ዜና ቅዱሳን
Open in Telegram
በዜና ቅዱሳን መርሐ ግብር ላይ ያላችሁን ሀሳብ አስተያየትና ጥቆማ @abrishte ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ
Show more842
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
842
🕤🕤የየካቲት ፲፬ ስንክሳር🕗🕗
🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀
🍁#ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳሳት ዘእስክንድርያ🍁
❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️
🌿🌿#እንኳን ለእስክንድርያ ሀገር ሰባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት ለአባ ቄርሎስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
❇️#ይህም አባት ፍዩም ከምትባል አገር ነው። በእርሷም ቅስና ተሹሞ ኖረ ከዚህም በኋላ ከዚያ፡ ለቆ ከምስር ከተማ ውጭ ወደ ሆነች የኢትዮጵያውያን የጒድጓድ ውኃ ወዳለበት ወደ ቅዱስ ፊቅጦር ገዳም ደረሰ በውስጡም ታላቅ ተጋድሎን እነተጋደለ ብዙ ዘመናትን ኖረ።
❇️#የዕውቀቱና የቅድስናው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ውዴታው ይዘው በእስክድርያ አገር ሊቀ ጵጵስና ሾሙት መንጋውንም በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ በቊርባንና በጸሎት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሊሠሩት የሚገባቸውን ለካህናት ሦርዓትን ሠራ። በሹመቱም ሰባት ዓመት ከዘጠኝ ወር ከሃያ ሰባት ቀን ኑሮ የካቲት14 በሰላም ዐረፈ።
🙏🙏#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏#
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
842
🕤🕤የየካቲት ፲፬ ስንክሳር🕗🕗
🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀
🍁#ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ያዕቆብ ሊቀ ጳጳሳት ዘእስክንድርያ🍁
❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️
🌿🌿#እንኳን ለእስክንድርያ ለኃምሳኛ ሊቀ ጳጳስ በጸሎቱ አንድ ሙት ላስነሳ ለከበረ አባት ለአባ ያዕቆብ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ከዳርዮስ፣ ከጳውሎስ፣ ከአኩደራስና ከሊድና ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።👆👆❤️
❇️#ይህም አባት እልመቱዝ ለተባለ የግብጽ ንጉሥ በነገሠ በ17 ዓመት ተሾመ እርሱም ለመኰንኑ ለወልደ ኀሮን ረሽድ ወንድም የሆነ ነው፡ በዚህም አባት ዘመን የአስቄጥስ ገዳማት ታድሰው መነኰሳቱ ወደሳቸው ተመለሱ።
❇️#አፎን በሚባል አገር ስሙ መቃርስ የሚባል ሰው ነበር ወደዚህ አባት ወደ ያዕቆብ መጥቶ ወደቤቱ በመሔድ ቤቱን ይባርክለት ዘንድ ለመነው እርሱም አብሮት ሔደ ታሞ የነበረ ልጁም ሞተ ወደ አባ ያዕቆብ አቅርቦ እንዲህ ብሎ ለመነው "ከርሱ በቀር ልጅ የለኝምና አባቴ ሆይ ራራልኝ እርሱም እነሆ ሞተ ስርሱ፡ ወደ እግዚአብሔር ትማልድ ዘንድ እለምንሃለው" አለው። አባ ያዕቆብም "እንደ እምነትህ ይሁንልህ አትፍራ" አለው። ሕፃኑንም ከአባቱ ተቀብሎ ታቀፈውና በላዩ ጸለየ በመስቀል ምልክትም አማተበበት ስለርሱም ወደ እግዚአብሔር ለመነ ጌታችንም ልመናውን ተቀበለው የሕፃኑ ነፍስ ተመልሳ ዐይኖቹን ገለጠ ከሞትም ድኖ ተነሣ አባቱንም "ልጅህን ውሰድ የሞተ አይደለም ያንቀላፋ ሁን ነው እንጂ" አለው። የሕፃኑም አባት ይህን ድንቅ ሥራ በአየ ጊዜ እጅግ ፈራ የገንዘቡንም እኩሌታ ለምጽዋት ብሎ ሰጠው እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ልኮ ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን ሁሉ ወደርሷ በመጡ ጊዜ መጠጊያ ይሆን ዘንድ ቤተ ክርስቲያንን ሠራበት።
❇️#የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ዲዮናስዮስም ወደ ምስር በመጣ ጊዜ ከአባ ያዕቆብ ጋር ተቀምጦ ወደ አገሩ ተመለሰ። ይህ አባት ያዕቆብ በሹመቱ ዐሥር ዓመት ከስምት ወር፡ ከሦስት ቀን ኑሮ የካቲት14 በሰላም ዐረፈ።
🙏🙏#ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ያዕቆብ በጸሎቱ ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏#
#ምንጭ፦ የየካቲት 14 ስንክሳር።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
842
🕤🕤የየካቲት ፲፬ ስንክሳር🕗🕗
🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀
🍁#ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳሳት ዘአንጾኪያ🍁
❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️
🌿🌿#እንኳን ለታላቁ አባት ሃይማኖታቸው ለቀና ምዕመናን መምህራቸው ለሆነ ለአንጾክያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት ለአባ ሳዊሮስ ለዕረፍቱ በዓል፣ በሰላም አደረሰን።
❇️#የዚህ ቅዱስ ዘመዶቹ ከሮሜ አገር ናቸው አባቱም ስሙ ሳዊሮስ የሚባል ኤጲስቆጶስ ነው። እርሱም ስለ ንስጥሮስ በኤፌሶን ከተማ ጉባኤ በሆነ ጊዜ ከሁለት መቶ አባቶች ኤጲስቆጶሳት ጋር መጣ በዚያም እንዲህ የሚለውን ራእይ አየ "ከአንተ የሚወለድ ልጅህ ስሙም እንደ ስምህ ሳዊሮስ ተብሎ የሚጠራ እርሱ ለቀናች ሃይማኖትን" ያጸናታል።
