en
Feedback
ዳሩል ሀዲስ ኢንስቲትዩት Darul Hadith institute

ዳሩል ሀዲስ ኢንስቲትዩት Darul Hadith institute

Open in Telegram

ዳሩል ሀዲስ የዓረብኛ ቋንቋ እና የሸሪዓዊ ትምህርቶች ኢንስቲትዩት ✔ ኢስላማዊ ቤተ መፃህፍት ✔ የቁርአን ሂፍዝ ፕሮግራም ✔ የአረብኛ ቋንቋ እና ሸሪዓዊ ትምህርቶች معهد دار الحديث لتعليم اللغة العربية والعلوم الشرعية (أديس أبابا – تأسيس 1436 هے) «من يرد الله به خيرا يفقهه في الدين» 👍ዳሩል ሀዲስ

Show more
2 742
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-2630 days
Posts Archive
📢إعلان محاضرة لفضيلة الدكتور الشيخ إبراهيم بن رافع الغامدي - للنساء، بعنوان ▫️"عشرون عائقا في طلب العلم " ▫️في مركز ابن مسعود الإسلامي ▫️الوقت: ٥ صباحا بتوقيت إثيوبيا https://t.me/darulhadis18

📢አጭር ኮርስ ሴቶች ለሴቶች ➤ሰኞና ሀሙስ ከ5:00-6:00 ➪የሚሰጠው ትምህርት ➤ሴቶች በኢስላም ያላቸው ደረጃና ያለባቸው ሀላፊነት "የልእልናሽ ጋሻ" በሸይኽ በክር አቡ ዘይድ የ ተጻፈውና በአጭሩ የተዘጋጀው "ተልኺስ ኪታብ ሒራሰቱል ፈዲላ" ➪ነገ ሀሙስ ህዳር 27 ይጀምራል! የኪታቡ ኮፒ እዛው ይገኛል ➪ቦታ:18 በሚገኘው መርከዝ ኢብኑ መስዑድ ⭐️መልእክቱን ለእህቶች በማድረስ የዳእዋ ሀላፊነታችንን እንወጣ! https://t.me/darulhadis18

📣አስደሳች ዜና ለእውቀት ፈላጊ እህቶች ☑️ዘወትር ከሰኞ እስከ ሀሙስ ከጠዋቱ 4:00-6:00 🌴የሚሰጡ ትምህርቶች ▫️አቂዳ(ሃኢያ ኢብን አቢ ዳውድ) ▫️ኡምደቱል አህካም ▫️ተፍሲር ▫️ተርቢያ 🌴ተማሪዋ ማሟላት ያለባት መስፈርት 1.ቁርአንን በነዘር የቀራች 2.መሰረታዊ የዲን ኪታቦችን የተማረች 3.አረብኛ ማንበብና መረዳት የምትችል 4.የመርከዙን ህግና ደንብ የምታከብር ✅ምዝገባ ከነገ ሰኞ ህዳር 17 ጀምሮ ✅ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ 18 በሚገኘው መርከዝ ✅ለበለጠ መረጃ 0904366666 ይደውሉ። "አላህ መልካም ለሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል” ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር https://t.me/darulhadis18

📢የማይቀርበት ልዩ ፕሮግራም ለሴቶች ➪በቤተሰብዎ፣ በግዜዎ፣ በልጅዋ፣ በስራዎ በአጠቃላይ በህይወትዎ በረካን (ረድዔትን) አጥተዋል? ዘመኑ "በረካ የመነመነበት ዘመን ነው!" የሚለው ስሞታ ዘውትር በጆሮዎ ያቃጭላል? ➪እነሆ! ለዚህ የዘመኑ ጠንቅ ለሆነው የበረካ መነፈግ መፍትሄ የሚሆን አስተማሪ ፕሮግራም ይዘን ቀርበናል። በእለቱ ➤የበረካ ምንነት፣ በረካ ከየት ይገኛል ከማንስ ይፈለጋል? በረካን ያለ ቦታው መፈለግ ወደ ሺርክ የሚያዳርስ አደገኛ ወንጀል ነውን? የሚሉ ከበረካ ጋር የተቆራኙ ትክክለኛ ቁርኣናዊና ነብያዊ አስተምሮዎች ይዳሰሳሉ። ➤የበረካ አስፈላጊነት በህይወትዎ ምን ያህል ድርሻ እንዳለውም ይረዳሉ። ▪️ታዲያ ከፕሮግራሙ ይቀራሉ?  በፍፁም! ➤እሁድ ህዳር 9፣2016 ➤ከጠዋቱ 3:00-:6:00 ➤18 በሚገኘው ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ▪️የፕሮግራሙ ታዳሚ በመሆን፣ እህቶችንም በመጋበዝ የእውቀትና የምንዳ ተካፋይ ይሁኑ! https://t.me/darulhadis18

