﻫﻢ ﻭَﺻَﻮﻣِﻬﻢ، ﻓﻴﻘﻮﻝ : ﻋﻴﺪ ﻣﺒﺎﺭﻙ ﻋﻠﻴﻚ، ﺃﻭ ﺗَﻬْﻨَﺄ ﺑﻬﺬﺍ ﺍﻟﻌﻴﺪ ﻭﻧﺤﻮﻩ، ﻓﻬﺬﺍ ﺇﻥْ ﺳَﻠِﻢَ ﻗﺎﺋِﻠُﻪ ﻣِﻦ ﺍﻟﻜﻔﺮ ﻓﻬﻮ ﻣﻦ ﺍﻟﻤﺤﺮﻣﺎﺕ، ﻭﻫﻮ ﺑﻤﻨﺰﻟﺔ ﺃﻥ ﻳُﻬﻨِّﺌﻪ ﺑِﺴﺠﻮﺩﻩ ﻟﻠﺼَّﻠﻴﺐ، ﺑﻞ ﺫﻟﻚ ﺃﻋﻈﻢُ ﺇﺛﻤﺎً ﻋﻨﺪ ﺍﻟﻠﻪ، ﻭﺃﺷﺪُّ ﻣﻘﺘﺎً ﻣﻦ ﺍﻟﺘﻬﻨﺌﺔ بِشُرب ﺍﻟﺨﻤﺮ، ﻭﻗَﺘْﻞﺍﻟﻨﻔﺲ، ﻭﺍﺭْﺗﻜﺎﺏ ﺍﻟﻔَﺮْﺝِ ﺍﻟﺤﺮﺍﻡ ﻭﻧﺤﻮﻩ ﻭﻛﺜﻴﺮ ﻣﻤَّﻦ ﻻ ﻗَﺪْﺭَ ﻟﻠﺪِّﻳﻦ ﻋﻨﺪﻩ ﻳﻘﻊ ﻓﻲ ﺫﻟﻚ، ﻭﻻ ﻳﺪﺭﻱ ﻗُﺒْﺢَ ﻣﺎ ﻓَﻌَﻞَ، ﻓﻤﻦ ﻫَﻨَّﺄَ ﻋﺒﺪﺍً ﺑﻤﻌﺼﻴﺔٍ ﺃﻭ ﺑﺪﻋﺔٍ ﺃﻭ ﻛُﻔﺮٍ ﻓﻘﺪ ﺗَﻌَﺮَّﺽَ ﻟِﻤَﻘﺖِ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺳَﺨَﻄِﻪ ..... ﺇﻟﺦ (ﺍﻧﻈﺮ ﺃﺣﻜﺎﻡ ﺃﻫﻞ ﺍﻟﺬﻣﺔ 1/161
•ኢማም ኢብኑል ቀይም እንዲህ ይላሉ፦
(ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ የሀይማኖት መገለጫዎች እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት ኩፋሮችን ማስደሰት፤ ይህ ሁሉም ኡለማኦች ሀራምነቱን የተስማሙበት ጉዳይ ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓሎችና ፆሞች ወቅት (ለአንዱ ካፊር) "በዐሉ የተባረከ ይሁንልህ" ወይም "እንኳን ደስ ያለህ" እና የመሳሰሉ የደስታ መግለጫዎችን ቢያቀርብ፤ ተናጋሪው ከኩፍር ቢድንም እንኳ ትልቅን ሀራም ሰርቷል። ይህም ልክ(ለካፊሩ) "እንኳን ለመስቀል ሰገድክ" ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው። ኧረ እንደውም አንድ ሰው አስካሪ መጠጥ በመጠጣቱ፣ ነፍስ በማጥፋቱ፣ ዝሙት በመስራቱና በመሳሰሉት ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ከማለት ወንጀልነቱ አላህ ዘንድ የከበደ እና በጣም የሚያስቀይም ነው። ለእስልምና ሀይማኖት ተገቢውን ክብር የማይሰጡ ብዙዎቹ ሰዎች እዚህ ጥፋት ውስጥ ይወድቃሉ። አስጠሊ ተግባር የፈፀሙም አይመስላቸውም። ወንጀልን ወይም ቢድዓን ወይም ኩፍርን የፈፀመን ግለሰብ እንኳን ደስ ያለህ የሚል ሰው፤ ይህ ራሱን ለአላህ ቁጣ እና ለአላህ ጥላቻ አጋልጧል።)
🚫 ማስታወሻ ”ክርስቲያኖች በኢድ በአረፋ እንኳን ደስ ያላችሁ ይሉን የለንዴ ፤እኛስ በበዓላቸው በማስደሰት ውለታቸውን እየመለስን የኢስላምን ገርነትና አብሮ አዳሪነት ብናሳያቸውስ" የሚሉ ሙስሊሞች ይኖራሉ ።
•«ለዚህ የሚሰጠው መልስ፦ እነሱ በበዓላታችን ቢያስደስቱን፤ እኛ በበዓላቸው አናስደስታቸውም።ምክኒያቱም በእኛና በእነሱ በዓላት መካከል ሰፊ ልዩነት ስላለ።
የኛ በዓላት ትክክለኛና የትክክለኛው ሀይማኖታችን አካል ናቸው። የነሱ በዓላት ግን ባጢል(ከንቱ) እና ከባጢል ሀይማኖታቸው አካል ናቸው። እኛን በእውነት ቢያስደስቱን፤ እነሱን በውሸት አናስደስታቸውም።
በዓላቶቻቸው ደግሞ ከበርካታ ወንጀሎችና አስፀያፊ ነገሮች አይፀዱም። ከሁሉም የሚከፋው ደግሞ በአላህ ማጋራታቸውና በእሱ መካዳቸው ነው።ክርስቲያኖች የመርየምን ልጅ ነቢዩላህ ዒሳን አምላክ ወይም የአምላክ ልጅ አድርገው ይዘወት የለንዴ!?