❇️#ይህም ኤጲስቆጶስ በዐረፈ ጊዜ ልጁን ሳዊሮስ ብለው ጠሩት ከቤተ ክርስቲያን ውጭ የሆነውን ጥበብን ሁሉ ተማረ። ከመምህሩም ወጥቶ ወደ አንድ ቦታ ሲጓዝ በዋሻ ራሱን እሥረኛ አድርጎ የሚኖር ጻድቅ ሰው ተገናኘው በእርሱም ደስ ብሎት "የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ሃይማኖታቸው ለቀና ምዕመናን መምህራቸው የሆንክ ሳዊሮስ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው" አለው። ሳዊሮስም ከቶ ሳያውቀው በስሙ በጠራው ጊዜ የሚደረግለትንም ከመሆኑ አስቀድሞ በመናገሩ አደነቀ።
❇️#ከዚህም በኋላ ሳዊሮስ ትሩፋት በመሥራት አደገ መልካም ስም አጠራሩና ዜናው ተሰማ በአባ ሮማኖስ ገዳም መንኵሶ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ በትሩፋትም ሥራ እጅግ የተጠመደ ሆነ የከበረ ወንጌል "በተራራ ላይ የተሠራች መንደር መሠወር አትችልም" እንዳለ ዜናው በሁሉ ዘንድ ተሰማ። የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳትም በዐረፈ ጊዜ አዋቂዎች ኤጲስቆጶሳት ይህን የከበረ ሳዊሮስን ይሾሙት ዘንድ ተስማምተው ያለ ውዴታው ወስደው በአንጾኪያ አገር ላይ ጵጵስና ሾሙት በሹመቱም እስከ ዓለም ዳርቻ ያለች ቤተ ክርስቲያን ብርሃን ሆነላት በአገሮች ሁሉ ወዳሉ መናፍቃን ከሀድያን ትምህርቱ በሚደርስ ጊዜ ሁለት አፍ እንዳለው ስለታም ሰይፍ ሥራቸውን ይበጥሳልና።
❇️#ከጥቂት ቀኖችም በኋላ አማኒ ንጉሥ ሙቶ በርሱ ፈንታ ስሙ ዮስጥያኖስ የሚባል መናፍቅ ነገሠ ንግሥቲቱ ሚስት ግን ሃይማኖቷ የቀና ነው ስማ ቴዎድራ ይባላል። ንጉሡም የኬልቄዶን ወደ ሆነች ወደረከሰች ሃይማኖቱ ይህን የከበረ አባት ያስገባው ዘንድ ያስፈራራው ነበር እርሱ ግን ፈርቶ አይትዘዝለትም ቊጣውንም የሚፈራ መስሎት በእርሱ ላይ አብዝቶ ተቆጣ ቊጣውንም ባልፈራ ጊዜ በሥው፡ ሊያስገድለው መከረ ንግሥቲቱም አውቃ ከንጉሡ ፊት ይሸሽ ዘንድ ሊቀ ጳጳሱን መከረችው እርሱም በሥውር ወጥቶ ገለል አለ። እግዚአብሔር የዚህን አባት ሞት አልፈቀደምና ስለ ምእመናንም ጥቅም ጠበቀው። በአንድ ተራ መነኵሴ አምሳል ሁኖ፡ በቦታዎችና በገዳማት የሚዘዋወርና ምእመናንን የሚያጠናክራቸው ሆነ ስካ በሚባል አገር ስሙ ዶርታኦስ ከሚባል ደግ ምእመን ባለ ጸጋ ሰው ዘንድ ተምጦ ሳለ ጌታችን በእጆቹ ብዙ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ስካ በተባለ አገር እስከ ዐረፈ ድረስ በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ሁሉንም ያስተምራቸው ነበር ከዚህም በኋላ ወደ ዝጋግ ገዳም አፈለሱት።
🙏🙏#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ሳዊሮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።🙏🙏#
#ምንጭ፦ የየካቲት ፲፬ ስንክሳር
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕤🕤2🕤🕤
🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀
##ርእሰ ገባሕታውያን ገዳማዊ አባ ጳውሊ
##አባ/አቡ/ ለንጊኖስ♥♥
🙏🙏ሰአሉ ለነ ጻድቃን ወሰማዕት
ቅድመ መንበሩ ለጸባዖት
አድኅኑነ እምዕለት እኪት
ወባልሑነ እምኵሉ መንሡት
ለዓለመ ዓለም አሜን!!!!#
☞የዓለም ብርሃን የሆናችሁ
ጻድቃንና ሰማዕታት ሆይ
ከሥላሴ መንበር ፊት ለምኑልን
ከዕለት መከራና ስቃይ አድኑን
ከፈተና ሁሉ አድኑን
ለዘለዓለም አሜን!!!!
ጸሎታቸው፣በረከታቸውና ረድኤታቸው በኛ ላይ ለዘለዓለም ይደር!!!!አሜን!!!!!
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕤🕤የየካቲት ፪ ስንክሳር🕗🕗
🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀
🍁#አቡነ/አቡ/ ለንጊኖስ ዘደብረ ዝጋግ 🍁#
❇️#እንኳን ከእስክንድርያ ውጭ ለደብረ ዝጋግ ገዳም አበ ምኔት የቅዱሳን ዐፅም ቃል በቃል በማጋገር የሃይማኖት ነገር ለተረዳ ለከበረ አባት ለአባ ለንጊኖስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።❇️
❇️#ይህም ቅዱስ ከኪልቅያ አገር ነው በዚያም መነኰሰ መምህሩም ክርስቶስን የሚወድ ሰው ከሚሰጠውም ክብር የሚሸሽ ነበር። በዚያንም ጊዜ የገዳማቸው አበ ምኔት ዐረፈ ይህንንም ስሙ ሉክያኖስ የተባለ አረጋዊ መምህሩን አበ ምኔትነት ሊሾሙት መነኰሳቱ ወደዱ እርሱም ደቀ መዝሙሩን ለንጊኖስን ይዞ በጭልታ ከኪልቅያ ወጥቶ ወደ ሶርያ አገር ሔደ በአንዲት ቤተ ክርስቲያንም ግቢ በአንድነት ተቀመጡ በእጆቻቸውም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን ያደርግ ዘንድ ከንቱ ውዳሴና ክብር ሆነባቸው።
❇️#አባ ለንጊኖስም በመምህሩ ምክር ወጥቶ ወደ ግብጽ አገር ሔደ ወደ ደብረ ዝጋግ ገዳምም በገባ ጊዜ በደስታ ተቀበሉትና ከእርሳቸው ጋራ ኖረ ከዚያም በኋላ አበ ምኔቱ ዐረፈ ተጋድሎውን ትሩፋቱንና ደግነቱን ስለ አወቁ በደብረ ዝጋግ ገዳም ላይ አባ ለንጊኖስን አበ ምኔት አድርገው ሾሙት። ከጥቂትም ወራት በኋላ መምህሩ አባ ሉክያኖስ መጣ የመርከቦችን ጣሪያዎች እየሠራ በእጆቻቸውም ከሚሠሩት እየተመገቡ በአንድ ልብ በመሆንም በአንድነት ኖሩ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ብዙዎች የሆነ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ከዚህም በኋላ አባ ሉክያኖስ ዐረፈ።
