981
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የጭንቅ ጊዜ ዱአ
👇👇👇👇👇👇
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የጭንቅ ጊዜ ዱኣ የሚከተለው እንደሆነ አስተምረውናል
"ላኢላሃ ኢለላሁል አዚሙል ሀሊም። ላኢላሃ ኢለላሁ ረቡል አርሺል አዚም። ላኢላሃ ኢለላሁ ረቡ ሰማዋቲ ወረቡል አርዲ ወረቡል አርሺል ከሪም።"
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ኢማን ማለት ምን ማለት ነዉ?
→ኢማን በቋንቋ አተስዲቅ እዉነት ብሎ መቀበልን ያመላክታል
→በሸሪዓዉ በልብ ማመን በምላስ መናገር በአካል መተግበር
ኢማን# ይጨምራል ይቀንሳል
#ኢማን መልካም ስራ ባበዛን ቁጥር አላህ ያዘዘንን በታዘዘን ቁጥር ይጨምራል
→በተቃራኒዉ ወንጀል በሰራን እን አላህ የከለከለንን በተዳፈርን ቁጥር ኢማናችን ይቀንሳል
ኢማን ወደ 73 ይካፈላል
የመጀመሪያዉ ላ ኢላህ ኢለላህ ሲሆን የመጨረሻዉ ከመንገድ ሰዎችን አዛ የሚያደርግን ማንሳት ነዉ
#ኢማን ስድስት አርካኖች አሉት
¹/ አልኢማኑ ቢላህ
²/ ወማላዒከቲሂ
³/ወኩቱቢሂ
⁴/ወሩሱሉሂ
⁵/ወቢል የዉሚል ኣኺር
⁶/ ወቀደሪሂ ኸይሪሂ ወሸሪሂ
ስለ ከባዒሩ አዙኑብ ሁለት አይነቶች ናቸዉ
①ከኢስላም የሚያስወጣ
②ከኢስላም የማያስወጣ ናቸዉ
ከኢስላም ከሚያስወጣዉ ለምሳሌ አሽርኩ ቢላህ ፣ አስህር
#ከማያከፍሩት ለምሳሌ ሰዉን መገድል፣ ዚና ፣ሪባ ግን በጣም ከባኢር ናቸዉ።
እንደዚሁ እንዚህን ከባኢሮች ሀላላነዉ ምንም ችግር የለዉም ያለ ይከፈራል
ዕውቀት ብርሃን ነው ቅድሚያ ዕወቅ))
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
⇛ጀነትን የገባ ሰው ፀጋ የተባለን ሁሉ
ያገኛል ምንንም አያጣም፤ልብሱ
አያልቅም፤ወጣትነቱ አያረጅም።
ጀነት ውስጥ ዓይን አይታ የማታውቀው
ጆሮ ሰምታ የማታውቀውን እንዲሁም
በሰው ልጅ ቀልብ ላይ በትውስታ እንኳ
ውል ያላለ ኒዕማ አለ።» "ረሱል ﷺ"
✦ አሏህ በረህመቱ ኡማውን ይወፍቀው
⇛አሚን ያረበል ዓለሚን 💚
⇛ሶሉ ዓለ ነቢ
˚˚˚˚
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
💠ሴት ልጅ ክቡር ናት💠
🚺ህፃን ሳለች ለወላጆችዋ ጀነትን ታስከፍታልች።
🚻ሚስ?ሚ?ስትም ብትሆን ለባሏ ግማሽ እምነትን ትሞላልች።
🤶እናት ስትሆን ጀነት በእርሷ እግር ስር ትሆናለች፡፡
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
አንድ ሶላት እያወቀ ያሳለፈ 84 አመት
ጀሀነም በር ላይ ስሙ ይፃፋል።
ኡበይዱላህ ኢብን ኡመር አንድ ጊዜ
እንዲህ ብለው ነበር “ጀምዐ ሰላት
በተለይ ኢሻና ሱብሂ አምልጦኝ
አያውቅም፡፡ ነገር ግን አንድ ጊዜ ቤቴ
እንግዳ መጣና ከርሱ ቆይቼ ኢሻ ሶላት
አመለጠኝ፡፡ ከቤት ወጣሁ፤ ጀምዐ
ሶላት ለማግኘት ብዬ በስራ ከተማ ላይ
የሚገኙ መስጂዶች በሙሉ ዞርኩ፤
ሁሉም መስጂዶች ተሰግዶ አልቋል፡፡
ሰዎቹ ባጠቃላይ ሰግደው
ወደቤታቸው ሄደዋል፡፡ እኔም ወደ
ቤቴ ተመለስኩና ማሰብ ጀመርኩ፤
ለራሴ እንዲህ አልኩኝ ‘በሀዲስ
በግለሰብ ከሚሰገደው ሰላት በጀምዐ
ሚሰገደው በ 27 ደረጃ ይበልጣል
ተብሎዋል፤ ስለዚህ 27 ጊዜ ኢሻን
ሰላት ብሰግደው በጀምዐ ከሰገዱት ጋር
እኩል ይሆናል’ ብዬ በማሰብ
ኢሻን ሰላት በቤቴ 27 ጊዜ ሰገድኩና
ተኛሁ፡፡ በዛው ቀን ለሊት በህልሜ
ከፈረሰኞች ጋር ፈረስ ውድድር
ስንወዳደር አየሁ፤ ፈረሴ ጠንካራ
ብትሆንም
እንኳ ሌሎቹ ላይ ልደርስባቸው
አልቻልኩም፤ ወደ ዃላ ቀረሁ፡፡ ፈረሴ
ትደርስባቸው ዘንድ እደበድባት
ጀመርኩ፤ ነገር ግን ምንም ለውጥ
ልታመጣልኝ አልቻለችም፡፡ አንደኛው
ፈረሰኛ ወደኔ በመዞር “ፈረስህን
አታሰቃያት እኛ ላይ ልትደርስብን
አትችልም” አለኝ፡፡ እኔም “ለምን?”