አላህ እነሱ ከሚቀጥፉበት ሁሉ ንፁህ ነው። ይህ ብቻ አይደለም። በበዓል ቀናቶቻቸው ውስጥ የፈጠራቸውን ብቸኛውን አንዱን አምላክ አላህን ሱብሃነሁ ወተዓላ ትተው ፍጡሮቹን ይማፀናሉ ፤ ረድኤትንም ከነሱው ይፈልጋሉ፤ እነሱንም ያመሰግናሉ። በዚያን ቀንም የሴትና ወንድ ትርምስ ይኖራል፣ አስካሪ መጠጦችን ራሳቸውን እስኪስቱ እንደልብ ይጠጣሉ፣ ዝሙትም ይሰራሉ፣ የአላህ ህግጋቶች በሰማዩ ጥላ ስርና በምድሩ ምንጣፍ ላይ ይጣሳሉ። ይህንና የመሳሰሉ አላህን የሚያስቆጡ ተግባራትን የሚሰሩበትን በዓላታቸውን፤ እኛ ታድያ በላ ኢላሀ ኢለላህ፤ ሙሀመዱን ረሱሉላህ፤ ዒሳ ረሱሉላህ" የምናምን ሙስሊሞች እንዴት አብረናቸው እናከብራለን!?
እንዴትስ እንኳን ያደረሳችሁ በማለት እናስደስታቸዋለን??
ፈጣሪን አስቆጥተን መጥፎ ፍጡሮቹን እንዴት እናስደስታቸዋለን!?ሱብሃላህ!
•እህት ወንድሞቼ! አላህን እንፍራ ፤በእንዲህ አይነት ጉዳይ ተዘናግተን የምንሳተፍ ካለን ወደ አላህ እንቶብት ፤በዲናችን ኢዕቲዛዝ ወይም ልቅና ይሰማን፤ዲናችንንም እንማር ፤ ልቅናንም ቁርኣንና ሀዲስን ቀደምት የኢስላም ትውልዶች በተረዱበት መልኩ እየተገነዘብን በኢስላም እንፈልግ።
قال عمر رضي الله عنه: "نحن قومٌ أعزَّنا الله بالإسلام فمهما ابتغينا العِزة من غيره أذلَّنا الله"
"እኛ በኢስላም ልቅናን የተጎናፀፍን ህዝቦች ነን፤ ከኢስላም ውጪ ልቅናን ከፈለግን የተዋረድን እንሆንና አላህ የበታች ያደርናል።
هذا والله أعلم.
📎 https://t.me/susui_slamic_channal
ሙስሊም ወንድሞችና እህቶች ስለ መስከረም አንድ በዓል ምን ያህል እናውቃለን?
በዓሉን በጋራ አብሮ ስለማክበርና የበዓሉን ባለቤቶች "እንኳን ደስ ያላችሁ " ወይም እንኳን ለአዲስ አመት አደረሳችሁ" ብሎ ስለማስደሰትስ ምን ያህል ታውቃላችሁ?
ወንድም እህቶቼ! ሁላችንም እንደምናውቀው የኢትዮዽያ ዘመን አቆጣጠር ሀ ብሎ የሚጀምረው በመስከረም ወር ነው።
የዚህ ወር መጀመሪያ (መስከረም 1) ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ዘንድ በከፍተኛ ክብርና በላቀ ደረጃ የሚከበር የሚዘከር አመት በአል ነው።
ዕለቱንም መስከረም1 ዓውደ አመት፣ ዘመን መለወጫ፣ ቅዱስ ዩሃንስ፣ እንቁጣጣሽ" በማለት ይሰይሙታል።
በዕንቁጣጣሽ የልጃገረዶች ጭፈራና የከነፈር ወዳጆቻቸው አጀብ!” ከጰንጠሊዮን፤
“ርእሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ”፣ በኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን።]
ይህ ቀን በዓልነቱ የክርስቲያኖች መሆኑ ከታወቀ ፤ እኛ ሙስሊሞችስ በዓሉን ልንጋራቸውና ልናስደስታቸው ይፈቀዳልን?