❇️#የኬልቄዶንን ጉባኤ በሰበሰበ በከሀዲው መርቅያኖስም ዘመን ወደ አገሮችም ሁሉ መልእክተኞችን ላከ ከእርሳቸውም ጋር አንዱን ክርስቶስን ወደ ሁለት ባሕርይ የምትከፍል የረከሰች የሃይማኖቱ ደብዳቤ አለች። ከንጉሥ መልእክተኞች ሦስቱ ወደ ደብረ ዝጋግ በደረሱ ጊዜ ያንን ደብዳቤ ለአባ ለንጊኖስ ሰጡት በዚህ "ጽሑፍ እንድታምኑ በውስጡም እንድትፈርሙ ንጉሥ መርቅያኖስ አዝዞአል" አሉት። አባ ለንጊኖስም "ከቅዱሳን አባቶቼ ጋር ሳልማከር እኔ ምንም ምን መሥራት አልችልም እንድንማከርም እናንተም ከእኔ ጋር ኑ" አላቸውና የቅዱሳን በድኖች ወደ አሉበት ዋሻ ውስጥ አስገባቸውና "የከበራችሁ አባቶቼ ሆይ እናንተ ዐርፈን ተኝተናል አትበሉ እነሆ አንዱን ክርስቶስን ሁለት ባሕርይ የሚያደርግ በውስጡ የተጻፈበትን ይህን ደብዳቤ አምጥተዋልና በቃሉ አምን ዘንድ በውስጡም እፈርም ዘንድ ታዙኛላችሁን ወይም አታዙኝም የምሠራውንም ካልነገራችሁኝ ሕያው እግዚአብሔር ዐፅማቻችሁን ከዚህ ቦታ አወጣለሁ" አላቸው።
❇️#ያን ጊዜ ሰዎች ሁሉም እየሰሙ ከአስከሬናቸው "የአባቶቻችንን የሐዋርያትንና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱን የቀናች ሃይማኖትን አትተው ይህንንም የረከሰ ደብዳቤ አትከተል ከአስከሬናችን ቦታ አርቀው እንጂ" የሚል ቃል ወጣ የንጉሥ መልክተኞችም ይህን ነገር ሰምተው እጅግ አደነቁ በላያቸውም ታላቅ ፍርሀት አደረባቸው ወደ ንጉሡም አልተመለሱም ራሳቸውን ተላጭተው መነኰሱ እንጂ እስከ ዐረፉም ድረስ ብዙ ዘመን እየተጋደሉ ኖሩ። የከበረ አባ ለንጊዮስ ያማረ ተጋድሎውን ጨርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ የካቲት 2 ቀን በሰላም ዐረፈ የሕይወት አክሊልንም ተቀበለ።
🙏🙏#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ለጊዮኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።🙏🙏
#ምንጭ፦ የካቲት 2 ስንክሳር።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕤🕤የየካቲት ፪ ስንክሳር🕗🕗
🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀
🍁#ተአምረ ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ🍁#
❇️#እንኳን ለከበረ ለሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አንድ ከይሲ ነድፎ የገደለው ሰው ተምራትን በማድረግ ከሞት ላስነሳበትና ከይሲውን በመግደል ብዙዎችን አስተምሮ ላጠመቀበት በዓል፣ በሰላም አደረሰን።
❇️#ጌታችን ወደ አዘዘው ሊአስተምር በወጣ ጊዜ ከመንገድ ጥቂት ፈቀቅ አለ ድንገትም የሞተ ጐልማሳ አየ መልኩ እጅግ የሚያምር ነበር ሐዋርያውም "አቤቱ ይህን ጥፋት አይ ዘንድ ወደዚህ አመጣኸኝን ነገር ግን ፈቃድህ ይሁን" አለ።
❇️#ከዚህም በኋላ ስለሞተው ሰው ጸለየ ያን ጊዜ ታላቅ ከይሲ ከደንጊያዎች ውስጥ ወጥቶ በጅራቱ ምድሩን እየደበደበ መጣ "የክርስቶስ ሐዋርያ ሆይ እኔ ካንተ ጋር ምን አለኝ ሥራዬን ልትዘልፍ መጣህን" ብሎ በታላቅ ድምጽ ጮኸ ሐዋርያውም "አዎን ሥራህን ተናገር" አለው። ከሲውም እንዲህ አለ "በዚህ ቦታ አንጻር መልከ መልካም ሴት ነበረች እኔ የምወዳት ናት ይህም ጐልማሳ ሲሰማት አየሁት በሰንበት ቀንም ከርሷ ጋር አደረ ስለዚህም ነክሼ በመርዝ ገደልኩት" ሐዋርያውም "መርዝህን ከሱ ትወስድ ዘንድ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝዤሃለሁ" አለው። ሒዶም ከዚህ ከሞተው መርዙን መጠጠና ወሰደ ወዲያውኑ ተነፍቶ አበጠ ተሠንጥቆም ሞተ የሞተውም ሰው ድኖ ተነሣ። ስለዚች ምልክትም ብዙዎች በክብር ባለቤት ጌታችን አመኑ እርሱም ሃይማኖትን አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።
🙏🙏#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው በአባታችን በቅዱስ ቶማስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏#
#ምንጭ፡-የየካቲት 2 ስንክሳር
🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔
🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
❇️# "ዳግመኛም ይህ ስም ያልፋል ስማቸውም መነኰሳት ይባላሉ እነርሱም ብዙ ዘመናት ደስ ይላቸዋል እግዚአብሔርም ከቁጣው ቀን አስቀድሞ ከዚያ ያፈልሳቸዋል። ከእነርሱም በኋላ ሰምተው ለመምህሮቻቸው የማይታዘዙ ትውልድ ይነሣሉ ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት በቀንና በሌሊት የማይተጉና የማይጸልዩ ናቸው። ያን ጊዜ እግዚአብሔር ተቆጥቶ ይፈርዳል የማያስተውሉ ሕግ የሌላቸው አረማውያንም ተነሥተው ገዳማቱንና አድባራቱን ያጠፋሉ ብዙ ዘመናትም ምድረ በዳ ይሆናሉ የቅዱሳን መታሰቢያቸው አይጠፋም እግዚአብሔርም በሌሎች ሰዎች ልቡና ይቅርታውን ያሳድርባቸዋል እነርሱም ወደ ገዳማቱና ወደ አድባራቱ በመሔድ በውስጣቸው ዳግመኛ ይኖራሉ ሰይጣንም ወደ ገዳማት ሔዶ በመካከላቸው ጸብን ይዘራል እነርሱም የእግዚአብሔርን ፍቅር ገንዘብ በማድረግ ጨክነው አልታገሡባትምና ምንኵስናቸውን አስኬማቸውን ትተው ወደ ዓለም ይወርዳሉ "በትዕግሥታችሁ ነፍሳችሁን ገንዘብ ታደርጓታላችሁ" የሚለውን ጽሑፍ አላስተዋሉምና"።