ብዬ
ስጠይቀው “ምክንያቱም እኛ ኢሻን
ሶላት በጀምዐ ነው የሰገድነው፤ አንተ
ግን ብቻህን ሰገድከው” በማለት
መለሰልኝ፡፡ ከዚህ ትልቅ ትምህርት
ወሰድኩ፤ በጣምም አዘንኩ፡፡” ይለናል
ኡበይዱላህ፡፡
ሱብሃነላህ!!
እኛ ስንት ሶላት ይሆን ጀምዐ
ያመለጠን?? ስንቶቻችን ይሆን በዚህ
ምክንያት ተፀፅተን የምናውቅ??
“አንድ ሶላት እያወቀ ያሳለፈ 84
አመት
ጀሀነም በር ላይ ስሙ ይፃፋል”
መባሉን ምናስታውስ ስንቶቻችን
ነን??
ዛሬውኑ እንነይት “ኢንሻ አላህ ካሁን
በሗላ አንድም ሶላት ጀምዐ
አያመልጠኝም” ብለን…ለኔም
ለናንተም ሰደቀቱል ጃሪያ ይሆናልና
መልክቱን
ሼር እናድርገው
ያረብ በሰላት ላይ ጥንካሬና ብርታት ስጠን ከሰይጣን ተንኮል ጠብቀን።
ዋ!! ፈራሁልሽ ነፍሴ
ሰላት ለተዉ እህትና ወንድሞቻችን ዱአ እናድርግላቸው አላህ እኛንም በዚሁ ያፅናን
يا ﷲ يا رب
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
📚አርባ ሀዲሶች (ከኢማም ነወዊ)
•••✿❒🌹❒✿•••
الحديث السادس
(ሰድሰተኛ"[❻]" ሐዲሰ)
#ከአሻሚ_ነገሮች_መራቅ!
عَنْ أَبِي عَبْدِ اللَّهِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ ﷺ يَقُولُ: "إنَّ الْحَلَالَ بَيِّنٌ، وَإِنَّ الْحَرَامَ بَيِّنٌ، وَبَيْنَهُمَا أُمُورٌ مُشْتَبِهَاتٌ لَا يَعْلَمُهُنَّ كَثِيرٌ مِنْ النَّاسِ، فَمَنْ اتَّقَى الشُّبُهَاتِ فَقْد اسْتَبْرَأَ لِدِينِهِ وَعِرْضِهِ، وَمَنْ وَقَعَ فِي الشُّبُهَاتِ وَقَعَ فِي الْحَرَامِ، كَالرَّاعِي يَرْعَى حَوْلَ الْحِمَى يُوشِكُ أَنْ يَرْتَعَ فِيهِ، أَلَا وَإِنَّ لِكُلِّ مَلِكٍ حِمًى، أَلَّا وَإِنَّ حِمَى اللَّهِ مَحَارِمُهُ، أَلَّا وَإِنَّ فِي الْجَسَدِ مُضْغَةً إذَا صَلَحَتْ صَلَحَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، وَإذَا فَسَدَتْ فَسَدَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، أَلَا وَهِيَ الْقَلْبُ". رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ، وَمُسْلِمٌ.
ከአቢ ዐብዲላህ አንኑዕማን ኢብኒ በሺር ረዲየላሁ ዐንሁማ ተይዞ የአላህ መልእክተኛን ﷺ እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ ይላል፦ "ሐላል (የተፈቀደ ነገር) ግልፅ ነው። ሐራምም (የተከለከለ ነገር) ግልፅ ነው። በመካከላቸው አሻሚ ነገሮች አሉ። በእርግጥም ከሰዎች ብዙ አያውቋቸውም። ከአሻሚ ነገሮች የተጠበቀ ሃይማኖቱንም ክብሩንም ጠበቀ። በአሻሚ ነገሮች ላይ የወደቀ ሐራም ላይ ወደቀ። [#8] ልክ በጥብቅ ክልል ዙሪያ (እንስሳቶቹን) እንደሚጠብቅ እረኛ። ከሱ ውስጥ (ግጦሽ) ሊግጡበት ይቀርባሉ። ንቁ! ለእያንዳንዱ ንጉስ ጥብቅ ክልል አለው። ንቁ! የአላህ ክልሉ ክልከላዎቹ ናቸው። ንቁ! በአካል ውስጥ ቁራጭ ስጋ አለች። እሷ ስትሰምር አካል በሙሉ ይሰምራል። እሷ ስትበላሽ አካል በሙሉ ይበላሻል። ንቁ! እሷም ልብ ነች።" ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል። [52] [1599]
📕 #ሐዲሡ_ያለው_የላቀ_ደረጃ፦
ይሄ ሐዲሥ ከሸሪዐ መሰረቶች ውስጥ አንዱ መሰረት ነው። አቡ ዳውድ አስሰጂስታኒ ረሒመሁላህ "ኢስላም በአራት ሐዲሦች ላይ ይሸከረከራል" ብለው ከጠቀሷቸው ሐዲሦች አንዱ ይሄ ሐዲሥ ነው። [ሸርሑል አርበዒን፣ ኢብኑ ደቂቀል ዒድ፡ 26]