የኢስላም ሊቃውንቶች እንደሚሉት ዓመት በአል ከትልልቅ የሀይማኖት መገለጫዎች ነው ።
ሙስሊሞች አመታዊ የሆኑ ሁለት በዓሎች ብቻ አሉን፤እነሱም ዒባዳዊ በዓሎቻችን ናቸው።
ክርስቲያኖች፣ አይሁዶችና ሌሎች ጣኦታዊያንም የራሳቸው ብቻ የሆኑ ሀይማኖታዊ በዓሎች አሏቸው።
የኢስላም ሊቃውንቶች ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ የቁርኣንና የሀዲስ እንዲሁም የሰለፎችን መነሻ መሰረት በማድረግ፦ ሙስሊሞች የራሳችንን በዓሎች እንጂ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮችን ወርሃዊም ይሁን አመታዊ በዓሎቻቸውን በጋራ ማክበርና እንኳን አደረሳችሁ በማለት ማስደሰት በኢስላም በጥብቅ የተከለከለና የተወገዘ ተግባር መሆኑን ገልፀውልናል።
قال ﺍﻟﻠﻪ «ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻻ ﻳَﺸْﻬَﺪُﻭﻥَ ﺍﻟﺰُّﻭﺭَ ﻭَﺇِﺫَﺍ ﻣَﺮُّﻭﺍ ﺑِﺎﻟﻠَّﻐْﻮِ ﻣَﺮُّﻭﺍ ﻛِﺮَﺍﻣﺎً»
«እነዚያም በውሸት የማይመሰክሩ ወይም ውሸት እና መሰረት የሌለው ነገር ላይ የማይጣዱ(የማይገኙ)፤ ውድቅ ቃልም(በሚናገር ሰው አጠገብ) ባለፉ ጊዜ የተከበሩ ኾነው የሚያልፉ ናቸው፡፡»
ታላቁ የቁርኣን ሙፈሲር ሙጃሂድ ኢብን ጀብር፣ አልቃዲ አቡ የዕላ፣ ኢማም ረቢዕ ኢብኑ አነስ፣ ኢማም ዶሃክ፣ ሙሀመድ ኢብን ሲይሪንና ሌሎችም የታቢዒንና የአትባዕ አታቢዒን የቁርኣን ተንታኞች ፦አንቀፁ ላይ ለማለት የተፈለገው የሙሽሪኮችን አመት በዓሎች መሆኑን ገልፀዋል ።(ተፍሲር ኢብኑ ከሢርንና የኢብኑ ተይሚያ ኢቅቲዷኡ ሲራጢል ሙስተቂምን "1/537 " ተመልከት)።
• ኢማሙ አቡ ዳውድ ፣አማሙ አህመድና ኢማሙ ነሳኢ ከአነስ ኢብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ ቀጣዩን ሀዲስ አስተላልፈዋል ፦
عن ﺃﻧﺲ ﺑﻦ ﻣﺎﻟﻚ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗﺎﻝ:(( ﻗَﺪِﻡَ ﺭﺳﻮﻝُ ﺍلله ﷺ ﺍﻟﻤﺪﻳﻨﺔَ ﻭﻟﻬﻢ ﻳﻮﻣﺎﻥِ ﻳَﻠﻌﺒﻮﻥَ ﻓﻴﻬﻤﺎ، ﻓﻘﺎﻝ : ﻣﺎ ﻫﺬﺍنِ ﺍﻟﻴﻮﻣﺎﻥِ؟ ﻗﺎﻟﻮﺍ : ﻛﻨَّﺎ ﻧَﻠﻌﺐ ﻓﻴﻬﻤﺎ ﻓﻲ ﺍﻟﺠﺎﻫﻠﻴَّﺔ، ﻓﻘﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝُ ﷺ : ﺇﻥ ﺍﻟﻠﻪ ﻗَﺪْ ﺃَﺑْﺪَﻟَﻜُﻢ ﺑِﻬِﻤﺎ ﺧﻴﺮﺍً ﻣِﻨﻬﻤﺎ ﻳﻮﻡ ﺍﻷَﺿَﺤﻰ ﻭﻳﻮﻡ ﺍﻟﻔِﻄﺮ).ﺭﻭﺍﻩ ﺃﺑﻮ ﺩﺍﻭﺩ
