en
Feedback
Nebiyu Sirak

Nebiyu Sirak

Open in Telegram

በማለዳ ወግ ... መረጃና ምክረ ሀሳቤን አጋራችኋለሁ ‼

Show more
670
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-830 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
May '26
May '260
in 0 channels
April '26
+1
in 0 channels
Get PRO
March '26
+1
in 0 channels
Get PRO
February '26
+1
in 0 channels
Get PRO
January '260
in 0 channels
Get PRO
December '25
+2
in 0 channels
Get PRO
November '250
in 0 channels
Get PRO
October '25
+3
in 0 channels
Get PRO
September '25
+3
in 0 channels
Get PRO
August '25
+2
in 0 channels
Get PRO
July '25
+3
in 0 channels
Get PRO
June '25
+1
in 0 channels
Get PRO
May '25
+9
in 0 channels
Get PRO
April '25
+2
in 0 channels
Get PRO
March '25
+104
in 0 channels
Get PRO
February '25
+3
in 0 channels
Get PRO
January '25
+3
in 0 channels
Get PRO
December '24
+4
in 0 channels
Get PRO
November '24
+7
in 0 channels
Get PRO
October '24
+3
in 0 channels
Get PRO
September '24
+1
in 0 channels
Get PRO
August '24
+1
in 0 channels
Get PRO
July '24
+2
in 0 channels
Get PRO
June '24
+9
in 0 channels
Get PRO
May '24
+9
in 0 channels
Get PRO
April '24
+4
in 0 channels
Get PRO
March '24
+4
in 0 channels
Get PRO
February '24
+827
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
25 May0
24 May0
23 May0
22 May0
21 May0
20 May0
19 May0
18 May0
17 May0
16 May0
15 May0
14 May0
13 May0
12 May0
11 May0
10 May0
09 May0
08 May0
07 May0
06 May0
05 May0
04 May0
03 May0
02 May0
01 May0
Channel Posts
Audio from Nebiyu Sirak

2
No text...
205
3
በአጠቃላይ የድምጻዊ አስቻለው ፈንቴ የጎንደርን ውብ ባህል በተላበሱ ወዝና ጣዕም ባላቸው በዘመን ተሻጋሪ ጣዕመ ዜማዎች በአፄ ቴዎድሮስ ልደት ቀን መታሰቢያ ተደርገው በአየር ከተለቀቁ ከ40 ሚላዮን በላይ እየታን በማግኘት ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ አርዲ ክብረ ወሰንን የተቆጣጠረ ድምጻዊ ሆኗል ። እጅግ የሚገርመው አስቻለው በዚህ ደረጃ ለእይታ የበቁት ስራዎቹ በማንም የስፖንሰር ያልተደረጉም ። ኢትዮጵያ ውስጥም ቢሆን ምንም አይነት ዝግጅት (ኮንሰርት -*አድርጎ የገንዘብ ጥቅም ላገኘባቸውም። ። አስቻለው ሁሌም እንደሚለው ጥቅም ክብር ኩራቱ የሃገሩን ቱባ ባህል ፣ ታሪኩንና ጀግኖች አርበኞቹ እንዲታወሱ ማድረጉ ከምንም በላይ የውስጥ ከፍ ያለ እርካታ እንደሚሰማው ይናገራል። " እናትዋ ጎንደር " ከተለቀቀ በኋላ በጎንደር ከተማ ፒያሳ በተወዳጁ የእናትዋ ጎንደር ጣዕመ ዜማ ስም አደባባይ መሰራቱ ይጠቀሳል ። 📍ለቃሉ የታመነው ድምጻዊ አስቻለውና ፕሮፌ ኃይሌ... =================================== አስቻለው ፈጠነ ፕሮፌሰር ኃንሌ ገሪማ ላለፉት 30 ዓመታት በደከሙበትና የ10 ሰዓት ታሪካዊ ፊልም በፕሮፌሰር ኀይሌ ገሪማ ጥቁር አንበሳ የአድዋ ልጆች - የሮማ ተኩላ "BLACK LIONS, ROMAN WOLVES፡ THE CHILDREN OF ADWA" ተብሎ ርዕስ በተሰጠው ፊልም ተሳትፏል ። በዚህ ታሪካዊ የአድዋ ጀግኖች መታሰቢያ ፊልም ሲሰራ ሙሉ በሙሉ የማጀቢያ 13 ሙዚቃውን የተሰራው በሃገር ወዳዱ ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ነው ። አስቻለው ሙሉ የማጀቢያ ሙዚቃ ሲሳተፍ የፌልሙ ባለቤት ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ ክፍያ ሊከፍሉት ሲጠይቁትም እኔም ነበርኩ የሰጣቸው ቀጥተኛ መልስ " ፕሮፌሰር ኃይሌ ይህ ለኢትዮጵያ የሰራህው ስራ ነው ። እኔም በዱር በገደሉ በአርበኝነት ተዋድቀው ሃገር ሰርተው ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞይ የማበረክተው የግል ስጦታዬ ነው ። " በማለት ክፍያ ለመቀበል ፍላጎት እንደሌለው በኩራት ሲመልስላቸው በውይይቱ እማኝ ምስክር ነበርኩ ። ጥምቀትን በጎንደር ፣ እናትዋ ጎንደርን ፣ የመነኩሴዋ እናቴን መለየት የከበደ ሀዘንና የመይሳው ልደትን ሳስታውሳቸው የተደባለቀ ስሜት ይሰማኛል ። ከሀዘኑ የጥምቀት ዋዜማ የደስታ ኩራት ድባቡ ትናንት ይናፍቃል ... ስለ ኢትዮጵያ ሚታመነው ለጥቅም ሳይሆን ለነፍሱ ታምኖ የሚያዜመው ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ይናፍቀኛል ... 😘 ፈጣሪ ፈቅዶ ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ለመይሳው ልደት ሶስተኛ ነጠላ ዜማ እየሰራ ነው ። መይሳው አፄ ቴዎድሮስ ልደት ደርሶ አስደማሚውን ሌላኛ የአስቻለው የጎንደር ባህላዊ ሙዚቃ ለማዳመጥ በእጅጉ ናፍቄያለሁ 😍 . ጥምቀትን በጎንደር የጥንቷን ኢትዮጵያ ያገኟታል ። እርግጥ ነው ጥምቀትን በጎንደር ማክበር መታደል ነው ✋ እስኪ ቸር ያሰማን ነቢዩ ሲራክ ጥር 4 ቀን 2018 ዓም
213
4
⭕️ ጥምቀትን በጎንደር ማክበር መታደል ነው ‼️ ================================ 📍የሁሉም ከተማ ጎንደር 🙏 📍የጎንደር ጥምቀት ዋዜማ የመይሳው ልደት ‼️ 📍ከእናትዋ ጎንደር እስከ አሞራው ካሞራው‼️ 📍ለቃሉ የታመነው ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ሲናፍቀኝ 😍 📍 የአስቻለው ፈጠነ የሁሉም ከተማ ጎንደር... =============================== ታሪካዊዋ የጎንደር ከተማና ነዋሪዎቿ ከጥንት ጀምሮ እንግዳ ተቀባይ ናቸው ። ይህ እውነት ነውና ህያው ምስክርነታቸውን የሚሰጡን ጎንደርን መሬት የረገጡት ከኢትዮጵያ ጎብኝዎች ብቻ አይደሉም ። ከተለያዩ ንፍቀ ክበብ ከመላው አለም ክፍሎች መጥተው ጎንደርን የጎበኟት ሁሉ የሃገር ውስጥና ውጭ ዜጎች ምስክርት ሰጥተዋል። ሁለም ጎብኝዎች ታዲያ እንግዶቹን ስቆ ተቀብሎ ተንከባክቦ ስላቆያቸው ደግ እንግዳ ተቀባይ ህዝብ ባህልና ስለ ተስማሚው ወይና ደጋ ተስማሚ የአየር ጸባይ አድንቀውና አመስግነዋል። ጎንደርን የጎበኙ እንግዶች ታዲያ እጅግ ውብና ድንቅ የማይረሳ ጊዜ እና ትዝታ ስለቋጠሩባት ከተማቸው ስለ ጎንደር በሚዲያ ከሚያሰራጯቸው ምስክርነቶች በተጨማሪ ስለ እንግዳ ተቀባይ ህዝብ ቅርስና ባህል መጽሐፍ ከመጻፍ ጀምሮ የተለያየ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል ። እናም እናትዋ ጎንደር የሁሉም ከተማ ናት እላለሁ ። 📍የድምጻዊ አስቻለው " እናትዋ ጎንደር " ... ============================ አመት አልፎ አመት ሲጠባ ከወርሃ ጥር ጀምሮ ጎንደር በጥምቀት ደምቃ ትዋባለች ፣ ታምራለች ። ሌላ የጎንደር ጥምቀት በዋዜማ በሚከበረው በመይሳው ካሳ የአፄ ቴዎድሮስ የልደት መታሰቢያ ቀን ነው ። ካለፉት ጥቂት አመታት ወዲህ ደግሞ ትውልድ ታሪክ ሰሪ አባቶቹን ሲያዘክር ጥምቀትና የቆፍጣና ንጉሠ ነገስት ልደት ተገናኝተዋል ። በጥምቀት ዋዜማ ያ ጉምቱ ባለ ቅኔና ድምጻዊ አስቻለው ጥር 5 ቀን 2015 ዓም አስቻለው በመይሳው ታላቅ የልደት ቀን መታሰቢያ ቀን በየሁለት አመቱ አንድ ባህላዊ ለጎንደር ክብር መግለጫ ነጠላ ዜማ ሲለቅ ቃል በገባው መሰረት " እናትዋ ጎንደር" ሰርቶ አጠናቋል። እኔም ከስደት መልስ አቅፋ ያሳደገች የ96 ዓመት የእድሜ ባለጸጋ እናቴን ጋር እትብቴ ከተቀበረበት እና ካደግኩባት መንደሬ ጎንደር ፋሲል ቤተ-መንግሥት አጥር ስር ከቆብ አስጥል መንደሬ ከትሜያለሁ ። ታዲያ ጥቅምት ሳይጠባ በመስከረም ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነና የፊልም ዳይሬክተሩ ሰውመሆን ይስማው ጋር የ"እናትዋ ጎንደር" ሙዚቃ ቪዲዮ ሲሰሩ ጎንደር ፒያሳ ተገናኘን ። እናትዋ ጎንደር ተጠናቆ ድንቅ ጣዕመ ዜማው ቃል በተገባበት የአፄ ቴዎድሮስ ልደት ቀን ተጠናቆ በአገሩ ተናኘ ጉድ ተባለ። የእናትዋ ጎንደርን ድንቅ ጣዕመ ዜማ በውል ሳላጣጥም በበነጋው ጥር 7 ቀን 2015 ዓም ንጋት ዶሮ ሳይጮህ በእኛ ቤት ግን ሐዘን ገባ 😪 ከእናቴ ጋር እስከ ወዲያኛው ተለያየን 😢 ለወሬት ከአጠገቧ ሆኘ ያስታመምኳት ስስቷ እናቴና እኔ ተለያይተን ስሜቴ ተደበላለቀ ...