📚
በዚህ ሐዲሥ መሰረት ነገሮች ለሶስት ይከፈላሉ። ግልፅ የሆነ ሐላል፣ ግልፅ የሆነ ሐራም እና አሻሚ ተብለው። ሐላሉን መፈፀም መብታችን ነው። ሐራሙን መራቅ ግዴታችን ነው። አሻሚውን መጠንቀቅ ሰላማዊ ቀጠና ነው። በህይወታችን በብዛት ለሚያጋጥሙን ወስዋሶች ይህንን ሐዲሥ ብንከተል ትልቅ እፎይታ እናገኛለን።
🔺 #ከሐዲሡ_የሚወሰዱ_ቁም_ነገሮች፦
✔️ ሐራምና ሐላል በአብዛሀኛው ግልፅ እንደሆኑ፣
✔️ መፈቀድ አለመፈቀዳቸው ከማይለዩ አሻሚ ነገሮች
ልንርቅ እንደሚገባ፣
✔️ አሻሚ ነገሮችን የሚዳፈር ሰው ወንጀል
እየቀለለው እንደሚመጣ፣
✔️ በሌሎች በክፉ የሚያስጠረጥሩን ነገሮችን ችላ
ልንል እንደማይገባ፣
✔️ በምሳሌ ማስተማር ጠቃሚ የሆነ ስልት እንደሆነ፣
✔️ ከአሻሚ ነገሮች መራቅ ዲናችንን ከጉድለት፣
ክብራችንን ከመጉደፍ እንደሚጠብቅ፣
✔️ ልብን ከሚበክሉ ጥፋቶችና ክፉ አመሎች
መጠንቀቅ ከምንም በላይ ቅድሚያ ሊሰጠው
እንደሚገባ፣
✔️ የውጭ መበላሸት የውስጥ ብልሽት ነፀብራቅ
እንደሆነ እንማራለን።
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
[#8] ይሄ ማለት ወይ ሳያውቀው ሐራም ነገር ላይ ሊወድቅ ይችላል ማለት ነው። ወይ ደግሞ ሐራም ላይ ለመውደቅ መቃረቡን ለማመላከት ነው። ወይም ደግሞ አሻሚ ነገሮችን መዳፈር ሲያበዛ በሂደት ወንጀል እየቀለለው ይሄዳል ማለት ነው።
📲 የነወውይ አርባ ሐዲሥ ከኢብኑ ረጀብ ጭማሪ ጋር!!
✹••••━━✿◾❁◾✿━━••••✹
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
🛌🚿ስንቶቻችን ነው ስለ ሰላተል ጀናዛ
አሰጋገድ የምናውቀው ???🚿
📂 #የጀናዛ_ሶላትየሶላቱል_ጀናዛ_ማእዘናት
➧➀ - ቅያም - ለሚችል ሰው መቆም፡፡
➧➁ - አ ራቱ ተክቢራዎች፡፡
➧➂- ፋቲሓን መቅራት፡፡
➧➃- በነቢዩ ﷺ ላይ ሶላት ማውረድ፡፡
➧➄ - ለሟቹ ዱዓእ ማድረግ፡፡
➧➅- ቅደም ተከተሉን መጠበቅ፡፡
➧➆ - ተስሊም (ሰላምታ)፡፡
💢#የሶላቱል_ጀናዛ_ሱንናዎች
➧➀- ከቅራኣ በፊት እስትዓዛ ማለት፡፡
➧➁ - ለራሱና ለሙስሊሞች ዱዓእ ማድረግ፡፡
➧➂ - ድምጽ ሳያሰሙ መቅራት፡፡
➧➃ - የሶላቱን ሶፍ ሦስት ረድፍ እንዲሆን ማብዛት፡፡
🕌 ➨የሶላቱል_ጀናዛ_አሰጋገድ
➾#ሟች #ወንድ ከሆነ ኢማሙ በአስከሬኑ ራስ አቅጣጫ፣
➾#ሴት ከሆነች ደግሞ በአስከሬኑ መሀል አቅጣጫ ይቆማል፡፡ ተከትለው የሚሰግዱት እንደ ሌላው ሶላት ከኢማሙ ጀርባ ይቆማሉ፡፡ ኢማሙ አራት ተክቢራዎች በሚከተለው ዝርዝር መሰረት ያደርጋል፡-
☄ ❶ - የእሕራም ተክቢራ አድርጎ እስትዓዛና በስመላ ካለ በኋላ ፋቲሓን ይቀራል፡፡ የእስትፍታሕ ዱዓእ ግን አይደረግም፡፡
☂❷ - ሁለተኛውን ተክቢራ አድርጎ በመደበኛው ሶላት የመጨረሻው ተሸሁድ የሚደረገውን ዓይነት ሶላት በነቢዩ ﷺ ላይ ያወርዳል፡፡
☄ ➌ - ሦስተኛውን ተክቢራ ካለ በኋላ ለሟቹ ለራሱና ለሙስሊሞች ዱዓእ ያደርጋል፡፡
✨ #ከዱዓእ_ዓይነቶች_የሚከተለውን_እናገኛለን፡-
‹‹አልሏሁም’መ እግፍርለሁ ወርሐምሁ፣ወዓፍህ ወዕፉ ዐንሁ፣ወአክሪም ኑዙለሁ፤ወወስ’ሲዕ ሙድኸለሁ፤ወግሲልሁ ብልማእ ወሥ’ሠልጅ ወልበረድ፤ወነቅ’ቂህ ምነልኸጣያ ከማ ነቅ’ቀይተ አሥ’ሠውበል አብየደ ምነድ’ደነስ፤ወአብድልሁ ዳረን ኸይረን ምን ዳሪሂ፣ወአህለን ኸይረን ምን አህሊሂ፤ወዘውጀን ኸይረን ምን ዘውጅህ፤ወአድኽልሁ አልጀን’ነተ ወአዕዝሁ ምን ዐዛበል ቀብር ወምን ዐዛብ አን’ናር፡፡››
#ትርጉሙ፡-
