✝SUECSF:-💖Offical
This is Samara University Evangelical Christian Students Fellowship official telegram channel.(EvaSUE) ለእግዚአብሔር ክብር ለቅዱሳንም መታነጽ ለአህዛብም በረከት እንሆን ዘንድ... Contact Us @JFcou @Deggii @ntremnant
Show more199
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-330 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
መልካም አዲስ ዓመት
2016 { ሁለት ሺህ አስራ ስድስት} ዓመተ ምህረት
እግዚአብሔርን በፍጹም #ታማኝነት የምናገለግልበት
#በመለየት #በመመለስ የእግዚአብሔርን ጉብኝት
#የምንጠብቅበት ዓመት ይሁንልን።
A Year of Faithfulness ‼️
Repost from አንድ🌍ደቂቃ🌎ለአንድ🌏ሕዝብ
Photo unavailableShow in Telegram
"አንቺ ኢትዮጵያ እረፍትሽ ይምጣ!
በምድራችን ላይ ጦር እና የጦር ወሬ ሰምተን መደንገጥ ካቆምን ቆየን፡፡ ሞት፣ ውድመት፣ እንባ ተለመዱ ምናልባት የቤታችንን በር ስላንንኳኩ መሰል በሩቅ የእነዚህ ስብራት አድማጭ የሆንን ሰዎች ለመናገር፣ እምቢ ለማለት ደነዘዝን፡፡ ወጣት ያለግዜው ሲሞት፣ እናት ስለልጆቿ ስታነባ፣ ቤተሰብ ሲበተን፣ ሕጻናት ያለ አሳደጊ ሲቀሩ አየን ተመለከተትን ዛሬም ግን ከአዙሪታችን መውጣት አልቻልንም፡፡
ምድራችን በንጹሃን ደም ጨቅይታለች በመበለቶች ዋይታ ፣ በሕጻናት ስቃይ እና ሰቆቃ ተሞልታለች ፡፡ ያለፉትን እረስተን ዛሬም ለሌላ እየተዘጋጀን፡፡ እውን ለምድራችን የእግዚአብሔር ሃሳብ ይሄ ነውን፣ ስለ ምድራችን የሰማነው የምንናፍቀው ተስፋ ይህ ነው? አይመስለኝም፡፡
ዛሬ ሙሉቀን በዜና አውታሮቻ ከ35 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በሚኖርበት የአማራ ሕዝብ ስላለው ግጭት ስንሰማ ውለናል፡፡ ይህ በእጅጉ በእግዚአብሔር ፊት ልጸልይበት እና ልናነባበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ በዚያ ያለ ሕዝብ ከዚህ የተሻለ እና የተለየ ተስፋ አለው፡፡ ሰላም፣ እረፍት፣ ልማት፣ መረጋጋት የሚገባው ሕዝብ በጦርነት ንጹሐን ሕይወታቸውን ሊያጡ ነጋሪት እየተጎሰመ ነው፡፡
እንደ ክርስቲያን ምላሻችን የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ እና የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነት እንዲመጣ አጥብቀን መጸለይ ነው፡፡ ዳግም ዋይታ አይሁን፣ ሞት ይብቃ፣ ሕጻናት ያለአሳዳጊ አይቅሩ፣ ቤተሰብ አይበተን በቃን ለምድራችን ኢትዮጵያ - ለሰሜን፣ ለደቡብ ፣ ለምስራቅ ምዕራብ ሁሉ ሰላም ይሁን፣ ማረፍ ይሁን፡፡
ወንጌል ሊያስመልጠው ሚገባውን ሕዝብ በጦርነት አይጨርሰው፡፡
አንቺ ኢትዮጵያ እረፍትሽ ይምጣ! ሁላችን ስለ አማራ ክልል እንድንጽልይ ይሁን !!
ስለ አማራ ክልል እጸልያለሁ!
#እግዚአብሔር ሆይ ጣልቃ ግባ፤ በቃ በለን!"
©AmaNuGeze
ዛሬ ከሰመራ ዩኒቨርስቲ የተመረቃችሁ የጌታ ውድ ልጆች እንኳን ደስ አላችሁ❤ እግዚአብሔር ስለእናንተ ይመስገን✋.. አንድን የህይወት ምዕራፍ ያስጨረሳችሁ ጌታ ሌላ በምትጀምሩት የህይወት ምዕራፋችሁን ተረክቦ ይምራችሁ✋ በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ❤