en
Feedback
መርጌታ ይኸይስ የባሀል መድሃኒት ቀማሚ እና

መርጌታ ይኸይስ የባሀል መድሃኒት ቀማሚ እና

Open in Telegram
981
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🌹 የጨረቃ ቁራጭ ይመስል ነበር... 🌹 ከርሶ የኖሩ ሰሃቦች ምንኛ ታደሉ... አነስ መልካም ስራውን አለህን ይውደድለት ሲናገር ... ውዱ ነብይ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም የቆዳቸው ቀለም የሚያምር ነው። ላባቸው ልክ እንደ ሉል ነበር። የአለህ መልዕክተኛን እጅ ያህል የሚለሰልስ ሀር ነክቼ አላውቅም ።ከነብዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ሽታ የተሻለ ሽቶም ሆነ እጣን አሽትቼ አላውቅም ። የእጃቸው ሽታ ከሽቶ ማምረቻ ቦታ የወጡ ይመስላል። ከሩቅ ሲመጡ በሽታቸው ይታወቃሉ... አነስ አክሎም " ነብዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ሽቶ ልቀባዎት የሚላቸውን ሰው ተቃውመው አያውቁም። ፊታቸው እንደፀሃይ የፈካ ነው። ደስ ባላቸው ግዜ ፊታቸው ቁራጭ ጨረቃ ይመስል ነበር" ብሏል። ጃቢር ቢን ሰሙራህ በበኩላቸው " አንዴ የአለህ መልዕክተኛን ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም በምሽት አገኘኋቸው። የሚያምር ቀይ ጀለቢያ ለብሰዋል። ጨረቃ ወጥታ ነበር። እሳቸውንና ጨረቃን ማወዳደር ጀመርኩ ለኔ እሳቸው ከጨረቃዋ ይበልጥ ያምራሉ " ብሏል ። ያ.....አለህ በጀነት የሳቸውን ጉርብትና ወፍቀን... ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም      ┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄ https://t.me/susui_slamic_channal

ከጠቢባን አንደበት 〰〰〰〰〰 🔜 « የአንተ መስተካከያና መታነጫ ዛሬ እንጅ ነገማ የፍፃሜህ ዕለት ሊሆን ይችላል ። » 🔜 « ራስህን ድል ሳታደርግ በሌላው ላይ አትዝመት ።» 🔜 « መታገስ ለራስ ጊዜ መስጠት ነው ። » 🔜 « ንደት ለችግሮች መፍትሔ ሳይሆን መንስኤ ነው ። » 🔜 « የውሸት እየኖርን የእውነት እንሞታለን ። » 🔜 « ደስታ ዱርዬ አይደለም ፤ ሰዎች ግን ዱርዬ እየመሰላቸው በየ መጠጥ ቤቱ ይፈልጉታል ። » 🔜 « ጠላቶችህን ባትወዳቸው እንኳን አድንቃቸው ፤ ስህተትህን ለመመልከት የመጀመሪያዎቹ ናቸውና ። » 🔜 « ጠላቶችህ ወደ አንተ ቢገሰግሱ ወደ ኋላ አታፈግፍግ ወደነሱም አትንደርደር ባለህበት ሆነህ ተዘጋጅና ጠብቃቸው ። » 🔜 « ብዙ ሰዎች ከአድማስ ማዶ የማይታያቸውን ቀን ይናፍቃሉ ። ዛሬን የሚንቋት በእጃቸው ስለገባች ነው ። » 🔜 « ዘልዓለም ለመኖር ዕድሉ ለሌላት ህይወትህ ሰላምን አትንፈጋት ። » 🔜 « ለሌሎች ይቅርታ የማያደርግ እራሱ የሚሸጋገርበትን ድልድይ የሚያፈርስ ነው ። » 🔜 « ቁጠኛ ጓደኛ የተረጋጋ ጠላት ነው ። » 🔜 « የቁጣ መድሀኒት ዝምታ ነው ። » 🔜 « ከመዝለልህ በፊት አስተውል ። » 🔜 « ገንዘብ መናገር ሲጀምር እውነት ዝም ትላለች ። » 🔜 « ትዕግስት ማለት ችግርህን ለአሏህ መንገር ማለት ነው ። » 🔜 « እምነት ማለት ግማሹ ትዕግስት ሲሆን ግማሹ ምስጋና ነው ።      ┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄ https://t.me/susui_slamic_channal