«የአላህ መልእክተኛ መዲና ሲገቡ የመዲና ሰዎች የሚደሰቱባቸውና የሚጫወቱባቸው ሁለት የአመት በዓል ቀን ነበራቸው። እናም የአላህ መልእክተኛ "እነዚህ ሁለት ቀኖች ምንድን ናቸው" በማለት ጠየቁ። የመዲና ሰዎችም " እነዚህማ በጃሂሊያ ዘመን የምንጫወትባቸው ቀኖች ናቸው" በማለት መለሱ። የአላህ መልእክተኛም: "አላህኮ በነሱ ምትክ ከነሱ ለናንተ የተሻሉ ሁለት በዓሎችን ተክቷችሇል: የአድሃ ቀንና የፊጥር ቀን" (በማለት ገሰፇቸው)።»
•ወንድም እህቶቼ! የየሁዳዎችንና የክርስቲያኖችን በአል ማክበር በእነሱ መመሳሰልን ነው የሚያሳየን። በእነሱ መመሳሰል ደግሞ ኢስላም አጥብቆ የከለከለውና የአላህ መልእክተኛም አጠንክረው ያስጠነቀቁን ጉዳይ ነው።
ﻓﻘﺪ ﺭﻭﻯ ﺍﻟﺘﺮﻣﺬﻱُّ ﻋﻦ ﺍﺑﻦ ﻋﻤﺮﻭ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﷺ ﺃﻧﻪ ﻗﺎﻝ :" ﻟﻴﺲ ﻣِﻨَّﺎ ﻣَﻦ ﺗﺸﺒَّﻪ ﺑﻐﻴﺮﻧﺎ، ﻻ تَشَبَّهُوا ﺑﺎﻟﻴﻬﻮﺩ ﻭﻻ ﺍﻟﻨَّﺼﺎﺭﻯ".
•ኢማሙ አቲርሚዚ ኢብኑ ኡመርን በመጥቀስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ማለታቸውን ዘግቧል፦ "ከእኛ ውጭ በሆኑ ህዝቦች የተመሳሰለ ከእኛ አይደለም፤ በአይሁዶችም ሆነ በክርስቲታኖች አትመሳሰሉ"።
ﻋﻦ ﺍﺑﻦ ﻋﻤﺮ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ عنه قال ﺍﻟﻨﺒﻲ ﷺ "ﻣَﻦ ﺗﺸﺒَّﻪ ﺑﻘﻮﻡٍ ﻓﻬﻮ ﻣِﻨﻬﻢ".
"በህዝቦች የተመሳሰለ ሰው ከእነሱው ነው።"
ﻭﺭﻭﻯ ﺍﻟﺒﻴﻬﻘﻲ ﻋﻦ ﻋﻤﺮ بن الخطاب رضي الله عنه ﻗﻮﻟﻪ: "ﺍِﺟْﺘَﻨِﺒُﻮﺍ ﺃﻋﺪﺍﺀَ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﻲ ﻋﻴﺪﻫﻢ"
•ኡመር ኢብኑል ኸጧብ ረዲየሏሁ አንሁ እንዲህ ብሏል "የአሏህን ጠላቶች በበዓላቸው ራቋቸው (አትቅረቧቸው)።"
•አል ኢማም አልዐላማ ዐብደል ዐዚዝ ኢብን ባዝ እንዲህ ይላሉ:
قال الإمام بن باز رحمه الله: "ﻻ ﻳﺠﻮﺯ ﻟﻠﻤﺴﻠﻢ ﻭﻻ ﻟﻠﻤﺴﻠﻤﺔ ﻣﺸﺎﺭﻛﺔ ﺍﻟﻨﺼﺎﺭﻯ ﺃﻭ ﺍﻟﻴﻬﻮﺩ ﺃﻭ ﻏﻴﺮﻫﻢ ﻣﻦ ﺍﻟﻜﻔﺮﺓ ﻓﻲ ﺃﻋﻴﺎﺩﻫﻢ ﺑﻞ ﻳﺠﺐ ﺗﺮﻙ ﺫﻟﻚ؛ ﻷﻥ (ﻣﻦ تشبه ﺑﻘﻮﻡ ﻓﻬﻮ ﻣﻨﻬﻢ ) ﻭﺍﻟﺮﺳﻮﻝ ﷺ ﺣﺬﺭﻧﺎ ﻣﻦ ﻣﺸﺎﺑﻬﺘﻬﻢ ﻭﺍﻟﺘﺨﻠﻖ ﺑﺄﺧﻼﻗﻬﻢ ﻓﻌﻠﻰ ﺍﻟﻤﺆﻣﻦ ﻭﻋﻠﻰ ﺍﻟﻤﺆﻣﻨﺔ ﺍﻟﺤﺬﺭ ﻣﻦ ﺫﻟﻚ ﻭﺃﻻ ﻳﺴﺎﻋﺪ ﻓﻲ ﺇﻗﺎﻣﺔ ﻫﺬﻩ ﺍﻷﻋﻴﺎﺩ ﺑﺄﻱ ﺷﻲﺀ؛ ﻷﻧﻬﺎ ﺃﻋﻴﺎﺩ ﻣﺨﺎﻟﻔﺔ ﻟﺸﺮﻉ ﺍﻟﻠﻪ، ﻭﻳﻘﻴﻤﻬﺎ ﺃﻋﺪﺍﺀ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﻼ ﻳﺠﻮﺯ ﺍﻻﺷﺘﺮﺍﻙ ﻓﻴﻬﺎ ﻭﻻ ﺍﻟﺘﻌﺎﻭﻥ ﻣﻊ ﺃﻫﻠﻬﺎ ﻭﻻ ﻣﺴﺎﻋﺪﺗﻬﻢ ﺑﺄﻱ ﺷﻲﺀ، ﻻ ﺑﺎﻟﺸﺎﻱ ﻭﻻ ﺑﺎﻟﻘﻬﻮﺓ ﻭﻻ ﺑﺄﻱ ﺷﻲﺀ ﻣﻦ ﺍﻷﻣﻮﺭ ﻛﺎﻷﻭﺍﻧﻲ ﻭﻧﺤﻮﻫﺎ ﻭﺃﻳﻀﺎً ﻳﻘﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺳﺒﺤﺎﻧﻪ : ﴿ﻭَﺗَﻌَﺎﻭَﻧُﻮﺍ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟْﺒِﺮِّ ﻭَﺍﻟﺘَّﻘْﻮَﻯ ﻭَﻻ ﺗَﻌَﺎﻭَﻧُﻮﺍ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻹِﺛْﻢِ ﻭَﺍﻟْﻌُﺪْﻭَﺍﻥِ﴾
ﻓﺎﻟﻤﺸﺎﺭﻛﺔ ﻣﻊ ﺍﻟﻜﻔﺮﺓ ﻓﻲ ﺃﻋﻴﺎﺩﻫﻢ ﻧﻮﻉ ﻣﻦ ﺍﻟﺘﻌﺎﻭﻥ ﻋﻠﻰ ﺍﻹﺛﻢ ﻭﺍﻟﻌﺪﻭﺍﻥ، ﻓﺎﻟﻮﺍﺟﺐ ﻋﻠﻰ ﻛﻞ ﻣﺴﻠﻢ ﻭﻋﻠﻰ ﻛﻞﻣﺴﻠﻤﺔ ﺗﺮﻙ ﺫﻟﻚ... "
"ወንድም ይሁን ሴት ሙስሊሞች ክርስቲያኖችን፣ የሁዳዎችንና የሌሎች የክህደት ሀይማኖት ተከታዮችን በዓላት አብሮ ማክበር አይፈቀድም። ይልቁንም መተዉ ግድ ነው። ምክኒያቱም "በህዝቦች የተመሳሰለ ከእነሱው ነውና"። የአላህ መልእክተኛ በነሱ ከመመሳሰልና ባህሪያቸውንም ከመላበስ አስጠንቅቀውናል። ስለዚህ ማንኛውም ወንድም ይሁን ሴት አማኝ በአላህ ጠላቶች በዓላት ከመሳተፍ ሊጠነቀቁና ሊርቁ ይገባቸዋል። በምግባቸው፣ በሻይ በቡና፣ በመስሪያ ቁሳቁሶችና በመሳሰሉት የበኣላቸው ማሳለጫ በሆኑ ነገሮች መተባበርና አብሮ መጠቀም ፈፅሞ የተከለከለ ነው።
(وتعاونوا على البر والتقوى ولا تعاونوا على الإثم والعدوان)
"በመልካም ነገርና አላህን በመፍራት ተባበሩ፤ በወንጀልና ወሰን በማለፍ አትተጋገዙ"
ካፊሮች ጋር በበዓሎቻቸው መሳተፍ፣ አብሮ ማክበርና (እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት) ይህ አላህን በመወንጀልና ወሰኑን በማለፍ ከመተባበር ውስጥ ይመደባል።ስለዚህ እያንዳንዱ ሙስሊም ከዚህ አይነት ተግባር ሊርቅ ግድ ይለዋል..."