❇️#እንጦንዮስም "የከበርክ አባቴ ጳውሊ ሆይ ፊትህን አይ ዘንድ የታደልኩባት ሰዓት የተባረከች ናት" አለ። የከበረ አባ ጳውሊም "አሁን ወደ ማደሪያህ ሒድ ቈስጠንጢኖስ ለሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስ የሰጠውን ልብስ እርሱም አንተን ያለበሳትን ያቺን ከአንተ ጋር ይዘሃት ና ሥጋዬን በርሷ ትገንዝ ዘንድ" ብሎ ተናገረው የተሠወረውን በማወቁ እጅግ አደነቀ የተነበየለትንም ትንቢት ሁሉ አመነ። ዳግመኛም እንዲህ አለው "በሰው ሁሉ ላይ እንደተሠራ ከዓለም የምወጣበት ጊዜዬ ቀርቧልና ፈጥነህ ሒድና ተመለስ እርሱም ከአባ ጳውሊ ዘንድ ወጥቶ ወደ በዓቱ እስኪደርስ የሁለት ቀን ጎዳና ተጓዘ ያቺንም ልብስ ይዞ ተመለሰ በመንገድም እየተጓዘ ሳለ በአየር ውስጥ አባ ቡላን የመላእክትንም ማኅበር አየ "ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን" ይሉ ነበር።
❇️#ሁለተኛም "እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የመረጠህ ሰላምታ ፍቅር አንድነት ይገባሃል የእግዚአብሔር ሰው አንተ ጳውሊ የተመሰገንክ ነህ እንግዲህስ በሰማያዊ መንግሥት ከመላእክት ጋር ደስ ይበልህ የጨለማውን ዓለም ትተህ የብርሃን ሀገርን አግኝተሃልና ወደ ዘላለማዊ ተድላ ደስታ ይወስዱሃልና የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆንክ አንተ ገዳማዊ ጳውሎስ በትውልድህ የከበርክና የተመሰገንክ ነህ" እንዲህ እያሉ ተሠወሩ።
❇️#የከበረ እንጦኒም "ይህች ወደ ሰማይ የሚያሳርጓት የአባቴ የጳውሊ ነፍስ ናት" አለ ወደ በዓቱም በገባ ጊዜ እንደ ሰገደ ሁኖ እጆቹም በመስቀል ምልክት ተዘርግተው አገኘው አንሥቶም ሸፈነው "አባቴ ሆይ በሰማያዊ ማደሪያህ ሁነህ አስበኝ" ብሎ በላዩ አለቀሰ።
❇️#ከዚህም በኋላ ተነሥቶ በዚያች ልብስ ሥጋውን ገነዘና በላዩ የቤተ ክርስቲያንን የጸሎት ሥርዓት ፈጸመ አደረሰም ከዚህም ቀጥሎ ከእርሱ ጋር የተማከርኩት ነገር የለም ምን ላድርግ ብሎ አሰበ በዚያንም ጊዜ አንበሶች መጡ እጅ ነሡትም ቀድሞ እንደሚያውቁትም ዘንበል ብለው የእግሩን ትቢያ ላሱ መቃብሩን በየት ቦታ እንቆፍርለት እንደሚሉ አመለከቱት እርሱም ምልክታቸውን አውቆ በቁመቱ ልክ ለክቶ ሰጣቸው አንዱ በራስጌ አንዱ በግርጌ ሁነው ቆፈሩ በአደረሱም ጊዜ "በቃችሁ" ብሎ አመለከታቸው እሊህ አንበሶችም ወጥተው ሰገዱለት። እርሱም ባረካቸውና ወደ ቦታቸው ሔዱ የከበረ እንጦኒ ወደ መቃብር አስገብቶ ዘጋው። ከሰኔል ቅጠልም የተሠራች ዐጽፉን ወሰደ የአባቱን ገንዘብ እንደሚወርስ ልጅ ነውና ወደ እስክንድርያም ሔደ፡፡ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም ገብቶ ከከበረ አባ ጳውሊ የሆነውን ሁሉ ነገረውና ያቺን ከሰኔል የተሠራች ዐጽፍ ሰጠው።
❇️#ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም የከበረ ጳውሊን ዜና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ያቺንም ዐጽፍ ተቀብሎ በእርሱ ዘንድ አኖራት በየዓመቱም በከበረ በልደት በዓል በጥምቀትም በዓል በመድኃኒታችን ክርስቶስ ትንሣኤ በዓልም ሦስት ጊዜ ይለብሳት ነበር።
❇️#ጌታችንም የቅዱስ ጳውሊን የልብሱን ክብር ሊገልጥ ወደደ በዚያችም ወቅት አንድ ወጣት ልጅ ሞተ አባ አትናቴዎስም ያቺን ልብስ በሞተው ላይ አኖራት ወዲያውኑ ተነሣ ይህንንም ያየ ኤጲስቆጶስ አባ ኤስድሮስ ምስክር ሆነ ይችም ተአምር በአገሮች ሁሉ ተሰማች።
🙏🙏#ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ በአባ ጳውሊ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።🙏🙏#
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕤🕤የየካቲት ፪ ስንክሳር🕗🕗
🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀
🍁#ርዕሰ ገዳማውያን ወባሕታውያን(መናንያን) አቡነ ጳውሊ🍁#
❇️#እንኳን ለመላእክት ወገን ለሆነ ለገዳማውያን ባሕታውያን (መናንያን) ሁሉ አለቃ ለሆነ ለከበረ ለታላቁ አባት ለአባ ጳውሊ ለዕረፍት በዓል፣ በሰላም አደረሰን።
❇️#ይህም ቅዱስ ከእስክንድርያ አገር ጴጥሮስ የሚባል ወንድም አለው አባታቸውም የገንዘቡ ብዛት ሊቈጠር የማይቻል እጅግ ባለጸጋ ነበር በዐረፈም ጊዜ የኀዘናቸው ቀን ሲፈጸም ርስቱንና ገንዘቡን ሊካፈሉ ጀመሩ ጴጥሮስም ታላቁን ክፍል ወደራሱ በመውሰድ የሚያንሰውን ለጳውሊ የሚሰጠው ሆነ። ስለዚህም ጳውሊ አዘነና "ከአባቴ ርስት በትክክል ለምን አትሰጠኝም?" አለው እርሱም "አንተ ወጣት ስለሆንክ ታባክነዋለህ እስከ ምታድግ እኔ እጠብቅልሃለሁ" ብሎ መለሰለት።
❇️#ስለዚህም ጳውሊ ተቆጣና እርስ በርሳቸው ተጣሉ ይፈርድላቸውም ዘንድ ወደ ዳኛ ሔዱ እነርሱም ወደ ዳኛ ሲሔዱ ሰዎች ተሸክመውት ወደ ሚቀብሩበት ሲወስዱት ብዙዎችም የተከተሉትን የሞተ ሰውን አገኙ ጳውሊም ከተከተሉት አንዱን ሰው "ዛሬ የሞተው ማን?" ነው ብሎ ጠየቀው። ያም ሰው እንዲህ ብሎ መለሰለት "ልጄ ሆይ ዕወቅ አስተውል ይህ የሞተ ሰው በወርቅ በብር እጅግ ባለጸጋ የሆነ ሁል ጊዜ ደስ የሚለው ነበር አሁንም እነሆ ይህን ሁሉ ትቶ ራቁቱን ወደ መቃብር ወደማይመለስበት መንገድ ይሔዳል በኃጢአት ማዕበል ውስጥ እያለ ሙቷልና። አሁንም ልጄ ሆይ ስለ ነፍሳችን ድኅነት ልንታገል ይገባናል እኛ መቼ እንደምንሞት አናውቅምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ውስጥ ገንዘብ ኑሮት ሥልጣንም ኑሮት ሳለ ይህን ሁሉ የተወ የተመሰገነ ነው እርሱ የቅዱሳን ሀገር በሆነች በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ታላቅ ክብርን ይቀበላልና"።
