𝙞𝙗𝙧𝙖𝙝𝙞𝙢 𝙝𝙚𝙮𝙧𝙚𝙙𝙞𝙣 𝙘𝙝𝙖𝙣𝙣𝙚𝙡
የቻናሉ ትኩረትና ዓላማ: – √ ቁርዓንን በማየት(በነዘር)መቅራት ለማይችሉ እገዛና ድጋፍ ማድረግ። እንዲሁም በተጨማሪ በኡስታዝ ኢብራሒም የሚሰጡ:– √ የተጅዊድ √ የቁርአን ሐለቃ √ እና የተለያዩ ደርሶች የሚለቀቁበት ቻናል ነው። 🏖 ለአስተያየት☞ @AbuHiba1 ወይም☞ @Ibrohalka_botይጠቀሙ!!
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel 𝙞𝙗𝙧𝙖𝙝𝙞𝙢 𝙝𝙚𝙮𝙧𝙚𝙙𝙞𝙣 𝙘𝙝𝙖𝙣𝙣𝙚𝙡
Channel 𝙞𝙗𝙧𝙖𝙝𝙞𝙢 𝙝𝙚𝙮𝙧𝙚𝙙𝙞𝙣 𝙘𝙝𝙖𝙣𝙣𝙚𝙡 (@ibrahim_furii) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 105 subscribers, ranking 5 629 in the Religion & Spirituality category and 2 258 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 105 subscribers.
According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -83 over the last 30 days and by 6 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 19.74%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.30% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 2 982 views. Within the first day, a publication typically gains 1 102 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 45.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የቻናሉ ትኩረትና ዓላማ: –
√ ቁርዓንን በማየት(በነዘር)መቅራት ለማይችሉ
እገዛና ድጋፍ ማድረግ።
እንዲሁም በተጨማሪ በኡስታዝ ኢብራሒም የሚሰጡ:–
√ የተጅዊድ
√ የቁርአን ሐለቃ
√ እና የተለያዩ ደርሶች የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
🏖 ለአስተያየት☞ @AbuHiba1
ወይም☞ @Ibrohalka_botይጠቀሙ!!”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | +3 | |||
| 07 September | +6 | |||
| 06 September | +18 | |||
| 05 September | +1 | |||
| 04 September | 0 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | +6 |
| 2 | የመርከዝ ኢብኑ አባስ የ2018 ተመራቂ ተማሪዎች የሽኝት ፕሮግራም
http://t.me/ibrahim_furii | 1 145 |
| 3 | የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት
🎓الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات
የመርከዝ ኢብን አባስ የቁርአን ሂፍዝ ማዕከል ተመራቂ ተማሪዎቻችን፤
ይህንን ፅሁፍ የምጽፍላችሁ በእናንተና ባስመዘገባችሁት ውጤት ልቤ በኩራትና በደስታ ተሞልቶ ነው።
ለሁለት ዓመታት ያህል በነበረው የቁርአንና የእውቀት ጉዞ ላይ ቆይታችሁን አጠናቃችሁ ለዚህ ታላቅ ማዕረግ የበቃችሁ 120 ተማሪዎቻችን፣ እንኳን ለዚህ አበቃችሁ! እንኳን ደስ አላችሁ!