https://binbaz.org.sa/fatwas/6539/حكم-المشاركة-في-اعياد-النصارى-وغيرهم-من-الكفرة
ኢናሊላህ ወኢና ኢላሂ ራጅኡን
"እኛ የአላህ ነን ወደ እርሱም ተመላሾች"
كُلُّ نَفْسٍ ذَائِقَةُ الْمَوْتِ ۗ وَإِنَّمَا تُوَفَّوْنَ أُجُورَكُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ۖ فَمَن زُحْزِحَ عَنِ النَّارِ وَأُدْخِلَ الْجَنَّةَ فَقَدْ فَازَ ۗ وَمَا الْحَيَاةُ الدُّنْيَا إِلَّا مَتَاعُ الْغُرُورِ
[ ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 185 ]
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ምንዳዎቻችሁንም የምትሞሉት በትንሣኤ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከእሳትም የተራቀና ገነትን የተገባ ሰው በእርግጥ ምኞቱን አገኘ፡፡ ቅርቢቱም ሕይወት የመታለያ መሳሪያ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡وَاتَّقُوا يَوْمًا لَّا تَجْزِي نَفْسٌ عَن نَّفْسٍ شَيْئًا وَلَا يُقْبَلُ مِنْهَا شَفَاعَةٌ وَلَا يُؤْخَذُ مِنْهَا عَدْلٌ وَلَا هُمْ يُنصَرُونَ
[ አል-በቀራህ - 48 ]
(ማንኛዋ) ነፍስም ከ(ሌላዋ) ነፍስ ምንንም የማትመነዳበትን፣ ከርሷም ምልጃን የማይቀበሉባትን፣ ከርሷም ቤዛ የማይያዝበትን፣ እነርሱም የማይረዱበትን ቀን ተጠንቀቁ፡፡
አሏህ ይዘንለት
አላህ ሆይ ባሪያህ የባሪያህ ልጅ ወደ አንተ መጥቷልና በእዝነትህ መልካም የሆነ አቀባባል ተቀበለው እዘንለት ማረውም የእኛንም ወደ አንተ መመለስ የምትወደው አድርግልን።
https://t.me/susui_slamic_channal
የዕለቱ ሐዲስ🌸🌸
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
ከአቢ-ሁረይረህ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተላለፈው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ፣
ገዳዩ የገደለበትን ወይም ሟችም የተገደለበትን ምክንያት የማያውቅበት ቀን በሰዎች ላይ እስኪመጣ ድረስ ዓለም አትወገድም( አትጠፋም።)] "ይህ እንዴት ይሆናል?" ተባሉ። ነቢዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):- [በእልቂት(ደም መፋሰስ) ብዛት፤ ገዳዩም ተገዳይም የእሳት ናቸው።] አሉ።
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
عنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ :
[ وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ ، لَا تَذْهَبُ الدُّنْيَا حَتَّى يَأْتِيَ عَلَى النَّاسِ يَوْمٌ لَا يَدْرِي الْقَاتِلُ فِيمَ قَتَلَ ، وَلَا الْمَقْتُولُ فِيمَ قُتِلَ] ، فَقِيلَ : كَيْفَ يَكُونُ ذَلِكَ ؟ قَالَ : [الْهَرْجُ ، الْقَاتِلُ وَالْمَقْتُولُ فِي النَّارِ ]
📚رواه مسلم
📚ሙስሊም ዘግበውታል።
𝚜𝚑𝚊𝚛𝚎
JOIN👇👇
┏━ 🦋 ━━━━ 🦋 ━┓
https://t.me/susui_slamic_channal
𖣘#ቁርአንን #የተመለከተ #አጭር #መረጃ
Part2
✵ #የቁርአን ምዕራፎች (ሱራዋች) 114 ናቸው።
✵ #የቁርአን "ሩቡዕ" 240 ናቸው።
✵ #የቁርአን ስሞች ብዛት 77439 ናቸው።
✵ #የቁርአን አንቀፅ ብዛት 6236 ናቸው።
✵ #የቁርአን ፊደላት ብዛት 321250 ናቸው።
➖✨➖🕋➖🕋➖✨➖⚡️➖ https://t.me/susui_slamic_channal
ምንም እንኳን ዱንያ ብታንገላቴን...