❇️#የከበረ ጳውሊም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ከልቡ አዘነ እንዲህም አለ "የዚህ የኃላፊው ዓለም ገንዘብ ምኔ ነው ምን ይጠቅመኛል ከጥቂት ቀኖች በኋላ ትቼው ራቁቴን የምሔድ አይደለሁምን" አለ። ከዚህም በኋላ ወደ ወንድሙ ተመልሶ "ወንድሜ ሆይ ወደ ቤታችን እንመለስ ከእንግዲህ ስለ ገንዘብ ምንም ምን ከአንተ ጋር አልነጋገርም" አለው።
❇️#ከዚህም በኋላ ከወንድሙ ሸሽቶ ከሀገሩ ወጣ ከመቃብር ቤት ውስጥም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት መንገዱን ይመራው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እየጸለየና እየማለደ ኖረ። ወንድሙ ጴጥሮስም በሀገር ውስጥ እየዞረ ሲፈልገው ሰነበተ ግን አላገኘውም ታላቅ ኃዘንንም አዘነ። የተመሰገነ ጳውሊ ግን ሦስት ቀኖች ያህል በዚያች መቃብር ቤት ሲኖር መብልና መጠጥን አላሰበም ፍርሀትና ድንጋፄም አልደረሰበትም አምላካዊ ኃይል ትጠብቀው ነበርና።
❇️#በአራተኛዪቱም ዕለት እግዚአብሔር ወደርሱ መልአኩን ላከ ከዚያም ነጥቆ ወሰደው በምሥራቅ በኵል በምትገኝ በረሀ ውስጥ አኖረው በዚያም የውኃ ምንጭ አለ መልአኩም ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ የከበረ ጳውሊም አራዊት የሚኖሩበትን ጒድጓዶች አግኝቶ ወደ አንዲቱ ፍርኩታ ገባ ልብሱንም ሰኔል ሠርቶ ለበሰ። እንዲህም ብሎ ጸለየ "የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርኀራኄ ከሌለው ጠላት እጅ ጠብቀኝ አድነኝም ተጋድሎዬን እስከምፈጽም ተጸናኝ ዘንድ ቸርነትህ ወደእኔ ትምጣ የትውልድ ሁሉ ንጉሥ ሆይ ኃይል ጌትነት ክብር ገንዘብህ ነውና ለዘላለሙ"።
❇️# በዚያችም ዋሻ ውስጥ ሰማንያ ዓመት ኖረ ከሰውም ከቶ ማንንም አላየም ልብሱም ከሰኔል ቅጠል የተሠራ ነው እግዚአብሔር ወደ ማታ ሁል ጊዜ ወደርሱ ቁራን ይልክለታል ከርሱም ጋራ ግማሽ እንጀራ አለ ያንን ለከበረው ጳውሊ ይሰጠዋል።
❇️#የክብር ባለቤት እግዚአብሔርም ቅድስናውንና ጽድቁን ይገልጥ ዘንድ በወደደ ጊዜ መልአኩን ወደ ታለቅ አባት ወደ እንጦንዮስ ላከ ይህም እንጦንዮስ በበረሀ ውስጥ መኖርን የጀመረ እርሱ እንደሆነ በልቡ ያስብ ነበር መልአኩም እንዲህ አለው "እንጦንዮስ ሆይ ከአንተ የሁለት ቀን ጎዳና ርቆ በበረሀ ውስጥ ሰው አለ የዓለም ሰዎች ከሚረግጥባቸው የእግሩ ጫማዎች እንደ አንዲቱ ሊሆኑ የማይገባቸው ስለ ርሱም ጸሎት ዓለም ተጠብቆ የሚኖር ምድርም ፍሬዋን የምትሰጥ ጠል በምድር ላይ የሚወርድ በምድር በሚኖሩ ኃጢአተኞች ሁሉ ላይ ፀሐይ የሚወጣ የሰውም ፍጥረት በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ተጠብቆ የሚኖር"።
❇️#አባ እንጦንዮስም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ተነሥቶ ወደ በረሀው መካከል ተጓዘ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ሁኖ ጎዳናውንም እንደሚጠርግለት አምኖ ሲጓዝ የሰውና የአራዊትን ፍለጋ አገኘ ያንንም ፍለጋ ተከትሎ ከቅዱስ ጳውሊ በዓት ደረሰ በሩንም አንኳኳ የከበረ አባ ጳውሊ ግን ከሰይጣን ሥራ እንደሆነ አስቦ ታላቅ ደንጊያ ወስዶ ከመዝጊያው ጀርባ አኖረ አባ እንጦንዮስም "ይሰጠኝ ዘንድ ፈለግሁ አገኝ ዘንድ ለመንኩ ይከፈትልኝም ዘንድ ቡሩን አንኳኳሁ" ብሎ አሰምቶ ተናገረ። በዚያንም ጊዜ ከፈተለትና ገባ እርስ በርሳቸውም በመንፈሳዊ ሰላምታ አጅ ተነሣሥተው በአንድነትም ጸልየው ተቀመጡ።
❇️#አባ እንጦንዮስም "አባቴ ሆይ ስምህ ማነው?" አለው አባ ጳውሊም "አንተ ስሜን ካላወቅህ እስከዚች ቦታ ለምን ተጓዝክ" ብሎ መለሰለት በዚያችም ሰዓት እግዚአብሔር የእንጦንዮስን ልቡን ገለጠለትና "ገዳማዊ ጳውሎስን አየው ዘንድ ስለተገባኝ እኔ ብፁዕ ነኝ" አለ ከዚህም በኋላ እርስ በእርሳቸው የእግዚአብሔርን ልዕልናውን ቸርነቱን ይነጋገሩ ጀመር በመሸም ጊዜ ቍራ መጥቶ አንዲት ሙሉ እንጀራ ጣለለት አባ ጳውሊም አባ እንጦኒን "አንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደሆንክ አሁን አወቅሁ እስከ ዛሬ ሰማንያ ዓመት በዚህ በረሀ ስኖር እግዚአብሔር ሁልጊዜ የሚልክልኝ ግማሽ እንጀራ ነበር እነሆ አሁን ምግብህን ላከልህ" አለው።
❇️#ከዚህም በኋላ ተነሥተው የማዕድ ጸሎት ጸለዩ በልተውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት መላ ሌሊቱንም ሲጸልዩ አደሩ። ነግቶ ፀሐይ በወጣ ጊዜም እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ እንጦኒም "አባቴ ሆይ በዚህ ሁሉ ዘመን ሥጋውንና ደሙን ከወዴት ትቀበላለህ?" አለው የከበረ ጳውሊም "እግዚአብሔር መልአኩን ይልክልኛል በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ሰንበት በየሳምንቱ ከሥጋውና ከደሙ ያቀብለኛል በዘመኑም ሁሉ እንዲህ ያደርግልኛል" ብሎ መለሰለት።
❇️#ከዚህም በኋላ አባ እንጦኒ አባ ጳውሊን "አባቴ ሆይ ይህ አስኬማ በምድር ላይ ይበዛ እንደሆነ ወይም አለመብዛቱን ትነግረኝ ዘንድ እሻለሁ" አለው። የከበረ ጳውሊም ወደ ሰማይ ተመለከተና ፈገግ አለ። ከዚህም በኋላ አዘነ ጩኾም አለቀሰ አባ እንጦንዮስም "ፈገግ ስትል በአየውህ ጊዜ ደስ አለኝ በአዘንክም ጊዜ አዘንኩ" አለው። የከበረ ጳውሊም እንዲህ ብሎ መለሰለት "እሊህ ተራሮችና በረሐዎች እግዚአብሔር ከሁሉ አገሮች መርጦ ለሚሰበስባቸው ንጹሐን ርግቦች ማደሪያዎች ይሆናሉ"።
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕝🕝ጥር 21🕝🕝
📖📖ዜና ቅዱሳን📖📖
🍒ቅድስት ማርያም ክብራ ዘጽላልሽ🍒