በዛሬው ዕለት የቁርአን ምርቃት ፕሮግራማችን በዚህ መልኩ ደምቆ፣ አምሮና ተውቦ በመጠናቀቁ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ በያላችሁበት ቦታ ሁሉ ይጠብቃችሁ፤ ዲኑንና ኡማውን በቅንነት የምታገለግሉ ያድርጋችሁ።
በቀጣይ የሕይወት ዘመናችሁ ሁሉ በደረሳችሁበት ቦታ የሸሪዓን እውቀት በመቅሰም የምትተጉ፣ የሰለፎችን መልካም ጎዳናና መንገድ የምትከተሉ ያድርጋችሁ፤ ሁልጊዜም ዱዓችን ከእናንተው ጋር ነው።
አብሮ በመኖር፣ አብሮ በመብላትና በመጠጣት ያሳለፍነውን የወንድማማችነት ጊዜ ስናስታውስ መለያየቱ ቢከብድም፣ ኢንሻ አላህ ወደፊትም በኸር ሥራዎች ላይ አብረን እንደምንቀጥል ሙሉ ተስፋ አለን። አላህ መልካሙን ሁሉ ይግጠማችሁ።
ለአላህ ብዬ እጅግ አድርጌ እወዳችኋለሁ
t.me/ibrahim_furii | 1 696 |
| 4 | በተሸሁድ ጊዜ ወደ አመልካች ጣት መመልከት ከሱና ነው።
የአላህ መልእክተኛ ﷺለተሸሁድ በሚቀመጡበት ጊዜ
የግራ እጃቸውን በግራ ጭናቸው ላይ ያደርጉ ነበር።
በአመልካች ጣታቸው ይጠቁሙ ነበር።
እይታቸውም ከሚያመልከቱበት ጣታቸው አያልፍም ነበር።
(ሶሒሕ አል-ነሳኢ)
t.me/ibrahim_furii | 1 750 |
| 5 | ለደስተኛ ህይወት አምስት ወርቃማ ምክሮች
~
*በራስህ ተማመን፦ በውስጥህ ላለው ማንነትና ችሎታ ቦታ ስጥ።
*መልካም ሰው ሁን፦ መልካም ማድረግ ለሌሎች ብቻ ሳይሆን ለራስህም ሰላም ይሰጣል።
*ሁልጊዜ ይቅር በል፦ ይቅርታ ማድረግ ከበደል ይልቅ ነፃነትን መምረጥ ነው።
*ቀና አስተሳሰብ ይኑርህ፦ በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ በጎውን መንገድ ለመመልከት ሞክር።
*ማንንም አትጎዳ፦ በንግግርህም ሆነ በተግባርህ የሌሎችን ሰላም አታደፍርስ።
t.me/ibrahim_furii | 2 318 |
| 6 | ለሰዎች ወሬ ጆሮ አትስጥ!
~
ነፍሳት ሁልጊዜ የሚከበቡትና ጥቃት የሚያደርሱት የሚያበሩትን መብራቶች ብቻ ነው። አንተም የምታበራና ስኬታማ ሰው ስለሆንክ የሰዎች ወሬ አይክበድህ፤ መንገደህን ቀጥል!
t.me/ibrahim_furii | 1 984 |
| 7 | ሐራም የሆኑ ግንኙነቶች
«ጊዜያዊ ደስታ…. ዘላቂ ጸጸት።» | 2 437 |
| 8 | አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
| [ مركز ابن عباس لتحفيظ القرآن الكريم والتربية والإسلامية ]|
📣 ታላቅ የምረቃ ጥሪ 📢
መርከዝ ኢብነ ዓባስ የቁርዓን ሂፍዝና ኢስላማዊ ተርቢያ ማእከል ለሁለት ዓመት ቁርዓን በመሀፈዝ እና መሰረታዊ የሆኑ ኢስላማዊ እውቀቶችን በመቅሰም የቆዩ ብርቅዬ ልጆቹን እሁድ ጳጉሜ 1/13/2012 ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ አየርጤና በሚገኘው አንተነህ አዳራሽ ውስጥ ያስመርቃ።
📮ማሳሰቢያ:–ለሴቶች የተዘጋጀ ቦታ አለን።
🗓በዕለቱ ከሚቀርቡ ፕሮግራሞች በጥቂቱ:–
🌿በአይነቱ ለየት ያለና አምስተኛ ጊዜ
ልዩ ሽልማት የሚያስገኝ የቁርኣን
ውድድር
🌿በቁርዓን ላይ አስደናቂ ትዕይንቶች
🌿አስደማሚ የሆነ የድምፅ ውድድር
🌿ነድዋዎች እና ሌሎችም ውብ የሆኑ
ምርጥ ምርጥ ፕሮግራሞች አሉን………
እሁድን ከእኛ ጋር ያሳልፉ አይደለም መቅረት ማርፈድ ያስቆጫል።
♻️ልብ ይበሉ
የመግቢያ ካርዱ የሚያገኙት ታች በተቀመጡት
ስልክ ቁጥሮች ላይ በመደወል ነው።
0910192594