ችግር ቢበረታብን ፤መከራ ቢፈራረቅብንም
በአላህ ላይ መቼም የማይደበዝዝ ተስፋ አለን
إِنَّ مَعَ الْعُسْرِ يُسْرًا
ከችግር ጋር በእርግጥ ምቾት አልለ፡፡
(ሱረቱል ሸርህ:5)h═ ❁🌹❁ ════━
👇👇JOIN👇👇
JOIN
https://t.me/susui_slamic_channal
[[---------አመስግን--------------]]
☞ሁሌም ካንተ የባሱ ሰዎች አሉ
አንተ የምትጠላውን ህይወት⇣
በዙ የሚመኛት ሰው ይኖራል ።
☞ሌላው ኖሮት አንተ የሌለህን ነገር
በመመልከት አትዘን‥
☞አንተ ኖሮህ ሌላው የሌለውን ነገር
ተመልከትና አላህን አመስግን 😘።
(አልሀምዱ ሊላህ)
💌:::::::::::Telegram::::::::::💌
https://t.me/susui_slamic_channal
💫💫 #ሀሰነል #በስሪ አንድ ቀን በጣም ታመሙ፡፡ የሌላ እምነት ተከታይ
የነበረው የጎረቤታቸው ሰውዬ ሊጠይቃቸው መጣ፤ ገና ቤቱ
እንደገባ “ #አንቱ ኢማም ምንድነው የሚሸተኝ ሽታ ?” በማለት
ጠየቀ፡፡ #ሀሰነል #በስሪ ሽታው ከህመማቸው የመነጨ መሆኑን
ለሰውዬው ነገሩት፡፡ ነገር ግን የጎረቤቱ ሰውዬ አላመናቸውም
💫“ኸረ ይሄ የህመም ሽታ አይደለም፤ የሽንት ቤት ሽታ ነው! በጌታ
ይሁንቦት ምንድነው እሱ ንገሩኝ” አላቸው፡፡ #ሰውዬው ይህ ፍሳሽ
ከራሱ ሽንት ቤት የመጣ መሆኑን አላወቀም፡፡ #ሰውዬው
#እንዲነግራቸው ሲጨቀጭቁት ሀሰነል በስሪ ነገሩት “ #ከተወሰነ
ወራቶች ጀምሮ ያንተ ቤት ፍሳሽ ወደቤቴ እየገባ ነበር፤
ለማስተካከል ብዙ ጥረት አደረኩኝ ግን አልተሳካልኝም” አሉት፤
✍ #የጎረቤቱ ሰውዬ እስካሁን እንደዚህ መሆኑን ለምን እንዳልነገሩት
ጠየቀ፡፡ #ታላቁ #ኢማም “ ስሜትህን እጎዳ ይሆናል ብዬ ነው”
በማለት መለሱለት፡፡ ሀሰነል በስሪ(አላህ ይርሀማቸው)
የታመሙት በሽታው ምክንያት መሆኑን ሰውዬው ይረዳል፡፡
🔰🔰ይህ ሙስሊም ያልሆነው ሰውዬ በሀሰነል በስሪ አመለ ሸጋ
ባህሪ በጣም ይገረማል፤ ይህ ቅንነት፣ መልካም ባህሪ
ከእስልምና የመነጨ መሆኑን በመረዳት #ሰውዬው #ወደ
#ትክክለኛው እምነት ተመለሰ፡፡
🌙🌙እንዲህ ነበሩ እንግዲህ ቀደምቶቻችን እስልምናው ወረቀት ላይ
ሳይሆን ራሳቸው ላይ ነበር፡፡ እየመነዘሩ ይጠቀሙበታል
ሰዎችንም ይጠቅሙበታል፡፡ ከእስልምና የምንጠቀም አላህ
ያድርገን…
ሼርርርርር አይዘንጉ Forward ማረግ የሰከንዶች ስራ ነዉ
┏━ 🍃 ━━━━ 🍂 ━┓
✒️ @ISLAMICPATH2 🖋
┗━ 🍂 ━━🖋━ 🍃 ━┛
#share #share #share
👇👇JOIN👇👇
JOIN👇👇
┏━ 🦋 ━━━━ 🦋 ━┓
https://t.me/susui_slamic_channal
ከዕለታት በአንዱ ቀን ነብያችን ﷺ ታላላቅ ከሚባሉት ሰሃቦች ጋር መስጂድ ውስጥ ተቀማምጠው ሳለ አንዲት ሴት ድንገት በሩ ላይ ብቅ አለች ፡፡ በቀጥታም ነብያችን ﷺ ወደተቀመጡበት አምርታ ከፊት ለፊታቸው ቆመችና ሃያዕ በተጫነው ድባብ ‹‹ አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ.......
✿ ያንተ ወንጀል የቱንም ያህል ቢገዝፍ ከ አላህ ምህረት አይበልጥም
✿ አንተ ሺ ጊዜ ድንበር ብታልፍ አላህ አንድም ቀን ቃሉን አያጥፍም
✿የሠው ልጅ እያፈቀርከው ጥሎህ ይሄዳል፣ አላህ ግን እያመፅከው ይጠብቅሃል
✿ የወንጀለኛነት ስሜት ከተሰማህ የኢማን ብርሃን ልብህ ውስጥ አለ ማለት ነው ምክንያቱም ያ ብርሃን ባይኖር የጥፋተኝነት ስሜት ባልተሰማህ ነበር፡፡
✿አንተ ለመመለስ እስካልሰለቸህ ድረስ አላህ ለማርታ ዝግጁ ነው፡፡
✿ ሸይጣን ሁለት ጊዜ እንዲያሸንፍህ አትፍቀድለት አንደኛ ወንጀል አሰርቶ ሁለት በአላህ ላይ ያለህን ተስፋ አስጠፍቶ
🍀 https://t.me/susui_slamic_channal
قَــالَ عُمَـرُ بْنُ عَبْدِ الْعَزِيزِ رحمــه الله تعالـﮯ.