‹‹አላህ ሆይ! ምሕረት አድርግለት፤እዘንለትም፡፡ ከቅጣትም አድነው፤ይቅር በለውም፡፡ መስተንግዶውንም አሳምርለት፤ ማረፊያውንም አስፋለት፡፡ ከኃጢአቱ በውኃ በበረዶና በአመዳይ (በረድ) እጠበው፡፡ ነጭ ልብስ ከቆሻሻ እንደሚጠራ ሁሉ ከኃጢአቱ አጥራው፡፡ ከመኖሪያው የተሸለ መኖሪያ፣ከቤተሰቡ የተሻለ ቤተሰብ፣ከሚስቱ የተሸለች ሚስት ቀይርለት፡፡ ወደ ጀነትም አስገባው፤ከመቃብር ውስጥ ስቃይና (ወይም) ከእሳት ቅጣትም ጠብቀው፡፡››
[📚በሙስሊም የተዘገበ] ማለት ነው፡፡
🌂 ሟች ሴት ከሆነች ዱዓኡ ተውላጠ ስሙ በሴቴ ጾታ ይለወጣል፡፡ ሟች ሕጻን ወይም ጭንጋፍ ከሆነ ‹‹አልሏሁም’መ እጅዐልሁ ዙኽረን ልዋሊደይህ፣ ወፈረጠን፣ወአጅረን፣ወሸፊዐን ሙጃበን››
‹‹አልሏሁም’መ ሰቅ’ቅል ብሂ መዋዚነሁማ፣ወአዕዝም ብሂ ዋጁ ብሷሊሕ ሰለፍልሙእምኒን፣ወጅዐልሁ ፊከፋለት ኢብራሂመ፣ ወቅህብረሕመትከ ዐዛበል ጀሒም፡፡›› ይላል፡፡
#ትርጉሙ ፡-
‹‹አላህ ሆይ! ለወላጆቹ አለኝታ፣(ወደ ጀነት) ቀድሞ የሚጠብቃቸው አጅር፣(አላህ ዘንድ) ተቀባይነት ያለው አማላጅም አድርግላቸው፡፡››
[📙በቡኻሪ የተዘገበ]
[አላህ ሆይ! የመልካም ሥራዎቻቸው ሚዛን ማክበጃም አድርገው፡፡ ምንዳቸውን በርሱ ትልቅ አድርግላቸው ፡፡ ከደጋግ አበው ሙእሚኖች ተርታም አሰልፈው፤በችሮታህም ከገሀነም ሥቃይ ጠብቀው፡፡›› ማለት ነው፡፡
☂ ➍ - ከዚያም አራተኛውን ተክቢራ አድርጎ ትንሽ ዝም ይልና ወደ ቀኝ ብቻ ሰላምታ ያደርጋል፣ወይም ሁለት ሰላምታ ያደርጋል!!!
✹••••━━✿◾❁◾✿━━••••✹
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
┄┄✽̶»̶̥❤️#Elham_እና_Harun ❤️✽̶┄┄
✍ Elham እና Harun የተሰኘው እጅግ ልብ አንጠልጣይ #የፍቅር ታሪክ እነሆ ጀባ ልንላችሁ ነው
በ zakiya Redi ተፃፈ
ፍቅርን መተሳሰብን እና መስዋትነትን ለወደዱት እራስን መስጠትን ፍንትው አርጎ የሚያሳይ ድንቅ ታሪክ
አሁኑኑ ||OPEN|| የሚለውን በመጫን የታሪኩ ተቋዳሽ ይሁኑ።
⛔️ወላሂ የውሸት ማስታወቂያ አይደለም አሁኑኑ ከታች #OPEN የሚለውን ይጫኑ⛔️
#የነቢዩሏህ_ኢድረስ_ዐ_ሰ_ታሪክ
#ክፍል2
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ኢድሪስ ዐ ሰ ከሞቱ በኋላ ለተወሰኑ አመታት የሰው ዘሮች አላህን ያለማጋራት በብቸኝነት ያመልኩት ነበር።
ያው ትውልድ ትውልድን ይተካል'ና አላህን በማምለክ ወደር የሌላቸው መልካም'ና በዘመኑ ለነበሩ ሰዎች አርዐያ የሆኑት ውስን ሰዎች ህዝቡን በሞት ይለዩ ጀመር....በዘመኑ የነበሩ ህዝቦችም በነዚያ ደጋግ ሰዎች ህልፈት እጅጉን አዝነዋል።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ሀዘናቸውን ለማስታገስ እና እነዚህን ደጋግ የአላህ ባሮችን ለማስታወስ ሀውልት ሊሰሩላቸው ተነጋገሩበትና እቅዳቸውንም እውን በማድረግ በ5 ትላልቅ እና ደጋግ ሰዎች ስም 5 ሀውልት በከተማ መሀል አቆሙላቸው።
ስማቸውም፦
1፦ወድ
2፦ሱዋዕ
3፦የጉስ
4፦የዑቅ
5፦ነስር...እነዚህ ናችው።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
በዚህ መልኩ እነዚህን ደጋግ ሰዎች ሁሌም ያወሷቸው ነበር...የከተማይቱ ሰዎች ለነዚያ ደጋግ የአላህ ባሮች ካላቸው ክብር አንፃር ሀውልቶቻቸውንም ወደር የለሽ ክብር ያከብሩ ነበር።
እንዲህ እንዲህ እያለ ሰዉ ለነዚህ ሀውልቶች ያለው ቦታ ሁኔታውን እየቀየረ መጣ።በሀውልቱ አጠገብ ሲያልፉ ለሀውልቱ ክብር በሚል እያጎበደዱም ማለፍ ጀመሩ።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ግዜው ይነጉዳል ክረምት እና በጋ ቀጠሮዋቸውን ጠብቀው በፍጥነት ይተካካሉ።ክረምት ሲመጣ ዝናቡ በጋ ሲመጣ ፀሀዩ የሀውልቶቹን ይዘት መቀየር ሲጀምር የከተማይቱ ነዋሪዎች ሀውልቶችን ከውድመት ለመታደግ አንድ ቤተ አምልኮ ውስጥ ሊያስገቧቸው ወስኑ።...እች ጠጋ ጠጋ እቃ ለማንሳት ሀ!!!