ሶላት አለን-ነብይ የማውረድ ትሩፋት قال صلى الله عليه وسلم « مَنْ صَلَّى عَلَيَّ صَلاَةً صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشْرًا » ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዳሉት‘መን ሶላ ዓለየ ሶላተን ሶለልሏሁ ዐለይሂ ቢሃ ዐሸራ’ ‹‹በኔ ላይ አንድ ጊዜ ሶላዋት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስር ጊዜ ሶለዋት ያወርድለታል›› وقال صلى الله عليه وسلم : « لاَ تَجْعَلُوْا قَبْرِي عِيْدًا وَصَلُّوْا عَلَيَّ؛ فَإِنَّ صَلاَتَكَ تَبْلُغُنِي حَيْثُ كُنْتُمْ » ሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዳሉት: ‘‹‹መቃብሬን የባዕል ማዕከል አታድርጉት ፡፡በኔ ላይም ሶለዋት አውርዱ፡፡ የትም ሆናቸሁ ሶለዋት ብታወርዱ ይደርሰኛል፡፡›› ’ وقال صلى الله عليه وسلم : « الْبَخِيْلُ مَنْ ذُكِرْتُ عِنْدَهُ فَلَمْ يُصَلِّ عَلَيَّ » እንዲህ ሲሉም ተናግረዋል፡-‹‹ስስታም ማለት ከርሱ ዘንድ እኔ እየተወሳሁ በኔ ላይ ሶለዋት ያላወረደ ነው፡፡››’ وقال صلى الله عليه وسلم : « إِنَّ لِلَّهِ مَلاَئِكَةً سَيَّاحِيْنَ فِي اْلأَرْضِ يُبَلِّغُوْنِي مِنْ أُمَّتِي السَّلاَمَ » እንዲህ ሲሉም ተናግረዋል: “ለአላህ ተጓዥ መላኢኮች አሉት፡፡ ምድር ላይ ከኡመቴ የሚላክልኝን ሰላምታ ለኔ ያደርሳሉ፡፡” وقال صلى الله عليه وسلم : « مَا مِنْ أَحَدٍ يُسَلِّمُ عَلَيَّ إِلاَّ رَدَّ اللهُ عَلَيَّ رُوْحِيَ حَتَّى أَرُدَّ عَلَيْهِ السَّلاَمَ » ነብዩ(ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡: “አንድ ሰው ሰላምታ ሲልክልኝ አላህ ነፍስ ይዝራብኝና ምላሽ እሰጠዋለሁ፡፡.” T.me/HijabNewWebta

📌✅ሰላት ከተጠናቀቀ በኋላ የሚባል ዚክር‼️ 📌✅لاَ إِلَـهَ إِلاَّ اللهُ وَحْدَهُ لاَ شَرِيْكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيْرُ، اَللَّهُمَّ لاَ مَانِعَ لِمَا أَعْطَيْتَ، وَلاَ مُعْطِيَ لِمَا مَنَعْتَ، وَلاَ يَنْفَعُ ذَا الْجَدِّ مِنْكَ الْجَدُّ. ↪️ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡አንድ ነው፡፡ አጋርም የለውም፡፡ ስልጣን የርሱ ብቻ ነው፡፡ ምስጋናም የሚገባው ለርሱ ብቻ ነው፡፡ አላህ ሆይ! አንተ የሰጠኸውን ነገር የሚከለክል የለም፡፡ የከለከልከውን የሚሰጥ የለም፡፡ የክብር ባለቤት ከአንተ ዘንድ ክብሩ ቅንጣት አይፈይደውም፡ T.me/HijabNewWebta

◼️ከትዳር በፊት ጥንቃቄ ለሴቶች‼️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ✅ ብዙ ጊዜ ከትዳር በፊት ከHIVና ሌላም በሽታ ፍራቻ የደም ምርመራ ይደረጋል። ነገር ግን ከደም ምርመራ በላይ የመንሀጅ፣ የአቂዳ፣ የሱናና የአኽላቅ ምርመራ ሊደረግ ይገባል። ↪️ የመንሀጅ ምርመራ፦ ለትዳር አጋር ይሆነኛል ብለሽ የምትመርጭው አካል መንሀጁ ምን እንደሆነ ማጤን ወሳኝ ይሆናል። በሶሀቦች መንገድ በሰለፎች ጎዳና ቀጥ ያላለ ከሆነ አልፎም፦ 🔻አህባሽ 🔻ኢህዋንይ 🔻ሱፍይ 🔻ሀዳድይ 🔻አሽአርይ 🔻ተክፊርይና ሌላም ከሆነ ♻️ከጠማሞችና ከጠፊዎች ስለሆነ ለትዳር አይበጅምና ጠንቀቅ በይ። ↪️ የአቂዳ ምርመራ፦ የትዳር አጋርሽ አቂዳው የተስተካከለ፣ አላህን በብቸኝነት የሚያመልክና አቂዳን ከሚያበላሹ ነገሮች የራቀ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅብሻል። ምክንያቱም የአላህን ሀቅ ያልተወጣ የኔን ሀቅ ይወጣል ብለሽ አታስቢ። ♻️ቀብር አምላኪ ♻️ሰይድና ኸድር አብዱልቃድር ጅላሌ የሚል ♻️ለቀብር ባለቤት የሚያርድና የሚሳል ♻️ከአላህ ውጪ ያሉትን ድረሱልኝ የሚል ♻️ወልይ ሷሊህና ነብያት የሚለምን ♻️ሁዝ ቢየዲ ያረሱሉላህ የሚል ♻️አብሬት ቃጥባሬ ንጉሶቹ ሸኸና ሁሴን አባድር አኒ ዳኒ ሌላም የሚል ከሆነ ♨️ሙሽሪክ ነውና ለትዳር ስለማይሆን ጠንቀቅ በይ። ↪️ የሱና ምርመራ፦ ለትዳር ያሰብሽው አካል አቅሙ በቻለ መጠን ሱናን የሚከተል፣ ከቢድአና ከቢድአ ባለቤቶች የሚርቅ መሆን አለበት። 🔸መውሊድ የሚያከብር 🔸ሀሙስ፣ እስነይን እያለ ቀን ሚከፋፍል 🔸ኢስራ ወል ሚእራጅ እያለ ሚያከብር 🔸የሸእባን ግማሽን ከሌላው ቀን የሚለይ ከሆነ ♨️ሙብተዲእ ነውና ለትዳር ስለማይሆን ጠንቀቅ በይ። ↪️ የዲን ምርመራ፦ ለትዳር ያሰብሽው አካል፦ 🔹ሶላት በቋሚነት ቀጥ ብሎ የማይሰግድ 🔹ሙዚቃ የሚሰማና ነሺዳ የሚያዳምጥ 🔹በፊልም በድራማና በኳስ ጊዜው ሚገል 🔹ቁርአን የማይቀራ ዲኑን የማይማር 🔹ሲጋራ የሚነፋ ጫት የሚቅም 🔹ፂሙን የሚላጭ ፀጉሩን የሚያበላልጥ 🔹ሱሪውን ሚጎትት ፋሽን የሚከተል 🔹ሴትን የሚጨብጥ ኢኽቲላጥ ሚያበዛ ከሆነ ♨️ለትዳር አይሆንሽምና ጠንቀቅ በይ። T.me/HijabNewWebta