🌿🌿እንኳን ለኢትዮጵያዊቷ ጻድቅት ቅድስት ማርያም ክብራ ዘጽላልሽ ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን🌿🌿
🍒ቅድስት ማርያም ክብራ ዠጽላልሽ🍒
🍁🍁ቅድስት ማርያም ክብራ ዘጽላልሽ፡- ትውልዷ ሸዋ ደብረ ጽላልሽ ሲሆን በወቅቱ የትልቅ ባለስልጣን የመስፍን ልጅ ነበረች፡፡ ወደ ደብረ በግዕ ገዳም ገብታ መነኮሳቱን በብዙ ድካም ስታገለግል ከኖረች በኋላ በአቡነ ሕፃን ሞዐ እጅ መንኵሳለች፡፡
🍁🍁አቡነ ሕፃን ሞዐ ማለት የደብረ በግዕህ ገዳምን የመሠረቱት ታላቅ አባት ሲሆኑ እንደበሬ በመታረስ ሰማዕትነት የተቀበሉ ናቸው፡፡ ጻድቁን ከአንድ በሬ ጋር ጠምደው ቀኑን ሙሉ ሲያርሷቸው በድካም ሆነው በኋይል የተነፈሱበት ቦታ ላይ ምድሪቱ ዛሬም ድረስ እንደእርሳቸው ስትተነፍስ የእስትንፋሷ ድምጹና ሙቀቱ ይሰማል፡፡ ለአስም ሕመም መድኃኒት ነው፡፡ ቦታውም ከደብረ ብርሃን በእግር የሁለት ሰዓት ተኩል መንገድ ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን የጻድቁ ቤተ ክርስቲያኑ ከወይንዬ ተክለ ሃይማኖት ገዳም አጠገብ ይገኛል፡፡
🍁🍁ቅድስት ማርያም ክብራ በጻድቁ ሕፃን ሞዐ እጅ ከመነኮሰች በኋላ ወደ አቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም ገብታ በታላቅ ተጋድሎ ስትኖር ሰይጣን ብዙ ጊዜ በሰው አምሳል እየተገለጠ በፈተና ሊጥላት ይሞክር ነበር፡፡ የእግዚአብሔርም መልአክ እየተገለጠ ያበረታት ነበር፡፡ እርሷም በበትረ መስቀሏ ሰይጣንን እያሳደደች ታባርረው ነበር፡፡
🙏🙏ከቅድስት ማርያም ክብራ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቷ ይማረን!።🙏🙏
ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
💧https://t.me/zenaakidusan 💧💧
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
.......... የቴሌግራም ቻናላችንን በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣የዜና ቅዱሳን ቤተሰብ ይሁኑ!!!
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕤🕤ጥር 21🕗🕗
🔔🔔ዜና ቅዱሳን🔔🔔
🌷አቡነ ማማስ ዘትግራይ(ማማስ የሚለው ቃል በማጥበቅ ይነበብ)🌷
🌿እንኳን ለታላቁ አባት አቡነ ማማስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ🌿
#ነሐሴ 7:-የልደታቸው ቀን
#ታኅሣሥ 30:-ተአምር ያደረጉበት ዕለት
#ጥር 21: -የዕረፍታቸው ዕለት
🌼አቡነ ማማስ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ሲሆኑ የነበሩበት ዘመን በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነበር።
🌼ተወልደው ያደጉት(የትውልድ ቦታቸው) በትግራይ ክልል በአጽቢ መምበርታ እንደሆነ የገዳሙ አባቶች ይናገራሉ፤እንደ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ ገለጻ ደግሞ የትውልድ ቦታቸው አምሐራ ሳይንት ነው ይላሉ።
🌼የትውልድ ቦታቸው በሐውዜን ሀረይክዋ ነው።
አቡነ ማማስን ያመነኮሷቸው አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ናቸው፣የአቡነ አሞኒ ሦስተኛ ልጅ ናቸው፡፡ለዚህም ""አቡነ ማማስ ረድኡ ለበጸሎተ ሚካኤል"" በመባል ይጠራሉ።
🌼እንደ ገዳሙ አባቶች ገለጻ ሙሉ ኢትዮጵያን ዞረዋል።
🌼አቡነ ማማስ በተለያዩ ቦታዎች ሰባት ገዳማትን ያቀኑ ሲሆን ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረው በስብከተ ወንጌል ብዙ አገልግለዋል፡፡
🌼በስማቸው የተሠራው አስደናቂ ገዳም በትግራይ አጋሜ አውራጃ ይገኛል፡፡ገዳማቸው የሚገኘው አንዱ በትግራይ ክልል ከአዲግራት ከተማ በስተሰሜን 23ኪ.ሜ ላይ በምትገኘው በወረዳ ጉሎ መኸዳ ቁሸት ሀገር በተባለው ቦታ ሲሆን ሌላው ገዳማቸው በኤርትራ ሀገር አካለ ጉዛይ ውስጥም ይገኛል።
🌼ትግራይ ውስጥ ከእዳጋ አርቢ ወደ ጥንታዊቷ ውቅሮ ማርያም ገዳም በሚወስደው መንገድ ላይ ነበለት ከምትባለው ትንሽ የገጠር ከተማ በስተሰሜን አቅጣጫ በሚገኘው አስደናቂ ገዳማቸው ውስጥ ለየት ያለ የማኅሌት ሥርዓት ይካሄድበታል፡፡
🌼የማኅሌቱ ድምጽ እጅግ የተለየ ሲሆን ማኅሌቱን ቅዱሳን መላእክት እንደሚሳተፉበት በቦታው ላይ ያሉ ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡
🌼በማኅሌቱም ወቅት ከዋሻው ጣራ ላይ ልዩ ጣዕም ያለውና ፈውስ የሚሰጥ ልዩ ጠበል ይፈልቃል፡፡
🌼ስለትንሳኤ የሚናገረው ተአምረ ማርያም ላይ ስለዚህ ታላቅ ቦታ እንደተጻፈ አባቶች ያስረዳሉ፡፡ ጻድቁን በመጀመሪያ ወደዚህ ታላቅ ቦታ እየመራ ያመጣቸው የታዘዘ መልአክ ነው፡፡
🌼ገዳሙ ሁለት ቤተ መቅደስ ያለው ሲሆን ቀድሞ በመነኩሴ ብቻ ይገለገል ነበር፡፡
🌼የአቡነ ማማስ መካነ መቃብራቸው ካለበት ተራራ ላይ የበቀለ የተለየ የዕፅ ተክል አለ።ይኽንንም ተክል የአካባቢው ነዋሪ ለእምነትነት በመጠቀም ከተለያዩ ሕመሞች ይፈወስበታል።
🙏🙏ከአቡነ ማማስ ፤እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!።🙏🙏
ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
💧https://t.me/zenaakidusan 💧💧
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
.......... የቴሌግራም ቻናላችንን በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣የዜና ቅዱሳን ቤተሰብ ይሁኑ!!!
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕝🕝ጥር 21🕝🕝
📖📖ዜና ቅዱሳን📖📖
🍒🍒አቡነ ተስፋ ኢየሱስ ዘጎዣም🍒🍒
🌿🌿እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ቅዱስ፤ለአቡነ ተስፋ ኢየሱስ ዘጎዣም ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን🌿🌿
🍒🍒አቡነ ተስፋ ኢየሱስ ዘጎጃም🍒🍒
🍁🍁የትውልድ ሀገራቸው ጎጃም ሲሆን የታላቁ ጻድቅ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ዘግሽ ዓባይ ታላቅ ወንድም ናቸው፡፡ እንደ ወንድማቸው የተወለዱት በመልአክ ብስራት ነው፡፡
🍁🍁አቡነ ተስፋ ኢየሱስን መልአክ እየመራ ወስዶ ጣና ሐይቅ ገዳም አደረሳቸውና በዚያ የቤተ ክርስቲያን ትምህርትና ሥርዓቷን ሁሉ በሚገባ ተማሩ፡፡ የዋሸራን ገዳም በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው ከመሠረቱት 300 ቅዱሳን መነኰሳት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በ300ው መነኰሳትም ተመርጠው የገዳሟ ባራኪ ሆነው ተሹመው አገልግለዋል፡፡
🍁🍁ሱባኤ ገብተው ስለ ዋሸራ ገዳምና ስለ አካባቢው ሕዝብ ምሥጢር የገለጠላቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ገዳሟ ፈልፈለ ሊቃውንት እንደምትሆን ተገልጦላቸዋል፡፡ ደግመው ሱባኤ ቢገቡ ገዳሟ በስተኋላ እንደምትቀዘቅዝ ተገለጠላቸው፡፡ ለ3ኛም ጊዜ ሱባኤ ቢገቡ ገዳሟ እስከ ዕለተ ምዕዓት ጸንታ እንደምትኖር ተገልጦላቸው በዚህም ደስ ተሰኝተዋል፡፡
🍁🍁ዋሸራ ገዳም በመጀመሪያ በባሕር የተከበበች ብትሆንም አቡነ ተስፋ ኢየሱስ ባሕሩን ቢባርኩት ተስተካክሎ እንደ ጸበል ሆኖላቸዋል፡፡ እመቤታችንም ዕለት ዕለት እየተገለጠችላቸው ትባርካቸው ነበር፡፡
🍁🍁ጻድቁ በተጋድሎ ብዙ ካገለገሉና ከጌታችን ታላቅ ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኋላ ጥር 21 ቀን ዐርፈው በዚያው ተቀብረዋል፡፡
🙏🙏ከአቡነ ተስፋ ኢየሱስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!።🙏🙏
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
💧https://t.me/zenaakidusan 💧💧
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕝🕝ጥር 21🕝🕝
📖📖ዜና ቅዱሳን📖📖
🍒🍒አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል🍒🍒
🌿🌿እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ቅዱስ፤ለአቡነ ቀውስጦስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን🌿🌿
🔔🔔🔔ቃልኪዳን🔔🔔🔔
🌿🌿ነፍሳቸው ከሥጋቸው ሳትለይ በስቃይ ላይ ሳሉም በዘመናቸው ሁሉ ስለነበራቸው ተጋድሎ፣ ንፅህናና ምናኔ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምንና ቅዱሳን መላእክትን አሰከትሎ በክበበ ትስብእት በግርማ መለኮት መጣና ቃል ኪዳን ሰጣቸው። እንዲህም አላቸው፦
👉👉"እኔ ለአንተ አይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን መንግሥተ ሰማያትን አዘጋጀውልህ። በዘመንህ ስላሳለፍከው ክርስቲያናዊ ፍፁም ተጋድሎህ ሰባት የብርሃን አክሊል (ዘውዶችን) ያዘጋጀውልህ ሲሆን ሁለቱ እንደ እነ ነቢዩ ኤልያስና ነቢዩ ሳሙኤል ለሆነ ንጽህናህ፣ ሁለቱ እንደ እነ ቅዱስ ጴጥሮስና ጳውሎስ ለሆነ የወንጌል ስብከትህ፣ ሁለቱ እንደ እነ ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ፊቅጦር በትዕግሥት ስለተጋደልክ፣ አንዷ ስለ ልብህ ርህራኄ ናት ።
👉👉 እንዲሁም ስለ እኔ ምስክርነት የሞትክባት ምድር እንደ ዳዊት አገር እንደ ኢየሩሳሌም ትሁንልህ፤ ወደእርሷ የሄደውንም ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ወደ መቃብሬ ጎልጎታ እንደሄደ እቆጥርለታለሁ።
👉👉ብዙ ኃጢያት የሥራ ሰው ንስሐ ገብቶ በዚያች አገር በስምህ ጥቂት ምጽዋት ቢሰጥ እኔ ኃጢያቱን እደመስስለታለሁ፤ በጠበልህም ቢጠመቅ በደሉን አጠፋለታለሁ ደምህ በምድሪቱ ፈሷልና፤
👉👉በዕረፍትህ ዕለት ለቤተ ክርስቲያንህ ኖኗቅዱ ቁርባን ስንዴ፣ ወይንና ዕጣን ያቀረበ ኃጢያት የሰራ ተነሳሒ(ንስሃ የገባ) ሰው ቅዱስ ሥጋውንና ክብር ደሙን እንደተቀበለ ንፁህ ሰው አደርገዋለሁ፣ ለስምህ መታሰቢያ በታነጸው ቤተ መቅደስ በንጽህና ቅዱስ ሥጋውንና ክብር ደሙን የሚቀበል (የሚቆርብ) ሰው ራሱን፤ ቤተነሰቡን ባልንጀሮቹን ያድናል"።
842
Repost from ዜና ቅዱሳን
🕝🕝ጥር 21🕝🕝
📖📖ዜና ቅዱሳን📖📖
🍒🍒አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል🍒🍒
🌿🌿እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ቅዱስ፤ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአክስት ልጅ፤ በሸዋ ክፍለ አገር ፈንታሌ ተራራ ላይ ሰሪቲ ለምትባ ጠንቋይ እየተላላኩ ሕዝቡን የሚያስቱና የሚያሰቃዩ አራት መቶ ሰባ ሽህ ሦስት መቶ አጋንንትን እንደ ነቢዩ ኤልያስ እሳት ከሰማይ አውርደው ላጠፋ ለታላቁ አባት ለአቡነ ቀውስጦስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን🌿🌿
🍁🍁ጻድቁ የተወለዱት ሸዋ ክፍለ አገር በወግዳና ቡልጋ ውስጥ ሲሆን አባታቸው ቅዱስ ገላውዴዎስ እናቸው ቅድስት እምነ ጽዮን ይባላሉ። የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት እናት እግዚእ ኃርያ እና እምነጽዮን ታናሽና ታላቅ እህትማማቾች ናቸው።
🍁🍁ቅዱስ ገላውዴዎስና ቅድስት እምነ ጽዮን እግዚአብሔር የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ለዓመታት በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስዕል ፊት ሲጸልዩና ሲለምኑ እመቤታችን በስዕሏ ላይ አድራ አናገረቻቸው፤ እንዲህም አለቻቸው፦" አንድ ልጅ አስቀድማችሁ ትወልዳላችሁ፤ የሚወለደውም እኔ በተወለድኩበት ግንቦት1 ቀን ዕረፍቱም በእኔ ዕረፍት ቀን ጥር21 ነው እሱም የሰማያዊ ንጉሥ ጭፍራ ይሆናል" አለቻቸው። በቃሏ መሰረትም ግንቦት1 ቀን ጻድቁ አቡነ ቀውስጦስ ተወለዱ።
🍁🍁ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ የዚህን ዓለም ተድላ፣ ደስታና ጠዐም ንቀው ፈለገ ሐዋርያትን ተከትለው በሸዋ፣ በከፋና በጅማ ዞረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በማስተማር አረማውያን፣ ነገሥታትና ባላባቶች የሚደርስባቸውን መከራና እንግልት በመታገስ በተጋድሎ ፀንተው ብዙውን ሕዝብ ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር ከኃጢያት ወደ ጽድቅ መልሰዋል። በተለይም በሸዋ ክፍለ አገር ፈንታሌ ተራራ ላይ ሰሪቲ ለምትባ ጠንቋይ እየተላላኩ ሕዝቡን የሚያስቱና የሚያሰቃዩ፬፻፸ሺ፫፻(አራት መቶ ሰባ ሽህ ሦስት መቶ) አጋንንትን እንደ ነቢዩ ኤልያስ በጸሎታቸው ከሰማይ እሳት አውርደው ተራራውን ደምስሰው አጋንንቱን አቃጥለዋል። ሕዝቡንም ለጣዖትና ለጠንቋይ ከመገዛት አድነውታል።
🍁🍁ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ በብዙ ተጋድሎ ሲኖሩ በሰማዕትነት ያርፉ ዘንድ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚተጉ እንጂ የዚህን ዓለም መንግሥት ሀብትና ስልጣን የማይሹ እውነተኛ መናኝ ነበሩና የታናሽ ወንድማቸው የአፄ ይኩኖ አምላክ ልጅ አፄ አምደ ጽዮን የአባቱን እቁባት በማግባቲ "ይህንን ልታደርግ አይገባህም"። ብለው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ መጥጥምቅ ቢገስጹት ዐሥራ አንድ አሽከሮቹን በሌሊት ልኮ ከበዩ ወደ እንሳሮ አገር ካስወሰዳቸው በኋላ ኮሶ አረህ ከሚባለው አፋፍ ላይ በእኩለ ሌሊት በጦር ጎናቸውን አስወግቶ ደማቸውን አስፈሰሰ። ደማቸውም እስከ ታላቁ ወንዝ ጀማ ድረስ ሆነ። የፈሰሰው ደማቸውም ቀይ ብርሃን ሲሆን የሌሊቱ ጨለማ ከፀሐይ ሰባት እጅ የሚበልጥ ብርሃን በአውራጃዎቹ ሁሉ ታየ።በዚህ የተነሳ እስከ ዛሬ ድረስ አገሩ ቀን ተብሎ ይጠራል።
🍁🍁ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው ዐረገ። ቅዱሳን መላእክትም ነፍሳቸውን ከስጋቸው በክብር ለዩ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በሰማይ መካከል ነፍሳቸውን በፈገግታ ተቀበለች።
🍁🍁የዕረፍታቸውም ዕለት እመቤታችን ባለፈችበት ጥር 21 ቀን በመሆኑ እመቤታችንም "መታሰቢያህን ለሚያደርጉ ሁሉ በልጄ በረከት እበርካቸዋለሁ" ብላ ቃል ኪዳን ገባችላቸው። ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ባረፉበት ዕለትም ብዙዎች ከዴዌአቸው ተፈውሰዋል። የጻድቁ አባታችን በረከትና ፈውስ አሁንም ድረስ መደማቸ በፈሰበትና አፅማቸው ባረፈበት ቦታ ሁሉ እየታየ ብዙ ምዕመናን ፈውስ ነፍስና ፈውሰ ሥጋ እያገኙበት ነው።
🍁🍁ገዳመ ቀውስጦስ የሚገኘው ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 120ኪ.ሜ ርቀት ላይ ሲሆን ወደ ደብረ ሊባኖስ በሚወስደው መንገድ ሙከጥሪ ከተማ ሲደርሱ ወደቀኝ በመታጠፍ ሜጤና ባዩ በሚባለው አካባቢ ልዩ ስሙ ተግባሬ(መገንጠያ) ከሚባል ቦታ ነው።
🙏🙏🙏ከጻድቁ አቡነ ቀውስጦስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!።🙏🙏
ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ቀውስጦስ (በአጭሩ) ከሚለው መጽሐፍ።
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
💧https://t.me/zenaakidusan 💧💧
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧
.......... የቴሌግራም ቻናላችንን በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣የዜና ቅዱሳን ቤተሰብ ይሁኑ!!!