ሀውልቶቹን መጠለያ ውስጥ ካስገቡ በኋላ ለሀውልቶቹ ያላቸው ቦታ ይበልጥ ጨመረ።በገቡ እና በወጡ ቁጥር ለሀውልቶቹ ማጎብደድ ጀመሩ።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ያን ግዜ አላሁ ሱብሀነሁ አተዓላ ከነዝያ ህዝቦች ወደ ቀጥተኛው መንገድ ይመራቸው ዘንድ ኑህ የተባሉ መልዕክተኛን አስነሳ።
#ተፈፀመ
: #በአላህ_ፍቃድ
:#የኑህ_ታሪክ_ይቀጥላል.....
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
#ነብዩሏህ_እድሪስ(ዐ.ሰ) ታረክ
# ክፍል1
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
በግዜው አባታችን አደም (ዐ ሰ) ከሞተ 15 ክፍለ ዘመናት(1500 አመት) ተቆጥሯዋል።የአደም ልጆች ቁጥር ምንም እንኳን ቢጨምርም በአደም ልጆች ዘንድ እስካሁን ምንም አይነት የኩፍር እንቅስቃሴ የለም ያን ዘመናት ሁሉ የአደም ልጆች አላህን በብቸኝነት እያመለኩት ነው።
አሁን አሁን ግን ሰዎች አስተሳሰባቸው እየተቀየረ መጣ፣ትንሽ ትንሽ የሸይጣን ኮቴ ያንሸራትታቸውም ጀምሯል።
(አሁን የዛሬውን እንግዳዬን ላስተዋውቃችሁ)
ነቢዩላህ ኢድሪስ (ዐ ሰ) ይባላሉ። ረጅም ሰዐት ዝምታ ያሚያስደስታቸው ሰው ናቸው።ከተናገሩም ሒክማ ያላትን እና አጠር ያለች ንግግር ነበር ሚናገሩት።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ለመጀመርያ ግዜ በቀለም መፃፍን የጀመሩትም እሳቸው ናቸው።
ለመጀመርያ ግዜ ልብስ ሰፍተው መልበስ የጀመሩትም ኢድሪስ ዐ ሰ ናቸው።
ሁሌም ልብስ ሲሰፉ መርፌዋን ባስገቡ'ና ባወጡ ቁጥር ሱብሀን አላህ ይሉ ነበር።
አላህም የኮከብ እውቀትን እና ስለ ሰነ ፈለክ አስተምሯቸዋል።
የእውቀትንም ሁሉ ቁልፍም አላህ ሰጥቷቸዋል።
በዘመናቸው የነበሩትን ሰዎች ስለ አፃፃፍም ያስተምሩ ነበር።
ሀገሪቷ ባቢሎን ትባላለች ዘመኑ ገና የስልጣኔ ጀምበር ብቅ ብቅ የሚልበት ዘመን ነበር። የከተማዋ ህዝብ ለሽርክ እና ለፈሳድ ገና ፍሬሽ ስለሆኑ ኢድሪስ ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ ቢመክሯቸውም ጥቂት ሰዎች ሲቀሩ ሰዉ ሁሉ አሻፈረኝ ብሎ ጥመት ላይ መፅናትን መረጠ።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ከብዙ እልህ አስጨራሽ የዳዕዋ ትግል በኋላ ኢድሪስ ዐ ሰ ሀገሪቱን ለቀው ወደ ሌላ ቦታ ለመሰደድ ወሰኑ።ጥቂት ተከታዮቻቸውንም ሲያማክሩ ምንም እንኳን ሀገራቸውን ጥለው ለመውጣት ትንሽ ቢያንገራግሩም በኢድሪስ ዐ ሰ አንደበተ ርቱዕነት በሀሳባቸው ሊስማሙ ቻሉ።
ኢድሪስ ዐ ሰ ከባቢሎን ከተማ ተከታዮቻቸውን ይዘው ወጡ'ና ብዙ ከተጓዙ በኋላ አፍሪካዊቷ ቀደምት ከተማ የሆነችውን ግብፅን ገና ስትቆረቆር ከህዝቧ ጋር ተቀላቀሉ።ገና ከተማዋን ከመግባታቸው ነበር ወደ አላህ እና ወደ መልካም ስነ ምግባር ዳዕዋ ማድረግ የጀመሩት።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
በዛም መሀል ወደ ሻም/ሶርያ አከባቢ እና ወደ ፊለስጢን በመሄድ ሰዎችን ወደ አላህ ይጣሩ ነበር።ይሁን እንጂ ለመቀመጫነት ግን ግብፅን ነበር የመረጡት።እዛው ለልጆቻቸውም የተለያዩ ዱንያዊ እና አኺራዊ ትምህርት ይሰጡም ነበር።