#የእleቱ_ምርጥ_ምክር لعن رسول الله ﷺ الواصلة والمستوصلة الواشمة والمستوشمة النامصة والمتنمصة #ነብያቺን ﷺ እንደነዚህ አይነት ሰወችን እረግመዋል👇👇 ☞ አርቴፊሻል ፀጉር የሚያስቀጥል ሰውን ☞ አርቴፊሻል ፀጉር ለሰው የሚቀጥልን ሰው ☞ንቅሳት የሚነቀስ ሰውን ☞ ንቅሳት ሰወችን የሚነቅስን ☞የቅንድብ ፀጉርን የሚያስወግድን #ለምሳሌ ☞ የቅንድቡ ፀጉር #ሰለበዛ ☞ወይንም #አቀማመጡ ስለሚያስጠላ በዚህ ምክንያት የሚከላ የሚስተካከለውን ሰው ነብያችን ﷺ እረግመውታል። ☞ የሰውን ቅንድብ የሚከላንም ሰው እረግመዋል 🌸አንቺ ውድ እህቴ ሆይ አሏህ ፀጉር ስለሰጠሽ #ሽኩር ማድርስ እንጅ በፍፁም አርቴፊሻል እንድ ምእራባዊያን ማስቀጠል የለብሽም። 🌺አንተ ውድ ወንድሜ ሆይ አሏህ አሳምሮ እንደ ሰው ልጅ ፈጥሮሀልና ሰውንትህን በመነቀስ #ፋሽን እከተላለሁ እያልክ አሳምሮ የፈጠረህን ጌታ እንዳትወንጅል። አንቺ ወድ 🌼ውድ እህቴ ሆይ #ፋሽን እከተላለሁ ወይንም ያምርብኛል ብለሽ የቅንድብሽን ፀጉር ከማስወገድ ከማስተካከል ተቆጠቢ ። አሏህ በሰጠን ነገር ላይ ምስጋና እንጅ የከለከለንን ከመስራት መቆጠብ አለብን t.me/HijabNewWebta