لَا تَكُنْ مِمَّنْ يَتَّبِعُ الْحَقَّ إِذَا وَافَقَ هَوَاهُ وَيُخَالِفُهُ إِذَا خَالَفَ هَوَاهُ ،
فَإِذًا أَنْتَ لَا تُثَابُ عَلَى مَا وَافَقْتَهُ مِنَ الْحَقِّ وَتُعَاقَبُ عَلَى مَا تَرَكْتَهُ مِنْهُ ،
لِأَنَّكَ إِنَّمَا اتَّبَعْتَ هَوَاكَ فِي الْمَوْضِعَيْنِ
ኡመር ኢብኑ አብደል አዚዝ ( رحمه الله)እንድህ ይላሉ፡–
ሀቅ ስሜትክ ሲገጥምልክ የምትከተል እና ስሜትክን ሲቃረን የምትተው ሰው አትሁን
እንዲህ ካደረክ ግን
ሀቅን በመከተልክ ምንዳ አይኖርህም፣
ሀቅን በመተውክ ግን ትጠየቃለክ(ትቀጣለክ)
ምክንያቱም ሁለቱም ቦታ ላይ የተከተልከው ስሜትክ ነውና‼
((شرح الطحاوية لابن أبي العز (٧٩٤/٢))
🍀 https://t.me/susui_slamic_channal
ጅነት ስንገባ የመጀመርያዎቹ ቅፀበቶች
ልክ ጀነት ስንገባ ጅረቶች ከህንፃዎቹ ስር ሲፈሱ፣ በየ ርቀቱ የተተከሉ ከወርቅ እና ከሀር የተሰሩ ድንኳኖችን እና የበሰሉ ፍራፍሬዎችን ስንመለከት ስሜቱ ይለያል።
ከረጅም ዘመን በፊት ሙተው ከአይኖቻችን የተሰወሩ ወዳጆቻችንን ስንገናኝ፣ ልጅ ሲንከባከባት ቆይቶ በሞት ያጣትን እናቱን ድንገት ሲመለከት፣ ወላጆች በህፃንነቱ ሞቶባቸው ናፍቆቱ የግር እሳት የሆነባቸውን ልጃቸውን ከጀነት ሲገናኙት፣
ሙቶ የተለየን እና ለዘመናት መልኩ ከአይናችን አልጠፋ ያለው አባታችንን ድንገት ከጀነት ህንፃዎች ስር ስናገኘው፣
ለዘመናት የአልጋ ቁራኛ ሁኖ ልባችንን የሰበረው በሽተኛው ወዳጃችን በጀነት ጎዳናዎች ከነሙሉ ጤንነቱ ስንመለከት፣
ሁሌም በህይወት ውጣ ውረድ ፊታቸው በሀዘን የተሞሉ ወላጆቻችን በደስታ ፈክተው ጀነት ውስጥ ስንመለከታቸው፣
ሽማግሌው ፈርጣማ ወጣት ሁኖ፣ ዛሬ የምናያቸው አሮጊቶች እሚገራርሙ ማራኪ እና ፈታኝ ልጃ ገረድ ሁነው፣
አርብ እለት የረሕማንን ዝያራ ለመታደም ስንሄድ እዝያው ነቢያትቶችን፣ ሰሐባዎችን፣ ዑለማኦችን ተገናኝተን ስንዘይራቸው፣
ጌታችንን አላህ ያለ ምንም ግርጆ ከፊታችን ስንመለከተው፣ ያለው የማይታመን የደስታ ስሜት ልዩ ነው።
የመጀመርያው የጀነት ንጋት እንዴት ይሆን!? የመጀመርያው የጀነት ምሽት ድባቡ እንዴት ይሆን!?
ዒባዳ የለም ተጠናቅቋል፤ ጭንቀት የለም ሒሳብ አልቋል፤ ያ የጨለማ፣ የመጠላላት፣ የማስመሰል፣ የጦርነት፣ የመሸምገል፣ የድካም፣ የበሽታ፣ የመርፌ፣ የመድሃኒት....አለም አልቋል።
«ባሮቼ ሆይ! እኔ ስለናንተ ወድጃለሁ፤ መቼም አልጠላችሁም።» እያለ አላህ ሲያበስረን የደስታችን ድባብ እንዴት ይሆን!?
--------------------------------------
አላሁመጅዓልና ሚን አህሊል ጀና
🍀 @ALQASAS_ISLAMIC