🪷መልካም እድል🪷 🍃ከጠዋቱ 1:00-2:30 ቁርአን ለመቅራት ለምትፈልጉ ሴቶች ▪️ትምህርቱ  ሰኞ ጥቅምት 12፣2016  የሚጀመር ይሆናል። ▪️ለበለጠ መረጃ 0904346666/ 0967671891 ይደውሉ ▪️አድራሻ: 18 አካባቢ በሚገኘው መርከዝ ኢብኑ መስዑድ 📬 እህቶች ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ መልእክቱን ሼር እናድርገው!                                   🪷🍃🪷🍃🪷🍃 https://t.me/darulhadis18

🪸ወርሀዊ የሙሀደራ ግብዣ ለሴቶች🪸 እንዳያመልጥሽ❗️ ☀️የአካላችን ንጉስ ስለሆነው የምንማማርበት ልዩ መድረክ 🍃እሁድ ጥቅምት 4፣2016 🍃ከጠዋቱ 3:00 - 6:30 🍃18 በሚገኘው ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ⚠️መልእክቱን ሼር በማድረግ ዳእዋን ተደራሽ ያድርጉ https://t.me/darulhadis18

ማስታወቂያ ለኢብኑ መስዑድ የ18 እና የቤተል ተማሪዎች በሙሉ ጁሙኣ እና ቅዳሜ መንገድ ዝግ ስለሚሆን በእለቱ ሁለቱም መድረሳ ዝግ ይሆናል።