በኢድሪስ ዐ ሰ ዘመን ዐለም ላይ ያለው ቋንቋ ብዛት 72 ነበር።የፈለጉበት በመሄድ ዳዕዋ ያደርጉ ዘንድም አላህ ሀሉንም ቋንቋዎች አሳውቋቸውም ነበር።
እንዲህ እንዲህ እያሉ ኢድሪስ ዐ ሰ እድሚያቸው 865 ደረሰ።አላህም እንዲህ ሲል ለኢድሪስ ወህይ አወረደላቸው፦"በያንዳንዱ ቀን የአደም ልጆች ሁሉ የሚሰሩትን አጅር ያህል ላንተም እፅፍልሀለሁ።"
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ኢድሪስም ዐ ሰ ግን እድሜያቸው እንዲጨመርላቸው እና ሌላም ብዙ መልካም ስራ መስራት ነበር ፍላጎታቸው።ይሁን እንጂ ፍላጎታቸውን በምኞት ብቻ ሊገድቡት አልፈለጉም ነበር።
አንድ መልዓክ ጓደኛ ነበራቸው'ና እሱን ወደ አላህ ዘንድ እንዲወስዳቸው እና አላህ በእድሚያቸው ላይም ይጨምርላቸው ዘንድ ሊጠይቁት እንደሆነም አስረድተውት ከመልዐኩ ጋር መልዓኩ በሁለት ክንፉ መካከል ይዟቸው አየሩን እየሰነጣጠቁ ጉዞ ወደ ሰማያት ጀመሩ።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ሰማያትን በመልዓኩ ክንፎች እየቀዘፉ በከፍተኛ ፍጥነት 1ኛ ሰማይ ደረሱ...2ኛ....3ኛ....4ኛ ሰማይ ላይ እንደረሱ መለከል መውት ወደ ምድር እየተምዘገዘገ አገኙት'ና ኢድሪስን ዐ ሰ የያዘው መልዓክ መለከል መውትን አስቆሞ የኢድሪስን ዐ ሰ እድሜ ስንት እንደቀረው መዝገቡን እንዲያይለት ጠየቀው።
መለከል መውትም መዝገቡን ተመለከተ'ና፦"ኢድሪስ የታለ" አለው።
መልዓኩም፦"እዚህ ክንፌ ውስጥ ነው" አለው።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
መለከል መውትም፦"ይገርማል! አሁን እኮ የሱ ቀጠሮ ደርሶ እሱ ጋ ነበር ምከንፈው። እኔ ልገረም የቻልኩት አላህ የኢድሪስን ሩህ በ4ኛ ሰማይ ላይ ሄደህ አውጣ ሲለኝ ግራ ተጋብቼ ነበር ምክንያቱም ኢድሪስ በምድር ላይ ሳለ እንዴት አላህ ከአራተኛ ሰማይ ሩሁን እንዳወጣ ያዘኛል ብዬ ነው።" አለ
መልዓኩም ትንሽ እንዲያቆየው ቢጠይቀውም መለከል መውትም፦"አሁን ነፍሱን እንዳወጣ እዚችው ነው'ና የታዘዝኩት እዚችው ነው ማወጣት" ብሎ ኢድሪስ ዐ ሰ በተወለዱ በ 865 አመታቸው በመልዓኩ እቅፍ ውስጥ ሳሉ ሩሀቸው በ4ኛ ሰማይ ላይ ወጣች።
🌹•••✿❒🌹❒✿•••🌹
ለዚህ ነው አላህ በሱረቱ መርየም እንዲህ ያለው፦"በመጽሐፉ ኢድሪስንም (ሄኖክን) አውሳ፡፡ እርሱ እውነተኛ ነቢይ ነበርና፡፡
ወደ ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው" ሰደቀላሁል አዚም..........
:
በአላህ ፍቃድ ክፍል 2⃣ ነገ
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል
⤵
ምንጭ፦"
القرءان الكريم
ﺍﻟﺒﺪﺍﻳﺔ ﻭﺍﻟﻨﻬﺎﻳﺔ /ﺍﻟﺠﺰﺀ ﺍﻷﻭﻝ /
صحيح مسلم
صحيح البخاري
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ኢብራሂም ዓለይሂ ሰላም አባታቸው ሙስሊም
እንዲሆንላቸው ተመኙ ...
ኑህም ዓለይሂ ሰላም ልጁ ሙስሊም
እንዲሆንላቸው ተመኙ...
የኛው ነብይም ﷺ አጎታችው ሙስሊም
ቢሆን ብለው ተመኙ...
ነገር ግን አላህ አልፈለገውምና አልሆነም
አላህ ግን ለኔና ላንተ/ላንቺ ሳንጠይቀው
እስልምናን ሰጠን
ለኢብራሂም አለባት ለኑህ ልጅ ለረሱሉ ﷺ አጎት
ያልሰጠውን ውብ እስልምናን ለገሰን አናመሰግንምን!!
ۚ إِنَّ اللَّهَ لَذُو فَضْلٍ عَلَى النَّاسِ وَلَٰكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَشْكُرُونَ
{አላህ በሰዎች ላይ በእርግጥ የችሮታ ባለቤት
ነውና፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያመሰግኑም፡፡}
[ሱረቱል ጋፊር: 61]
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
➪💎ሙስሌሟ እህቴ ሆይ⚠️
➛◉ሱናን የሚጋጭ ነገር ከመስራት አደራሽን‼️
⇨ሸይኽ ኢብኑ ባዝ ((አላህ ይዘንላቸዉና))
➣ እንድህ አሉ:-
➛◉ጥፈርን ማስርዘም( ማሳደግ) ሱናን ይጋጫል‼
➛◉ከአዉሪዎችና ከካፊሮች ጋር መመሳሰል ነዉ‼
📚ሚንጭ((ፈተዎ 49/10]
➪◉ሸይኽ ፈዉዛን ((አላህ ይጠብቃቸዉና))
➣እንድህ አሉ:-
➛◉ከፊሎች ሙስሊሞች ጥፍርን በማሳደግ በእርግጥም ተፍትነዎል‼
➛◉ሱናን በመሳት እና ካፊሮችን በመመሳሰል ሙስሊም ሴቶች ተፍትነዎል‼
➛◉ሴት ልጂ ጥፍሯን መቆርጥና ማፀዳት ከሱና ነዉ‼
➛◉ባጠቃላይ የእዉቀት ባለቤቶች እንደተስማሙበት የነብዩን ሐድስ መሰርት በማድርግ ጥፍርን መቆርጥና ማፀዳት ሱና ነዉ በማለት ልዪነት የላቸዉም‼
➛◉ነገር ግን ጥፍርን ማስርዘም(ማሳደግ) ከአዉሪዎችና ከካፊሮች ጋር መመሳሰል ብሎም ከጥፍሩ እርዝመት ዉስጥ ቆሻሻ መጠራቀሚያ ገዳ ይሆናል ዑዱኡ ስታደርግ ዉሃዉ መድርስ ካለበት ቦታ ላይ እንዳይደርስ ይከለክላል ‼
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
🎋አላህን ጠይቅ በሁሉ ሁኔታ ላይ አትራፊ ነህ አላህን የለመነ አይከስርም🌸
▣አልሼይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን ••ረሂመሁላህ• እንዲህ ይላሉ▣
➞°✮እወቅ ➷አላህን ከጠየክ ➷በሁሉ ሁኔታ ➷ላይ አንተ ➷አትራፊ ነህ ምክንያቱም ➷ወይንም ➷አላህ ሱብሀነሁ ➷ወተአላ ሊሰጥህ ነው ➷የጠየከውን~°✮
➞°✮ወይንም ➷መከራን መጥፎ ➷ነገርን ችግርን ➷ሊያስወግድልህ ዘወር ➷ሊያደርግልህ ነው ➷ጠይቀሀው ከሚሰጥህ ➷በላይ ወይንም ➷ይህን አላህ ➷ለውመልቅያማ ያከማችልሀል ➷አጂር~°✮
➞°✮አላህን ➷የለመነ አይከስርም ➷አላህን መለመን አብዛ ➷አላህን ምህረት ➷መጠየቅ አብዛ ➷ወደ አላህ ➷ተውበት ማድረግን ➷አብዛ~°✮
#ምንጭ
📚{{شرح رياض الصالحين |6\52}}
"ሀያዕ ከ ኢማን ነዉ
ይህ ምክሬ ላንቺ ነው!"
ውዷ እህቴ ሆይ ተሸፈኚ
በሀያዕሽም ንግስት ሁኚ
•┈┈•◈◉❒{💎}❒◉◈•┈┈•
【ምክር ለሙስሊሟ እህቴ➧
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
አስተውል ‼️
«ከሰው ጋር አትፎካከር:- ምክንያቱም ሁሉም አላህ የፈቀደለት ነውና የሚያገኘው።ደግሞም መፎካከር ወደ ቅናት ይወስድሀል፤ቅናት ወደ ጥላቻና መጥመም ይጋብዛልና‼️
«ያለህን ተመልከት:-ያለህ ነገር ተመልክተህ አላህን አመስግን፤የሌለህን ምትመኝና ሁሉም የሚያምርህ ከሆነ በሀሳብ ዋልለህ ትጠፋለህ፣ያለህንም ታጣለህ‼️
👌ምኞታችሁ የሚሳካበት ቀን ተመኘሁ
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
🌸"አቡ ዐብዱረህማን ዐብደላህ ኢብን ዑመር ኢብኑ አል-ኸጧብ (ረዲየላሁ ዐንሁም) የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ በማለት አስተላልፈዋል ፡-
🌸‹‹ከናንተ በፊት ከነበሩ ሰዎች መሀከል ሶስት ሰዎች ለጉዞ ተንቀሳቀሱ ሲመሽባቸው ለአዳር ከአንድ ዋሻ ውስጥ ገቡ ከተራራ ላይ የነበረ አንድ ቋጥኝ ተንከባሎ ዋሻውን ዘጋባቸው አላህን በመልካም ተግባራቹ ካለመናቹት በቀር ከዚ ቋጥኝ የሚያድናቹ ነገር አይኖርም ተባባሉ ከመካከላቸው አንዳቸው እንዲህ አለ፡-
🌸‹‹አላህ ሆይ! አዛውንት ወላጆች ነበሩኝ እነሱ ከመጠጣታቸው በፊት ቤተሰቦቼንም ከብቶቼንም ወተት አላጠጣም ነበር እንጨት ለቀማ ሩቅ ቦታ ሄድኩ እስከተኙበት ጊዜ ድረስ አልተመለስኩም ወተታቸውን አለብኩላቸው ተኝተው አገኘኋቸው ልቀሰቅሳቸው አልከጀልኩም ከነርሱ በፊት ቤተሰቤንና ከብቶቼን ማጠጣትም አልፈቀድኩም ወተት የያዘውን ዋንጫ በእጄ እንደያዝኩ መንቃታቸውን ስጠባበቅ ጎህ እስኪቀድ ድረስ ቆየሁ ህጻናት ከእግሮቼ ስር ይንጫጫሉ ወላጆቼ ከእንቅልፋቸው ነቅተው ወተታቸውን ጠጡ አላህ ሆይ! ይህንን ድርጊት የፈጸምኩት ያንተን ውዴታ ከጅዬ ከሆነ በዚህ ቋጥኝ ሰበብ ከደረሰብን መከራ አውጣን ፡፡