በጥቅምቀት ዋዜማ ደስታና በሀዘን ተጫነኝ ... 📍ስስትዋ እናትዋ ጎንደር 😍 ==================== በሀዘን ላይ ሆኘ በጦርነት ስጋት የዳመነው የጎንደር ሰማይና ደጉ ወገኔ በ"እናትዋ ጎንደር " ድንቅ ጣዕመ ዜማ አንገቱን ቀና ማድረጉን እየተመለከትኩ ። የመይሳው ልደት ፣ የጎንደር እና ጥምቀት እና እናትዋ ጎንደር ሲገናኙ ያ የከፋ የጨለመበት ዜጋ ፍርሃት ስጋት ያደራበት ጥቁር ደመና ተገፈፈ። ደስታ እና ልዩ ፌሽታ ሆነ... ዛሬ ላይ ያ ቀን፣ ያ ስሜት ፣ ያ ኩራት ይናፍቃል ... ስለ ጎንደር ብዙ ዘፈኖች ወጥተዋል ። በእኔ እምነት የጎንደር ከተዘፈኑ ባህላዊ ጣዕመ ዜማዎች መካከል የምንጊዜም ምርጫና ጎንደርን ደርዝ ባለው መልክ የገለጸው የጎጃም አገው ምድር ተወላጁ አርበኞች ልጅ ጉምቱ ባለ ቅኔውና ድምጻዊ Aschalew Fetene Ardi ነው ። ለአገው ሞድሩ ለድምጻዊ አስቻለው ጎንደር ስስት እናቱ ናት ... " እናትዋ ጎንደር " ይላታል " ባልቴቷ ጎንደር " ይልና መልሶ "ወይዘሪት ሙሽርት...ምሰሶዋ ጎንደር እያለ ያሞካሻታል .... አስቻለው ሹም ሲለዋዎጥ ፣ ዘመን በዘመን ሲተካ መጭ ሂያጁን የምትታዘብ የማይነጥፍ ውበት ባለቤት ባለቤቲት እናቱን የአፄ ፋሲር ውቅር ከተማ ጎንደርን ሲያሽሞነሙናት ልብ ያሞቃል ። ጎንደር እርጅና ውበቷ ፣ እርጅና ክብሯ ፣ እርጅና የማይነጥፍ ውበቷ የሆናት ጎንደር የኢትዮጵያነት ክብር ነጻነት መሰሶነቷን እንዲህ ሲል ይገልጸዋል... " በባልቴት ውበት ሁሌም ወይዘሪት ፣ ማይነጥፍ ጅረት ጎህ ለነፃነት፣ ፈጣሪ ጦቢያን ሲከልላት ፣ የምሰሶዋን ስም ጎንደር አላት ፣ እንዳለች አለች ታተይ ሙሽሪት ፣ ሂያጅና መጭን እንደታዘበች ..." 🥉 አዎ የእናትዋ ስስትዋ ጎንደር ስሟ በሙዚቃው አለም ከፍ ያደረገው ፤ በነዋሪው ህመም ህመሙን መሆኑን አጉልቶ ያሳዬው ለሃገር ወገኖቹ ታማኝ ባለ ቅኔ ድምጻዊ ልጇ እሱ አስቻለው ፈጠነ አር ዲ ይባላል 🙏 እንቀጥል ... 📍 ታሪክ አስታዋሹ አስቻለው በ "አሞራው ካሞራ " ================================ ለኢትዮጵያ የታመነው ድምጻዊ አስቻለው " አሞራው ካምራ"ብሎ አምና በጥምቀት ዋዜማ ባወጣው ነጠላ ዜማ አሰራጭቷል ። ይህ ጣዕመ ዜማ መታሰቢያነቱ ለአፄ ቴዎድሮስ ልደት ሲሆን በክፉው ወራሪው ፋሽሽት ኢጣሊያን ሰራዊትን ጎንደር ሲቆጣጠር ወራሪው በገባ እግሩ ፈርጥጦ እንዲወጣ ገድል የፈጸሙትን ጀግና አርበኛ ራስ አሞራው ውብነህ ተሰማና አርበኞቻችን ለማዘከር የተሰራ ታሪካዊ አስተዋሽና ታሪክ ነጋሪ ሙዚቃ ነው ። ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ በአሞራው ካሞራው ውብ ታሪክ ዘካሪ ሙዚቃው መግቢያ በሰላም እጦት ውጋት ህመሟን አስታውሶታል ። ባለ ቅኔው ድምጻዊ አስቻለው በማይጠገብ ውብ ግጥም ዜማና ባለ ግርማ የድምጽ ቅላጼው ዘመኑን ያዘከረ ፣ ዘመኑን በዋጄ መልኩ በጥበብ ከሽኖ ባቀረበበት የአሞራው ካሞራ ነጠላ ዜማ ተከታዩን አንጎራጉሮ ለጨነቀው ወገኑ ያለመድረሱን የቁጭት ስሜት እንዲህ በማለት አንጸባርቋል ... 🔸አሞራው ካሞራ ============= " እቴ ወይ ልዋል ... ከደረትሽ መሀል ናፈቀችኝ ጎንደር ... የእነ አሞራው ሀገር በቅዳሴው ቦታ ቀለሀ ሲዘምር ፣ እንዴት ሰንብተሻል እናትዋ ጎንደር ? እናትዋ ብልሽ ትንፋሽዋ ብልሽ አካልዋ ብልሽ መቼ ደረስኩልሽ‼️ " ይላታል ። አሰቻለው 📍አስቻለው በጥምቀት ዋዜና በመይሳው ልደት... ============================== ድምጻዊ አስቻለው በጥምቀት ዋዜማ በሚከበረው በመይሳው ካሳ የአፄ ቴዎድሮስ የልደት መታሰቢያ ልዩ መታሠቢያ ቃል በገባው መሰረት በየሁለት አመቱ አንድ ነጠላ ዜማ ይለቃል ። ከዛሬ ሶስት አመት በፊት የለቀቀው "እናትዋ ጎንደር" ሲሆን ይህ ድንቅ ሙዚቃው 22 .9 ሚሊዮን በላይ ሰው ያየው ተመልክቶታል ። አምና የተሰራጨው "አሞራው ካሞራን " በሚል ርዕስ እጅግ ቀልብ ሳቢ የሆነው ወኔ ቀስቃሽ እና የጀግንነት ገድል አስተዋሽ ነጠላ ዜማ የአርበኛው ራስ አሞራው ውብነህ ተሰማና ጀግኖቻችኝ ባዘከረበት " አሞራው ካሞራ " ሙዚቃ በአንድ አመት 17.6 ሚሊዮን የህዝብ እይታን አግኝቷል።
186
5
No text...
172
6
አንባገነኗ አሜሪካ በአለም አቀፍ ህግ የምትዳኘው መቸ ነው ⁉️ ኦ አሜሪካ‼️
አንባገነኗ አሜሪካ በአለም አቀፍ ህግ የምትዳኘው መቸ ነው ⁉️ ኦ አሜሪካ‼️
297
7
🛑 የስራ ሥምሪቱ መወሳሰብ እና ህገ-ወጡ ስደት እየከፋ መምጣት ‼️
🛑 የስራ ሥምሪቱ መወሳሰብ እና ህገ-ወጡ ስደት እየከፋ መምጣት ‼️
169
8
No text...