የመርከዝ ፕሮጀክት... የትብብር ፍሬ! ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር፤ ከ2001 አብነት አካባቢ ከሁለት በጎ ፈቃደኛ ወንድማማቾች ባገኘው ትንሽ ቤት ውስጥ ኢስላማዊ ቤተ መፃህፍት፣ ነሲሓ ኢስላማዊ
+2
የመርከዝ ፕሮጀክት... የትብብር ፍሬ! ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር፤ ከ2001 አብነት አካባቢ ከሁለት በጎ ፈቃደኛ ወንድማማቾች ባገኘው ትንሽ ቤት ውስጥ ኢስላማዊ ቤተ መፃህፍት፣ ነሲሓ ኢስላማዊ ስቱዲዮ፣ ዳሩል ሐዲስ የሰርተፊኬትና የዲፕሎማ ፕሮግራሞች፣ መስማት የተሳናቸው ወገኖችን ጨምሮ በርካታ የትምህርት ፕሮግራሞችን እውን በማድረግ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። ሆኖም በጠባብ ቦታ ላይ የተጀመሩትን እንቅስቃሴዎች ማሳለጥ ይችል ዘንድ፤ በተለምዶ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ቦታ ለመግዛትና ቋሚ የመርከዝ ህንፃ ለመገንባት ፕሮጀክት ነድፎ ህዝበ ሙስሊሙን በማስተባበር ቦታ ገዝቶ ግንባታ ማከናወን ጀመረ። ከዚያ በፊት በአብዛኛው መሰል ፕሮጀክቶች የሚፈፀሙት በውጭ ድጋፍ ስለነበር የመርከዙ እቅድ ለአንዳንዶች የማይሳካ ህልም መስሏቸውም ነበር። ሆኖም በአላህ ፈቃድ በአጭር ግዜ ውስጥ ውጥኑ የብዙዎችን ቀልብ በመሳብ የአስተሳሰብ ለውጥ ከማምጣቱ ባሻገር በራስ አቅም ዳዕዋን መደገፍ እንደሚቻል ህያው ማሳያ ሆኖ ነበር። እጅግ አስደናቂ በሆነ ተነሳሽነትና የአላማ አንድነት ከሴት ተማሪዎች እሰከ ባለሀብቶች ባደረጉት ድጋፍ ሁለት ወለል ማጠናቀቅ ተችሏል። በወቅቱ የዳዕዋ ተቋማት ላይ የተጋረጡ አደጋዎች፣ ጫናዎችና እጅግ ፈታኝ ሂደቶች ስለነበሩ በትዕግስትና በጥበብ ማለፍን ይጠይቅ ነበር። ስለሆነም በከፊል ከተጠናቀቀው ግንባታ ከፊሉን በማከራየት በአብነት ለሚገኘው መርከዝ ቋሚ የዳዕዋ ድጋፍ ማግኘት ተችሏል። የተወሰኑ ወለሎች ቢቀሩትም ግንባታውን ከፍ ወዳለ ደረጃ በማሸጋገርና የተገነቡ ወለሎችን በዘመናዊ ሁኔታ በማጠናቀቅ መስጅድ፣ የሙሐደራትና ኮርሶች አዳራሽ፣ ቤተ መፃህፍት በማሟላት የታህፊዝና የሴቶች ማዕሐድ ከጥር 1/2008 ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ሲሰጥ ቆይቷል። በሁለቱም መርከዞች በሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ተምረዋል። ይህ መርከዝ ከምስረታው ጀምሮ ለሴቶች ከፍተኛ ትኩረት የሰጡ የትምህርት የተርቢያና የስልጠና መርሐ ግብሮችን ተፈፃሚ አድርጓል። አሁንም በአላህ ፀጋና በረከት ቀሪውን ግንባታ በማድረግ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ በመጠናቀቁ በቀጣይ ኢስላማዊ ኮሌጅን ጨምሮ በርካታ ፕሮግራሞችን ማካሄድ የሚያስችል ሆኗል። እሁድ መስከረም 13 /2016 ረፋዱ ላይ ለፕሮጀክቱ እውን መሆን አሻራቸውን ያኖሩ ሁሉ በመርከዙ በመገኘት የልፋታቸውን መልካም ፍሬ የሚያዩበት፣ ለዋለላቸው ፀጋ አላህን የሚያመሰግኑበት ቀን ነው። وَمَا بِكُم مِّن نِّعۡمَةࣲ فَمِنَ ٱللَّهِ (ማንኛውም በእናንተ ላይ ያለው ጸጋ ከአላህ ነው) አል-ነሕል: 53 የብዙ ጀግኖች አሻራ አርፎበት ለስኬት የበቃው ይህ ፕሮጀክት፤ ለቀጣይ የዳዕዋ ጉዟችንና ወኔ ለሚጠይቁ ፕሮጀክቶቻችን ተግባራዊ ምሳሌ ስለሆነ ለቀጣይ ስኬቶች እንዘጋጅ። አልሐምዱሊላህ! ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር መስከረም 7/2016 ____ 🕌 ibnu Masoud islamic Center @merkezuna

«አል‐ዐቂደቱ አል‐ዋሲጢያህ» የኪታብ ቂራአት ማሟያ በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ 📌 ከእሮብ መስከረም 2/2016 ጀምሮ 4:00 ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት የሚቆይ ትምህርት 🔖 ባሳለፍነው ክረምት በነሲሓ የ
«አል‐ዐቂደቱ አል‐ዋሲጢያህ» የኪታብ ቂራአት ማሟያ በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ 📌 ከእሮብ መስከረም 2/2016 ጀምሮ  4:00 ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት የሚቆይ ትምህርት 🔖 ባሳለፍነው ክረምት በነሲሓ የዒልም ቅፍለት ኮርስ ቁ.10 መካሄዱ ይታወሳል።  ይህ ደርስ በወቅቱ ያልተጠናቀቀውን የ አል‐ዐቂደቱ አል‐ዋሲጢያህ ማብራሪያ ለማጠናቀቅ ያለመ ነው። አላህ ይጠብቀው፤ ለኛም የዲን ዕውቀትና ግንዛቤን ይለግሰን። ቦታ:– 18 አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር (መርከዝ) ____ t.me/merkezuna