#ጠያቂ፦ አንድን ሰው ለአላህ ብሎ የወደደ ሰው "ለአላህ ብየ እወድሃለሁ" ብሎ ማሳወቅ አለበትን? #ሸይኹል_አልባኒ፦ አዎ፡፡ ግን ለአላህ ብሎ መውደድ ዋጋው ከባድ በመሆኑ የሚከፍለው ጥቂት ነው፡፡ ለአላህ ብሎ የመውደድ ዋጋ ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? እስኪ ማነው የሚያውቅ መልሱን የሚሰጠን? #አንዱ_አድማጭ፦ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡ [ሰባት አይነት ሰዎች አላህ ከሱ ጥላ ውጪ ጥላ በሌለበት (በቂያማ) ቀን ከጥላው ስር ያስጠልላቸዋል፡፡] ከነዚህም ውስጥ [ለአላህ ብለው ተዋደው በዚያም ላይ ተገናኝተው በዚያው ላይ የተለያዩ ናቸው፡፡] #ሸይኹል_አልባኒ፦ እሱ በራሱ ትክክለኛ ንግግር ነው፡፡ ግን የጥያቄው መልስ አይደለም፡፡ አንተ የጠቀስከው ነገር ሙሉ ለሙሉ ሳይሆን ቀረብ ባለ መልኩ ለአላህ ብሎ መውደድ ምን እንደሆነ የሚገልፅ ነው፡፡ የኔ ጥያቄ ግን "ሁለት ለአላህ ብለው የተዋደዱ ሰዎች አንዱ ለሌላው ሊከፍለው የሚገባው ዋጋ ምንድን ነው?" የሚል ነው፡፡ እንጂ የአኺራ ሽልማቱን (አጅሩን) ማለቴ አይደለም፡፡ ስለዚህ ማለት የፈለግኩት ሁለት ሰዎች እውነት መዋደዳቸው ለአላህ እንደሆነ በተግባር የሚያመላክተው ምንድን ነው የሚል ነው፡፡ ሁለት ሰዎች ሊዋደዱ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውዴታቸው እውነተኛ ያልሆነ እንዲሁ ቅርፃዊ ሊሆን ይችላል፡፡ እውነተኛ እንደሆነ የሚያመላክተው ምንድነው? #አንዱ_አድማጭ፦ ለራሱ የሚወደውን ለወንድሙ መውደዱ፡፡ #ሸይኹል_አልባኒ፦ ይሄ የመውደድ ነፀብራቅ ነው ወይም ከመውደድ ነፀብራቆች አንዱ ነው፡፡ #አንዱ_አድማጭ፦ የላቀው ጌታችን እንዲህ ብሏል፡ {"አላህን የምትወዱ ከሆናችሁ መልእክተኛውን ተከተሉ፡፡ አላህ ይወዳችኋልና" በላቸው፡፡} #ሸይኹል_አልባኒ፦ ይሄ ትክክለኛ መልስ ነው- ግን ለዚህ ሳይሆን ለሌላ ጥያቄ! #አንዱ_አድማጭ፦ ምናልባት መልሱ በዚህ ሶሒሕ ሐዲስ ውስጥ ሊሆን ይችላል፡ [ሶስት ነገሮች በውስጡ ያሉበት የኢማን ጥፍጥና አግኝቷል...] ከነዚህ ውስጥ [ለአላህ ብለው የተዋደዱ ናቸው፡፡] #ሸይኹል_አልባኒ፦ ይሄ ለአላህ ብሎ መውደድ የሚያስከትለው ውጤት ነው- በልቡ የሚያገኘው ጥፍጥና! #አንዱ_አድማጭ፦ የላቀው ጌታችን እንዲህ ብሏል፡ {በዘመን እምላለሁ! በእርግጥ ሰው ሁሉ በክስረት ውስጥ ነው፡፡ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሰሩት፤ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡} #ሸይኹል_አልባኒ፦ በጣም ጥሩ ብለሃል! ይህ ነው ትክክለኛው መልስ!! ይህም ሲብራራ እኔ አንተን እውነት ለአላህ ብየ የምወድህ ከሆነ በምክር ልከተልህ ይገባል፡፡ አንተም እንደዚያው፡፡ ለዚህም ነው "ለአላህ ብለን እንዋደዳለን" በሚሉ ሰዎች ዘንድ ይሄ አንዱ ሌላውን በምክር መከተል በጣም ውስን የሆነው፡፡ ምናልባት መዋደዳቸው ከፊል እውነት ሊኖረው ይችላል፡፡ ግን ሙሉእ አይደለም፡፡ ለምን ቢባል አንዳቸው የሌላውን ስሜት ይጠብቃልና፡፡ "እውነቱን ስነግረው ቢቆጣስ፣ ቢሸሽስ፣... ወዘተ" እያለ ሐቅን ሳያስተላልፍ ይቀራል፡፡ ስለዚህ ለአላህ ብሎ መውደድ ዋጋው አንዳችን ለሌላው በምክር ኢኽላስ ሊኖረው ነው- እውነተኛ መካሪ ሊሆን፡፡ ሁሌም በመልካም ሊያዘው ከመጥፎም ሊከለክለው ይገባል፡፡ ወዳጅ ለሚወደው ከጥላው የበለጠ በምክር የሚከተለው ሊሆን ይገባል ማለት ነው፡፡ ሶሐቦች ተገናኝተው ሲለያዩ አንዱ ለሌላው ይችን ምእራፍ ይቀሩ እንደነበር የሚያመላክተው ሶሒሕ ማስረጃ ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው፡፡ (አልሓዊ ሚን ፈተወል አልባኒ፡ 165-166) https://t.me/susui_slamic_channal

አትቅረቡ እህቴን 🍂🍂🍂🍂🍂 ያቺን ሂጃቢስቷ ያቺን ጅልባብ ለባሽ፣ ያቺን ቆራጠኛ አትንኳት በጭራሽ፣ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 አትቅረቡ እህቴን አጠቁሙባት፣ ባያችኀት ቁጥር ስም አታውጡላት፣ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ይመስላቹሀል እንጂ ይዟቹ ጅህልና፣ የተሸፈነችው የማታምር ሆና፣ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 በል እንደው ቆንጆ ነት ኒቃቢስቷ ጀግና፣ አትምጡብኝ ምትል ከለላ ለዲኗ፣ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 የኔ እህትኮ ባላት ምትብቃቃ፣ ሁሉን ላግኝ አትል አደለች ሞልቃቃ፣ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ለ'ናትና አባቷ ታዛዛዥኮ ናት፣ ለታናናሾቿ ሁለተኛ እናት፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿ እህቷን ነይ ምትል ተማሪ ዲንሽን፣ ጌታሽን ታዘዢ ሸፍኚ ጌጥሽን፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿ ለወንድሟ አዛኝ ለሱ ተቆርቋሪ፣ ጥፋት ስታይበት ናትኮ መካሪ፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿➿ ከአጅነቢ ጋራ አትልከሰከስም፣ መዝናናትም ብላ ስትዞር አትውልም፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿➿ ካልሆንኩኝ አትልም ዘመናዊት ሴት፣ በሶሻል ሚድያው ፎቶ ልፖስት፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿ እርም የሆነውን ታውቀዋለችና፣ መሆን አትፈልግም ለወንድሟ ፊትና፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿ ትንንሽ ወንጀልን የማትዳፈር፣ የማትታለል ናት በሰው ንግግር፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿ ማታውቋት እንደሆን አሁን እወቋት፣ የስድቡን መአት አትልቀቁባት፣ ➿➿➿➿➿➿➿➿➿ https://t.me/susui_slamic_channal

〘ከሰላት በኃላ የሚባሉ ዚክሮች〙 الدعاء الوارد بعد السلام وهو جالس • 〘 أستغفر اللهx3، اللهم أنت السلام، ومنك السلام، تباركت ياذا الجلال والإكرام،〙 〘አላህ ሆይ ምህረትን እጠይቅሀለሁ።x3 አሏህ ሆይ አንተ ሰላም ነህ ሰላም የሚመነጨው ከአንተ ነው። የልዕልናና የልግስና ባለቤት የሆንከው አምላክ ሆይ አንተ እርዳታ ብዙ ነህ〙 〘 ሙስሊም ዘግበውታል〙 〘 لا إلـه إلا الله وحده لاشريك له، له الملك، وله الحمد وهو على كل شيء قدير، لاحول ولا قوة إلا بالله، لا إلـه إلا الله، ولانعبد إلا إياه، له النعمة وله الفضل وله الثناء الحسن، لا إلـه إلا الله مخلصين له الدين ولو كره الكافرون 〙 〘 ከአሏህ ውጭ በእውነት የሚመለክ ሌላ አምላክ የለም። አንድ ነው ፣ አጋር የለውም ፣ ንግስና ለርሱ ብቻ ነው ፣ ምስጋናም ተገቢነቱ ለርሱ ብቻ ነው ፣ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው ፣ ብልሃትም ሀይልም የለም በአሏህ ብቻ ቢሆንጂ። ከርሱ ውጭ ሌላን (ሀይል) አናመልክም።ፀጋዎች ሁሉ የርሱ ናቸው። መልካም ውዳሴ የሚገባውም እርሱ ነው። ከአሏህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም። ለእርሱ ሀይማኖት ፍፁም ቅኖችና ታማኞች ሆን። ካህዲያኖች ባይወዱም እንኳን〙 〘ሙስሊም ዘግበውታል።〙 *سبحان الله، والحمد لله، والله أكبر (33x) لا إلـه إلا الله وحده لاشريك له، له الملك وله الحمد وهو على كل شيء قدير, رواه مسلم* ለአሏህ ጥራት ይገባው። ምስጋና ለአሏህ ነው። አሏህ ከሁሉም የላቀ ነው። "33" ጊዜ። «ከአሏህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም ፣ አንድ ነው ፣ አጋር የለውም ፣ ንግስና ለርሱ ነው ፣ ምስጋና ተገቢነቱ ለርሱ ብቻ ነው ፣ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው»ሙስሊም ዘግበውታል። ثم يقرأ (قل هو الله احد) و (قل اعوذ برب الفلق ) و (قل اعوذ برب الناس) ሱረቱል ኢኽላስ ሱረቱል ፈለቅ ሱረቱል ናስ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ ۚ لَا تَأْخُذُهُ سِنَةٌ وَلَا نَوْمٌ ۚ لَّهُ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ ۗ مَن ذَا الَّذِي يَشْفَعُ عِندَهُ إِلَّا بِإِذْنِهِ ۚ يَعْلَمُ مَا بَيْنَ أَيْدِيهِمْ وَمَا خَلْفَهُمْ ۖ وَلَا يُحِيطُونَ بِشَيْءٍ مِّنْ عِلْمِهِ إِلَّا بِمَا شَاءَ ۚ وَسِعَ كُرْسِيُّهُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ ۖ وَلَا يَئُودُهُ حِفْظُهُمَا ۚ وَهُوَ الْعَلِيُّ الْعَظِيمُ አላህ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ራሱን ቻይ ነው፡፡ ማንገላጀትም እንቅልፍም አትይዘውም፡፡ በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው፡፡ ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢኾን እንጅ የሚያማልድ ማነው? (ከፍጡሮች) በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ በሻውም ነገር እንጂ ከዕውቀቱ በምንም ነገር አያካብቡም (አያውቁም)፡፡ መንበሩ ሰማያትንና ምድርን ሰፋ፡፡ ጥበቃቸውም አያቅተውም፡፡ እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው፡፡ (አል-በቀራህ - 255) *الله لآ إلـه إلا هو الحى القيوم ويقول بعد صلاة الفجر وصلاة المغرب مع ما تقدم( لا إلـه إلا الله وحده لا شريك لـه، له الملك وله الحمد يحيـي ويميت وهو على كل شيء قدير)"*x10 ከመግሪብ ሶላትና ከሱብሂ ሶላት በኋላ ላይ ካሉትም ጭምር «ከአሏህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም ፣ አንድ ነው አጋር የለውም ፣ ንግስና የእርሱ ብቻ ነው ፣ ምስጋና ተገቢነቱ ለርሱ ብቻ ነው ፣ ህያው ያደርጋል ፣ ይገድላልም ፣ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው» x10 ቲርሚዚይና ሌሎችም ዘግበውታል። ويقول تمام المئة (لا اله الا الله وحده لا شريك له له الملك وله الحمد وهو علي كل شئ قدير) x100 ከአሏህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም ፣ አንድ ነው ፣ አጋር የለውም ፣ ንግስና ለእርሱ ብቻ ነው ፣ ምስጋናም ተገቢነቱ ለእርሱ ነው እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው።x100 📚المصدر :- [تفسير العشر الاخير من القرأن الكريم ]* ✅ جزى اللَّهُ خيراً كل من قرأها وساعدنا على نشرها ➖➖➖➖➖➖➖➖➖ https://t.me/susui_slamic_channal

🔖በዲኗ ላይ ችልተኛ የሆነች ጎደኛ ካለሽ ምን ማድረግ አለብሽ ⚠️ ▣አልሼይኽ ኢብኑ ባዝ ••ረሂመሁላህ••▣ ♻️ #ጥያቄ ♻️ ➞°✮ጠያቂዋ ➷እንዲህ ትላለች ➷እኔ የ19 አመት ልጅ ነች ➷በዲኔ በሂጃቤ ➷በሶላቴ በፆሜ ላይ የፀናሁ ➷ነኝ አልሀምድ ➷ሊላህ~°✮ ➞°✮ነገር ➷ግን በጣም እምወዳት ➷ጎደኛ አለችኝ እናም ➷አንዳድ ስተቶችን ➷አይባታለሁ እንዲሁም ➷በሂጃብ ላይ ➷ችልተኛ ናት ➷በተለያዩ በዲን ላይ ➷ግድ የላትም ➷ትኩረት አትሰጥም~°✮ ➞°✮እሷጋ ➷ጎደኛነቴን ልቀጥልን ➷ወይስ ከሷጋ ጎደኛነቴን ➷መለየት ነው ➷ያለብኝ⁉️ ✅ #መልስ ➞°✮ለሷ ➷ነሲሀ በማድረግ ➷በመምከር ትቀጥል ➷ሂጃብ እንድትለብስ ➷ነሲሀ ታድርግላት ➷በሷ ሰበብ ➷አላህ ሂድያ ➷ቢሰጣት~°✮ ➞°✮ነሲሀ ➷አድርጋላት መክራት ➷ካልተስተካከለች ነሲሀዋን ➷ካልተቀበለች ይሄኔ ➷ከሷ መለየት ➷አለባት~°✮ ➞°✮እሷ ➷ወዳለችበት አመለካከት ➷አስተሳሰብ እንዳትስባት ➷የተከለከሉ ነገሮችን ➷እንዳትዳፈር ከንደዚህ ➷አይነት ጎደኛነት ➷መራቅ ከሷም ➷መለየት ➷ይኖርባታል~°✮ ➞°✮ነገር ግን ➷በተቻላት መጠን ➷በምትችለው ያህል ➷ለሷ ነሲሀ ➷ማድረግ መምከር ➷አለባት ወደ መልካም ➷ነገር በማመላከት~°✮ ➞°✮ወይም ➷ደግሞ ከሷ የተሻሉ ➷እምትላቸውን መልካም ➷የሆኑ እህቶች እንዲመክሯት ➷ነሲሀ እንዲያደርጉላት ➷ማድረግ ይህ ➷በመልካም ነገር ➷ማዘዝ ነውና~°✮ ➞°✮ለናቷ ➷በማሳወቅ ወይም ለሷ ቅርብ ➷ለሆነ ሰው ወይም ➷ደግሞ መልካም ሷሊህ ➷የሆኑ ሴቶችን ➷በማሳወቅ እንዲመክሯት ➷በማድረግ ይህ በኸይር ➷በመልካም ነገር መተባበር ➷ነውና~°✮ ➞°✮ነገር ግን ➷ነሲሀ ምክር ➷እማትቀበል ከሆነ እና ግድ ➷የለሽ ከሆነች ሙሉ ➷በሙሉ ከሷ ➷መራቅ እና ከሷ ➷መለየት መልካም ሷሊህ ➷የሆኑ ሴቶች ➷ጋር ነው ➷ጎደኛ አድርጋ ➷መያዝ ያለባት~°✮ ● #ምንጭ ● 📚الموقع الرسمي للشيخ ابـن بـاز https://t.me/susui_slamic_channal

✅ክረምቱን እንጠቀምበት! ➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ..ክረምቱን ነፃ የሆናችሁ ተማሪዎችና መምህራን በምትችሉት አቅም ጊዜያችሁን ስለዲናችሁ በመማር አሳልፉት፡፡ ..የሚያስተምራችሁ ካጣችሁ በድምፅ የተለቀቁ ትምህርቶችን በማዳመጥ፣ ቁርኣን በመሐፈዝ፣ መፃህፍትን በማንበብ እራሳችንን እንለውጥ፡፡ ..ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡- “አላህ መልካም የሻለትን ሰው ዲኑን ያሳውቀዋል፡፡” ባይሆን የወላጆችን ሐቅ በማይጋፋ መልኩ መሆኑ እየተስተዋለ፡፡ ..ማስተማር የምትችሉ ደግሞ ያላችሁን በማካፈል ላይ ተጠመዱ፡፡ ..ቁርኣን በደንብ የያዘ እሱን ያስተምር ዛሬ ዛሬ ነብዩ ﷺ “ከናንተ በላጫችሁ ቁርኣንን ተምሮ ያስተማረ ነው” ማለታቸውን ብዙዎቻችን ትኩረት ነፍገነዋል፡፡ ..አጫጭር የተውሒድ ኪታቦችን የቀራ ሰው ያንኑ ያካፍል ደዕዋ ማድረግ የሚችል በተለይም በገጠር አካባቢ አቅሙ በሚችለው ሰዎችን ያስተምር፡፡ ..ወላጆች ልጆቻችሁ ክረምቱን ባግባቡ እንዲጠቀሙ አግዙ የክረምት ትምህርት የሚሰጡ መድረሳዎች ካሉ ልጆቻችሁ፣ ታናናሽ ወንድምና እህቶቻችሁ እዚያ እንዲከታተሉ አድርጓቸው፡፡ ..አስተማሪዎች አመቱን ሙሉ እንደ ልብ የማታገኙት ሙስሊም እንዳለ አስባችሁ የተሻለ ጥረት ለማድረግ ተንቀሳቀሱ፡፡ነብዩ ﷺ “ወደ መልካም የሚያመላክት እንደሚተገብረው ሰው ነው” ማለታቸው ይታወስ፡፡ አላህ ሁላችንንም ያግዘን፡፡ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ||ሃፊዘሁአሏህ|| https://t.me/susui_slamic_channal

*👉🏻እጅግ ልብ የሚነካ ታሪክ* {ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያረሱለላህ} 😪 ነብዩ ሱለሏህ አለይሂ ወሰለም አንድ ቀን ለዒድ ሶላት ሲወጡ ልጆች ሰፈር ላይ ሲጫወቱ ነበር አንድ ልጅ ተገንጥሎ ያለቅሳል እረሱልም ጠጋ ብለው ሂደው ጠየቁት *ምን ያስለቅስሀል* ከልጆች ጋር ለምን አትጫወትም አሉት ። ልጁም ነብያችን መሆናቸውን አላወቀም ነበር ~~ አባቴ ከረሱል ሱለሏህ አለይሂ ወሰለም ጋር *ፊሰቢሊላህ ወጥቶ ሸሂድ ሆነ* እናቴም ሌላ ባል አግብታ ባሏ አባረረኝ *ምግብ መጠጥ ልብስም ቤትም የለኝ* እነዚህን ልጆች ሳይ *አባት ያላቸው ናቸው* *እና አባቴን አስታወስኩ አላቸው* *እረሱልም ( ሱለሏህ ዐለይሂ ወሰለም) እጁን ይዘው በቃ እኔ አባትህ* አኢሻ እናትህ ዓሊይ አጎትህ ሀሰንና ሁሴን ወንድሞችህ ፋጢማ እህትህ እንድሆኑልህ አትሻም ሲሉ ያኔ አወቃቸው *🔅እንዴት` አልፈልግም *ያረሱለሏህ* አላቸው ይዘውት እቤት ሂደው *ጥሩልብስ አልብሰው አብልተው አጠጥተው ሽቶ ቀቡት* ደስተኛ ሁኖ ወጣ ልጆች ቅድም እያለቀስክ ነበር አሁን ምን አገኘህ ደስተኛ ሁነሀል አሉት ልጁም *እርቦኝ ነበር ጠገብኩ ራቁት ነበርኩ ለበስኩ የቲም ነበርኩ እረሱለሏህ አባቴ* አኢሻ እናቴ ዓሊይ አጎቴ ሀሰንና ሁሴን ወንድሞቼ ፋጢማ እህቴ *ሁነው እንደት አልደሰትም አለ* ልጆቹም አሉ ምን አልባት አባቶ ቻችን *ፊሰቢሊላህ ሸሂድ ሁነው በነበር እንደሱ እንሆን ነበር አሉ* 🇸🇦 እረሱል ( ሱለሏህ አለይሂ ወሰለም ) ወደ አኼራ የሄዱ ጊዜ ልጁ አፈር ወደላዩ እየበተነ *አለቀሰ አሁን ነው የቲም የሆንኩት* ሲል *አቡበክር* (ረድየሏሁ አንሀ ) ሰሙት ሒደው እቅፍ አደረጉት 🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇸🇦 *እውነትም የዝነት ነብይ* ፊዳክ አቢወኡሚ *የያረሱለሏህ* https://t.me/susui_slamic_channal

✍. #ሰሃቦች_እና_መጠሪያቸው!! ①. አቡበክር አሲዲቅ (ረዲየላሁ ዐንሁ ) ๏ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ቅርብ ጓደኛ ነበር ๏ ከወንዶች መጀመሪያ በረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያመነና የተቀበለው ነው ๏ ለእስልምና ሲል ንብረቱን በሙሉ አውጥቷል ๏ በጀነት ከተበሰሩት 10 ሰሃቦች ውስጥ አንዱ ነው ๏ ልክ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በሞቱ እለት ኺላፋውን የተረከበውና የመጀመሪያው ኸሊፋ ነው ๏ የተለያዩ ጦርነቶች አድርጓል ሻምና ዒራቅን ከፍቷል የዐረብ ግዛትን ባጠቃላይ ኢስላማዊ መንግስት ያደረጋትም እርሱ ነበር ๏ ኺላፋው ላይ 2 አመት ከቆየ በኋላ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በሞቱበት እድሜ ከዚህ ዓለም ወጣ … . ⇨. ትክክለኛ ስሙ አብደላህ ኢብኑ አቢ ቁሃፋህ ይባላል ነገር ግን አቡበክር አሲዲቅ ተብሎ ይታወቃል ምክኒያቱ ደግሞ የተለያዩ ንግግሮች አሉ ከነዛ ውስጥ… ①. ከእስልምና ህይወቱ በፊት በጣም እውነተኛ እና ታማኝ በመሆኑ ነበር አንድ ነገር ከተናገረ ቁረይሾች ምንም ሳይከራከሩት ያምኑት ነበር ለዛም ነው አሲዲቅ ብለው የሰየሙት ②. ሌላኛው ንግግር ደግሞ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ወደ ኢስራእና ሚዕራጅ ሄደው ከተመለሱ በኋላ ሁሉም ውሸታም ሲሏቸው እሱ ብቻ ስላመናቸው አሲዲቅ ተባለ‥ ๏ እናቱ ኡሙል ኸይር ሰልማህ ቢንት ሰኽር ትባላለች ። . . . ☆. ኑ ስለሰሀቦች እንተዋወስ ሌሎችንም አናስታውስ ... 🌹. https://t.me/susui_slamic_channal

➴ስለ ተውሒድ ማወቅ ስለ ሰላት እና ስለ ዘካ ከማወቅ በላይ አንገብጋቢ ነው፡፡ ➴ስለ ሺርክ አደገኝነት ማወቅ ስለ ሶላትን ከሚያበላሸው ነገር እውቀት በላይ መታወቁ ግድ ይላል፡፡ ➠ ተውሒድ ፊቂሁል አክበር (ታላቁ ፊቂህ) ተብሏል፡፡ ተውሒድ ከሌለ ምንም ነገር የለም፡፡ ሁሉም ኢባዳዎች ሰላት፣ ዘካ፣ ፆም ተውሒዱ ለተስተካከለ ብቻና ብቻ ነው ጥቅም ያላቸው፡፡ ➴መቀደም ያለበትን እና ትኩረት ሊሰጠው ለሚገባው ትኩረት እንስጥ፡፡ አሏህ በተውሒድ ላይ አኑሮ በተውሒድ ላይ ይግደለን፡፡ ➴አንድ ሙስሊም በአደባባይ ቢድኣ ሲሰራ፣ ዲን ሲፈርስ፣ የባጢል ሰዎች ቢድአቸውን ሲረጩ ካየ ከቁርኣን፣ ከሀዲስ፣ ከሰለፎች ወይንም ከኡለማዎች ንግግር ጠቅሶመልስ መስጠት ይችላል ብቻ ሳይሆን ተገቢም ነው፡፡ ቢድአ እና ጥፋትን ለማስጠንቀቅ ከየትኛውም ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ ዲግሪ፣ ማስተርስ፣ ዶክትሬት ብሎም የየትኛውም መርከዝም ይሁን ግለሰብ ፍቃድ አያስፈልገውም፡፡ https://t.me/susui_slamic_channal

የአላህ መልእክተኛ (ሰ ዐ ወ) እንዲህ ብለዋል… አንድኛችሁ በሚሞትበት ግዜ ማረፊያው ጠዋትና ማታ ይታየዋል ፤ ከጀነት ሰዎች ከሆነ የጀነት መቀመጫው ፣ ከእሳት ሰዎች ከሆነም የጀሃነም መቀመጫው ይታየዋል ፤ በዕለተ ትንሳኤ እስከምትቀሰቀስ ድረስ መኖሪያህ ይህ ነው። ይባላል። ((ቡኻሪ እና ሙስሊም)) 🌹. https://t.me/susui_slamic_channal