305
9
🌎 ክብር ለሚገባው ክብር ሲሰጥ ‼️ ========================= ⭕️ ለታላቁ የቱሪዝም ባለውለታ የክብር ሽኝት ተደረገ🙏 📍ጋሽ ጌትነት ስላደረግከው አበርክቶ ከልብ እናመሰግንሃለን 🙏 አቶ ጌትነት ይግዛው ይባላል ። ትውልድ እድገቱ በፋሲል መዲና ጎንደር ላይ ነው። የጎንደር አፄ ፋሲል ቤተ- መንግሥትን ኪነ-ህንጻ ሲገባና ሲወጣ እያየና አስደማሚ የነገሥታቱን ታሪክ ከወላጆቹ ሲሰማ አድጓል። ገና በጎልማሳነት እድሜው ሲሰማ ባደገው የቀደመ ስልጣኔ ማሳያ የአፄ ፋሲል እና የነገሥታቱ ድንቅ ድርሳናት ነፍሱ ተገዛች ። ዝንባሌው ባህልና ቱሪዝም ላይ ሆነና ታሪኩን በዘመናዊ አጎለበተው ። እናም እንጀራውን ከሚወደው የቱሪዝም ስራ ጋር አጋምዶ ኑሮን መግፋት ያዘ ... በ1970ዎች አጋማሽ በቱሪዝም ሙያ ሰልጥኖ እንደወጣ የጎንደር አፄ ፋሲል ቤተ- መንግሥትን ከፍተኛ አስጎብኝ ሆነ ። ለመጣ ለሄደው ሃገር ጎብኝ ለሃገሬው ሰው በቋንቋዎ ለውጭ ጎብኝው በደረጀና ጥርት ባለ እንግሊዝኛ ቋንቋ በአስጎብኝነት እና በከፍተኛ የባህልና ቱሪዝም ባለሙያነት አገልግሏል። ለጋሽ ጌትነት የቀደምት ስልጣኔ መገለጫዎቻችን ቅርስ እና ታሪክ ትልቅ ቦታ አላቸው ። የአፄ ፋሲል ቤተ-መንግሥት ውስጥ የሚገኙ ፍርስራሽ ድንጋኖች የታሪካችን አካል ናቸውና በልዩ ሁኔታ ጠብቀዋቸዋል። ድንጋዮቹንና በአጸደ ግቢው ለሚገኙ ሃገር በቀል እጽዋትን ሰምረው ያውቋቸዋል ። ዘመን በዘመን ሲተካ የቀደመ ስልጣኔያችን አሸራ ፣ በዘመን የሆነውን እና የሆነብንን የሚናገሩ የታሪክ አሻራ ናቸውና ለሶስት አስርት አመታት ከቦታቸው ከነክብራቸው ጠብቀው ካስረከቡን ጉምቱ የቱሪዝም ከፍተኛ ሙያተኛ ጋሽ ጌትነት አንዱ ነው ። ጋሽ ጌትነት በመላ ሃገራችን ስላሉ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ውድ ቅርሶቻችንና ስለ ቱባ ባህላችን ጥልቅ ጥናትና ምርምር አድርጓል ። ስለ ቱሪዝም ባህልና ቅርሶቻችንን ያልተነካና ገና ያልሰራነው ለእድገት ዋልታ የሚሆን ያልገባን ጥቅም በተባ አንደበቱ ሲናገር ልብ ያሞቃል። አስቆጭቶ በቱሪዝም ተግተን እንድንሰራ ያነቃቃል ። ጉምቱ ባለሙያው ጋሽ ጌትነት ይግዛው ለእያንዳንዷን የቅድመ ስልጣኔ መገለጫ ቅርሶቻችንና ቱባ ባህላችን አለም ጠንቅቆ ኦንዲያውቀው አስተዋጽኦ በማድረግ እና በአለም አቀፍ ቅርስ ጥበቃ እንዲመዘገቡ ትልቁን ድርሻ ተወጥቷል ። ጋሽ ጌትነት በቱሪዝም ሚ/ር ከፍተኛ አማካሪነትን ጨምሮ በተለያዩ የስልጣን እርከኖች ሃገራቸውን አገልግሏል። ከቀናት በፊት ከአገልግሎት በጡረታ ከመሰናበቱ በፊት የቱሪዝም ኮሚሽን የኮንቬንሽን ቢሮ ሥራ አስፈፃሚ ሆኖ አገልግሏል ። ከሚወደው ሙያ በጡረታ የተገለለው ጋሽ ጌትነት ግዛው ሃገሩንና ወገኑን ለአራት አስርት አመታት በባህል እና ቱሪዝም መስክ ላደረገው ከፍ ያለ አበርክቶ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከፍ ያለ የክብር ሽኝት አድርጎለታል ። በዚህ ክብርት ሚኒስትሯ በተገኙበት በሽኝት መርሃ-ግብር የመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የቱሪዝም ባለሙያዎች እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶለት ተመልክቸ እጅግ በጣት ደስ ብሎኛል 🙏 ለብርቱው የታሪክ ተመራማሪ ፣ ለቅርስ ፣ ለቱሪዝም ፣ ለባህልና ቅርስ ባለሙያው እድሜ ልኩን ከእውነት ጋር ወግኖ ብዙ ታግሎ ያሳካው ብዙ ነውና የተሰጠው ክብር ተገቢ ነው ። ባለውታው ጋሽ ጌትነት ግዛው የሃገሬ ቱሪዝም በትምህርት እና በልምድ ባካበተው ክህሎቱ ብዙ መስራት በሚችልበት ወቅት በጡረታ በመሰናበቱ የምንጎዳው እኛው ነን። ያም ሆኖ ጋሽ ጌትነት በጡረታ መገለሉ እረፍት ነው ። በእውነት ለመናገር የቀረብን የሚጎድልብን እኛው ነን ... 📍እኔም እላለሁ... ============ ተንከባክበህ ባቆየህን የሃገርና የወገን ቅርስ ላይ አይንህን አትንቀል ። ከቦታህ ርቀህ የጎደለብን ብዙ ነው ። ዛሬም ምክር ዝክርህን እና ከፍ ያለ ሙያዊ እገዛህን ትውልድ ይሻል ። እኔ የምለው ይህን ነው ። ጋሽ ጌትነት በሙያህ ለትውልድ ስላደረግከው ከፍ ያለ አበርክቶ ከልብ እናመሰግንሃለን 🙏 ነቢዩ ሲራክ ህዳር 3 ቀን 2018 ዓም
283
10
ውድ ግብር ከፋያችን (ቲን 0068158160) ብር 48202.96 ግብርዎን በመክፈል ግዴታዎን ስለተወጡ እናመሰግናለን፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮውድ ግብር ከፋያችን (ቲን 0068158160) ብር 10232.71 ግብርዎን በመክፈል ግዴታዎን ስለተወጡ እናመሰግናለን፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮውድ ግብር ከፋያችን (ቲን 0068158160) ብር 9730.53 ግብርዎን በመክፈል ግዴታዎን ስለተወጡ እናመሰግናለን፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮውድ ግብር ከፋያችን (ቲን 0068158160) ብር 1853.41 ግብርዎን በመክፈል ግዴታዎን ስለተወጡ እናመሰግናለን፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
1
11
No text...
326
12
🔴 ስለ ሰላምና ፍቅር ... 📍የትግራይ እናት የሰላም ናፍቆት ተማጽኖ ‼️ ============================== 📍አምላኬ ሆይ በቃችሁ በለን ... ይህን ተንቀሳቃሽ ልብ ሰባሪ ምስል ሲዘዋዎር ተመለክቸ ልቤ ተሰበረ። እናት በልጆቿ ሰላም አጥታ ስሰላምና ፍቅር ተማጽኖ መሬት እየጠበጠበችና እየተንከባለለች ሁን ያለው የሚፈጸም ፤ ምንም ማድረግ ለማይሳነው አምላኳ አልቅሳ ስትማጸን መመልከት የማያመው አለ አልልም😪 በመንገዴ የሰላም እጦት ስጋት በሁሉም የሃገሬ ክፍል ጥያቄ መሆኑን የማውቀውን እውነት የማገኛቸው ወገኖቸ ሁሉ ሁነኛ ጥያቄ መሆኑን እንደ አዲስ ተረድቻለሁ። እናም የቀረው ወገኔ በተንቀሳቃሽ ምስሉ እንደምናያቸው የትግራይ በአደባባይ ተማጽኗቸውን ባየነው መልኩ አቅርበውት ባናያቸው በየእምነት ተቋማቱ እንባቸውን እያዘሩ ሰለ ሰላም አልቅሰው ለፈጣሪ ተማጽኖ ያቀርባሉ። በአንፃሩ እኛ ልጆቻቸው በዘር ፣ በእምነትና ረብ የለሽ በሆነው ፖለቲካ ወግነን እንደተጠፋፋን እንደኖርነው ዛሬም ከክፋቱ መንገድ አልዎጣንም ። ሰለጠንን ተማርን ብለን ያልተማርን ያልሰለጠገንን ያልተማርን ደንቆሮዎች ሆነናል ። ንቁ ነን ብለን አልነቃንም ። ወገኖቻችን በየእምነት ባህላቸው ስለ ሰላም እርጥብ እሳር ይዘው ፣ ስለ ፍቅር ዝቅ ብለው በሰማይ መሬቱ ገዥ የፈጣሪን ስም እየጠሩ ሲማጸኑን" የዝሆን ጀሮ ይስጠን " ብለን ለገናዥ አስቸግረናል። መካሪ፣ ዘካሪና አስታራቂ የሃገር ሽማግሌ አባት እናቶቻችን አልሰማ ብለናል ደንቁረናል። እኛ ክፉዎች ግብዝ ጭፍን የታበይን ልጆቻቸው ጨካኞች ሆነናል ...ይህን ወገኖቻችን ያስመረረ የሰላም እጦት ተመካክረን ለመፍታት ቀናኢ ልቦና አጥተናል ። ይህ የመረረ ልብ ሰባሪ የሚያደማ እውነት የእኛ ክፋት ማሳያ መራራ ታሪካችን አካል ሆኖ ማየት ያማል 😪 ጀሮ ያለው ይስማ ‼️ አምላኬ ሆይ በቃችሁ በለን ...ሰላምና ፍቅሩን ይመጣ ዘንድ እርስ በርስ መፋጀቱ ይቆም ዘንድ የሚማጸኑ የሃገሬ እናቶቻችን ጸሎትና ልመና ተቀበል ✋ ሃፐራችን ሰላም አድርግልን 🙏 ነቢዩ ሲራክ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓም
296
13
🔴 በመንገዴ .... 📍በኦሮሚያ - በሌመን የስፖኩዮ መብራት አዳኙ ወጣት 😪 ====================================== 📍ታማሚውን አስጠምቁት ወይም ህግ አስከብብሩ ‼️ በሌመ
🔴 በመንገዴ .... 📍በኦሮሚያ - በሌመን የስፖኩዮ መብራት አዳኙ ወጣት 😪 ====================================== 📍ታማሚውን አስጠምቁት ወይም ህግ አስከብብሩ ‼️ በሌመን ከተማ - በተንጣለለው አውራ ጎዳና ፊት የፊት እየመጣ የቤት መኪና የስፖኩዮ መብራት አዳኙ ወጣት 😪 ምክንያቱ ምንድነው ? ብዬ ጠየቅኩ ..." መኪና እያስቆመ የስፖኪዮ መብራቱን እገነጥላለሁ በማለት ገንዘብ ይጠይቃል የሚጠይቀው ገንዘብ ደግሞ ከ50 ብር በላይ እንጅ በታች ፍጹም አይቀበሌም ። " ሲሉ መረጃውን አቀበሉኝ 😪 ይህን ጉዳይ ሰምቸ አላምንም ብልም ዛሬ አደገኛ ድርጊት ሲፈጸም ተመለከትኩ ። ከአዲስ አበባ ወደ በደቡብ ሶዶ - ኦሮሚያ ክልል 60 ኪ.ሜትር ላይ በሌመን ከተማ ተመለክቸ ይህ መረጃ ለሌላቸው አደጋው የከፋ እንደሚሆንና ወጣቱ በዚህ ድርጊት መካከል ሊደርስበት የሚችለውን አደጋ አሻግሬ በአይነ ህሊናዬ አየሁት ። ተሳቀቅኩ ፣ አዘንኩም 😪 ለአዲስ አሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ወደ ደቡብ የሚጓዙ ይህ መረጃ የሌላቸው ወገኖች አደጋ እንያጋጥማቸው ለመምከር እና የሚመለከተው የመንግሥት አካል የማስተካከያ እርምጃ ቢወስዱ መልካም ነው እላለሁ። ካልሆነ የከተማው ነዋሪዎች በተለይ ወጣቶች የታማሚውን ድርጊት እያያችሁ ዳር ሆኖ ከመሳቅ ወይ ወይ ወደ ህክምና ውሰዱት ወይም ታስጠምቁት ዘንድ አደራ እላለሁ ‼️ ቸር ያሰማን ነቢዩ ሲራክ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓም
235
14
የዛሬ አመቱ አከባበር በጋርመንት ጋራ ፖርክ 🙏+1
የዛሬ አመቱ አከባበር በጋርመንት ጋራ ፖርክ 🙏
333
15
+2
No text...
261
16
ደስ ብሎኛል ✋ 🛑 በደመራ በዓል የአባዎራዎች ቅሬታ ተፈቷል‼️ ================================ 📍በጋርመንት የሃገር ሽማግሌዎችን እናመሰግናለን🙏 📍 የ300 አባዎራዎች ቅሬታ ... ===================== አዲስ አበባ ጋርመንት ጋራ ግራር ፖርክ አካባቢ የሚኖሩ እስከ 300 የሚደርሱ ማህበረሰብ አባላት ከመስቀል ዋዜማ ጀምሮ ቅሬታ እያሰሙ ነው። "ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ውስጥ የመስቀልን ደመራ በዓል ለ15 ዓመታት በድምቀት የሚከበርበት ወደ 3,500 ካሪ ቦታ ያለው የግራር ፖርክ ዘንድሮ ደመራ እንዳናበራ በክፍለ ከተማው ኃላዎች ተከልክለናል " በማለት ሰፈሩ ነዋሪ የሆኑ ወገኖች ዛሬ ማለዳ ቅሬታቸውን ገልጸውልኝ ነበር ። ከዚህ ቀደም የአካባቢው አባዎራዎችና ነዋሪዎች በመስቀል የደመራ በዓልን በመተሳሰብ ተሰባስበው ገንዘብ በማዋጣት ከብት አርደው ፣ ማዕድ ተጋርተው በታላቅ ድምቀት የሚያከብሩት የሚያከብሩበት ፖርክ ቢከለከልም ተለዋጭ ቦታ እንዳለመሰጠቱን ዛሬ ያደሱኝ መረጃ ያስረዳል ። እኒሁ ቅሬታ የሚያሰሙ ወገኖች " ከዚህ ቀደም እንደሚከበረው በሰፊው ፖርክ ላይ ልማቱን በማይጎዳ መልኩ በታላቅ የህብረት ዝማሬ ተሰባስበው በፍቅር የሚያከብሩት የደመራ በዓልን በመከልከሉ ያዘኑ በርካታ ነዋሪዎች ናቸው ። ደመራው ቢቀርም ምሽቱን ተሰባስበው በአሉን በጸሎት ለማሳለፍ ወስነው የነበሩ ነዋሪዎች ምሽቱን ሰናይ መረጃ አካፍለውኛል ። 📍 አሁን የደረሰኝ አስደሳቹ መረጃ 💐 ========================= ከትናንት የበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ የአካባቢው ታዋቂና ሽማግሌዎች የደመራ ቦታው በፖርክ በመከልከሉ እና ተለዋጭ ቦታ አለመሰጠትን አሳሳቢነት በመረዳት በሽምግልና ያደረጉት ጥረት ተሳክቶ ደመራ ለማብራት መፍትሔ መገኘቱን ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የደረሰኝ ሰናይ መረጃ ያስረዳል ። በመረጃው መሰረት ችግሩ በአርቆ አሳቢ ወገኖች ጊዜናዊ እልባት እና መፍትሔ ያስገኙ የአካባበቢው ፖሊስ አስተባባሪዎች እንዲሁም የአካባቢው ሽማግሌዎች ሲሆኑ የተለመደው የደመራ በዓል እንዳይስተጓገል ለግዜው መንገድ ላይ መጠነኛ ዳመራ እንዲሰራ መደረጉን ታውቋል ። መረጃውን ያደረሱኝ ነዋሪዎች በማከል " መንግሥት ለዚህ መሰል ችግሮችን ተመልክቶ ዘላቂ መፍትሔ ያበጅ ዘንድ እንፈልጋለን " በማለት መልዕክታቸውን እንዳደርስ የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል ። 📍እንደኔ እንደኔ ከፍ ሲል በመንግሥት ሚዲያ ደረጃ እና ዝቅ ሲል በየወረዳና ሰፈሩ ህዝብና መንግሥተን ለማራራቅ በርትቶ የሚሰራ ኃይል ያለ ይመስለኛል ። መፍትሔው ባይገኝ ኑሮ በዓውደ አመቱ የነዋሪው መከፋት ጥሩ አልነበረም ። ከህዝቡ ጎን በቆሙ የፖሊስ አካላትና የአካባቢው ሽማግሌዎች ለችግሩ መፍትሔ ላላለጉ ወገኖች ከፍ ያለ ምስጋና ማቅረብ እወዳለሁ 🙏 ሰው በገዛ ሃገሩ በአውደ አመት አዝኖ እና ተከፍቶ በዓልን ማሳለፍ የለበትም ። ያሳዘነ ያስከፋን ችግር በመጨረሻ ሰዓት በሰላማዊ መንገድ በመፈታቱ በጣም ደስ ብሎኛል ✋ መልካም የመስቀል ደመራ በዓል ይሁንላችሁ 💐 ነቢዩ ሲራክ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓም
239
17
⭕️ የአዲስ አመት ዋዜማ ምስጋናዬ... 🌼የግብፆች የእግር እሳት መሐመድ አል አሩሲ ‼️ ================================= 📍 ወንድም መሐመድ ኢትዮጵያ ታመሰግንሃለች 🙏 በአዲ
⭕️ የአዲስ አመት ዋዜማ ምስጋናዬ... 🌼የግብፆች የእግር እሳት መሐመድ አል አሩሲ ‼️ ================================= 📍 ወንድም መሐመድ ኢትዮጵያ ታመሰግንሃለች 🙏 በአዲሱ አመት ዋዜማ ህዳሴ ግድብ ሲመረቅ ሳላመሰግነው ማለፍ ሐጢያት የሚሆንብኝ ወዳጄ ግብፆች የህዳሴ ግድብን አጣመው አለምን ሲያሳስቱ ሀገሬን አትንኩ ባይ ቋሚ ጠቃው ሆኖ የማውቀው መሐመድ አል አሩሲ ነው ። በአረብ ታዋቂ ቴሌቪዥኖች እየቀረበ የግብፅና የደጋፊዎቻቸው በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ የተደራጄ መረጃና ማስረጃ ይዞ ግብፃውያን ምሁራንን ያረጄ ያፈጄ ፕሮፖጋንዳ አፈር ድሜ ያጋጠ ጀግናችን ነው ። ትሁቱና ሰው አክባሪው መሐመድም አል አሩሲ እንደ ትንታጉ ወንድም ሱሌማን አብደላ ሀገሬ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ የመገንባት የማይገሰስ መብት አላት በሚል አንድምታ ግብፅ እና ደጋፊዎቻቸውን በመረጃ እና ማስረጃ ያርበደበደ የቁርጡ ቀን ወንድማችን ነው። መሐመድ አልአሩሲ ለግብፆች ግርማው የሚያስፈራ የእግር እሳታቸው ነው ። እነሆ መሐመድ እድለኛም ነው ። የተዋደቀለት የህዳሴ ግድብ ምርቃትን በአካል ተገኝቶ ታድሟል ። ይህንን በማየቴ ደስተኛ ነኝ 😃 ወንድም መሐመድ አል አሩሲ ከቀናት በፊት በትውልድ መንደሩ ባሌ በተጓዝኩበት አጋጣሚ አግኝቸው የሁሌም አክብሮቴን ገልጨለታለሁ ። ቁመተ ለግላጋው መሐመድ አል አሩሲ መሐመድ የድል አጥቢያ ጀግና አይደለም ። ሙሄ ስለ ሀገር እና ስለ ወገን በሰራውን ውለታ ትናንት ፣ ዛሬም ነገም ሁሌም አከብረዋለሁ 🙏 በህዳሴ ግድቡ የፕሮፖጋንዳ ተጋድሎ በፈታኙ ጊዜ ግንባሩን ሰጥቶ ስለከፈለልን ኢትዮጵያ ታመሰግነዋለች 🙏 መልካም የአዲስ ዋዜማ ተመኘሁላችሁ 🌼 ነቢዩ ሰራክ ጷጉሜ 5 ቀን 2017
288
18
🌼 በአዲሱ አመት ዋዜማ ብስራቴ .🌼 ⭕️ ወንድም ሱሌማን አብደላ ሰላም ነው ✋ ============================= በርካታ ኢትዮጵውያን ወገኖቸ የህዳሴው ግድብ እውነተኛ ታጋይ የግብፅና
🌼 በአዲሱ አመት ዋዜማ ብስራቴ .🌼 ⭕️ ወንድም ሱሌማን አብደላ ሰላም ነው ✋ ============================= በርካታ ኢትዮጵውያን ወገኖቸ የህዳሴው ግድብ እውነተኛ ታጋይ የግብፅና የወዳጆቿ የራስ ምታት ጠላታቸው የወንድም ሱሌማን ጉዳይ እንዳሳሰባቸው የተለያየ ጥያቄ አዘል የሆነ መልዕክት አድርሰውኛል ። እነሆ በአዲስ አመት ዋዜማ ደስ የመሚለውን የመረጃ ብስራት ልንገራችሁ ። እውነት እውነት እላችኋለሁ ሱሌማን ሰላም ነው ። ሱሌማን አልታሰረም ። በአደጋ ላይም አይደለም ። ሱሌማን የህዳሴን ግድብ ለመቀልበስ የግብፅና የደጋፊዎቿን ፕሮፖጋንዳ በመቀልበስ ከፍተኛ ተጋድሎ አድርጎ እንደ ዜጋ የሚጠበቅበትን ስራ ሰርቶ አልፏል ። ሰላማዊ ኑሮን እየኖረ ነው ✋ ሱሌማን ዛሬም ነገም ለሀገርና ለወገን በሰራው ስራ እናመሰግነዋለን 🙏 ይህው ነው ... መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ 🌼 ነቢዩ ሲራክ ጷጉሜ 5 ቀን 2017 ዓም
227
19
📍ወዳጆቸ ሆይ ... በዚህ የደስታ የፌሽታ ቀን ክብር ለሚገባው ስሙ የተዳፈነው የሀገርና ወገን ባለውለታ ስለ ወንድማችን ሱሌማን አብደላ ክብርና ምስጋና እናንተም ምስክርነት ስጡበት ፣ ላደረገልን ተጋድሎ ታላቅ ክብር ምስጋና ትሰጡት ዘንድ እማጸናችኋለሁ 🙏 🔸ሱሌ ኢትዮጵያ ታመሰግንሃለች ፤ ኢትዮጵያውያን በታላቅ ክብር እናመሰግንሃለን ። ሁሌም ህዳሴ ግድብ ሲዘሳ ስምክን እናዘክረዋሃለን ✋ አክባሪ ወገኖችህ... ነቢዩ ሲራክ ጷግሜ 5 ቀን 2017 ዓም
217
20
የማለዳ ወግ ... ⭕️ የግድቡ ባለውለታ ወንድም ሱሌማን አብደላ ‼️ ================================ 📍 ኢትዮጵያ ታመሰግንሃለች 🙏 📍የግብፅና የደጋፊ አረቦች ቀንደኛ ጠላት ... ============================= የህዳሴው ግድብ ጉዳይ ሲነሳ ግብፅና የግብፅ አቋም ደጋፊ አረቦችን በሚያቀርበው መረጃ መሬት ጠብ አይልም ። የግድቡ ተቃዋሚዎች መረጃ ማስረጃ ይዞ ሲሞግታቸው ትንፍሽ አይሉም ። የሚያቀርበው መረጃው ጠንካራ ነውና ደፍረው አይሞግቱትም ። ይፈሩታል ። ስሙ ሱሌይማን አብደላ የሚባለው ሃበሻ ለግብጾች ትልቅ ጠላት ሆኖ ስሁት ፕርፖጋንዳቸውን ያከሸፈ ቆፍጣና የሃገሬ ልጅ ነው ። የህዳሴው ግድብ ተሟጋች የትውልዴ ጽናት ምልክት ወንድም ሱሌማን አብደላ መሆኑን ስመሰክር በታላቅ ክብርና በኩራት ነው ... በመረጃና ማስረጃ ፤ በእውቀት እና በፍጹም ድፍረት ስለ ህዳሴው ግድብ የፕሮፖጋንዳ ጦርነት ለአመታት ስለ ሀገር ወገኑ ጥቅም የሞገተልን ትንታጉ ወንድም ሶሻል እድሜው ከ30ዎቹ የማያልፍ ገና ጎልማሳ ነው ። ሱሌማን ኑሮውን ያደረገው በሳውዲ አረቢያ ዋና ከተማ በሪያድ አድርጎ ለአመታት በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ግብፅና ደጋፊ አረቦች የሚያሰራጩትን ረብ የለሽ የተሳሳተ ስሁት መረጃ ያከሸፈ ጀግናችን ሱሌማን አብደላ ነው። እሱ የግብፅና የደጋፊ አረቦች ቀንደኛ ጠላት የእኛ የቁርጥ ቀን ልጃችን ወንድማችን ነው ። 📍 ሱሌማን አብደላ የሰጠኝ ቃል ‼️ ======================== ወንድም ሱሌማን አብደላን በቅርብ አውቀዋለሁ ። ባንድ ወቅት ከአረቦች ጋር በገጠመው የህዳሴ ግድብ የፕሮፖጋንዳ ፍጥጫ ስሙ ገናና እያለ ስልክ ደውየለት አወራን ። እንዲህም አልኩት ሱሌማን አንተ አሁን ታዋቂ ሆነሃል ። ስለ ዜጎችም ድምጽ ሁንልን እባክህ አልኩት ። እንዲህ ሲል መለሰልኝ " ስለ ዜጎች አንተ በቂ ነህ ። የዜጎች ችግር ጊዜያዊ ነው ። እኔ ስለ ትልቁ የህዳሴ ግድብ ልታገል ። ህዳሴ ግድብ እውን ሲሆን ድህነት የሚገፋው የዜጎች ስደት ያቆማል ። አንተም በርታ እኔም እበረታለሁ " ብሎ የሰጠኝ ቃል በህሊናዬ መቸም አይጠፋም ... 📍.ግብፅና አረቦች ተቋም የሚሉት ሱሌማን ... ============================== የምናውቀው ተራ ጎልማሳ ይምሰለን እንጅ በአረቦች ዘንድ ሱሌማን ሌላ አስፈሪ ግርማና መልክ አለው ። አረቦች "ሱሌማን አብደላ "ሲባል በሳውዲና በአረብ አገራት ከነበሩት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ዲፕሎማቶቻችን በላይ ይፈሩታል ። በአረብ አገር ስደት ላይ እያለሁ እሰራበት በነበረው የሳውዲ - ጀርመን አለም አቀፍ ኩባንያ አብሮኝ ይሰራ ከነበረ ግብጻዊ ጋር ስንገናኝ ዋና ርዕሳችን የሱሌማን አቅምና የአለማ ጽናት እንደነበር አይዘነጋኝም ። ከግብፃዊ ወዳጄ ጋር በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ስንወያይ ሱሌማን ሃገር ወገኑን ወዳድ መሆኑን ጠቅሸ ከመንግሥት ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው ተራ ዜጋ ነው ስለው አያምነኝም ነበር ። እሱ እንደተቀሩት ወገኖቹ ሱሌማን ተቋም ነው ብሎ ያምናል ... ለግብፃዊው ወዳጄም ሆነ ለብዙ አረቦች ሱሌማን ተቋም ነው የሚሉት ለምን እንደሆነ ይገባኛል ። እሱ ሱሌማን አብደላ የግብፆች ስሁት መረጃ እንደ ተቋም አነፍንፎ ወደፊት በማምጣት በግብረ መልሱ ልካቸው የሆነ ምላሽ ይሰጣቸዋልና ነው ። በቀድሞው ትዊተር ገጹ በሰፊው ያቀርብ በነበረው መረጃ ትልቅ አቅምም ሱሌማን ከፍተኛ በጄት ተመድቦለት በሚሰራ ተቋም የሚመራ የፕሮፖጋንዳ ክንፍ ነው እንጅ ሱሌማን አንድ ወጣት ጎልማሳ ነው ብለው አያምኑም ። የህዳሴው ግድብ ተሟጋች ሱሌማን ለግብፃውያኔና አረቦች ዘንድ በመንግሥት የስለላ መዋቅር የሚጠበቅ አንድ ሰው ብቻ አይደለም ። ሱሌማን ማለት ለእነሱ ብዙ የፕሮፖጋንዳ ሰዎች በአንድ ላይ በአንድ ሱሌማን አብደላ ስም በወጉ ተደራጅተው መረጃ በመንግሥት እየተሰጣቸው በህዳሴ ግድብ ሌት ተቀን የሚሞግቱ እስከ አስር ያህል ሰዎች ናቸው ። በቅርብ የምናውቀው ሱሌማን ለግብፆች በመካከለኛው ምስራቅ የተቀመጡ የፕሮፖጋንዳ ሰራዊት እንደሆኑ አድርገው ያምናሉ ። ሱሌማን አንድ ሰው አልነበረም የሚሊዮን ኢትዮጵያዊ ድምጽና ምልክት ነው እንጅ ... 📍ላለመስማማት የምንስማማባቸው ጉዳዮች... =============================== እኛ በምናውቀውና አረቦች የማያውቁት በሱሌማን አብደላ ዙሪያ ከማውቀው ጥቂቱን ልጨምርላችሁ ። በቅርብ ከማውቃቸው ግብፃዊና አረቦች የሱሌማንንም ሆነ የህዳሴን ግድብ ስም አንስተን ስንጨዋዎት በሉት ስንወያይ የምንለያየው ሳንስማማ ነው ። ክስተቱን ሳስታውሰው ላለመስማማት የምንስማማባቸው ጉዳዮች ብዬ ስም እሰጠዋለሁ። " ሱሌማን የኢትዮጵያ የፕሮፖጋንዳ ሰራዊት ስም ነው " ሲሉኝ ብሽቅ እላለሁ። በአጓጉል ሙግታቸው ተናድጄ ሱሌማን ከመንግሥት አካላት ፍጹም ግንኙነት የሌለው ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ሆነ ከስለላ ተቋሙ ምንም አይነት ጥቅም የማያገኝ ኩሩ ኢትዮጵያዊ መሆኑን እገልጽላቸዋለሁ። እነሱ ግን ሁሌም ይህ መረጃዬ አይዋጥላቸውም ። ፈጽሞ አይቀበሉትም ። እንደ ትልቅ ተቋም የሚታይ የሚፈራውን የህዳሴውን ዋና ጠበቃ ወንድም ሱሌማን አብደላን ባላስታውሰው ክብሩን የነካሁና እና ብዙ ያጎደልኩበት ይመስለኛልና ይህን የምስክርነት ማስታወሻ ለመጻፍ ተነሳሁ... 📍ስለጎልማሳው ሱሌማን ልመሰክር መጣሁ ... ============================= ወንድም ሱሌማን አብደላ ለእኔና ለእናንተ ይህ ከዚህ በፊት ባላያላችሁት ፎቶ የምታዩት አንድ ሀገር ወገኑን ወዳድ ጎልማሳ ነው ። ለአረቦች ግን ስሙና ምስሉ ሀሰተኛ የሆነ መንግሥት የመደባቸው በጄት የመደበለት ታላቅ ፕሮፖጊንዳ ሰራዊት አድርገው ነው የሚቆጥሩት ብርቱ ተጋድሎ ያደረገ ባለውለታ ነው ። ትናንት በግድቡ ምርቃት ዋዜማና በምርቃቱ እለት በተሰራጩ መረጃዎች የቀደመው የወያኔና የብልፅግና መንግሥት ደጋፊ ካድሬዎች ታላቁን ባለውለታ ሱሌማን አብደላን ማስታወስ ተስኗቸው ተመለከትኩ ። ከምር አዘንኩ😢 እናም የተዳፈነ እውነት አለና ደፍሬ እውነቱን ልመሰክር መጣሁ እንጅ ከቶ ከማንም ጋር ታሪክ ልሻማ እና ልበሻሸቅ አልመጣሁም ‼️ 📍ስለ ሱሌማን አብደላ ክብር ባንድ እንቁም... ============================== ዛሬ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ታላቅ የምረቃ ቀን መባቻ ከውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤትም ሆነ ከታዋቂ ሰዎቻችን በላይ ስለ ግድቡ የታገለውን ወንድም ማስታወስ ግድ ብሎኛል ። ወንድሜ ሱሌማን ሆይ እነሆ የታገልክበት ፣ የታሰርክ የተንገላታህበት ፣ ስለ ዜጎችም ድምጽ ሁን ስልህ " ስለ ዜጎች አንተ በቂ ነህ ። እኔ ስለ ትልቁ የህዳሴ ግድብ ልታገል ። ህዳሴ ግድብ እውን ሲሆን ድህነት የሚገፋው የዜጎች ስደት ያቆማል ። አንተም በርታ እኔም እበረታለሁ " ያልከኝን እውን ይሆን ዘንድ ግድቡ ተመርቋል ... ድህነት ገፋኢ የሆነው ስደቱ ነገ ማቆሙ ቀርቶ ከቀነሰ ደስታዬ ነው ። ዛሬ አንተ እኔ የሀገር የወገን እዳ የለብንም ስል ደፍሬ እናገራለሁ ። እዳ ያለባቸው ስለ ሀገርና ወገናቸው ታምነው ይሰሩ ዘንድ ፊታችን ወደ ፈጣሪ ከማዞር የተሻለ አማራጭ አለ ግን አልልም ... ወንድማለም ሱሌማን አብደላ ዛሬ ህዳሴው እውን እንዲሆን ስላደረግከው ተጋድሎ ከፍ ያለ የአድናቆት ምስጋናዬን ሳቀርብልህ ባለህበት በማይመቸው ቦታ ታላቅ ክብርና ኩራት ስንቅ ይሁንህ ብዬ ተመኘሁ 🙏
221