🌸ቅዳሜ ተጋብዛችኋል🌸 የክረምት ትምህርት መዝጊያ የሙሀደራ ግብዣ ለሴቶች ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር በክረምቱ በዋናው መርከዙና በቅርንጫፎቹ ሲሰጥ የቆየውን ትምህርት መጠናቀቁን ምክኒያት በማድረግ የተዘ ጋጀ ልዩ መድረክ። ▪️የሚዳሰሱ ርእሶች ⭐️የተውሂድ አሳሳቢነትና ፍሬዎቹ ⭐️የኢስላም ውበት 🗓 የፊታችን ቅዳሜ ጿግሜ 4፣2015 ⏱ ከ3:00-6:30 🕌18 አካባቢ በሚገኘው መርከዝ ⚠️መልእክቱን ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን! https://t.me/darulhadis18

📣በምዝገባ ላይ(ለሴቶች) "አላህ መልካም ለሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል” ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር አዲስ አበባ 18 በሚገኘው መርከዝና በቤተል ቅርንጫፍ ለ2016 የትምህርት ዘመን የዲን ትምህርቶችን ለመስጠት ምዝገባ ጀምሯል። የሚሰጡ ትምህርቶች 📖 ቁርአን 🔅 በነዘር (ለጀማሪዎች) 🔅በተጅዊድ 🔅በሂፍዝ 📚እንዲሁም የተለያዩ ኪታቦች ቂራአት 🕥የሰአት አማራጭ ▪️ጠዋት፣ከሰአት፣ከአስር በኋላ ▪️ለተማሪና ለሰራተኛ ቅዳሜ ጠዋት ወይም ከሰአት ለበለጠ መረጃ፦ ለ18☎️ 0904 36 66 66 ወይም 0967 67 18 91 ለቤተል☎️0911062499/ 0913840323 ወይም 0911692377 ይደውሉ። ⚠️መልእክቱን ሼር በማድረግ የበኩላችንን አስተዋጽዖ እናድርግ።

በምዝገባ ላይ(ለሴቶች) ለ2016 የትምህርት ዘመን የቁርአንና ሌሎች የዲን ትምህርቶችን በደረጃዎ የሚመጥንዎትን በሚመቾት ሰአት

“አላህ መልካም ለሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል” 📌 ታላቅ የምስራች ለኢስላማዊ እውቀት ፈላጊ ሴቶች በሙሉ በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ዳሩል ሀዲስ የሸሪዓ ትምህርቶችና የዐረብኛ ቋንቋ መማሪያ
አላህ መልካም ለሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል” 📌 ታላቅ የምስራች ለኢስላማዊ እውቀት ፈላጊ ሴቶች በሙሉ በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ዳሩል ሀዲስ የሸሪዓ ትምህርቶችና የዐረብኛ ቋንቋ መማሪያ ኢንስቲትዩት  እድሜያቸው  ከ15 አመት በላይ ለሆኑ ሴቶች የዲን ትምህርት ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቆ ምዝገባ መጀመሩን ሲገልፅ በታላቅ ደስታ ነው 1⃣ቁርአን (ከሰኞ -ጁሙኣ) ▪️የቁርአን ሂፍዝ(ሙሉ ቀን)* ▪️ቁርአንን በተጅዊድ (ከ3:00-6:30)* ▪️ለጀማሪዎች የቁርአን ንባብ * ጠዋት ከ3:00-6:30 ከሰአት ከ8:00-10:00 አስር    ከ10:00-12:00 *ከመሰረታዊ የዲን ትምህርት ጋር 2⃣የኪታብ ቂረኣ እና አረብኛ ት/ት (3:00-6:30) ▪️ የሁለት አመት የሰርተፊኬት ፕሮግራም(ከሰኞ-ጁሙኣ) ▪️በሳምንት ቅዳሜ ብቻ 🗓 የምዝገባ ጊዜ፦ ከሰኞ እስከ ጁሙዓ ከነሐሴ15- 30/2015 ⏱የምዝገባ ሰአት ከ3:00_7:00 🕌 የምዝገባ ቦታ፦ 18 አካባቢ በሚገኘው መርከዝ ☎️ ለበለጠ መረጃ፦ በስልክ ቁጥር  0904 36 66 66 ወይም 0967 67 18 91 ይደውሉ    ⚠️መልእክቱን ሼር በማድረግ ከአጅሩ እንቋደስ! ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር @darulhadis18