ቋጥኙ ትንሽ ከፈት አለ መውጣት የማያስችላቸው ያክል፡፡
#ሌላኛው ደግሞ እንዲህ አለ ፡-
🌸‹‹ የአጎት ልጅ ነበረችኝ እጅግ አፈቅራት ነበር፡፡››
በሌላ ዘገባ እንደተወሳው
🌸‹‹ አንድ ወንድ አንዲትን ሴት የሚያፈቅራትን የመጨረሻው የፍቅር እርከን ያህል አፈቅራታለሁ በወሲባዊ ተራክቦ ጠየቅኳት ፍቃደኛ አልሆነችም አንድ የድርቅ ዓመት ተከሰተ (እርዳታዬን ፈልጋ) ወደኔ መጣች የምፈልገውን እንድፈጽም ቃል አስገብቼ አንድ መቶ ሀያ ዲርሀም ሰጠኋት ቃሏን አከበረች ያሻኝን መፈጸም እስክችል ድረስ››
በሌላ ዘገባ ላይ እንደተወሳው ደግሞ
🌸‹‹በጭኖቿ መሀል እንደገባሁ አላህን ፍራ ያለ አግባብ ክብረ-ንጽህናዬን አትገርስስ አለችኝ:: ዘወር አልኩ ምንም ነገር ሳልፈጽም፡፡ ከማንም አብልጬ እዎዳታለሁ የሰጠኋትንም ወርቅ ተውኩላት አላህ ሆይ! ይህንን ተግባር የፈጸምኩት የአንተን ውዴታ ከጅዬ ከሆነ ካለንበት መከራ አውጣን::»
ቋጥኙ ትንሽ ከፈት አለ መውጣት ግን አይችሉም፡፡››
#ሦስተኛው እንዲህ አለ ፡-
🌸‹‹ ሰራተኞችን ቀጠርኩ ለሁሉም ያገለገሉበት ክፍያቸውን ከፈልኳቸው ከመካከላቸው አንዱ ሲቀር ድርሻውን እኔ ዘንድ ትቶ ሄደ ትቶት የሄደውን ገንዘብ አባዛሁለት ብዙ ሀብት እስኪሆን ድረስ ከዘመናት በኋላ ወደ እኔ መጣ እንዲህም አለኝ ፡- ‹‹ዐብደላህ ሆይ! ድርሻዬን ስጠኝ›› ይህ የምትመለከተው ሁሉ ግመሉም ከብቱም ፍየሉም ባሪያውም ድርሻህ ነው አልኩት ‹‹ ዐብደላህ ሆይ! አትቀልድብኝ›› አለኝ፡፡ እየቀለድኩብህ አይደለም አልኩት ሁሉንም ተረክቦ እየነዳ ወሰደ አንዳችም ነገር አልተወም አላህ ሆይ! ይህንን የፈጸምኩት ያንተን ውዴታ በመሻት ከሆነ ካለንበት መከራ አውጣን::»
ቋጥኙ ተከፈተ ወጥተው ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡
📚 ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበዉታል
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
ድሃ ማለት ማን እንደሆነ ታወቃላችሁ⁉️
የአላህ መልክተኛ (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከዕለታት አንድ ቀን ከባለደረቦቻቸው ቁጭ ብለው ሳለ፦
“ድሐ ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ?” በማለት ይጠይቃሉ።
||
ሰሐቦችም ፦ “እኛ ጋር ድሀ ማለት ምንም ንብረትና ገንዘብ የሌለው ነው” በማለት ይመልሳሉ።
*
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ግን፦ “ከኡመቴ ደሀ ማለት የትንሳኤ ቀን በብዙ ሰላቶች፤ ዘካዎችና፤ ፆሞች የሚመጣ ሰው ነው፣ ነገር ግን ይህ ሰው አንድ ወንድሙን ሰድቧል፣ ሌላው ላይ ዋሽቷል፣ የአንዱን ገንዘብ ያለአግባብ ወስዷል፣ የሌላውን ደም አፍስሷል፣ አንዱን መትቷል፣ በሌላው ላይም ድንበር አልፏል፣
ያኔም የቂያም ቀን (የምርመራ ቀን) የራሱን ጥሩ ሥራዎች ለበደላቸው በካሳ መልክ አሳልፎ ይሰጣል፣ ጥሩ ሥራው ለመካሻ አልበቃ ይለውና የበደላቸውን ሰዎች ኃጢያት ይሸከማል፣ ከዚያም ወደ ጀሀነም ይወረወራል” በማለት መለሱላቸው።
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
➩ ነቢዩ (ﷺ)እንዲ ብለዋል።
“በዚያ ከአርሹ ጥላ በስተቀር ምንም ጥላ በሌለበት ቀን (የፍርዱ ቀን)፤ አላህ ሰባት ሰዎችን በአርሽ ጥላ ስር ያኖራቸዋል።እነሱም፡-
➊ ፍትሃዊ መሪን፣
➋ አላህን በመገዛት ወጣትነቱን ያሳለፈ፣
➌ ልቡ ከመስጅድ ጋር የተቆራኘን ሰው፣
➍ ለአላህ ብቻ ብለው በአላህ መንገድ ላይ የተዋደዱንና በርሱም መንገድ ላይ የተለያዩ (ሲለያይም ለአላህ ብለው)፣
➎ አንዲት ቆንጆ ሴት ራሷን ለዝሙት አዘጋጅታለት ‘አላህን እፈራለሁ’ በማለት እምቢ ያለች፣
➏ በድብቅ ምጽዋት የሚሠጥ ሰው፣
➐ ብቻውን ሆኖ አላህን ሲያስታውስ አላህን ፈርቶ አይኖቹ በእንባ የሚሞላና ጉንጮቹ የሚርሱ ሰው”
(አል-ቡኻሪ ዘግበውታል )
:::::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌
@susui_slamic_channal