https://t.me/merkaz_ibnuAbas | 2 162 |
| 9 | መወድሰ ቁጥብያ
~
የቀደሙት ሰለፎች ያስተላለፉትን ትምህርት እንዲሁም የሶሃባዎችን ታላቅ ክብርና ማዕረግ የሚሸረሽሩ የአስተሳሰብ አዝማሚያዎችን ማስፋፋት ለኡማው ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል፤ በመሆኑም ጥንቁቅና አርቆ አሳቢ የሆኑ የሱና ዑለማዎች ባሉበት ሁኔታ የዚህ አይነት የተሳሳቱ አመለካከቶችን ማስተዋወቅና መደገፍ ተገቢ አይደለም።»
t.me/ibrahim_furii | 2 123 |
| 10 | እንደሚታወቀው በትናንትናው እለት በመርከዛችን 22 ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ቁርአንን ሀፍዘው አጠናቀዋል።
ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ተማሪ ተራው ደርሶ የሱረቱል በቀራህን የመጨረሻ አንቀጽ እያነበበ ሂፍዙን ሲያጠናቅቅ፣ ሲገለገልበት የነበረው የቁርአን ሽፋን ላይ ይህችን የቁርኣን አንቀፅ አስተዋልኩ፦
(إِنَّهُ مَن يَتَّقِ وَيَصْبِرْ فَإِنَّ اللَّهَ لَا يُضِيعُ أَجْرَ الْمُحْسِنِينَ)
"እነሆ፤ አላህን የሚፈራና የሚታገስ፤ አላህ የበጎ አድራጊዎችን ምንዳ በፍጹም ውድቅ አያደርግም።"
ቁርአን የማህፈዝ ጉዞ በውጣ ውረድና በትግል የተሞላ ቢሆንም፣ ይህ ተማሪ ሽፋን ላይ ባሰፈራት በዚህች አንቀጽ ጥንካሬ እያገኘ ለዚህ ታላቅ ደረጃ በቅቷል።
በማንኛውም የበጎ ስራ ጉዞ ላይ ሲደክመንና ተስፋ ልንቆርጥ ስንል ይህችን የአላህ ቃል እናስታውስ። በፅናትና በትዕግስት ከተጓዝን፣ አላህ ድካማችንን ከንቱ አያደርገውም።
አላህ ለተማሪዎቻችን በቁርአን የመመራት፤ እኛንም በበጎ መንገድ ላይ ፅናቱን ይስጠን!🤲
http://t.me/ibrahim_furii | 2 951 |
| 11 | 🎉 እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉
الحمد لله رب العالمين 🤲
ለአላህ ምስጋና ይገባውና፣ በዛሬው እለት በመርከዝ ኢብኑ አባስ በአንድ ቀን ሃያ ሁለት (22) ተማሪዎች የቁርአን ሂፍዛቸውን በአላህ እገዛ ሙሉ በሙሉ አጠናቀዋል።
አላህ ቁርኣንን በልቦቻቸው ውስጥ እንዲያጸናላቸው፣ ወደፊትም በክለሳቸው (በሙራጃዓው) ላይ ጠንክረው የሚሰሩና የሚተጉ እንዲያደርጋቸው ዱዓችን ነው! | 3 192 |
| 12 | ምናባዊ ዓለም... እውነተኛ ወንጀል!
~
ከስክሪን በስተጀርባ በምናያቸውና በምናደርጋቸው ነገሮች አንሸወድ! የሶሻል ሚዲያ ድረ-ገጾችና መተግበሪያዎች ምናባዊ ቢሆኑም፡ የምንሰራቸው ወንጀሎች ግን እውነተኛና ዋጋ የሚያስከፍሉ ናቸው።
🛑ወዳጄ ሆይ... አላህን ፍራ፤ ተጠንቀቅ!
t.me/ibrahim_furii | 2 504 |
| 13 | ሞትን አብዝቶ ማስታወስ እጅግ የተወደደ (ሙስተሐብ) የሆነ ተግባርና የነቢዩﷺ ምክር ነው፤ ዓላማውም ልብን ማነቃቃትና ወደ አላህ (ሱ.ወ) ያለንን ቅርበት ማሳደግ ነው። | 2 528 |
| 14 | «እዚህ ቦታ ሁሉም ነገር ያበቃል ሀብት፣ ዝና እና ሥልጣን፤ የሚቀረው መልካም ሥራ ብቻ ነው። የታሪካችን ማጠቃለያም እዚሁ ላይ ነው ።🍂»
http://t.me/ibrahim_furii | 2 895 |
| 15 | ወንድሙን በስህተቱ(በጥፋቱ) የናቀ ወይም የነቀፈ ሰው ያንን ነገር ሳይፈፅመው አይሞትም።
ጌታዬ ሆይ! በ ሰዎች ጉዳይ እራሴን ( በማማት፣በመተች፣በመገምገም) ከማልፋት ጠብቀኝ፤ እራስን ማስተካከልና ማነፅ ላይ ብቻ አበርታኝ።
http://t.me/ibrahim_furii | 2 799 |
| 16 | 🍒. የአንድ አፍታ ስሜት፤ የዘላለም ጸጸት! 🍒
ስንትና ስንት ወጣቶች (ወንዶችም ሆኑ ሴቶች) በግል መልእክት (Inbox) የሚደረጉ ወሬዎች ዝም ብለው የሚያልፉ ተራ ቃላትና ለጊዜያዊ መዝናኛ ብቻ ይመስሏቸዋል።
በማህበራዊ ሚዲያ በሚላኩ ምስጢራዊ መልእክቶች ውስጥ የሚጀመሩ ጨዋታዎች መጀመሪያቸው ቀለል ያሉ ይመስላሉ። ነገር ግን በጊዜ ሂደት ልብን በሐራም ፍቅር እያጠመዱ፣ የነፍስን ሰላም እያደፈረሱ ከአላህ ጋር የነበረን ጥልቅ ግንኙነትና የኢባዳ ጥካሬንና ጣዕምን እያጠፉ ይሄዳሉ።
ድብቅ ንግግሮችና ከአጅነቢ ጋር የሚደረጉ የጽሑፍ ልውውጦች ተራ ስህተት አይደሉም፤ ይልቁንም ወንጀልን ወንጀል የሚወልድበት፣ የልብን ብርሃን የሚያጠፋበትና ሰውን ወደ አደገኛ ጥፋት የሚስብ የሸይጧን የመጀመሪያ መረብ ናቸው።
t.me/ibrahim_furii | 2 331 |
| 17 | በሕይወትህ ውስጥ የሚፈጠረው እያንዳንዱ መዘግየት ከበስተጀርባው በውስጡ የተሸሸገ የራሱ የሆነ ስውር ሚስጥር አለው።ቀስ ብለውና መሠረታቸውን ጠብቀው የሚገነቡ ነገሮች የጸኑና ውበታቸውም ዘላቂ ነው። 🏛️
t.me/ibrahim_furii | 2 292 |
| 18 | ስፖርት እና እምነት ከሰሞኑ የቦክስ ውድድሮች በስተጀርባ ያለው እውነት
~
ስፖርት እና እምነት ሙሉ በሙሉ የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ከሰሞኑ በቲክቶክ እና በሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የሚሰራጩ የቦክስ ውድድሮች የብዙዎችን ትኩረት ሲስቡ እና ሲያነጋግሩ ይስተዋላል። ነገር ግን እነዚህን ውድድሮች ከእስልምና እሴቶችና መርሆች ጋር ማያያዝ ተገቢ አይደለም።
በመሰረቱ የቦክስ ውድድር የፊት ገጽታን መምታት እና የሰውነት ክፍሎችን ማጉደል ወይም መስበር ስላለው፣ በርካታ ኡለማዎች ዘንድ የተከለከለ (ሀራም) የስፖርት አይነት እንደሆነ ብዙዎች ሲገልጹት ቆይተዋል።
በውድድሩ ወቅት ተወዳዳሪዎች «አላህ ነው የሚረዳኝ» እና መሰል ሃይማኖታዊ ቃላትን ከአንደበታቸው ስለሚያወጡ ብቻ ውድድሩን የእምነት አካል ወይም ሃይማኖታዊ ሊያስመስለው አይችልም።
ተወዳዳሪዎቹ የራሳቸውን ጥቅም እና ዝና ለማሳደግ የሚጠቀሙበትን አካሄድ፣ በጭፍን በመደገፍ ሃይማኖታዊ ሽፋን መስጠት አይገባም።
ባጭሩ፤ የቦክስ ውድድር በባህሪው የአካል ጉዳት የሚያስከትል በመሆኑ ከእስልምና መርሆች ጋር የሚጋጭ እንጂ ከእምነት ጋር የሚያያዝ ተግባር አይደለም።
t.me/ibrahim_furii | 3 259 |
| 19 | የልብ እረፍት
ሁለት ሰከንድ "ኢስቲግፋር" በማለት የምታሳልፋትን አንዲት ቅጽበት በከንቱ አትቁጠራት። ከዚያች አጭር ቅጽበት ስንት የእዝነትና የሲሳይ በሮች እንደሚከፈቱልህ፣ ስንት የመከራና የፈተና ጭንቀቶችህ እንደሚገፈፉ አታውቅም።
t.me/ibrahim_furii | 2 886 |
| 20 | ......
ከረመዳን እስከ ረመዳን ቁርኣንን እንደምትተወው ሁሉ፣ ሙሉ አንድ ዓመት ሙሉ ከሙዚቃና ከዘፈኖች ርቀህ ታውቃለህን?
መልስህ "አልራቅሁም" የሚል ከሆነ፣ የዑለማዎችን (የእውቀት ባለቤቶች) ንግግር ትርጉም ተረድተህ ይሆናል፦ "የቁርኣን ፍቅርና የሙዚቃ/የዘፈን ፍቅር በአንድ አማኝ ልብ ውስጥ በፍፁም አይሰበሰቡም"።
t.me/ibrahim_furii | 3 047 |