❓ዲን እየተማሩ ነውን? ኢስላም ከማንኛውም ነገር በፊት ዕውቀትን በመገብየት ላይ አደራ ይላል፡፡ ምክንቱም የምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ዕውቀትን መሰረት ያላደረጉ ከሆነ አላዋቂ ሳሚ ... እንደሚባለው ብሂል ከልማቱ የምንዘፈቅበት አዘቅቱ ያመዝናል፡፡  አንዳንዴም በኛ ሳይገደብ የኛው የጥፋት ረመጥ ይቀጥልና ሌሎችን እኛ የሰመጥንበት አዘቅጥ ውስጥ እንዲዋኙ የጥፋት ጀልባ እና መቅዘፊያ እንድንሆን ያደርገናል፡፡          ቁርአን ስለ እውቀት ፋይዳዎችና ስለ አዋቂዎች ደረጃ ብዙ ይላል። ዓዋቂው አምላካችን ስለ እውቀት ባለቤቶች ከፍ ያለ ደረጃ ዓዋቂዎች በሚገነዘቡት መልኩ እንዲህ ይላል፡- "يَرْفَعِ اللَّهُ الَّذِينَ آمَنُوا مِنكُمْ وَالَّذِينَ أُوتُوا الْعِلْمَ دَرَجَاتٍ" [٥٨:١١] «አላህ ከናንተ እነዚያ ያመኑትንና እነዚያ ዕውቀት የተሰጡትን በደረጃ ከፍ ያደርጋል» ሙጃደላህ፡11                             ታላቁ ሶሃብይና የቁርአን ተፍሲር ዓዋቂ ዓብደላህ ኢብኑ ዓባስ እንዲህ ሲል የአንቀፁን መልዕክት የሚያጠናክር ንግግር አላቸው «የተማሩ ሰዎች ደረጃ ከተራው ሙዕሚን ሰባት መቶ እጥፍ ይበልጣል፡፡ ከአንዱ ደረጃ ወደ ሌላ ደረጃ ያለው ርቀት የአምስት መቶ ዓመት ርቀት ይሆናል» በሌላ የቁርአን አንቀፅ አላህ እንዲህ ይላል፡- "إِنَّمَا يَخْشَى اللَّهَ مِنْ عِبَادِهِ الْعُلَمَاءُ" [٣٥:٢٨] «አላህን ከባሮቹ ውስጥ የሚፈሩት ዐዋቂዎቹ ብቻ ናቸው»  ፋጢር፡28 መልዕክተኛው (ﷺ)  እንዲህ አሉ፤ «ዕውቀትን ቅሰሙ አላህን የምትፈሩት ባወቃችሁት ልክ ነውና» አዎን! የማያውቁትን አካል እንዴት ተገቢውን ፍራቻ ይፈሩታል?! አላህ መልዕክተኛው (ﷺ) እንዲጨምርላቸው እንዲጠይቁት ያዘዘው ብቸኛ ነገር ዕውቀት ነው! ከየት አመጣኸው ትይኝ ይሆናልና ማስረጃውን :- "وَقُل رَّبِّ زِدْنِي عِلْمًا " «ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ጨምርልኝ በል» 20፡114 የትኛውም የዕውቀት ደረጃ ላይ ብንገኝ በአላህ ከታገዝንና ጥረት ካደረግን ብዙ መሻሻል ይቻላልና አሁኑኑ ጥረት ማድረጉን እንጀምር። አላህ  በኢስላማዊ ዕውቀት ወደተሻለ ደረጃ ከፍ እንል አንድ ያግዘን፤ እውቀትን ያግራልን። ልባችንን በቁርአን ያብራልን። አሚን ! _ @abujunaidposts

📢ነገ ተጋብዛችኋል ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር የታዳጊዎች የአዳሪ የክረምት ኮርስ መዝጊያ ፕሮግራም ⭐️ምክር ለወላጆች በኡስታዝ ሁሴን ዒሳ ⭐️በተማሪዎች የሚቀርቡ ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች 🗓 እሁድ ነሀሴ 14፣2015 ⏰ከጠዋቱ 3:00 🕌18 አካባቢ በሚገኘው መርከዝ https://t.me/darulhadis18

🌐 ترقبوا بمشيئة الله قريبا... دورة ميراث الأنبياء الثالثة في مركز ابن مسعود الإسلامي __ @merkezuna
🌐 ترقبوا بمشيئة الله قريبا... دورة ميراث الأنبياء الثالثة في مركز ابن مسعود الإسلامي __ @merkezuna

አስደሳች ዜና ለቁርኣን ሒፍዝ ፈላጊዎች! ኢስላማዊ ዕውቀትን ለሁሉም ማህበረሰብ ለማዳረስ ለረጅም ዓመታት ጥረት በማድረግ ላይ የሚገኘው ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር እነሆ ለ2016 የበጋ የተመላላሽ
አስደሳች ዜና ለቁርኣን ሒፍዝ ፈላጊዎች! ኢስላማዊ ዕውቀትን ለሁሉም ማህበረሰብ ለማዳረስ ለረጅም ዓመታት ጥረት በማድረግ ላይ የሚገኘው ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር እነሆ ለ2016 የበጋ የተመላላሽ ትምህርት ፕሮግራም ይዞላችሁ ቀርቧል። ትምህርቱ የተዘጋጀው ለማን ነው? ዕድሜያቸው ከ12 ዓመት በላይ ላሉ ታዳጊ ወንዶች የትምህርቱ ይዘትስ? ቁርኣን ሒፍዝ እና መሰረታዊ የዲን ትምህርት የትምህርት ሰዓቱስ? ከጥዋቱ 2:00 – መግሪብ መቼ ይጀምራል? መስከረም 2016 የምዝገባ ጊዜ : ከነሀሴ 5 – 15 2015 ወላጆች ልጆችዎን በጊዜ በማስመዝገብ ኃላፊነትዎን ይወጡ! የረጅም ጊዜ የማስተማር ልምድ ባላቸው ኡስታዞች ታግዘን ልጆችዎን በኢስላማዊ ዕውቀትና ተርቢያ አናንፃለን! ለበለጠ መረጃ: 09 12 02 31 90 / 09 46 46 68 46 የምዝገባ ቦታ: 18 አካባቢ በሚገኘው የመርከዝ ኢብኑ መስዑድ ዋና ቢሮ ________ @Merkezuna

ነሲሓ የዒልም ቅፍለት ኮርስ ቁ.10 ልዩ የክረምት የኪታብ ቂራአት 📌 ከእሮብ ሐምሌ 19/2015 ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ ሐሙስ ከጠዋቱ 3:00 እስከ 6:00 ለተከታታይ አራት ሳምንታት የሚቆይ መ
ነሲሓ የዒልም ቅፍለት ኮርስ ቁ.10 ልዩ የክረምት የኪታብ ቂራአት 📌 ከእሮብ ሐምሌ 19/2015 ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ ሐሙስ ከጠዋቱ 3:00 እስከ 6:00 ለተከታታይ አራት ሳምንታት የሚቆይ መሰረታዊ የዒልም ኮርስ 1‐ «አል‐ዐቂደቱ አል‐ዋሲጢያህ» (የዐቂዳ ትምህርት) — በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ 2‐ «ተስሪፍ አል‐ዒዝዚ» (የዐረብኛ ሶርፍ ትምህርት) — በሸይኽ ሙሐመድ ኢድሪስ ቦታ:– 18 አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ________ t.me/merkezuna

🔖 ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ በ 2002 በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/219 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts